Degu Samrawi

Degu Samrawi

የበጎ ስራዎች ማስተዋወቂያ

Photos from Degu Samrawi's post 22/10/2022

በኃጢአት ባርነት ተይዘን በችግር እና በመከራ ውስጥ ተዘፍቀን ለምንኖር ሰዎች ስለ ሕዝበ እስራኤል በእግዚአብሔር ፊት የቆምኸው አንተው ነህና ለእኛም ታማልደንና ትራዳን ዘንድ በጸሎት እንማጸንሃለን።
አምላካችን እግዚአብሔርም የምሕረት ፊቱን ወደ እኛ በመመለስ በጸብና በጦርነት ምትክ ፍቅርን፣ ሰላምንና መግባባትን፤ በመለያየት ምትክ አንድነትን እንዲሰጠን በቅዱስ ሚካኤል ስም እንለምን።
የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል አማላጅነትና ተራዳኢነት አይለየን፤ አሜን፡፡

17/10/2022

ቅድስት ሥላሴ አንድም ሦስትም ናቸው፡፡ ‹‹ሥላሴ›› የሚለው ቃል ‹‹ሠለሰ፤ ሦስት አደረገ›› ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙ ሦስትነት ማለት ነው፡፡ (መጽሐፍ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ገጽ ፮፻፷፱)
ቅድስት ሥላሴ ስንልም አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ማለታችን ነው፡፡ ‹‹ቅድስት›› ተብሎ ደግሞ በሴት አንቀጽ /ቅድስት ሥላሴ/ ይጠራል፤ ‹‹ቅድስት›› እና ‹‹ልዩ ሦስት›› የሚባልበትም ሃይማኖታዊ ምሥጢር፡-
፩. ቅድስት
ሥላሴ ‹‹ቅድስት›› ተብለው በሴት አንቀጽ መጠራታቸው ሴት /እናት/ ልጅዋን መውለዷን እንደማትጠረጥረው ሁሉ ሥላሴም ይህን ዓለም መፍጠራቸውን ስለማይጠረጥሩ ነው፡፡ ሁሉም ከእነርሱ፣ ለእነርሱ፣ በእነርሱ ሆኗልና፡፡ ሴት ወይንም እናት ልጅዋ ቢታመምባት እንዲሞትባት አትሻም፤ ሥላሴም ከፍጥረታቸው አንዱ እንኳን በጠላት ዲያብሎስ እንዲገዛባቸው አይፈቅዱም፡፡ ሴት ፈጭታ ጋግራ ቤተሰቦቿን እንደምትመግበው ሥላሴም በዝናም አብቅለው በፀሐይ አብስለው ፍጥረቱን ሁሉ ስለሚመግቡ ‹‹ቅድስት ሥላሴ›› እያልን እንጠራቸዋለን፡፡
፪. ልዩ ሦስትነት
በትምህርተ ሃይማኖት ሥላሴ በቅድምና፣ በፈጣሪነት፣ በሥልጣን፣ በመመስገን፣ በክብር፣ በፈቃድ አንድ /እግዚአብሔር/ ሲሆኑ በስም፣ በአካል፣ በግብር ሦስት መሆናቸውን ይገልጻል፡፡
አቤቱ ከክፍ ሁሉ ጠብቀን

Photos from Degu Samrawi's post 19/08/2022

በዓለ ደብረ ታቦር እና ቡሄ

ጌታችን ምሥጢረ መለኮቱን ለገለጠበት ለበዓለ ደብረ ታቦር እንኳን በሰላም አደረሰን!
ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ታቦር ብርሃነ መለኮቱን፣ ክብረ መንግሥቱን መግለጡን በማሰብ በየዓመቱ ነሐሴ ፲፫ ቀን በዓሉ በድምቀት ይከበራል፡፡ ይህ በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ዘንድ ‹ቡሄ› በመባል ይታወቃል፡፡ ቡሄ ማለት ‹መላጣ፣ ገላጣ› ማለት ነው፡፡ በአገራችን ክረምቱ፣ ጭጋጉ፣ ደመናው ተወግዶ የብርሃን ወገግታ የሚታይበት በዚሁ በዓል አካባቢ ስለ ኾነ በዓሉ ‹ቡሄ› ተብሎ ይጠራል፡፡ በዓለ ደብረ ታቦር ጌታችን ምሥጢረ መለኮቱን የገለጠበት፤ ብርሃን የታየበትና ድምፀ መለኮቱ የተሰማበ ዕለት ስለ ኾነ ‹የብርሃን› ወይም ‹የቡሄ› በዓል ይባላል፡፡
ቡሄ ሲመጣ የክረምቱ ጨለማነት አልፎ ወደ ብርሃን፣ ወደ ጥቢ የሚያመራበት፤ ወደ መፀው የሚገባበት፤ ወገግታ የሚታይበት፤ ሰማይ ከጭጋጋማነት ወደ ብሩህነት የሚሸጋገርበት ወቅት በመኾኑ ከቡሄ በኋላ የጠነከረ ክረምት አይኖርም፡፡ ‹‹ቡሄ ከዋለ የለም ክረምት፤ ዶሮ ከጮኸ የለም ሌሊት›› እንዲሉ፡፡ በአንዳንድ የአገራችን አካባቢዎች የቡሄ ዕለት ማታ ምእመናን ችቦ ያበራሉ፡፡ ይህም በደብረ ታቦር ለታየው ብርሃነ መለኮት ምሳሌ ነው፡፡ ሕፃናቱ ይህ በዓል ከመድረሱ በፊት ቀደም ብለው ጅራፍ ሲገምዱና ሲያጮኹ (ሲያኖጉ) ይሰነብታሉ፡፡ እናቶችም ለዚህ በዓል የሚኾን ዳቦ ለመጋገር ስንዴያቸውን ሲያጥቡ፣ ሲፈትጉ ይሰነብታሉ፡፡ በበዓሉ ዋዜማ (ነሐሴ ፲፪ ቀን) ሕፃናት በየቤቱ እየዞሩ ‹‹ቡሄ ና በሉ፤ ቡሄ በሉ፡፡ ቡሄ መጣ፤ ያ መላጣ፤ ቅቤ ቀቡት እንዳይነጣ …›› እያሉ ይጫወታሉ፡፡ በዚህ ጊዜ እናቶች ካዘጋጁት ዳቦ እያነሡ ይሰጧቸዋል፡፡ ሕፃናቱ ‹ቡሄ› የሚሉትም ዳቦውን ነው፡፡
ጌታችን ብርሃነ መለኮቱን በገለጠበት ዕለት እረኞች ከብርሃኑ የተነሣ እየተገረሙና እየተደነቁ ወደ ቤት አልተመለሱም ነበር፡፡ የልጆቹን መዘግየት ያዩ ወላጆች ችቦ አብርተውና ዳቦ ይዘው ፍለጋ ወጥተዋል፡፡ ‹ቡሄ› ለሚሉ ልጆች ሙልሙል ዳቦ የሚሰጠውና በበዓሉ ችቦ የሚበራውም ከዚህ ታሪክ በመነሣት ነው፡፡ ለክርስትና ልጅ፣ ለአማች፣ ለምራት፣ ለዘመድ አዝማድ ዅሉ የቡሄ ዳቦ ይሰጣል፡፡ ልጆችም ዳቧቸውን እየገመጡ ጅራፍ ሲገርፉ ይውላሉ፡፡ የጅራፉ መጮኽ የድምፀ መለኮት ምሳሌ ሲኾን፣ ጅራፉ ሲጮኽ ማስደንገጡም ነቢያትና ሐዋርያት በድምፀ መለኮት መደንገጣቸውንና መውደቃቸውን ያስታውሳል፡፡
መምህረ ሐዋርያት ኢየሱስ ክርስቶስ ሦስቱን ተማሪዎቹን ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን ይዞ በደብረ ታቦር ምሥጢር መግለጡን በማስታዎስ የአብነት ተማሪዎች ከመምህራቸው ጋር በመኾን በዓለ ደብረ ታቦርን (ቡሄን) ያከብራሉ፤ ስሙን ይጠራሉ፡፡ የአብነት ተማሪዎች ‹‹ስለ ደብረ ታቦር›› እያሉ እኽል ከምእመናን በመለመንና ገንዘብ በማዋጣት ጠላውን ጠምቀው፣ ዳቦውን ጋግረው፣ ቆሎውን ቆልተው ለደብረ ታቦር ዕለት ሊያስቀድሱ የመጡትን ምእመናን በመጋበዝና እርስበርስ በመገባበዝ፣ እንደዚሁም ቅኔ በማበርከት በዓለ ደብረ ታቦርን በታላቅ ድምቀት ያከብራሉ፡፡ ይህም እስከ አሁን ድረስ በአብነት ትምህርት ቤቶች የሚሠራበት ነባር ትውፊት ነው፡፡
እንኳን አደረሰን

Photos from Degu Samrawi's post 07/08/2022
Photos from Degu Samrawi's post 03/08/2022

በልጅነታችን ያልተውከን በወጣትነታችን የረዳኸን በጎልማሳነታችን የደገፍከን መድሐኔአለም ሆይ ቸርነትህ በዝቶልን አሁንም በምህረትህ ጎብኘን

Photos from Degu Samrawi's post 14/07/2022

ይህ ጊዜ የኑሮው ቅጥ ማጣት ለብዝዎች ከባድ ሁኗል በተለይም ለአረጋውያን በችግር ውስጥ ለሚገኙ ደግሞ ምን ያህል አሰቃቂ እንደሆነ መገመት አያዳግትም እናም በአለችን ትንሽ የማስተባበር አቅም ልክ አንድ ሰው ካለችው ላይ አለያም ሁለት ሶስት በመሆን በቋሚነት በወር አለያም በሁለት ወር አንድ ሰው እንደ ቤተሰብ ተረክበን ይህን አስቸጋሪ ጊዜ ብቻችንን ከምንሻገር መሻገር ያቃታቸውን ይዘን ማዝገም ስለሚሻል እኛ እናስባለን እሱ እግዚአብሔር ይፈፅማልና በእሱ ፈቃድ ዛሬ የመረካከቡን ስራ ጀመርነው።
አጥናፍ ይትባረክ ይባላል በሀገር መከላከያ 16 አመት ሰርቷል። ዛሬ በጡረታ በግል ስራ በትንሹ ተሰማርቶ የሚገኝ ወንድማችን ነው ኑሮት አይደለም ታውቁታላችሁ ነገር ግን ከሚያገኛት ላይ አስረክበኝ ብሎ ዛሬ እኝህን እናት በቋሚነት በየወቅቱ ሊጠይቅ የመጀመሪያውን ሃላፊነት ወስዶ አስረክበናል። የእውነት ደስም ብሎኛል። ወንድሜ አጥናፉ አንድ ብሎ ጀምሮታል እኛ ደግሞ እስኪ እናስፋውና ቢያንስ ከተማችን ውስጥ በርሃብ የሚጎዳ የሚሞት ሰው አይኑር።
እናም በዚህ መንገድ በበጎ ተግባር አብራችሁኝ መስራት ለምትፈልጉ በውስጥ መስመር አለያ በቴሌግራም ቻናሌ መመዝገብ ትችላላችሁ
ካለን ቀጥታ ከምትደግፏቸው አረጋውያን ጋር ማገናኘት ነውና ስራየ ከዚህም በላይ ማድረግ የምችለው ስለሌለ መላክ ነውና አድርስ አለያ መልክት መደወል ብቻ በቂ ነው አጥናፉ ወንድሜ ከልብ እናመሰግናለን የእናት አባቶች ፀሎትና ልመና አይለይህ ወንድሜ

Photos from Degu Samrawi's post 13/07/2022

እንኳን ለቅድስት ስላሴ አመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ/መልካም ስራው እናመሰግናለን/
ደምበጫ ቅድስት ስላሴ ባዞላም በእለተ ቀኑ እንዲህ ተጠናቋል። የተሳተፋችሁ ያሰባችሁ ያስተባበራችሁ በሙሉ ክብሩን ያድልልን በዚሁም አንድ እህታችን መልካም ስራው ከውጭው አለም 1000/አንድ ሽህ ብር ለባዞላ መጠናቀቂያ በሚል ትናንት ገቢ አድርጋለች በአለሽበት ይጠብቅልን እናመሰግናለን።
ነገ ሁላችንም ወደ ንግስ

Photos from Degu Samrawi's post 10/07/2022

ወንድም እህቶቼ ሰላማችሁ ይብዛልኝ
አቶ ላቀ አለኸኝ ለአስር በችግር ውስጥ ላሉ የብርድ ልብስ ድጋፍ አደረጉ
እንደምታውቁት ክረምቱ ጠንከር እያለ ብርዱ እየጨመረ በመምጣቱ ምክንያት በፍሬ ደምበጫ በጎ አድራጎት ማህበር መጠለያ ቦታ ተጠልልለው ለሚገኙ 6/ስድስት/ አረጋውያንና ከውጭ በችግር ውስጥ ለሚገኙ 4/አራት በድምሩ አስር ብርድልብስ ከአዲስ አበባ ለወገኔ ይድረስልኝ ብለው አቶ ላቀ አለኸኝ በዚህ መንገድ በዕለተ እሁድ መልካም ነገር አድርገውልናል። ከልብ እናመሰግናለን።
ለተቸገሩ ወገኖች በአለሁበት አካባቢ መደገፍ ለምትፈልጉ በ0912745936 መደወል ይቻላል እንታዘዛለን

Photos from Degu Samrawi's post 24/06/2022

ኪዳነ ምህረት - 16

ስሟን ለሚጠሩ፣ በእርሷ አማላጅነት ለሚታመኑ በምድር በረከትን በሰማይ የዘለዓለም መንግስትን እንደሚወርሱ የምህረት እና የቸርነት ቃልኪዳን ሰጥቷታል፡፡

ታላቁ መፅሐፍ እንዲህ ይላል፦ ". . . ቀስቲቱም በደመና ትሆናለች፤ በእኔና በምድር ላይ በሚኖር ሥጋ ባለው በሕያው ነፍስ ሁሉ መካከል ያለውን የዘላለም ቃል ኪዳን ለማሰብ አያታለሁ። " ኦሪት ዘፍ. 9፥16
እናታችን ኪዳነ ምህረት ሆይ የአስራት አገርሽን ከአለም መፍትሔ አጠናልና ልጅሽ በቃችሁ ይለን ዘንድ ከልጅሽ አሳስቢ
እንኳን ለ«ኪዳነምህረት» አደረሳችሁ። የእመቤታችን ምህረት እና ረድዔት፤በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን ፫

22/06/2022
Want your organization to be the top-listed Non Profit Organization in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Telephone

Website

Address

Addis Ababa
Other Nonprofit Organizations in Addis Ababa (show all)
Noble Cause Elder Care and Support Noble Cause Elder Care and Support
Office Addis Ababa
Addis Ababa, P.O.BOX21261,CODE1000

We are working for/with the most poorest and potentialy vulnerable elders in Ethiopia!

Rotaract Club of Keroggie Rotaract Club of Keroggie
Bole Subcity, Woreda 03, Zewdu Gessese Bldg, House No. 2414/2nd Foor
Addis Ababa

We are visionary, committed and disciplined young Ethiopians passionate to make a positive difference in the lives of our fellow citizens and the humanity through community service...

Rotaract Club of SOLYANA Rotaract Club of SOLYANA
Addis Ababa

Rotaract Club of Solyana is one of the 16 clubs in Ethiopia, and has been running since 2007 as a partner in service of Rotary International

Rotaract club of Ra'ey Rotaract club of Ra'ey
Addis Ababa

RAC Ra'ey is a rotaract club with members of different professions and knowledge in Ethiopia working for the realization of Ethiopia's visions VISION IN ACTION!

Strong Hearts International Strong Hearts International
Nifas Silk Lafto Sub City, Kore Mekanissia Area
Addis Ababa

We are a 501c3 non profit organization, our mission is to bring about transformation from the insideo

AIESEC in Ethiopia AIESEC in Ethiopia
EiABC, Dej. Baltcha Aba Nefso Street
Addis Ababa

Welcome to the AIESEC in Ethiopia Official Fan Page! AIESEC is the World's largest student‐run organi

The School of St Yared, Ethiopia The School of St Yared, Ethiopia
Opposite French Embassy
Addis Ababa

The School of St Yared opened in 2009 with the aim of offering a top class education to talented, imp

The Ethiopian Film Initiative The Ethiopian Film Initiative
Addis Ababa

Empowering Ethiopian filmmakers

Life4all Life4all
Addis Ababa
Addis Ababa, 41303

Great Commission Ministry Ethiopia on the journey of spiritual movement every where is impacting stu

Goh Bedembia Charitable Association Goh Bedembia Charitable Association
Addis Abeba
Addis Ababa, FUTUREPARK

Goh Be Dembia Charitable Association

Cancer Care Ethiopia Cancer Care Ethiopia
Ambo Street, Melka Gefersa
Addis Ababa, 10620,ADDISABABA

This is page of cancer care ethiopia. Updates about works will be presented here.