Ethio1888 media

Ethio1888 media

አዳዲስና ወቅታዊ ፕሮግራሞችን ከኢትዮ1888 ሚዲያ ያግኙ።
ኢትዮ1888 ሚድያ
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/channel/UC74xVlm9etNg

30/03/2023

"ተለቀቁ❗️"

ኬሪያ ኢብራሂም፣ ዶ/ር አብርሃም ተከስተ እና ዶ/ር አዲስዓለም ባሌማ ከእስር ተፈቱ

በዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል እና በሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ መዝገብ ተከስሰው በእስር ላይ የነበሩ የህወሓት ሲቪል እና ወታደራዊ አመራሮች ዛሬ ሐሙስ መጋቢት 21፤ 2015 አመሻሽ ላይ ከእስር መፈታታቸውን የተከሳሾቹ ጠበቆች አስተባባሪ የሆኑት አቶ ሃፍቶም ከሰተ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። በዛሬው ዕለት ከእስር ተለቅቀው ወደ ቤታቸው መግባታቸው ከተረጋገጡ ተከሳሾች ውስጥ፤ የህወሓት ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም፣ ዶ/ር አብርሃም ተከስተ እና ዶ/ር አዲስዓለም ባሌማ እንደሚገኙበት ጠበቃው አስታውቀዋል።

የፍትህ ሚኒስትር በዛሬው እለት መጋቢት 21/2015 ዓ.ም የቀድሞ የህውሀት ባለስልጣናትና ወታደራዊ አባላት ላይ ተመስርቶ የነበረውን ክስ አቋርጫለሁ ብሎ ማስታወቁ ይታወሳል። ይህንንም ተከትሎ ማምሻውን ባለስልጣናቶቹ እንደተለቀቁ ተገልፃል።

ምንጭ ፦ (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

ኢትዮ1888 ሚድያ
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/channel/UC74xVlm9etNg3IWsuiXkyrA
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/ethio.1888/
በቴሌግራም
https://t.me/ethio1888media

10/03/2023

በአንድ ወር 40 እናቶች በርሀብ መሞታቸው ተነገረ❗️

በአማራ ክልል፣ ዋግኽምራ ዞን፣ ጻግብጅ ወረዳ፣ ተከስቷል በተባለው ሰው ሰራሽ ረሃብ ምክንያት ከ40 በላይ እናቶች ሕይወታቸው ማለፉን የፃግብጂ ዞን አስተዳደር በዛሬው እለት መጋቢት1/2015 ዓ.ም ገልፀዋል። አስተዳሪው እንደ ምክንያት ብለው የጠበሱት አካባቢዎቹ አሁንም በህውሐት ቁጥጥር ስር በመሆናቸው ህክምናና እርዳታ መድረስ ከባድ በመሆኑ ነው ብለዋል።

የፃግብጂ ወረዳ ከአስተዳደር

ኢትዮ1888 ሚድያ
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/channel/UC74xVlm9etNg3IWsuiXkyrA
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/ethio.1888/
በቴሌግራም
https://t.me/ethio1888media

Photos from Ethio1888 media's post 04/03/2023

ሆብዬ.. መጣለሁ ....ሆብዬ... በድል
ጥንትም የአባቴነው ጠላትን መግደል!
**
ከየካቲት23 የአድዋ ድል አለፍ ስንል ሌላኛው የካቲት 26የሚከበረው የድል በአላችን ላይ እናርፋለን!

የካቲት 26/1970 ዓ.ም የኢትዮጵያን ምስራቃዊ ግዛት እስከ አዋሽ ድረስ ሰተት ብሎ ገብቶ ለመጠቅለል የቋመጠው የወራሪው ሲያድ ባሬ ጦርን በወቅቱ የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት የነበሩት ሌተናል ኮሌኔል መንግስቱ ሀ/ማሪያም አስተባባሪነት፤ መላው ኢትዮጵያንን በማሰባሰብ በሰማይም በምድርም ወራሪውን በማጣደፍ በካራማራ ተራራ ግብአተ መሬቱን ፈፅመውታል። ክብር በየዘመኑ እየሞቱ ሉዓላዊ ሀገር ላስረከቡን አባቶቻችን🙏

45ተኛው የካራ ማራ ድል !

ኢትዮ1888 ሚድያ
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/channel/UC74xVlm9etNg3IWsuiXkyrA
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/ethio.1888/
በቴሌግራም
https://t.me/ethio1888media

02/03/2023

በአስለቃሽ ጭስና በጥይት የታጀበው 127ተኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በአል ላይ የተገኙ ህፃናትና አቅመ ደካሞች በነበረው ትርምስ ጉዳት እንደደረሰባቸው ተገለፀ።

#127ተኛው የአድዋ ድል
ኢትዮ1888 ሚድያ
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/channel/UC74xVlm9etNg3IWsuiXkyrA
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/ethio.1888/
በቴሌግራም
https://t.me/ethio1888media

02/03/2023

127ተኛው የአድዋ ድል እንዳይከበር ተከለከለ❗️

የፀጥታ ሀይሎች በፈጠሩት ግርግር፣ አስለቃሽ ጭስናበተተኮሰ ጥይት ምክንያት127ተኛው የአድዋ
ድል በአል የዳግማዊ ሚንሊክ ሀውልት በሚገኝበት ህዝቡ በአሉን ሳያከብር ቀረ።

አ....ድ...ዋ !

#127ተኛው የአድዋ ድል
ኢትዮ1888 ሚድያ
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/channel/UC74xVlm9etNg3IWsuiXkyrA
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/ethio.1888/
በቴሌግራም
https://t.me/ethio1888media

Ethio 1888 Media - YouTube 01/03/2023

የጦር መሪዎች እና የፈረስ ስሞቻቸው
*, አባ_ዳኘው………ዳግማዊ አፄ ምኒልክ
*,አባ_ታጠቅ………አፄ ቴዎድሮስ
*,አባ_በዝብዝ………አፄ ዮሐንስ
*,አባ_ጠቅል………አፄ ኃይለስላሴ
*,አባ_ዳምጠው………ንጉስ ኃይለመለኮት
*,አባ_ሻንቆ………ንጉስ ሚካኤል
*,አባ_ጤና………ልጅ እያሱ
*,አባ_ነፍሶ………ደጃዝማች ባልቻ ሳፎ
*,አባ_ኮስትር……ደጃዝማች በላይ ዘለቀ
*,አባ_መላ………ፊታውራሪ ሀብተጊዮርጊስ ዲነግዴ
*,አባ_ጎራው………ፊታውራሪ ገበየሁ
*,አባ_ዲና………ንጉስ ሣህለስላሴ
*,አባ_ገስጥ……ራስ አበበ አረጋይ
*,አባ_ንጠቅ ገብሬ………ደጃዝማች ገብረማርያም ጋሪ
*,አባ_ይትረፍ………ራስ አባተ
*,አባ_ግርሻ………ራስ ዳርጌ
*,አባ_ድልድል……ራስ ዘውዴ
*,አባ_ጥጉ………ራስ ጎበና
*,አባ_ጠጣው………ራስ ወሌ
*,አባ_ነጋ………ፊታውራሪ ሸዋዬ ጓንጉል
*,አባ_ኮራን………ደጃዝማች ዘውዴ
*,አባ_ቃኘው………ልዑል ራስ መኮንን
*,አባ_ጠቅልል………ራስ ስብሃት አረጋዊ
*,አባ_ነጋ………ራስ አሉላ
*,አባ_ቀስቅስ………ልዑል ራስ እምሩ ኃይለስላሴ
*,አባ_ይርጋ………ልዑል ራስ ስዩም መንገሻ
*,አባ_ቀማው………ራስ ደስታ
*,አባ_ትንታግ………ቀኛዝማች ታደሰ
*,አባ_ግርማ………ደጃዝማች ስዩም ሉልሰገድ
*,አባ_ሰይጣን………ደጃዝማች ወልደ ገብርኤል
*,አባ_መብረቅ………ራስ ናደው
*,አባ_ሙላት………ቢትወደድ ኃይለጊዮርጊስ
*,አባ_ደፋር………ደጃዝማች ባሻህ አቦዬ
*,አባ_ሰብስብ………ደጃዝማች በየነ
*,አባ_ክረምት………ደጃዝማች ስለሺ ወልደ ሰማዕት

#127ተኛው የአድዋ ድል
ኢትዮ1888 ሚድያ
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/channel/UC74xVlm9etNg3IWsuiXkyrA
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/ethio.1888/
በቴሌግራም
https://t.me/ethio1888media

Ethio 1888 Media - YouTube Share your videos with friends, family, and the world

28/02/2023

ምንሊክ የባርያ ንግድን በህግ ገድበዋል❗️

በአንድ ወቅት የጅማው ገዥ ዳግመዊ አባጅፋር በመባል የሚታወቁትና በምስራቅ አፍሪካም የጅማና አካባቢው ተወላጆችን" ባሪያ "የሚል ስም ሰጥተው የሰውን ልጅ እንደ እቃ በዋጋ ተምነው ሲሸጡ የተመለከቱትና መረጃው የደረሳቸው ንጉስ ምንሊክም እንዲህ ሲሉ ለጅማው ገዥ አባ ጅፋር መልክት ሰደዱላቸው" ደሀ በወደደበት ይቀመጥ ፤ሁላችንም የክርስቶስ ባሪያዎች ነን ። ከዛውጭ የሰውልጅ ሁሉ እኩል ነው። አቁም የባሪያ ንግድህን ካልሆነ ትጣላኛለህ" ሲሉ ሰውን መሸጥ የሚከለክለ ህግም አውጥተው ነበር። ምንሊክ እንኳን ለሰው ልጅ ለዱር አራዊትን ለሚያጠቁም የሚቀጡበት ህግ አርቅቀው እንደነበር የታሪክ ድርሳናት ይናገራሉ።

#127ተኛው የአድዋ ድል
ኢትዮ1888 ሚድያ
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/channel/UC74xVlm9etNg3IWsuiXkyrA
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/ethio.1888/
በቴሌግራም
https://t.me/ethio1888media

Photos from Ethio1888 media's post 28/02/2023

የኢጣሊያን ጦር ሁለቴ የገጠሙት ራስ ሀውልት እንደተገነደሰ ይገኛል❗️ ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን የት ነህ?

በዳግማዊ አጤ ምንይልክ ዘመን እና ከአርባ አመታት በኋላም በአጤ ኃ/ስላሴ ዘመን ከመጣው የኢጣሊያ ጋር ጦራቸውን ይዘው የተዋጉና ያዋጉ ፤በወቅቱ ከነበሩ ጥቂት የአፍሪካ ጀነራሎች አንዱና በኢትዮጵያ የውጭ ዲፕሎማሲ ዘርፍም ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱት ራስ መኮንን ወ/ጊዮርጊስ ናቸው። በሀገር ውስጥም ቢሆን እሳቸው ሲያስተዳድሩት በነበረው የሀረርጌ ክፍለ ሀገር መዘመን ጋርም ተያይዞ ቀላል የማይባል አስተዋፅኦ ማበርከታቸው በከተማው የቀሩ የታሪክ አሻራዎች ምስክ ናቸው። ይሁን እንጂ ንጉስ በሀገሩ አከበሩም እንደሚባለው ለእኚህ ታላቅ የሀገር ባለውለታ በሀረር ከተማ ለመታሰቢያነት የቆመላቸውን ሀውልት በቂ የታሪክ አረዳድና እውቀት በሌላቸው ፖለቲከኞች የተመሩ ወጣቶች 2012ሰኔ 23 አፍርሰውታል። መንግስትም ሆነ የሚመለከተው የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን ተገንድሶ ስለወደቀው የታሪክ አሻራ ተጨንቆ ከመስራት ይልቅ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ እዚህ ግባ አልያም ለማህበረሰቡ ጠቃ ነገር ያልሰጡ ግለሰቦች ን እየፈለጉ ሀውልት ማቆም ላይ ተጠምደዋል ። አንዳንዴ ለሀገር የለፉትን በማንኳሰስ አገር ያፈረሱትንና ህዝብን ከህዝብ የሚያባላ ሃሳብ አመንጪዎች ግን ሲሞገሱና ሲሸለሙ ይውላሉ። ታሪክ ስለማይሰሩ ታሪክ ሰሪዎችን እያሳደዱ ይኮረኩማሉ፤ምክንያቱም የእነሱን ድክመት ለመደበቅ። ወይ ጉድ! ሳገድሉ ጎፈሬ ሳያጣሩ ወሬ አለች ፍቅር አዲስ🤔 የጀግናው ራስ መኮንን ሀውልት ሀረር ላይ ከ2012 መጨረሻ ጀምሮ እስካሁን ተገንድሶ እንደወደቀ ነው። ኧረ የኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን የት ነህ?

ኢትዮ1888 ሚድያ
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/channel/UC74xVlm9etNg3IWsuiXkyrA
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/ethio.1888/
በቴሌግራም
https://t.me/ethio1888media

24/02/2023

የአፍሪካ ፊት አውራሪ፣ እንኳን ለሰው ልጆች ለአራዊት መብት የቀረፁ🙏 እንኳን ለ127ተኛው የአድዋ ድል አደረሳችሁ።

ኢትዮ1888 ሚድያ
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/channel/UC74xVlm9etNg3IWsuiXkyrA
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/ethio.1888/
በቴሌግራም
https://t.me/ethio1888media

22/02/2023

ዝክረ አድዋ!!

ዝክረ አድዋ ኢትዮጵያዊነት የተሰኘ ልዩ የኪነ-ጥበብ ዝግጅት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ማክሰኞ የካቲት 21 ቀን 2015 ዓ.ም ይቀርባል፡፡አዘጋጅ አብርሀም ግዛው ኢንተርቴመንት ‹‹ኢትዮጵያዊነት ዝክረ አድዋ› › የተሰኘ የምሁራን ጥናታዊ-ፅሁፍና፣ ዲስኩር የግጥም ምሽትናየስታንዳፕ ፣ ኮሜዲ ትልቅ የኪነ-ጥበብ እና የማነቃቂያ ዝግጅቶች እንዲሁም ስለ ሰላምና አንድነት ዙሪያ ላይ ታዋቂ ፖለቲከኞች ንግግር ያቀርባሉ፡፡ በእለቱ ዶ/ር መምህር ዘበነ ለማ፣መጋቢ ሀዲስ እሸቱ አለማየሁ ፣ አንባሣደር ዲና ሙፍቲ፣ደራሲ ገጣሚ ፀሀፊ ተውኔትና ባለ ቅኔ አያልነህ ሙላቱ፣ ፣የሰብአዊ መብት ተሟጋች ኦባንግ ሜቶ ፣ዶ/ር ወዳጄነህ ማህረነ፣ ዶ/ር ዮናስ ዘውዴ፣ የታሪክ መምህር ታዬ ቦጋለ ፣ኡስታዝ አቡበከር አህመድ፣ አርቲስት ሐረገወይን አሰፍ፣ ጋዜጠኛና ደራሲ ጥበቡ በለጠ ፣ አርቲስት ሰለሞን ቦጋለ በእለቱ ከጥንታዊ ኢትዮጵያ አርበኞች ማህበር ጀግኖች አርበኞች ሽለላን ፉከራ በሻሎም የባህል ባንድ ታጅበዉ ያቀርባሉ።

ተጋባዥ ሰርፕራይዝ እንግዶች በእለቱ በመገኘት መልክቶቻቸውን ያስተላልፋሉ፡፡ የዚህ የኢትዮጵያውያን የአፍሪካም ብሎም የጥቁር ህዝቦች የአሸናፊነት ምልክት በሆነው የአድዋ ድል ዋዜማ በሚካሄው ፕሮግራም ላይ ከፍተኛ የመንግስትየስራ ኃላፊዎች፣ታዋቂ ግለሰቦች ፣አርቲስቶች፣ጋዜጠኞች እና የስነ-ጽሁፍ አፍቃሪዎችና የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች በሚገኙበት ማክሰኞ የካቲት 21 ቀን 2015ዓ/ም ከቀኑ 11፡00 ሰአት ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ ይካሄዳል።

07/02/2023

የብልፅግና ማዕከላዊ ኮሚቴ አባሉ ስልጣናቸውን በወቅታዊ ጉዳይ ምክንያት መልቀቃቸዉን ገለፁ❗️

"በብልፅግና ፓርቲ የተሰጠኝን ኃላፊነት በፈቃዴ ለቅቂያለሁ!"
(አብርሃም አለኸኝ)

(መልቀቁ ትክክል ነው አይደለም፣ ለምን በብዕር ስሙ አሳወቀን ወዘተ የሚለው እንደተጠበቀ ሆኖ አቶ አብርሃም አለኸኝ የሚከተለውን ፅሁፍ ከዚህ በፊት በሚፅፍበት የብእር ስሙ አስቀምጧል።)
===============
ሃይማኖት ብቻ !!!

ፖለቲካና ፖለቲከኛ ባልተገናኘበት የፖለቲካ ባህል ውስጥ ፖለቲከኛ መሆን ትርፉ ስቃይ ብቻ ነው። የኔ በምትለው ፖለቲካ ውስጥ የእነሱ የሆነውን ትጨፈልቃለሁ። በጥቅምህ የመጡ ከመሰለህ የያዙትን አጀንዳ ሁሉ ለማስጣል ራስህን ብቸኛ ቅዱስ ታደርጋለህ። የአለም ፖለቲካ ጠባይ ይኸ ነው።

በኢትዮጵያ ሰማይ ስር በጠላትነት መፈራረጅን ሊያስቆም የሚችል ፖለቲካም ሆነ ፖለቲከኛ የለም። ጥላቻን መሰረት ያደረገ ፖለቲካ ይቅርታንና ርህራሄን የሚያውቅ ፖለቲከኛ ሊኖረው አይችልም። በጥላቻ መቃብር ላይ ራሱን መስዋዕት ማድረግ የማይችል ፖለቲከኛም የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ቁስል የመፈወስ ጉልበት አይኖረውም። የአገሪቷ ችግር ይኸ ይመስለኛል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አሁናዊ አደጋ ዛሬ የተጀመረ ሳይሆን አስርተ አመታትን የተሻገረ ጥላቻ ወለድ ውጥን ነው። ዛሬ የተመለከትነው ውጤቱን ነው። አገሪቷ ተንገዳግዳ እስክትወድቅ ድረስ ነገም ሌላ መልክ ይዞ ይቀጥላል። ሃይማኖትም ሆነ ምግባር የሌለው ትውልድ የመፍጠር ሁሉ አቀፍ ፕሮጀክትም ነው። ጠንካራ አገሮች የተፈረካከሱበትና ለሩስያና ለዩክሬን ወቅታዊ መካረር ስረምክንያት የሆነውም ይኸ ሀቅ ነው። የጋራ ጥቅምን ሰክኖ ከማየት ይልቅ የኔ ብቻ የሚል ባዕድ ፍላጎት።

መፍትሄው ከፖለቲካና ከፖለቲከኞች ፈቀቅ ብሎ (ርዕዮተ ዓለማዊ ግጭት ስለሚጫናቸው ቤተክርስቲያኗንም ሆነ ህዝበ ክርስቲያኑን ያደናግሩታል ብየ ስለምሰጋና የትችትን በር ለመዝጋት ስለሚጠቅም) የተጀመረውን አንድነት አጠናክሮ መቀጠል፤ ሰክኖና ተደማምጦ ልባዊ ምክክር ማድረግ፤ ከቤተክርስቲያኗ ዋኖች ጋር ተመካክሮ ዘላቂ መፍትሄ ማበጀት ያስፈልጋል ። በምድረ ኢትዮጵያ የምትገኘዋን አሐቲ ቅድስት ቤተክርስቲያን በእርግጥም የአገር ፈርጥ ማድረግ ይገባል። አጀንዳው ሃይማኖት ብቻ ሲሆን ነው በዕኩይ ፖለቲከኞች ከመጠለፍ አደጋ ተጠብቆ ማሸነፍ የሚቻለው።

ኦርቶዶክስ አገር ናት በሚል ጥቅል ሀሳብ ከመታጠር ወጥቶ ጉዳዩን አምልቶና አስፍቶ መረዳትና ማስረዳትም ይገባል።

አዎ ኦርቶዶክስ አገር ናት። ታላላቆቸ ቆነፀልከው እንዳይሉኝ እንጂ:-

በየጊዜው የተነሱ ፖለቲከኞች ወዲያና ወዲህ እያላጉ ሌላ ቀለም እንዲሰጣት አደረጉ እንጂ የእስልምናን፣ የካቶሊክን፣ የፕሮቴስታንትንና የአይሁድን እምነት በጨዋ ባህልና በትህትና ተቀብላ ያስተናገደች፣ በፍትህ ርቱዕ የምታምን፣ የብዝሀነት መሰረትና ስንዱ እመቤት ናት። እንደአለመታደል ሆኖ ቤተክርስቲያኗን ለመክሰስና ለመውቀስ ሲፈለግ "ቀዳሽና አንጋሽ" በሚል ምፀት ይሞግቷታል። በተቃራኒው በዚህ ሙሉ የስልጣን ክብር በነበረችበት ዘመን ለብዝሀነት መከበር የነበራትን አበርክቶ በደምሳሳው እናልፈዋለን። የዴሞክራሲ ፍልስፍና በውል በማይታወቅበት በዚያ ዘመን የመንግስት ድርሻ ስላለኝ እኔ ብቻ በሚል ጭፍን ብሂል አልታጠረችም።

ጥንታዊ መንግስታት በየዘመናቸው ለሚፈጥሩት የህልውና ስጋት ቤተክርስቲያኗን ተጠያቂ ማድረግ የፈጠረው ጥላቻ አምርረው በሚጠሏት ወገኖች በኩል ዱላ እንዲበዛባት አድርጓል። የቤተክርስቲያኗን መለያዎች ሁሉ ብንመለከት መለኮታዊ እንጂ ስጋዊ አይደለም። ስለአገር መሪዎች መፀለይ የቤተክርስቲያኗ ርቱዕ ግብረገብ መገለጫ እንጂ ሌላ ትርጉም የሚያሰጥ ሊሆን አይችልም። እነዚህንና መሰል ጉዳዮችን በመሰንጠቅ ልጆቿን መከፋፈል ያስተዛዝብ ካልሆነ በስተቀር የቤተክርስቲያኗን አገርነት አያጎድለውም።

ቤተክርስቲያኗ ከአስራ ምዕት ዘለግ ባለው ታሪኳ ያቀፈቻቸው ምዕመናንና ምዕመናት ከአንድ ወገን ብቻ የተቀዱ ይመስል የፅርፈት ናዳ ማግተልተል ነውር ነው። ትክክል አይደለም እንጂ ትክክል ነው ቢባል እንኳ አሁን ላለንበት ሁኔታ የሚጠቅም እንጥፍጣፊ ፋይዳ የለውም።

ሶርያዊ፣ ግብፃዊ፣ አርመናዊ፣ ሊቢያዊ፣ ቱርካዊ ፣ ግሪካዊ፣ ሮማዊ....አበውና እመው ተቀብላ በረከታቸውን ያገኘችና በቃላቸውና በህይወታቸው ከሚፈሰው የትምህርታቸው ጅረት የተደራጀችንና የፀናችን ቤተክርስቲያን የሆነ አውራጃ አክስዮን አድርጎ መፈረጅ "በሬ ሆይ በሬ ሆይ ሳሩን አየህና ገደሉን ሳታይ" አይነት መጤ ስሁት ትርክት ነው።

ቀለም በጥብጣ፣ ብራና ዳምጣ፣ ብዕር ቀርፃ፣ ቋንቋን ከእነፊደሉ፣ የዘመን አቆጣጠር ፍልስፍናን ከእነቀመሩ ሰንዳ ከፍትሐነገስት እስከ ዘመናዊ ህገመንግስት አዘጋጅታ ስርአተ መንግስትን ላፀናችና የታሪክ መዛግብት ለሆነች አሀቲ ቤተክርስቲያን ፅርፈት አይገባትም። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ለሁሉም እምነቶች አክብሮት እንዳላት በብዙ መለኪያዎች ማስረዳት ይቻላል። ለዚህ ነው ኦርቶዶክስ አገር ናት ይሚባለው።

የጥላቻ ታሪክ መንስኤው የፖለቲከኞች እንጂ የቤተክርስቲያኗ አይደለም። አንድ አንድ በቤተክርስቲያኗ ስም የተነሱ ፀሀፍት ሆን ብለውና በቸልተኝነት የገደፉትንና የፀረፉትን ስህተት በመጥቀስ ቤተክርስቲያኗን አውራጃዊና ዘውጋዊ ካባ በማልበስ ማጠየም የክፉዎች ሴራ እንጂ ትክክለኛ መልኳ አይደለም። ከቤተክርስቲያን የስዕል ጥበብ ታሪክ ጋር በማያያዝ እገሌ ለሚባለው ንጉሰ ነገስት ታደላለች፣ እንዲወደስ ታደርጋለች የሚለው ክስ የወቅቱን ባህላዊ መስተጋብር (the cultural effect of state society relationship) በተዛባ መንገድ በመገንዘብ የሚመጣ ስሁት ብያኔ ነው።

ይህንን ማንሳት ያስፈለገው ለአሁናዊው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንና አገሪቷ ላለችበት ፖለቲካዊ ምስቅልቅል ስረ ምክንያት የሆነውን የተቀናጀ ፖለቲካዊ ሴራ ለመጠቆም ነው።

ፖለቲካ የቤተክርስቲያኗ ካንሰር ነው የምለው በምክንያት ነው። ከቤተክርስቲያኗ መሰረታዊ እውነት በተቃርኖ የተሰለፉት ፖለቲከኞች ደግሞ የካንሰሩ መንስኤ ናቸው። አሁን ላይ ቤተክርስቲያኗን እየናጣት ያለው ግራና ቀኝ የተሰለፈ ፍፁም ገለልተኛ ያልሆነ የፖለቲካ ጨዋታ ነው። አገር የማፍረስ የቆየ ዕቅድ ያላቸው ፖለቲከኞች የአገር ምልክት የሆነችውን ቤተክርስቲያን በመከፋፈል ጀምረውታል።

ለቤተክርስቲያኗ የወገኑ የሚመስሉ ስውር ፖለቲከኞችም ከጀርባ ሆነው የቤተክርስቲያኗ አላማ ባልሆነ የትግል ስልት (አግላይና ከፋፋይ) መንፈሳዊ ቀለሟን ሲደልዙ ይስተዋላሉ። ከችግሩ ፊት የሚታዩት አካላት ግን ህጋዊው፣ መንፈሳዊውና ሰማያዊው ሲኖዶስና ህገወጥ በሚል የተጠቀሱት የእምነት አባቶች ናቸው።

የቤክርስቲያኗ ልጆች ይህንን ስውር ደባ በውል የተረዱት አይመስልም። እነዚህ የእፉኝት ፖለቲካ አቀንቃኞች ቤተክርስቲያንን የመሰንጠቅ ግባቸውን ካሳኩ በኋላ በሁሉም የኢትዮጵያ አውራጃዎች ለሚገኙ ምዕመናንና ምዕመናት የሚያተርፉለት ነገር ቢኖር ለቅሶና ዋይታ ጥርስ ማፋጨት ብቻ ነው።

ከፖለቲካም ሆነ ከፖለቲከኞች ጥድፍያና ትንቅንቅ ፈቀቅ ብለን፣ ለመንፈሳዊና ሰማያዊ ዜግነት ያደላ ወይም የወገነ ስነልቦና ገንዘብ እናድርግ። በባህርይ ክርስቶሳዊት የሆነችዋን ቤተክርስቲያንን እናስብ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን በማጎሳቆል ወርቅ የሚጨብጡ የሚመስላቸው ስውር እጆች በተለይም የአገሬ ሰዎች አውራ እያጠፋችሁ መሆኑን ተረዱት። አውራውን ማጥፋት መንጋውን መበተን ነው። አንድ ቀን አውራ ሊያስፈልጋችሁ እንደሚችል ማሰብ ይጠቅማችኋል።

እንኳንስ ቤተ እምነት (ክርስትና፣ እስልምና፣ ካቶሊክ ሙሉ ወንጌል፣ መካነ ኢየሱስ....) የጋሞ ሽማግሌዎች በቁጣ የገነፈሉ ልጆቻቸው ፊት በመንበርከክ ያስቀሩትን መአት (ሊፈጠር የሚችል የቅርብ አደጋ) ማስታወስ ግድ ይላል።

ቤተ-እምነቶችማ ይኑሩ ....አይከፋፈሉ ...
በመከራችን ቀን....እንዲሸመግሉ።

ቤተክርስቲያን በጥልቅ ሀዘን ውስጥ ትገኛለች። ብሽሽቁ ጊዚያዊና ፖለቲካዊ ነው። ለማንም ስለማይጠቅም እንተወው። ከስጋ ፈቃድ ፈቀቅ ብለን ከማይነጥፍ መንፈሳዊ ጓዳዋ ያሻንን ለመቅዳት ፣ ቀድተንም ለመጠጣት፣ ጠጥተንም ለመርካት ዝግጁ እንሁን። ልሳንም ሆነ ባለብዙ ልሳን ሐዋርያት የሚቸግራት ቤተክርስቲያን አይደለችም።

እየሆነ ያለው ነገር ሁሉ ግን በእውነት ያማል። ሰው መሆንንም አያስመኝም። ሁለት ክፍለዘመን የተሻገረችን አሐቲ ቤተክርስቲያን ፈቅዶና ወዶ ለማጎሳቆል ከመወሰን በላይ ታሪካዊ ስህተት የለም። በኢትዮጵያ ሰማይ ስር የተዘራው ጥላቻ የአገሪቷን ምሰሶ እየነቃቀለ በመጣል አገር እስከማፍረስ ሊደርስ የሚችል ግብ ያለው ነው።

ይህማ ባይሆን ኖሮ አንድ እንኳን ነፍስ ያለው የተደራጀ ተቋም ባልተፈጠረበት አገር (በኔ ግምት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ውጭ አብዛኞቹ ተቋማት በጅምር የግንባታ ሂደት ውስጥ ያሉ ናቸው) አስራ ምዕት የተሻገረን ተቋም በዚህ ልክ መነቅነቅ ባልተሞከረ ነበር። የእፉኝት ፖለቲካ ማለት ይኸ ነው።

ፖለቲካ ዜግነት ቢኖረው ኖሮ በጥቅሉ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ዜግነቱ መሰረዝ ነበረበት !!!

በኔ ዘመን ይህንን ስላየሁ መፈጠሬን ጠልቸዋለሁ።

የፓርቲ ፖለቲካ ልገልፀው በማልችለው አሳማኝ ምክንያት (መፍትሄ ባይሆንም) እርም እንድል ተገድጃለሁ።

በብልፅግና ፓርቲ የተሰጠኝን ኃላፊነት በፈቃዴ ለቅቂያለሁ !

የማሰብም ሆነ የመናገር ተፈጥሯዊ ነፃነቴ ያለበትን መንገድ መርጫለሁ !!!

ፈጣሪ ከሆነውና ከሚሆነው መከራ ይሰውረን !!
ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም.

28/01/2023

ኢትዮ1888 ሚድያ
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/channel/UC74xVlm9etNg3IWsuiXkyrA
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/ethio.1888/
በቴሌግራም
https://t.me/ethio1888media

25/01/2023

አቶ በረከት ስሞኦን ከእስር መፈታታየቸው ተሰማ!

ምንጭ ሪፖርተር

ኢትዮ1888 ሚድያ
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/channel/UC74xVlm9etNg3IWsuiXkyrA
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/ethio.1888/
በቴሌግራም
https://t.me/ethio1888media

25/01/2023

ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ውጪ የሚደረግን ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳት እንደማይቀበል የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በአቋም መግለጫው አስታውቋል።

የአቋም መግለጫ

ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ታዋድሮስ ዳግማዊ የመንበረ ማርቆስ ፓትርያርክ
ልዩ ጽሕፈት ቤት፣

ካይሮ፡ 24 ጃንዋሪ 2023 ዓ/ም (ጥር 16 ቀን 2015 ዓ/ም)

የአቋም መግለጫ

የእስክንድርያ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ አቡነ ሳዊሮስ በተባሉ ጳጳስ የተፈጠረውን ቤተ ክርስቲያንን የመክፈልና ራሳቸውን በኢትዮጵያ የኦሮሞ ክልል ፓትርያርክ አድርገው የመሠየም ተግባር ሙሉ ለሙሉ የማይቀበለው ፍጹም ሕግን የጣሰ መሆኑና እና በእሳቸው መሪነት ተሾሙ የተባሉ 26 ጳጳሳት የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሕግ የጣሱ እንዲሁም መሠረት ያለውን እና ቋሚ የሆነን ከጥንት ጀምሮ በትውልዱ ሁሉ ሲተላለፍ ከመጣውን ከኦርቶደክስ ቀኖና እና መመሪያ ሕገ ወጥ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

የእስክንድርያ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ከሕጋዊው የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ዕውቅና ውጭ የሚደረግን ሢመት ዕውቅና አትሰጥም አትቀበልም።

ከዚህ በተጨማሪ ኮሚቴው (የውጭ ጉዳይ) ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጋር ያለውን ወዳጅነት እና አጋርነት እየገለጽን፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጳጳሳት፤ ሜትሮፖሊታን የሆናቸሁ ሁላችሁ ጥንታዊነት እና በታሪክ የበለጸገች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አንድነት እና ትሥሥር በፍቅርና በሰላም ሁናችሁ እንድትጠብቁ በጥብቅ አደራ እንላለን፡፡

የእስክንድርያ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ አባ ቶማስ የቂሊያ ሜትፖሊታን እና የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ ዋና ጸሐፊ።

ምንጭ፡ EOTC TV

ኢትዮ1888 ሚድያ
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/channel/UC74xVlm9etNg3IWsuiXkyrA
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/ethio.1888/
በቴሌግራም
https://t.me/ethio1888media

17/01/2023

በስምንተኛው የአፍሪማ ውድድር ኢትዮጵያውያኑ ድምጻውያን አሸነፉ

ኢትዮጵያውያን ድምጻውያን በዘንድሮው የመላው አፍሪካ የሙዚቃ ሽልማት (አፍሪማ) በተለያዩ የሙዚቃ ዘርፎች ማሸነፋቸው ተሰማ።
በስምንተኛው የአፍሪማ ሽልማት በተለያዩ ዘርፎች ታጭቶ የነበረው ካሥማሰ 'ሰዋሰው' በተሰኘ ሥራው በምርጥ የምሥራቅ አፍሪካ አርቲስት ዘርፍ ማሸነፍ ችሏል።
ካሥማሰ ታጭቶባቸው የነበሩት ዘርፎች ምርጥ የምሥራቅ አፍሪካ አርቲስት እና ምርጥ የአፍሪካ አነቃቂ ሙዚቃ ሲሆን በምርጥ የአፍሪካ የሙዚቃ ቪዲዬ ዘርፍ 'ሰዋሰው' በተሰኘው ሙዚቃው ማራናታ ተገኘ ታጭታለች።
ሌላው አሸናፊ ጉቱ አበራ ሲሆን ‘ዴሚ’ በተሰኘው ዘፈኑ በምርጥ የአፍሪካ ጃዝ አርቲስት/ጥምረት ዘርፍ አሸንፏል።
ጉቱ በትዊተር ሰሌዳው ላይ እንዳሰፈረው 'ዴሚ' በተሰኘው ሙዚቃው ምርጥ የአፍሪካ ጃዝ አርቲስት/ጥምረት በማሸነፉ ደስታ እንደሚሰማው ገልጿል። "በአፍሪካ የተከበረ ውድድር ማሸነፍ ክብር ነው" ሲልም ጽፏል።
በዚህ ዘርፍ አዲስ ለገሰ ‘እንጃ’ በተሰኘው ዘፈኑ ሲካተት ጃኖ ባንድ በ ‘ዘብናናው’ ሙዚቃም ታጭተዋል።
በሴኔጋል ዳካር በተካሄደው ስምንተኛው ‘ኦል አፍሪካ ሚውዚክ አዋርድ’ ወይም አፍሪማ ውድድር ላይ ቴዲ አፍሮ ፣ ቤቲ ጂ፣ ሔዋን ገብረወልድ፣ አዲስ ለገሰ እና ሌንጮ ገመቹ በተለያዩ ዘርፎች የታጩ ኢትዮጵያውያን ነበሩ።
በዘንድሮው የአፍሪማ ውድድር ቤቲ ጂ በምሥራቅ አፍሪካ ምርጥ ድምጻዊት ዘርፍ ‘ሰማይ’ በተሰኘው ዘፈኗ ፣ አዲስ ለገሰ ደግሞ በምሥራቅ አፍሪካ ድምጻዊ ዘርፍ ‘እንጃ’ በተሰኘው ዘፈኑ ታጭተዋል።

በምሥራቅ አፍሪካ ምርጥ ድምጻዊት ዘርፍ ሔዋን ገብረወልድ ‘ሼሙና’ በተባለው ሙዚቃዋ ትገኛለች።
በምርጥ የአፍሪካ ባንድ ሥር ጃኖ በ ‘ዘብናናው’፣ በምርጥ የአፍሪካ ሬጌ፣ ራጋ እና ዳንሶል አርቲስት/ጥምረት ዘርፍ ቴዲ አፍሮ በ ‘ናዕት’ ታጭተዋል።
በምርጥ የአፍሪካ ባህላዊ ሙዚቃ አርቲስት/ጥምረት ዘርፍ ቤቲ ጂ በ‘ሰማይ’ ዘፈኗ፣ ሌንጮ ገመቹ በ ‘ሰግሊ’ እና በዓመቱ አዲስ ታዋቂ ዘርፍ ደግሞ ሔዋን ገብረወልድ ‘ሼሙና’ በተባለው ሙዚቃ ታጭተዋል
በዘንድሮው አፍሪማ ናይጄርያውያኑ አሳኪ፣ በርና ቦይ እና ዴቪዶ በርካታ ሽልማቶች ሰብስበዋል።
አሳኪ የዓመቱ አዲስ ታዋቂ ዘርፍ አሸናፊ ሲሆን፣ በርና ቦይ የዓመቱ ምርጥ አርቲስት፣ ዴቪዶ የዓመቱ ምርጥ አነቃቂ የአፍሪካ አርቲስት፣ ዊዝኪድ ደግሞ የዓመቱ ምርጥ የምዕራብ አፍሪካ አርቲስት ተብለዋል።
‘ታላ’ የተሰኘው የአይቮሪ ኮስታዊው ዲቢ ቢ ሙዚቃ የዓመቱ ምርጥ ዘፈን ተብሏል።
ሴኔጋል አፍሪማን በማዘጋጀት የመጀመሪያዋ ፈረንሳይኛ ተናጋሪ አፍሪካዊ አገር ሆናለች።
ኢትዮ1888 ሚድያ
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/channel/UC74xVlm9etNg3IWsuiXkyrA
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/ethio.1888/
በቴሌግራም
https://t.me/ethio1888media

14/01/2023

ኢትዮ1888 ሚድያ
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/channel/UC74xVlm9etNg3IWsuiXkyrA
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/ethio.1888/
በቴሌግራም
https://t.me/ethio1888mediaኢትዮ1888 ሚድያ

25/12/2022

ቀስተ ንኀብ"
ያልተነገረው የሸዋ አናብስት ጀግንነት

በረ/ፕሮፌሰር ሲሳይ አውግቸው የተፃፈው እና 365 ገፅ ያለው " ቀስተንኀብ" ያልተነገረው የሸዋ አናብስት ጀግንነት በሚል የተፃፈው መፅሀፍ ዛሬ ታህሳስ 16/2015 ዓ. በርካታ ሙህራንና የሚዲያ ባለሙያዎች በተገኙበት ራስ አንባ ሆቴል በይፋ ተመርቆ ለአንባቢያን ይፋ ተደርጓል።

ኢትዮ1888 ሚድያ
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/channel/UC74xVlm9etNg3IWsuiXkyrA
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/ethio.1888/
በቴሌግራም
https://t.me/ethio1888media

13/12/2022

ታህሳስ 4/2015

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር በሚገኙ የመንግስት ትምህርት ቤቶች ውስጥ ለሚነሱ ሁከቶች መንግስት በቂ ትኩረት በመስጠት ጉዳዩ ከቁጥጥር ውጭ ከመውጣቱ በፊት አስቸኳይ ዘላቂ መፍትሔ ይስጥ ሲል መግለጫ ሰጠ!

መግቢያ፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር በሚገኙ የተለያዩ የመንግስት ትምህርት ቤቶች ውስጥ በተደጋጋሚ ጊዜ ከኦሮሚያ ክልል ባንዲራ እና ከመዝሙር ጋር ተያይዞ ሁከቶች ተነስተዋል እነዚህንም አለመግባባቶች ተከትሎ የተለያዩ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች በትምህርት ቤቶች ሰላም ማጣት፣ የአካል ጉዳትና ንብረት ውድመት እንዲሁም ሌሎችም ተፈጽመወል፡፡

ባሳለፍነው ዓመት 2014 ዓ.ም በለሚ ኩራ ፣ በየካ፣ በቂርቆስ እና በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማዎች ውስጥ በሚገኙ የተወሰኑ የመንግስት ትምህርት ቤቶች ውስጥ ከኦሮሚያ ክልል ባንዲራ እና መዝሙር ጋር ተያይዞ ሁከቶች ተነስተው እንደነበር እና ይህንንም ተከትሎ የሚመለከታቸው የክፍለ ከተማ ትምህርት ቢሮ ተወካዮች፣ ወላጆች እና የትምህርት ቤቶች አመራሮች ባደረጉት ስብሰባ እና ውይይት ጉዳዩ በጊዜያዊነት ተፈትቶ ቆይቶ እንደነበር ይታወሳል፡፡

ይህ ጉዳይ በቂ ትኩረት ባለማግኘቱና በዘላቂነት ባለመፈታቱ በ2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር ባሉ ትምህርት ቤቶች ውስጥ አለመግባባቶች ሊቀጥሉ ችለዋል፡፡ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በሚገኙት የሽመልስ ሀብቴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ የአብዮት ቅርስ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የጠመንጃ ያዥ አንደኛ ደረጃና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ከኦሮሚያ ክልል ባንዲራ እና መዝሙር ጋር ተያይዞ አለመግባባቶች የተነሱ ሲሆን በዚህም ምክንያት የተለያዩ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ተፈጽመዋል፡፡

እነዚህ ትምህርት ቤቶች የተፈጠረውን አለመግባባት ለመፍታት ከወላጆች ጋር በ13/02/2015 ዓ.ም ስብሰባዎችን ያደረጉ ሲሆን የቋንቋ ትምህርቱ ላይ አለመግባባት እንደሌለ ነገር ግን ዋነኛ አለመግባባቶችን እየፈጠረ ያለው የሰንደቅ አላማ እና የመዝሙር ጉዳይ መሆኑን እንዲሁም ልጆች የማያውቁትን መዝሙር እንዲዘምሩ መገደድ የለባቸወም የሚሉ ሃሳቦች በስብሰባዎቹ ላይ መነሳታቸውን ኢሰመጉ የክትትል ስራን ለመስራት በአካል በስብሰባዎቹ ላይ በመገኘት ለመረዳት ችሏል፡፡

ነገር ግን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ስር በሚገኘው ጠመንጃ ያዥ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ሁከቱ በድጋሚ አገርሽቶ በ29/03/2015 ዓ.ም እና በ30/03/2015 ዓ.ም ዳግም መነሳቱን እና በዚሁ ሁከት ምክንያት በርካታ ተማሪዎች ላይ ድብደባ መፈጸሙን፣ የትምህርት ቤቱ ንብረቶች መውደማቸውን፣ በአንድ የፖሊስ አባል ላይ ድብደባ መፈጸሙን እና ከዚሁ ጋር ተያይዞ ቁጥራቸው ለጊዜው ያልታወቁ ተማሪዎችና የአካባቢው ነዋሪዎች መታሰራቸው ታውቋል ኢሰመጉ ካሰባሰባቸው መረጃዎች ለመረዳት ችሏል፡፡

በጉለሌ ክፍለ ከተማ በእንጦጦ አምባ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ22/03/2015 ዓ.ም በተመሳሳይ ሁኔታ ከሰንደቅ አላማ እና መዝሙሩ ጋር ተያይዞ በትምህርት ቤቱ ሁከት ተነስቶ ንብረት መውደሙን፣ በተማሪዎች ላይ ድብደባ እና እስራት መፈጸሙን እና በእዚህ የተነሳ የመማር ማስተማሩ ሥራ መስተጓጎሉን ኢሰመጉ ካሰባሰባቸው መረጃወች ለመረዳት ችሏል፡፡ ይህንንም ተከትሎ ኢሰመጉ ለትምህርት ቤቱ በደብዳቤ ቁጥር EHRCO- C/E/011/049/15 በቀን 26/03/2015 ዓ.ም መረጃ እንዲሰጠን ጠይቆ የነበር ሲሆን በጥያቄው መሰረት ትምህርት ቤቱ የተባለው ሁከት መፈጠሩን፣ ለሁከቱም መነሻ የነበረው የኦሮሚያ ክልል ባንዲራ በትምህርት ቤቱ እንዲሰቀል እና መዝሙሩ እንዲዘመር በሚፈልጉ እና በማይፈልጉ ተማሪዎች መካከል የተፈጠረ አለመግባባት መሆኑን፣ በእዚህም ምክንያት ንብረት ላይ ጉዳት እንደደረሰ፣ ትምህርት ቤቱ የሚያውቀው ሶስት ተማሪዎች እንደታሰሩ እና በአንድ ተማሪ ላይ የአካል ጉዳት እንደደረሰ ለኢሰመጉ ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም በ03/04/2015 በእንጦጦ አምባ ትምህርት ቤት ዳግም ሁከት የተነሳ ሲሆን በዚህም ምክንያት ተማሪዎች እና መምህራን ላይ ጉዳት መድረሱን እና በጊዜያዊነት ፖሊሶችን ወደ ጊቢው በማስገባት ችግሩን ለመቆጣጠር መቻሉን ኢሰመጉ ካሰባሰባቸው መረጃዎች ለመረዳት ችሏል፡፡

በተመሳሳይ በጉለሌ ክፍለ ከተማ በ23/03/2015 ዓ.ም አምሀ ደስታ ትምህርት ቤት፣ ድል በትግል እና አዲስ ተስፋ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራንና ተማሪዎች ከሰንደቅ አላማ እና መዝሙር ጋር ተያይዞ በተፈጠረ አለመግባባት ግቢውን ለቀው መውጣታቸወን ኢሰመጉ ካሰባሰባቸው መረጃዎች ለመረዳት ችሏል፡፡

በየካ ክፍለ ከተማ በሚገኘው ከፍተኛ 12 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ26/03/2015 ዓ.ም ከሰንደቅ አላማ እና መዝመር ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ሁከት ተነስቶ የነበረ ሲሆን በአካባቢውም የተኩስ ድመጽ ነበር፡፡ ኢሰመጉ በእለቱ በቦታው በመገኘት ባሰባሰበው መረጃ መሰረት የአንድ ተማሪ ህይወት ማለፉንና ከአስር በላይ ተማሪዎች እና አንድ አስተማሪ ተጎድተው ሆስፒታል መግባታቸውን ለመረዳት ችሏል፡፡

በዚሁ መነሻነት በትምህርት ቤቱ የተከሰተውን ሁኔታ በተመለከተ ተምህርት ቤቱ መረጃ እንዲሰጥ በደብዳቤ ቁጥር EHRCO-C/E/012/04715 በቀን 27/03/2015 ዓ.ም ኢሰመጉ የጠየቀ ቢሆንም ይህ መግለጫ እስከወጣበት ጊዜ ድረስ ከትምህርት ቤቱ ምንም አይነት ምላሽ አልተገኘም፡፡

በእዚሁ ክፍለ ከተማ ውስጥ በሚገኘው በወንድራድ ትምህርት ቤት ውስጥ በ03/04/2015 ዓ.ም በተመሳሳይ ምክንያት ሁከት የተነሳ ሲሆን በእዚህም ምክንየት በተማሪዎች እና በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን ኢሰመጉ ካሰባሰባቸው መረጃዎች ለመረዳት ችሏል፡፡

በተጨማሪም ህዳር 28 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከሰንደቅ አላማ እና መዝሙር ጋር ተያይዞ ሁከት መነሳቱን እና ይህንን ተከትሎ ከተማሪዎች ሲወረወሩ በነበሩ ድንጋዮች በትምህርት ቤቱ በርና መስኮቶች ላይ ጉዳት መድረሱን እና በዚህም ምክንያት በርካታ ተማሪዎች መታሰራቸውን ኢሰመጉ ካሰባሰባቸው መረጃዎች ለመረዳት ችሏል፡፡ በተመሳሳይ በ03/04/2015 ዓ.ም በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ውስጥ በሚገኙት አየር ጤና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና ሚሊኒየም የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስት ከእዚሁ ከኦሮሚያ ክልል ባንዲራ እና መዝሙር ጋር ተያይዞ ሁከቶች መነሳታቸውን እና በእዚህም ምክንያት በተማሪዎች ላይ ድብደባ መፈጸሙን እና በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን ኢሰመጉ ካሰባሰባቸው መረጃዎች ለመረዳት ችሏል፡፡

ኢሰመጉ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውስጥ ባሉ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ከኦሮሚያ ክልል ባንዲራና መዝሙር ጋር ተያይዞ በተደጋጋሚ ስለሚፈጠሩ ሁከቶች እና እነሱንም ተከትሎ ስለደረሱ የተለያዩ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን አስመልክቶ የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ስለጉዳዩ ዝርዝር ማብራሪያ እንዲሰጥ በደብዳቤ ቁጥር EHRCO-C/E/014/048/15 በቀን 27/03/2015 ዓ.ም የጠየቀ ቢሆንም የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ይህ መግለጫ እስከወጣበት ጊዜ ድረስ ምንም አይነት ምላሽ አልሰጠም፡፡ በተጨማሪም ኢሰመጉ ከላይ በተዘረዘሩት ጉዳዮች ላይ ከአዲስ አበባ ፖሊስ በስልክ መረጃን ለማግኘት ተደጋጋሚ ሙከራን ቢያደርግም ሳይሳካ ቀርቷል፡፡

ተያያዥ የህግ ድንጋጌዎች፡
የሰብዓዊ መብቶች ዓለም አቀፍ መግለጫ አንቀጽ 26 እና የኢኮኖሚ፣ የማህበራዊና የባሕለዊ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃልኪዳን አንቀጽ 13 ሰዎች የመማር መብት እንዳላቸው፣ ቢያንስ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ነጻና አስገዳጅ እንደሆነ፣ የተግባረዕድነና የሙያ ትምህርተ በጠቅላላ እንዲዳረስ እንደሚደረግ እና የከፍተኛ ትምህርት ደግሞ በችሎታ ላይ ተመስርቶ ለሁሉም እኩል ዕድል እንዲሰጥ መደረግ እንዳለበት እና ወላጆች ለልጆቻቻው የሚሰጠውን የትምህርት ዓይነት ለመምረጥ የቅድሚያ መብት እንዳላቸው እንዲሁም ትምህርት መግባባትን፣ በሕዝቦች፣ በተለያዩ ዘሮችና በሀይማኖቶች መካከል መቻቻልንና ወንድማማችነትን ማበረታታትና የተባበሩት መንግስታት ለሰላም ጥበቃ የሚያደርገውን ጥረት የሚያራምድ መሆን እንደሚገባው ይደነግጋሉ፡፡

የኢፌዴሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 90 ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የትምህርት ዋስትና እንዲኖረው እንደሚደረግ እና ትምህርት በማናቸውም ረገድ ከሀይማኖት፣ ከፖለቲካ አመለካከቶች እና ከባህላዊ ተጽእኖዎች ነጻ በሆነ መንገድ መካሔድ አንዳለበት ይናገራል፡፡

የኢሰመጉ ጥሪ፡
#መንግስት በአዲስ አበባ ከተማ አስስዳደር ስር በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ውስጥ በተደጋጋሚ ከኦሮሚያ ክልል ባንዲራ እና መዝሙር ጋር ተያይዞ ለሚነሱ አለመግባባቶችና ግጭቶች ዘላቂ መፍትሔ እንዲሰጥ፣

 በትምህርት ቤቶች የሚሰጥ ትምህርት እና የሚከናወኑ ስርአቶች በማናቸውም ረገድ ከሀይማኖት፣ ከፖለቲካ አመለካከቶች እና ከባህላዊ ተጽእኖዎች ነጻ በሆነ መንገድ መከወን እንዳለባቸው የኢፌዴሪ ህገ መንግስት እንዲሁም ሌሎች ህጎች በግልጽ አስቀምጠዋል በተጨማሪም ብዝሃነት እና ህብረ ብሔራዊ አንድነት በሚንጸባረቅባት እና ወደፊትም ሊንጸባረቅባት በሚገባ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የከተማው ነዋሪ በግልጽ ፈቃደኝነቱን ባልገለጸበት ሁኔታ የአንድን ክልል ባንዲራ እና መዝሙር እንዲዘመር በማስገደድ ምክንያት በተማሪዎች፣ በመምህራን፣ በወላጆች እንዲሁም በንብረት ላይ እየደረሰ ያለው ጉዳት ምንም አይነት የህግም ሆነ የአሰራር መሰረት ስለሌለው ሊቆም እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የሚመለከታቸው የከተማ አስተዳደሩ ቢሮዎች ይህንን ከግምት ባስገባ መልኩ እንዲሁም ህግን እና የከተማውን ነዋሪ ፈቃድ እና ፍላጎት ከግምት ውስጥ ባስገባ መልኩ ህጋዊ የሆነ ዘላቂ መፍትሔን እንዲያበጁ እና በእዚህ ውስጥ እጃቸው ያለበት አካላት ከእዚህ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ፣

 በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የተነሱ ሁከቶችን ተከትሎ በተማሪዎች እና በመምህራን ላይ የሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን እንዲያስቆም፣

 በአዲስ አበባ ከተማ አስስዳደር ስር በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የተፈጠሩ ሁከቶችን ተከትሎ በርካታ ቁጥር ያላቸው ሰዎች ተይዘው በፖሊስ ጣቢያ ውስጥ የሚገኙ በመሆኑ መንግስት ተገቢውን ማጣራት በማድረግ ንብረት እንዲወድም ምክንያት የሆኑትን እና ንብረት ያወደሙ ሰዎችን በመለየት በህግ ተጠያቂ እንዲያደርግ፣

 ይህን ጉዳይ ሰላማዊ መፍትሄ እንዳያገኝና ወደተባባሰ አለመግባባት እንዲያመራ በተለያዩ መግናኛ ዘዴዎች የሚደረጉ ግጭት ቀስቃሽ ንግግሮችን ከማድረግ ሁሉም አካል እንዲቆጠብ፣

 ትምህርት ቤቶች የእውቀት ቤት እንደመሆናቸው በእዚያ አግባብ ብቻ ከማንኛውም ፖለቲካዊ፣ ሀይማኖታዊ እና ባህላዊ ተጽእኖዎች ነጻ በሆነ መንገድ ስራቸውን እንዲያከናውኑ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ኢሰመጉ ጥሪውን ያቀርባል፡፡

አዲስ አበባ ፤ኢትዮጵያ

ኢትዮ1888 ሚድያ
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/channel/UC74xVlm9etNg3IWsuiXkyrA
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/ethio.1888/
በቴሌግራም
https://t.me/ethio1888media

Ethio 1888 Media - YouTube 12/12/2022

ሰበር ዜና❗️

የደቢዶሎ ዩኒቨርስቲ 8 ተማሪዎች ታገቱ

ወደ ደምቢደሎ ዩኒቨርሲቲ ሲጓዙ ከነበሩ ተማሪዎች መካከል ስምንቱ ታግተው ደብዛቸው መጥፋቱ ተገለፀ!

መነሻቸውን ከአማራ ክልል እና ከደቡብ ክልል እንዲሁም ከአዲስ አበባ ከተማ አድርገው ወደ ደምቢደሎ ዩኒቨርሲቲ ሲጓዙ ከነበሩ ተማሪዎች መካከል ምዕራብ ወለጋ ሲደርሱ ስምንቱ በብሔራቸው ተለይተው በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ከታገቱ ቦኋላ ደብዛቸው መጥፋቱን ከእገታው ያመለጡ የአይን እኞች ለአማራ ድምፅ ገለፁ።

ተማሪዎቹ አዲስ አበባው በሚገኘው አስኮ መናኸሪያ ከንጋቱ 11 ሰዓት በኦዳ ባስ ተሳፍረው ወደ ደምቢደሎ ዩኒቨርሲቲ ጉዞ የጀመሩ ሲሆን የምዕራብ ወለጋ ዞን ዋና መቀመጫ የሆነችው ጊምቢ ከተማን አልፈው በግምት 30 ኪሎ ሜትር እንደተጓዙ የአማራ ብሔር ተወላጅ የሆኑ 8ቱ ተማሪዎች በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ታግተው ደብዛቸው መጥፋቱን ነው የአይን እማኞቹ ለአማራ ድምፅ ያረጋገጡት።

1ኛ ብርሀኑ አባባው የ5ኛ አመት የህግ ተማሪ ሲሆን የትውልድ ስፍራው መራዊ

2ኛ ቤዛዊት ተሾመ የ5ኛ አመት ሲቪል ኢንጂነሪንግ ተማሪ ስትሆን የትውልድ ስፍራዋ አዲስ አበባ

3ኛ ሰኢዳ መሀመድ የ5ኛ አመት መካኒካል ኢንጂነሪንግ ተማሪ ስትሆን የትውልድ ስፍራዋ ጉንደር

4ኛ ቡዛየሁ አረጋ የ5ኛ አመት የህግ ተማሪ ሲሆን የትውልድ ስፍራው ሰሜን ሸዋ

5ኛ ሲሳይ ጋሻው የ4ኛ አመት የሳይኮሎጂ ተማሪ ሲሆን የትውልድ ስፍራው ደብረማርቆስ

6ኛ ኪሩቤል መለሰ የ5ኛ አመት ሲቪል ኢንጂነሪንግ ተማሪ ሲሆን የትውልድ ስፍራው ደባርቅ

7ኛ ደጀን ያለው የ4ኛ አመት የአይሲቲ ተማሪ ሲሆን የትውልድ ስፍራው ደቡብ ጎንደር

8ኛ መሃሌት ዘላለም የ4ኛ አመት ማኔጅመንት ተማሪ ስትሆን የትውልድ ስፍራዋ ደብረማርቆስ መሆኑን ለአማራ ድምፅ ያረጋገጡት የአይን እማኞቹ፡ ከቀኑ 10 ሰዓት ገደማ የጊምቢ ከተማን እንዳለፉ በብሔራቸው ምክኒያት ተለይተው በታጣቂዎቹ መታገታቸውን ገልፀዋል።

ታጣቂዎቹ ተማሪዎቹ ተሳፍረውበት የነበረውን ኦዳ ባስ ካስቆሙ ቦኋላ ተሳፋሪዎቹን አስወርደው የአማራ ተወላጅ የሆኑ 8ቱን ተማሪዎች ለይተው ወደ ጫካ እንደወሰዷቸው የገለፁት የአይን እማኞቹ፡ ቀሪ የሌላ ብሔር ተወላጅ የሆኑ ተማሪዎችን ግን ወደ ዩኒቨርስቲያቸው እንዲሄዱ እንደፈቀዱላቸው ተናግረዋል።

አጋቾቹ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ተጓዦችን አሳፍሮ የነበረውን ኦዳ ባስ ካቃጠሉ ቦኋላ አማራ በመሆናቸው ለይተው ያገቷቸውን 8ቱን ተማሪዎች እየደበደቡ ወደ ጫካ እንደወሰዷቸው ነው የአይን እማኞቹ ለአማራ ድምፅ ያረጋገጡት።

እናንተ አማራ አይደላችሁም በሚል ከእገታው የተለቀቁት ቀሪዎቹ ተማሪዎች በእለቱ ለኦሮሚያ ልዩ ኃይል የተፈጠረውን ያስረዱ ቢሆንም ነገር ግን የፀጥታ ኃይሎቹ የታገቱትን ተማሪዎች ለማስለቀቅ ሙከራ ከማድረግ ይልቅ ጉዳዩን በቸልተኝነት ማየታቸውን ለአማራ ድምፅ የገለፁት የአይን እማኞቹ፡ወደ ደምቢደሎ በማቅናት ለዩኒቨርስቲው አስተዳደር አካላት ቢያመለከቱም ነገር ግን እስካሁን የተገኘ መፍትሔ አለመኖሩንም ተናግረዋል።

መረጃው፦ የአማራ ድምፅ ሚዲያ ነው

ኢትዮ1888 ሚድያ
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/channel/UC74xVlm9etNg3IWsuiXkyrA
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/ethio.1888/
በቴሌግራም
https://t.me/ethio1888media

Ethio 1888 Media - YouTube Share your videos with friends, family, and the world

Photos from Ethio1888 media's post 07/12/2022

በኦሮሚያ ክልል በአምስት ወራት ውስጥ ብቻ “በብዙ መቶዎች የሚገመቱ” ሰዎች በታጣቂዎች እንደተገደሉ ኢሰመኮ አስታወቀ❗️❗️❗️❗️

በኦሮሚያ ክልል ውስጥ በሚገኙ አስር ዞኖች ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ቡድኖች፤ ባለፉት አምስት ወራት ውስጥ “በብዙ መቶዎች የሚገመቱ” ሰዎችን “በአሰቃቂ ሁኔታ” መግደላቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ። በእነዚህ አካባቢዎች የሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ቡድኖች “አይነት እና ቁጥር” ጨምሯል ያለው ኮሚሽኑ፤ የታጣቂዎቹ ጉዳይም “የመወሳሰብ አዝማሚያ” ማሳየቱን ገልጿል።

ኢሰመኮ ይህንን ያለው፤ በኦሮሚያ ክልል የሚፈጸሙ ጥቃቶችን እና ተያይዞ የተከተሉ “መጠነ ሰፊ ሰብአዊ ቀውሶችን” አስመልክቶ ዛሬ ረቡዕ ህዳር 28፤ 2015 ባወጣው መግለጫ ነው። በኦሮሚያ ክልል ጥቃት የሚፈጸምባቸው አካባቢዎች ስፋት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሆኑን የጠቆመው ኮሚሽኑ፤ ባለፉት አምስት ወራት ብቻ በ54 አካባቢዎች ግጭቶች መመዝገቡን አትቷል።

በመንግስታዊው የሰብዓዊ መብት ተቋም ዝርዝር መሰረት፤ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ አራት የወለጋ እና ሶስት የሸዋ ዞኖች ግጭቶች ተከስተዋል። በአርሲ፣ በኢሉ አባቦር እና በቡኖ በደሌ ዞኖች የሚገኙ አካባቢዎችም በተመሳሳይ ሁኔታ ግጭቶች እንደነበሩ ኮሚሽኑ ገልጿል።

በተጠቀሱት አካባቢዎች ውስጥ የሚከሰቱት አብዛኛዎቹ ጥቃቶች “ሆን ተብሎ ሲቪል ሰዎችን ኢላማ ያደረጉ” መሆናቸውን ኢሰመኮ ዛሬ ባወጣው ባለ አምስት ገጽ መግለጫ ላይ አመልክቷል። አብዛኞቹ ጥቃቶች “ብሔርን መሰረት ያደረጉ ናቸው” ያለው ኮሚሽኑ፤ “በተወሰኑ ሁኔታዎች የፖለቲካ አመለካከትን” መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች እንደሚፈጸሙም አክሏል።

ኢትዮ1888 ሚድያ
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/channel/UC74xVlm9etNg3IWsuiXkyrA
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/ethio.1888/
በቴሌግራም
https://t.me/ethio1888media

ምንጭ ኢትዮጵያን ኢንሳይደር

06/12/2022

#አሳዛዝ መረጃ❗️

በምስራቅ ወለጋ ዞን በተፈጸም ጥቃት በርካቶች በአስቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን ነዋሪዎች ገለጹ

በምስራቅ ወለጋ ዞን በተፈጸም ጥቃት በርካቶች በአስቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን ነዋሪዎች ለአል ዐይን አማርኛ ተናገግረዋል።

ነዋሪዎቹ እንደገለጹት በተለይ በኪረሙ በመቶዎች የሚቆጠሩ የአማራ ተወላጆች ብሄራቸው እየተለየ ተገድለዋል፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችም ተጨማሪ እልቂትን ሽሽት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅተዋል፡፡

የሰሞኑ ግጭት መንስኤ በኪረሙ በእስራ ላይ የነበሩ የአማራ ተወላጆች ግድያ መሆኑን ከአንገር ጉቴ ሸሽተው ስቡንሱሬ ቀበሌ የሚገኙ ስማቸው እንዳይጠቅሰ የፈለጉ ነዋሪ ተናግረዋል።

“የመንግስት አካላት ሸኔ ይገድላችኋል ኑ ወደ ካምፕ ግቡ በማለት የአማራ ገበሬዎችን ስብስበው ኪረሞ ማዘጋጃ ቤት ውስጥ አስረዋቸው ነበር፤ ሽማግሌዎች የታሰሩት እንዲፈቱ ጥረት ቢያደርጉም ኦሮሞዎች እየተለቀቁ አማራዎች ግን እንዳይወጡ ተደርጓል” የሚሉት አስተያየት ሰጪው የስሞኑ ችግር መንስኤም ከዚሁ ጋር ይያያዛል ብለዋል።

እኝህ ነዋሪ በእስራ ላይ የነበሩትን የአማራ ተወላጆች ጊዳ ወደተባለ ቦታ አግቶ ለመውሰድ የተደረገው ጥረትም የአማራ ተወላጆችን ከኦሮሚያ ልዩ ሃይል ጋር እንዲጋጩ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

ቅዳሜ ህዳር 24/2015 ማለዳ ላይ የተጀመረው ጥቃትም ከ200 በላይ የአማራ ተወላጆችን ህይወት መቅጠፉንና በርካቶችም መቁሰላቸውን ነዋሪው ጨምረው ተናግረዋል።

“ከነቀምቴ በርካታ የኦሮሚያ የጸጥታ ሃይል ወደ ጉቴን እየመጣ ነው” መባሉም በከተማዋ የሚኖሩ የአማራ ተወላጆች የመኖሪያ ቤታቸውን ለቀው በጫካ ውስጥ እንዲደበቁ ምክንያት ሆኗል ብለዋል፡፡

የኪረሙን አሰቃቂ ጥቃት ተከትሎ “አማራው ለቆ ወደ ሃሮ፤ ኦሮሞው ደግሞ ወደ ጊዳ አያና ሸሽቷል” የሚሉት የአይን እማኙ፤ ህፃናት፣ ሴቶችና አቅመ ደካሞች ህይወታችንን ለማትረፍ በመሰደዳቸው ጉትን ሰው አልባ ሆናለች ብለዋል።

ነዋሪው አንገር ጉቴ ላይ ብቻ 56 ሰዎች መቀበራቸውን እና በየጫካው የሟቾች ፍለጋው ስለቀጠለም ቁጥሩ ከፍ ሊል እንደሚችል ተናግረዋል፡፡

ሌላኛው የአንገር ጉቴ ከተማ ነዋሪ በነበረው ችግር የኦሮሞ ተወላጆችም የጥቃቱ ሰለባ መሆናቸውን ለአል አይን ገልጸዋል።

እስካሁን ሁለት ኦሮሞዎች መገደላቸውን አውቃለሁ የሚሉት የአይን እማኙ፣ ግድያን ሽሽት የአንገር ጉቴ ከተማ የኦሮሞ ተወላጆችም ወደ ነቀምትና ሌሎች አካባቢዎች ተፈናቅለው ከተማዋ ባዶ ሆናለች ብለዋል።

“ፋኖ ተደራጅቶ ሊወጋችሁ እየመጣ ነው” የሚል መረጃ መሰራጨቱም ህዝቡን ሽብር ውስጥ መክተቱን ተናግረዋል።

በሺዎች የሚቆጠሩ የኦሮሞ ተወላጆች በጊዳ አያና ተፈናቅለው እንደሚገኙና ቀጣይ እጣ ፈንታቸውም አሳሳቢ መሆኑን የአይን እማኙ ገልጸዋል።

ለሰሞኑ ጥቃት የአማራ ተውላጆች የኦሮሚያ ልዩ ሃይልን፣ የኦሮሞ ተወላጆች ደግሞ የአማራ ታጣቂዎችን ተጠያቂ በማድረግ ላይ ይገኛሉ።

በአካባቢው እየተፈጸመ ስላለው ግድያ አስመክቶ የፌዴራሉም ሆነ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት እስካሁን ያሉት ነገር የለም።

ምንጭ፦ አዲስ ማለዳ

ኢትዮ1888 ሚድያ
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/channel/UC74xVlm9etNg3IWsuiXkyrA
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/ethio.1888/
በቴሌግራም
https://t.me/ethio1888media

በወለጋ ጉዳት ከደረስባቸው አማራዎች ጋራ የተደረገ የስልክ ጥሪ፡ ይደመጥ 03/12/2022

https://youtu.be/jtvSXafLQQk

በወለጋ ጉዳት ከደረስባቸው አማራዎች ጋራ የተደረገ የስልክ ጥሪ፡ ይደመጥ ሰሞኑን በወላጋ ( ኦሮሚያ) ንፁሃን አማሮች ከቤታቸው እና ከእስር ቤት እየተወሰዱ በግፍ ተረሽነዋል ተገላዋል ጥቂቶች አገር ወንዝ አቋርጠው ወደ አማራ ክልል ሲገቡ ሌሎች በአካባብው በሚገ....

Ethio 1888 Media - YouTube 03/12/2022

#ሰበር ዜና #

በፖሊስ ታፈኑ❗️❗️❗️

በቤተሰቦቻቸው ላይ የተከፈተውን ጥቃት ለማስቆም የሰብአዊ መብቶች ተቋማት ግፊት እንዲያደርጉላቸው ለመጠየቅ የተሰባሰቡ የወለጋ ተወላጆች በአዲስ አበባ ፖሊስ ታፈኑ!

ዛሬ ህዳር 24/2015 ዓ/ም የኦሮሚያ ክልል ፀጥታ ኃይሎች በምስራቅ ወለጋ ዞን ስር በምትገኘው የአንገር ጉቴ ከተማ ነዋሪዎች ላይ የከፈቱትን ጥቃት ለማስቆም የሰብአዊ መብቶች ተቋማት ግፊት እንዲያደርጉላቸው ለመጠየቅ የተሰባሰቡ በአዲስ አበባ የሚኖሩ የአከባቢው ተወላጆች በፖሊስ ታፍነው ወዳልታወቀ ስፍራ እንደተወሰዱ የአይን እማኞች ለአማራ ድምፅ ገለፁ።

በቤተሰቦቻቸው ላይ የተከፈተውን ጥቃት ለማስቆም የሰብአዊ መብቶች ተቋማት ግፊት እንዲያደርጉላቸው ለመጠየቅ ከሚኖሩበት አዲስ አበባ የተለያዩ ክፍለ ከተሞች የተሰባሰቡት የወለጋ ተወላጆች ከ30 እስከ 40 ይደርሳሉ ሲሉ የገለፁት የአይን እማኞቹ፡ በልደታ ክፍለ ከተማ በሚገኘው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ(ኢሰመጉ)ቢሮ ጉዳዩን አስረድተው ሲወጡ ቀድመው ሲከታተሏቸው በነበሩ የአዲስ አበባ ፖሊሶች ታፍነው ወዳልታወቀ ስፍራ መወሰዳቸውን ተናግረዋል።

ብዛታቸው ከ30 እስከ 40 ይሆናል የተባሉት የወለጋ ተወላጆች የታፈኑት ዛሬ ህዳር 24/2015 ዓ/ም አመሻሹን ሲሆን አፍነው የወሰዷቸውም የአዲስ አበባ ፖሊስ መለዮ ልብስ የለበሱ የፀጥታ አካላት መሆናቸውንም የአይን እማኞቹ ለአማራ ድምፅ አረጋግጠዋል።

በምስራቅ ወለጋ የሚኖሩ ቤተሰቦቻቸው ላይ የተከፈተውን ጥቃት ለማስቆም የሰብአዊ ተቋማት ግፊት እንዲያደርጉላቸው ለማሳሰብ እንደተሰባሰቡ ታፍነው የተወሰዱ የወለጋ ተወላጆቹ፡ ወዴት እንደተወሰዱ አድራሻቸው ባለመታወቁ ዘመድ ወዳጆቻቸው ከባድ ጭንቀት ላይ መውደቃቸውም ተመላክቷል።

ምንጭ፦ የአማራ ድምፅ ሚዲያ

ኢትዮ1888 ሚድያ
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/channel/UC74xVlm9etNg3IWsuiXkyrA
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/ethio.1888/
በቴሌግራም
https://t.me/ethio1888media

Ethio 1888 Media - YouTube Share your videos with friends, family, and the world

03/12/2022

የፌደራል መንግስት በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ የወለጋ አካባቢዎች በአማራ ተወላጆች ላይ እየተፈፀመ ያለውን የዘር ጭፍጨፋ በአፋጣኝ እንዲያስቆም የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ይጠይቃል፣
********
በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ የወለጋ አካባቢዎች የአማራ ተወላጆች ላይ እየተፈፀመ ያለው ማንነትን መሰረት ያደረገ የዘር ጭፍጨፋ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ እና እየሰፋ ይገኛል:: የኦሮሚያ ክልል መንግስት በወለጋ እና ሌሎች አካባቢዎች በንፁሃን አማሮች ላይ እየተፈፀመ ያለውን ጭፍጨፋ፣ ማፈናቀል፣ እገታ እና ንብረት ዝርፊያ ለማስቆም ፍላጎት እና አቅም እንደሌለው በተደጋጋሚ ጊዜ ታይቷል፣ ቀላል የማይባለው የክልሉ መዋቅርም የጭፍጨፋው ተሳታፊና ሽፋን ሰጭ ሆኗል ። ጭፍጨፋው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ መጥቶ በዚህ ሳምንት እጅግ አደገኛ ወደ ሆነ ደረጃ ተሸጋግሯል። የክልሉ መንግስት ክልሉ ውስጥ የሚኖሩ ዜጎችን ማንነት፣ ዘር እና ኃይማኖት ሳይለይ እኩል የመጠበቅ እና ከለላ የመስጠት መንግስታዊ ግዴታውን መወጣት ሳይችል ቀርቶ የአማራ ተወላጆች በተለይ የመከራ ዶፍ እየወረደባቸው ይገኛል። ስለሆነ የፌድራል መንግስት በኦሮሚያ ክልል እየተካሄደ ያለውን የዘር ጭፍጨፋ በአስቸኳይ ጣልቃ ገብቶ ማስቆም እና ጥፋተኞች ላይ እርምጃ መውሰድ ይገባዋል ሲል አብን በጥብቅ ያሳስባል። የፌደራል መንግስት በኦሮሚያ ክልል አመራሮች ላይ ተጠያቂነት እንዲያረጋግጥ አብን እያሳሰበ የወገኖቻችንን ሕይወት ለመታደግ ጭፍጨፋ እየተፈጸመ ባለባቸው አካባቢዎች የመከላከያ ሠራዊት በፍጥነት ማሰማራት እንዳለበት አብን ያሳስባል።

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለ እና ዝርዝር መረጃ በማሰባሰብ ላይ ሲሆን፣ በቅርቡም ሰፋ እና ዘርዘር ያለ መግለጫ የሚያወጣ መሆኑን እያሳወቅን ችግሩ በፍጥነት እልባት እንዲያገኝ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን የሚችለውን ሁሉ ማድረጉን የሚቀጥል ይሆናል።

ኢትዮ1888 ሚድያ
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/channel/UC74xVlm9etNg3IWsuiXkyrA
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/ethio.1888/
በቴሌግራም
https://t.me/ethio1888media

Ethio 1888 Media - YouTube 02/12/2022

ሰበር መረጃ❗️

በምስራቅ ወለጋ ኪረሙ ከተማ በእስር ላይ እንዳሉ የተረሸኑት የአማራ ተወላጆች ብዛት 81 መድረሱ ተገለፀ!

የአማራ ድምፅ ሚድያ ህዳር 22/2015 ዓ/ም ባሰራጨው ዘገባ፡ ታስረውበት ከነበረው 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በጅምላ የተረሸኑት የአማላ ተወላጆች ብዛት ከ50 መሆኑን ማመላከቱ አይዘነጋም።

የአከባቢው ነዋሪዎች ዛሬ ህዳር 23/2015 ዓ/ም በእስር ላይ እንዳሉ የተረሸኑ ሰዎችን ስም ዝርዝር ለአማራ ድምፅ በላኩት መሰረት፡ ብዛታቸው 81 መድረሱን ነው ማረጋገጥ የተቻለው።

እነዚህ 81 የአማራ ተወላጆች በእስር ላይ እንዳሉ የተረሸኑት ህዳር 19/2015 ለህዳር 20 ሲሆን:ስም ዝርዝራቸውም፦
1ኛ ኡመር አሊ
2ኛ ወርቂት ሙሀመድ
3ኛ መዲና ከማል
4ኛ አህመድ ከማል
5ኛ ጦይብ ከማል
6ኛሸህ ከማል በድሩ
7ኛ ኢብራሂም አሊ
8ኛ ሙሀመድ አሊ
9ኛ ታጁ መሀመድ
10ኛ ሙሀመድ ዳውድ
11ኛ አስናቀው እባቡ
12ኛ ተመስገን መልክ ነው
13ኛ ሳኒ ከማል
14ኛ መሀመድ ከማል
15ኛ አህመድ ከማል
16ኛ ዚነት ሰይድ
17ኛ ሰሚራ ሰይድ
18ኛ ሽኩር ሙሀመድ
19ኛ ፋጢማ ጅብሪላ
20ኛ አስናቀው ካሳው
21ኛ ዩኑስ ሙሀመድ
22ኛ ኡመር ሙሀመድ
23ኛ ጥላሁን ዘነበ
24ኛ ኢስማኤል ደሳለኝ
ከዚህ በታች ያሉት ደግሞ ከነ ቤተሰቦቻቸው የተረሸኑ ሲሆኑ፦
1ኛ ጀማል ዳምጤ እሱን ጨምሮ 5 የቤተሰብ አባላቱ
2ኛ አበባው መኮነን እሱን ጨምሮ 6 የቤተሰብ አባላቱ
3ኛ ሸህ ሙሳ የሱፍ እሱን ጨምሮ 5 የቤተሰብ አባላቱ
4ኛ ቃሲም ሲራጅ እሱን ጨምሮ 3 የቤተሰብ አባላቱ
5ኛ ከማል ፈድሉ ከነ ባለቤቱ ቤተሰቦች ጨምሮ 21 የቤተሰብ አባላቱ
6ኛ ሙሳ አሊ እሱን ጨምሮ 7 የቤተሰብ አባላቱ
7ኛ አሊ ሀሰን እሱን ጨምሮ 10 የቤተሰብ አባላቱ ናቸው።

እነዚህ በእስር ላይ እንዳሉ የተረሸኑት 81 ሰዎች የክልሉ ፀጥታ ኃይሎች ህዳር 9 እና ህዳር 20/2015 ዓ/ም ቤት ለቤት እየዞሩ ከገደሏቸው 47 የአማራ ተወላጆች ተጨማሪ መሆናቸውን ነው የአከባቢው ነዋሪዎች ለአማራ ድምፅ ያረጋገጡት።

ኢትዮ1888 ሚድያ
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/channel/UC74xVlm9etNg3IWsuiXkyrA
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/ethio.1888/
በቴሌግራም
https://t.me/ethio1888media

Ethio 1888 Media - YouTube Share your videos with friends, family, and the world

Videos (show all)

ኢትዮ1888 ሚድያየዩቱብ ቻናላችንhttps://youtube.com/channel/UC74xVlm9etNg3IWsuiXkyrAበፌስቡክhttps://www.facebook.com/ethio.1888/በቴሌግራም...

Telephone

Website