የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office

የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office

ይህ የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ትክክለኛ የፌስ ቡክ ገፅ ነው። ገፁን ላይክ ሼር እና ኮሜንት በማድረግ ወቅታዊና አዳዲስ መረጃዎችን ይከታተሉ!

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 29/12/2023

ማዕከላት ቴክኖሎጂዎችን ወደ አርሶ አደሩ ለማድረስ በምርምር ሊደገፉ ይገባል -
አቶ ኃይለማርያም ተስፋዬ

#ታኅሳስ 19/2016 ዓ.ም በክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ የተመራ ቡድን በወላይታ ሶዶ ገጠር ቴክኖሎጂ ማስፋፊያ ማዕከል ወቅታዊ ተግባራትን ተመልክቷል።

በማዕከሉ የተገኘው ቡድን የቅድመ-ምርትና ድኅረ-ምርት ግብርና ሥራ ማከናወኛ የሆኑና ጊዜን፣ ጉልበትንና ወጭን በመቀነስ የምርት ጥራትን የሚያሳድጉ ቴክኖሎጂዎችን ጎብኝተዋል።

በማዕከሉ የተመረቱ ልዩ ልዩ ማረሻዎች፣ የእንስሳት መኖ መከረታተፊያዎች፣ የአገዳና ብርዕ ዕብሎች መውቂያዎች፣ የምርት ማበጠሪያዎች፣ የምርት ማከማቻ ጎተራዎች፣ ልዩ ልዩ የዶሮ ቤቶች፣ የፍራፍሬ ማጓጓዣዎች፣ የካሳቫ መከረታተፊያዎች፣ የንብ ቀፎዎች፣ የወተት መናጫዎች፣ የእንሰት መፋቂያና ምርት ማቀነባበሪያ እና ሌሎች ቴክኖሎጂዎችን ያቀረቡ ባለሙያዎች ለቡድኑ በቴክኖሎጂዎች አሠራርና አጠቃቀምን አብራርተዋል።

የግብርና ቢሮ ኃላፊ የሆኑት አቶ ኃይለማርያም ተስፋዬ እንደገለፁት ማዕከሉ የሚያመርታቸው ቴክኖሎጂዎችን ተመራጭ ለማድረግ በምርምር የተደገፈና ወጣቶችን በማሽነሪ የሚያሳትፍ ሊሆን እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የማዕከሉ ሥራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ደስታ ዳዊት በማዕከሉ የሚሰጠውን አገልግሎት ለማጠናከርና ያልተተገበሩ የምርምር ፕሮጀክቶችን ለመተግበር የአቅም ግንባታ ድጋፍ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

የወላይታ ሶዶ ገጠር ቴክኖሎጂ ማስፋፊያ ማዕከል በ1983 ዓ.ም ተመስርቶ በምርምር የተገኙ ቴክኖጂዎችን በማምረትና ለአርሶ አደሩ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ እየሠራ ይገኛል።

ዘገባው የክልሉ ግብርና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 29/12/2023

የዲላ ዩንቨረሲቲ አባል መምህራን እና ሰራተኞች የአቅም ግንባታ ስልጠና በሁለተኛ ቀን ውሎው

#ታህሳስ 19/2016 ዓ/ም

የዲላ ዩንቨረሲቲ አባል መምህራን እና ሰራተኞች የአቅም ግንባታ ስልጠና በሁለተኛ ቀን ውሎው "ገዢ ትርክት መገንባት" በሚል ርዕስ እየተሰጠ ይገኛል

ሰልጣኞቹ ስልጠናውን እንደተለመደው ብሔራዊ መዝሙር በመዘመር የጀመሩት ሲሆን፤

"ከተናጠል ትርክት በመውጣት ገዢ ሀገራዊ ትርክት መገንባት" በሚል ታላቅ ሀሳብ የተዘጋጄ ሀገራዊ የስልጠና ሰነድ የጌዴኦ ዞን ቴክንክና ሙያ መምሪያ ኃላፊ በሆኑት በአቶ አካሉ ሀልቻየ ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ይገኛል።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 29/12/2023

ለዲላ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ የመምህራን አባላት ''ከዕዳ ወደ ምንዳ'' በሚል መሪ ቃል የሚሠጠው የአቅም ግንባታ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ

#ታህሳስ 19/2016 ዓ.ም

ለዲላ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ የመምህራን አባላት ''ከዕዳ ወደ ምንዳ'' በሚል መሪ ቃል የሚሠጠው የአቅም ግንባታ ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል።

ስልጠናው በከተማው ከተለያዩ ትምህርት ቤት የተወጣጡ የፓርቲው አባላት እየተሳተፉ የሚገኝ ሲሆን የአራት ቀናት ቆይታ እንደሚኖረው ተመላክቷል።

የስልጠናው ተሳታፊ መምህራን የሚሠጣቸውን የአቅም ግንባታ ስልጠና በአግባቡ በመከታተልና ተግባራዊ ምላሽ በመስጠት ለሁለንተናዊ ብልፅግና ሊተጉ እንደሚገባ ተመላክቷል።

በተለይም ከስልጠናው በኃላ በሀገር አቀፍ ደረጃ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የሚሠራው ስራ ውጤታማ መሆን እንዲችል የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተገልጿል።

ዘገባው የዲላ ከተማ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ነው።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 29/12/2023

DSW ኢትዮጵያ ለጌዴኦ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ያደረገውን የቁሳቁስ ድጋፍ ርክክብ ተደረገ

#ታህሳስ 19/20161 ዓ/ም

DSW ኢትዮጵያ ለጌዴኦ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ያደረገውን የቁሳቁስ ድጋፍ ርክክብ ተደረገ

ድገፉ የተደረገ ድርጅቱ ካቀፋቸው ሶስት የጌዴኦ ዞን ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደር መካከል ለዲላ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት በተለይም ሀሮ ወላቡ ወጣቶች ማዕከል ሲሆን በቁጥር 140 ወንበር፣ አንድ 43 ኢንች ፍላት ተሌቪዢን፣ በርካታ ማጣቀሻ መጽሐፍት፣ መደርደሪያዎች እና ሌሎች ለማዕከሉ አገልግሎት የሚሰጡ ቁሳቁሶች እንድሁም ለዞኑ ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ 1 ሞቴር ሳይክል መሆኑ ታውቋል ።

አቶ ፈየራ አሰፋ የDSW ካንትሪ ዳይረክቴር በወቅቱ እንደ ገለጹት ድርጅቱ ከUNFPA KOICA ፈንድ በሚያገኙት ፈንድ በጤና እና በወጣቶች ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን እንደሚያከናውኑ ገልጿል። እንደ አቶ ፈየራ ገለጻ ድርጅቱ በጤና ተቋማት one stop center እና Women and girls friendly service በማቋቋም የሴቶችን ወጣቶችን ጥቃት ይከላከላል ብለዋል።

ዳይረክቴሩ አያይዘውም በቀጣይ ቀሪ ወረዳዎችን የመደገፍ ሥራ ይቀጥላል ብለዋል።

የተደረገውን ድጋፍ ለመረከብ የተገኙ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) እንደተናገሩት ድርጅቱ ስላደረገው ድጋፍ በዞን አስተዳደር ስም ምስገናቸውን አቅርበው የተገኘው ድጋፍ በአግባቡ ለታለመለት አላማ ብቻ እንድውል አሳስበዋል።

የጌዴኦ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ም/ኃላፊና ወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ታደሰ በወቅቱ እንደተናገሩ DSW በወጣቶችና አፍላ ወጣቶች ስብዕና ግንባታ፣ ተዋልዶ ጤና እና የህይወት ክህሎት ስልጠና በመስጠት በርካታ ሥራዎችን በዲላ ከተማ፣ ይ/ጨፌ ወረዳ እና ገደብ ወረዳ ላይ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል።

አቶ ዳንኤል አያይዘውም ድርጅቱ ከመንግስት ጎን በመሆን የወጣቶች ስብዕና ግንባታ ሥራ እያገዘ እንደሚገኝ ገልጾ ለተደረገ ድጋፍ አመስግነዋል።

የዲላ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መላኩ አየለ በርክክቡ ወቅት እንደተናገሩት የተደረገልን ድጋፍ የስብዕና ግንባታ ሥራችንን የሚያግዝ ነው ካሉ በኋላ እንደ ጽ/ቤት ቀሪ ሥራዎችን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 28/12/2023

የዲላ ዩንቨረሲቲ አባል መምህራን እና ሰራተኞች የአቅም ግንባታ ስልጠና በመጀመሪያ የስልጠና ቀን "ሀብት መፍጠር፣ መምራትና ማስተዳደር" በሚል ርዕስ እየተሰጠ ይገኛል

#ታህሳስ 18/2016 ዓ/ም

ሰልጣኞቹ ስልጠናውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ መዝሙር በመዘመር የጀመሩት ሲሆን፤ ስልጠናው እስከሚጠናቀቅ ድረስ በብሔራዊ መዝሙር የሚጀመር መሆኑ የስልጠናው አቀራረብ አካል ሆነው ብሔራዊነትን ለማጠናከር እንደሆነ ታውቋል።

"ሀብት መፍጠር፣ መምራትና ማስተዳደር" በሚል ሀሳብ የተዘጋጄ ሀገራዊ የስልጠና ሰነድ የዩንቨርስቲው አካዳሚክ ም/ፕረዚዳንት በሆኑት ታምራት በየነ (ዶ/ር) ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ይገኛል።

27/12/2023
Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 27/12/2023

የዲላ ዩንቨረሲቲ አባል መምህራን እና ሰራተኞች የአቅም ግንባታ ስልጠና ጀመረ

#ታህሳስ 17/2016 ዓ/ም

የዲላ ዩንቨረሲቲ አባል መምህራን እና ሰራተኞች የአቅም ግንባታ ስልጠና ጀመረ።

እንደ ሀገር በ5ኛ ዙር "ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል መርህ ሀሳብ እየተሰጠ የሚገኘው የአቅም ግንባታ ስልጠና በዲላ ዩንቨረሲቲ የተጀመረው በዛሬው ዕለት በዲላ ከተማ ጌዴኦ ባህል አዳራሽ በተሰጠው ማስጀመሪያ ኦሬንቴሽን መሆኑ ታውቋል።

የኦሬንቴሽን መድረኩን በንግግር የከፈቱት የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ርዕኦተ አለም እና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተስፋጽዮን ዳካ እንደገለጹት የስልጠናው ዋና ዓላማ የብልጽግና ፓርቲ አባላት እንደ ሀገር የተቀራረበ ግንዛቤ እንዲኖራቸውና ሀብት በመፍጠር፣ ስልጡን ሲቪል ሰርቫንት በመሆን፣ በሠላም እሴት ግንባታ እና ገዢ ትርክት በማሳደጉ ረገድ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጡ ማስቻል ነው ብለዋል። አቶ ተስፋጽዮን አክለውም በተለይም ብሔራዊነት እና አርበኝነት ጠንቅቀን በመረዳት ከስልጠናው በኃላ በየመስካችን በአርበኝነት ሞዴል መሆን ትልቁ ግብ ነው ብለዋል።

በዩንቨሲቲው የፕሬዝዳንቱ ልዩ አማካሪ እና የስልጠናው የበላይ አስተባባሪ ተመስገን እንግዳ(ዶ/ር) እንደገለጹት ስልጠናውን በጥብቅ ድስፕሊንና በነቃ ተሳትፎ እንዲከታተሉ አባላቱን ጠይቀው፤ ስልጠናው የተሳካ እንዲሆን ሁኔታዎችን ለማመቻቸት ዩንቨረሲቲውም ሆነ ኮሚቴው በቂ ዝግጅት ማድረጉን ገልጿል።

በዩንቨረሲቲው የምሁራን አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አፈወርቅ በኦሬንቴሽኑ እንዳነሱት ስልጠና የሚሰጥባቸው አራት ዋና ዋና ርዕሶች በሰዓት እና በቀናት በአግባቡ ተሸንሽኖ የተቀመጠ በመሆኑ ሰልጣኞች መርሃ ግብሩን ጠንቅቆ በመረዳት በድስፕሊን በመመራት ተባባሪ እንዲሆኑ ጠይቋል።

አስተያየታቸውን የሰጡ ሰልጣኞችም እንዳነሱት ግልጽና ተገቢ ኦሬንቴሽን ማግኘታቸውን አንስቶ በስልጠናውም ተገቢውን እውቀት እና መረዳት ለመገብየት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 27/12/2023

የዞን ማዕከል እና የክልል ተቋማት ፐብልክ ሰርቫንት ስልጠና አፈጻጸም ተገምግሟል

#ታህሳስ 17/2016 ዓ/ም

ላለፉት አራት ቀናት በጌዴኦ ዞን ከክልል ተቋማት መካከል መንገዶች ባለስልጣን ደቡብ ድስትርክትና የዞን ማዕከል ስቪል ሰርቫንት በሦስቱም ማህበራዊ መሠረት የተሰጠ አቅም ግንባታ ስልጠና አፈጻጸምና አጠቃላይ ሁኔታ ግምገማ ተደርጓል።

የሁሉም ቡድን አወያዮች የተገኙበትን የግምገማ መድረክ የመሩት የጌዴኦ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አበባየሁ ኢሳያስ እንደገለጹት የአስተሳሰብ እና የተግባር አንድነትን መፍጠር እና ከተናጠል ትርክት በመውጣት ገዢ ትርክት መፍጠርን ትኩረት ያደረገ ይህ ስልጠና በተለይም በፐብልክ ሰርቫንቱ የሚጠበቀውን ግብ መቷል ማለት ይቻላል ብለዋል።

ፐብልክ ሰርቫንቱ ከተገመተ በላይ በትግስት እና በንቁ ተሳትፎ ስልጠናውን ማጠናቀቃቸውን በአድናቆት ያነሱት የመንግስት ዋና ተጠሪው በስልጠናው ወቅት ከአባላት የተነሱ ገንቢ ሀሳቦችን ብልጽግና ፓርቲ በትኩረት በመውሰድ ህዝቡን በሚጠቅም መልኩ ወደ ተግባር ይቀይራል ብለዋል።

በዞኑ የተጀመረው የአንድነትና የይቅርታ ሂደትም ለሀገርም ሆነ ለክልል ተሞክሮ በሚሆን መልኩ መተግበሩን ይቀጥላል ያሉት አቶ አበባየሁ አባላቱ በስልጠናው የተገኘውን እውቀት በየተሰማሩበት የሥራ መስክ በተግባር እንደሚያሳዩ እምነታቸው እንደሆነ አሳስቧል።

የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ርዕዮተ አለምና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተስፋጽዮን ዳካ በወቅቱ እንዳነሱት ከሁሉም የስልጠና ቡድኖች በሚባል ደረጃ ገንቢና ጠቃሚ ሀሳቦችና የትግል አጀንዳዎች መንጸባረቃቸውን ገልጸው በየተቋማቱ ያሉ አባሎቻችን ሕዋሶቻቸው መታገያና መተራረሚያ መድረክ አድርገው በቀጣይ መወሰድ አለባቸው ብለዋል።

ከሰልጣኞቹ ተነስተው በየቡድን አወያዮች የቀረቡ ሀሳቦች በትክክልም ስልጠናው የታለመውን ግብ መምታት መቻሉን ማረጋገጥ ተችሏል።

በቀጣይ በዲላ ዩንቨርስቲ ሠራተኞች እና መምህራን እንዲሁም በየደረጃ ለሚገኙ መምህራን ስልጠናው እንደሚሰጥ ተገልጿል።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 27/12/2023

የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ዝናቡ ወልዴ በዲላ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተገኝተው የዘንድሮ ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞችን አበረታተዋል

#ታህሳስ 17/2016 ዓ/ም

የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ዝናቡ ወልዴ በዲላ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተገኝተው የዘንድሮ ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞችን አበረታተዋል።

በጌዴኦ ዞን ወጣቶች ሊግ አስተባባሪነት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን የማበረታታት ንቅናቄ በዲላ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት መጀመሩ የሚታወስ ሲሆን አላማውም ባለፉት ሁለት እና ሶስት ዓመታት የተፈጠረውን የውጤት መቀነስ ለማስተካከል የተማሪዎችን ስነ ልቦና መገንባት መሆኑ ታውቋል።

ለተማሪዎቹ ንግግር ያደረጉት ዶ/ር ዝናቡ ወልዴ እንደተናገሩት ተማሪዎች ለፈተና የቀራቸውን ግዜ በእቅድ በመምራት በዜዴ በማጥናት እራሳቸውን ለፈተና ዝግጁ እንዲያደርጉ እና ውጤት የመቀልበስ አቅም እንዳላቸው አንስተዋል።

ዶ/ር ዝናቡ ጨምረው እንደገለጹት ተማሪዎች ያላቸው አቅም አሟጠው ከተጠቀሙበት አለምን መቀየር የሚችሉበት በመሆኑ ከፍተኛ ውጤት በሚያስመዘግቡበት ቁጭት ውስጥ በመግባት ያለፉ አመታትን ታሪክ መቀየር እንደሚችሉ እንደሚተማመኑበት ነው የተናገሩት።

የዲላ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አቢነት አክሊሉ በወቅቱ እንዳነሱት የትምህርት ጠቀሜታው ተመርቀው ሥራ መቀጠር ብቻ ሳይሆን በስነ ምግባር ታንጸው ሕይወትን በተሻለ መንገድ ለመምራት ጭምር መሆኑን በመገንዘብ ተማሪዎች በዚህ ግዜ ባለመዘናጋት እራሳቸውን እንዲያበቁ ጠይቋል።

የጌዴኦ ዞን ወጣቶች ሊግ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢዩኤል ተሾሜ እንደገለጸ ይህን መሠል ተግባር በሁሉም የዞኑ መዋቅር በሚገኙ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶ በቀጣይነት የሚካሄዱ መሆኑን ገልጸዋል።

አስተያየታቸው የሰጡ ተማሪ ሳሌም ሳሙኤል እና ተማሪ ሠላም አዳነ እንደተናገሩ የተሰጠን ማበረታቻ ንግግር ውጤታችንን እንድናሻሽል ይረዳናል ካሉ በኃላ የዞኑም ሆነ የከተማ አስተዳደር ድጋፍ በቀጣይም እንዳይለያቸው ጠይቀዋል።

የት/ቤቱ አስተዳደር እና ተማሪዎችም የዞኑ አስተዳደር ለተማሪዎች ውጤት ትኩረት ሰጥተው ለማበረታታት በመገኘታቸው አመስግነዋል።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 26/12/2023

በገደብ ከተማ አስተዳደር "ከዕዳ ወደ ምንዳ" አቅም ግንባታ ስልጠና መጠናቀቁን ተከትሎ አጠቃላይ ሲቪል ሰርቫንቱ ያለውን በማዋጣት የአንዲት አቅመ ደካማ እናት ቤት በበጎ ፈቃድ ተሰርቷል

#ታህሳስ 16/4/ 2016 ዓ/ም

የገደብ ከተማ ከንቲባና የገደብ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት አመራሮችና አጠቀላይ የገደብ ከተማ የሴክተር ስራ አስፈፃምዎች ቤት መስራት በጎ ተግባር ላይ በገነዘብም ሆነ በጉልበት ዝቅ ብሎ በመስራት ለበጎ ተግባር ተምሳሌት ሆነዋል።

የገደብ ከተማ ሲቭል ሰርቫንት የበጎ ማህበር የበጎ ተግባር አርበኞች ናቸው በማለት ሀሳባቸውን የገለጹት የገደብ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ታሪኩ ሮቤ አጠቃላይ ሲቪል ሰርቫንቱ የጀግና ተምሳሌት ናችሁ በማለት የዚህ በጎ ማህበር ሀሳብ መንሴ የሆኑትን ስፖርትና ወጣቶችን ጽ/ቤቱን በማመስገን የገደብ ከተማ ሲቭል ሰርቫን በጎ አድራጎት ማህበርን መመስረቱን አብስረዋል።

በገንዘቡም ሆነ ጉልበቱን ሳይሠስት የ አንዲት አቅመ ደካማ ቤት መስራታችው ለቀጣይ በጎ ተግባራቶች ትልቅ ተስፋን ያሳያል በማለት አክለውበታል።

"የገደብ ከተማ ሲቪል ሰርቫንት የበጎ አድራጊያን ማህበር ትልቅ አላማን ያነገበና ከገደብ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ሀሳብ አመንጪነት የተቋቋመ መህበር ነው።

"በበጎነት ከዕዳ ወጥተን ምንዳን እናኖራለን" በሚል መፎክር አጠቃላይ ስለ ማህበሩና ወደፊት ስለሚሠሩ በጎ ተግባራትን በሰፊ ያብራሩት የገደብ ከተማ ስፖርትና ወጣቶች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አረጋኽኝ ነጋሽ ናቸው ።

በመጨረሻም ፦ የሲቭል ሰርቫን የበጎ ተግባር ማህበር መከፈትን ምክንያት በማድረግ ዳቦ ቆረሳ ተካሄዶ የማህበሩ ስራ አስፈጻሚዎች ና አስተባባሪዎቹ ተመርጠው የ ማብሰሪያውን ዳቦ ቆረሳ አካሄደዋል።

ዘገባው፦ የገደብ ከተማ መንግስት ኮሙንኬሽን ነው።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 26/12/2023

የኮቾሬ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላት የአቅም ግንባታ ሰልጣኞች በወረዳው እየተከናወነ ያለዉን የግብርና ልማት ስራዎችን ጎበኙ

#ዲላ ታህሳስ 16/2016 ዓ.ም

ከዕዳ ወደ ምንዳ በሚል መሪ ቃል ለኮቾሬ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ፐብሊክ ሰርቫንት አባላቶች ፣ለቀበሌ ፊት አመራሮችና አባላቶች የአቅም ግንባታ ሰልጣኞች በወረዳው በተለያዩ ቀበሌያት እየተከናወነ ያለዉን የግብርና ልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።

በጎብኝት መርሃግብሩ የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ረዳት የመንግስት ተጠሪና አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ምህረቱ ተፈሪ ጨምሮ፣ የዞን፣ የወረዳ ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች እና የስልጠና ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።

በጉብኝት መርሀግብር ላይ የተገኙት የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ረዳት የመንግስት ተጠሪና አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ምህረቱ ተፈሪ ሰልጣኞች በወሰዱት ስልጠና ወደ ተጨባጭ ተግባር በመቀየር፤ ሰልጡን ሲቪል ሰርቫንት በመሆን ጊዜዉን በአግባቡ በመጠቀም በተሰማራበት ሙያ ህዝባችንን መካስ በሚችል መልኩ መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

አቶ ምህረቱ አክለውም በመልካምነት፣ በቅንነት፣ በአክባሪነት፣ በአገልጋይነት መንፈስ ለህዝብ አንድነትና ልማት በይቅርባይነት መንፈስ ለህዝብ ልማት በቁጭት መስራት እንደሚባ ገልጿል።

በጉብኝት ወቅት በወረዳው እየተከናወነ ያለዉን የግብርና ልማት ስራዎች ማብራርያ የሰጡት የወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸዉ ታርኩ እንደገለጹት ሰልጣኞቹ በወሰዱት ስልጠና መነሻ እንደ ሀገር እያጋጠሙን ያሉ ችግሮችን በደንብ በመረዳት የጋራ የሆኑ ትርክቶችን በመያዝ ሀብት በማፈራት ላይ ልዩ ትኩረት በማድረግ ሀገሪቱን ከዕዳ ወደ ምንዳ ለማሸጋገር መዘጋጀት እንደሚገባ ተናግሯል።

በመጨረሻም ሰልጣኞቹ ከራሳቸው ኪስ ገንዘብ አዋጥተው ለአንድት እናት ቤት ሰርተዋል።

በተመሳሳይ ዜና የጨለለቅ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ፐብሊክ ሰርቫንት አባላቶች ፣ለቀበሌ ፊት አመራሮችና አባላቶች የአቅም ግንባታ ሰልጣኞች በከተማው አየተከናወነ ያለወን የተለያዩ የመሠረተ ልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱ የተሳተፉት ሰልጣኞች፣በወረዳዉ ውስጥ እየተሰራ ባለው የግብርና ልማት ስራዎች መደሰታቸውን ገልጸዉ በስልጠናው ያገኙትን ክህሎት በተግባር በመታገዝ ወደ ውጤት ለመቀየር መሠረት የሚጥል መሆኑ ተናግሯል ሲል የጌዴኦ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ከስፍራው ዘግቧል።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 26/12/2023

የወናጎ ከተማ አስተዳደር 2ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ተከበረ

#ታህሳስ 16/2016

በጌዴኦ ዞን የወናጎ ከተማ አስተዳደር 2ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በከተማው ተከብሯል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ እና ረዳት የመንግስት ተጠሪ እንዲሁም የዞን አስተዳደር ተወካይ አቶ ተስፋፅዮን ዳካን ጨምሮ፣ የዞን፣የከተማ እና የወረዳ ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ሀላፊዎች ፣ ታዋቂ ግለሰቦች ፣ የባህል እና የሐይማኖት ተቋማት መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ።

የወናጎ ከተማ አስተዳደር ታህሳስ 4/2014 ዓ/ም በፈርጅ ሶስት ከተማ ተመስርቶ ስራ የጀመረበት ቀን መሆኑ ይታወሳል ።

በዕለቱ የመክፈቻ ንግግር ያደርጉት የከተማው ከንቲባ አቶ አስራት በየነ ፣ ባለፉት ሁለት ዓመታት የረዥም ጊዜ የህዝብ ጥያቄ ሆነው የቆዩት የመሠረተ ልማት እና የመልካም አስተዳደር ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል።

ከንቲባው ከተማውን ለማስፋት እና ለማሳደግ በከተማ አስተዳደር ፣ በማዘጋጃ እና በህብረተሰቡ ድጋፍ ለሚከናወነው የ10 ኪ/ሜ መንገድ ከፈታ ሥራ በዛሬው ዕለት እንደሚጀመር ገልፀዋል።

ከዚህ በበለጠ መሰረተ ልማቱን ለማስፋፋት በትኩረት እንደሚሰራ የገለፁት ከንቲባው፣ ለዚህም የከተማው ነዋሪዎች ከመንግስት ጎን በመሆን የተጀመረውን ልማት እንዲደግፉ ጠይቀዋል።

የዞኑ ብልፅግና ፓርቲ አቅም ግንባታ ዘርፍ እና ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ ተስፋፅዮን ዳካ ፣ ከተማን የማሳደግ ስራ የመንግስት ስራ ብቻ እንዳልሆነ ገልፀው ፣ ከተማውን ለማልማት እና ለመለወጥ ሁሉም በጋራ መስራት እንዳለበት ጠቁመዋል።

በመርሃ ግብሩ መጨረሻ በከተማው ውስጥ ባለፉት ሁለት ዓመታት የተሰሩ የልማት ስራዎች ጉብኝትን ጨምሮ የ10 ኪ/ሜ የመንገድ ከፈታ ስራ አስጀምረዋል።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 26/12/2023

የዲላ ከተማ ስልጣኝ ፐብልክ ሰርቫንት የስልጠናውን መጠናቀቅ ተከትለው በከተማው እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ተመለከቱ

#ታህሳስ 16/2016 ዓ.ም

የዲላ ከተማ አቅም ግንባታ ስልጣኞች በከተማው እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

ስልጣኞቹ በከተማው እየተከናወኑ የሚገኙ የግብርና ፣ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ፣ የመንገድ ከፈታ ስራዎችና የዳራሮ ፓርክ ሥራ ሂደት እንዲሁም በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ እየተሰሩ ያሉ ተግባራትን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

ጉብኝቱ ሰልጣኞች በከተማው እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ተግባሮችን በይበልጥ ተገንዝበው ለአፈፃፀማቸው እንዲተጉ አቅም የሚፈጥር መሆኑ ተመላክቷል።

ሰልጣኞች በበኩላቸው ጉበኝቱ በከተማው እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ተግባራትን በተጨባጭ እንዲገነዘቡ እድል እንደፈጠረላቸው ገልፀው በቀጣይ በተሠማሩበት የሥራ መስክ ጠንክረው በመስራት ለከተማው ሁለንተናዊ እድገት እንደሚጥሩ ተናግረዋል።

ዘገባው የዲላ ከተማ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ነው

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 26/12/2023

በጌዴኦ ዞን 5ተኛ ዙር የብልፅግና ፓርቲ አባላት የአቅም ግንባታ ስልጠና በዞን ማዕከል ለሚሰሩ ፐብልክ ሰርቫንት ሲሰጥ ቆይቶ ሠልጣኞቹ የመስክ ጉብኝት እያደረጉ ነው

#ታህሳስ 16/2016 ዓ.ም

"ከዕዳ ወደ ምንዳ'' በሚል መሪ ሀሳብ ለብልፅግና ፖርቲ አባላት 5ኛው ዙር ለፐብልክ ሰርቫንት ቀደም ሲል ለወረዳና ከተማ አስተዳደር ስልጠና መሰጠቱ ይታወሳል ።

በዞን ማዕከል ስልጠና የወሰዱ ለሠልጣኞች በዞኑ የተሰሩ የሌማት ትሩፋቶችን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ በእንሰት, በቡና እና በሙዝ ላይ የተሰሩ ስራዎች ናቸው ጉብኝት የተደረገው ።

በቡና ምርታማነትና ችግሮችን ለመቅረፍ ያረጁ ቡናዎች የመጎንደል ሥራ በጉብኝቱ ወቅት መከናወኑን ለማወቅ ተችሏል ።

በጉብኝቱ አንዳንድ ሠልጣኞች እንደገለፁት በተመለከቱት ልማታዊ ተግባራትና መሠረተ ልማቶች እጅግ እንዳስደሰታቸውና ትምህርት እንደወሰዱበት ገልፀው ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባልም ብለዋል ።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 25/12/2023

በወረዳዉ በተያዘዉ በበጋ መስኖ 3 ሺህ በላይ ሄክታር መሬት በመደበኛና በበጋ መስኖ ሰንዴ ይሸፈናል :-የራጴ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት

#ታህሳስ 15/2016 ዓ.ም

በወረዳው በዘንድሮ መስኖ ልማት ስራ ከ3 ሺህ 54 ሄ/ር በላይ መሬት ለመስኖ ስራ መዘጋጀቱንና ከመደበኛ መስኖ 451 ሺህ 950 ኩ/ል እና ከበጋ መስኖ ስንዴ 3 ሺህ 375 ኩ/ል ምርት ይሰበሰባል ተብሎ እንደሚጠበቅ የራጴ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ገልጿል።

ይህ የተገለጸው ወረዳዉ የ2016 ዓ.ም የመደበኛና የበጋ መስኖ ሰንዴ ማስጀመሪያ መርህግብር በማንዶወላጌ ቀበሌ ባካሄደበት ወቅት ነዉ።

የወረዳዉ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታምራት ደልቦ በወቅቱ እንደገለጹት እንደ ሀገራችን ትኩረት አቅጣጫ መሠረት በወረዳው በዘንድሮው የመስኖ ልማት ስራ በበጋ መስኖ ስንዴ ላይ ትኩረት መደረጉን አብራርተዋል።

ለዚህም ለረጅም ጊዜ ሳይታረስ የቆዩ የመንግስት የወል መሬቶችን ወጣቶችን በማደራጀት የበጋ ሰንዴን እንዲያለሙ መደረጉን አቶ ታምራት ገልጸዋል።

በዘንድሮው ከአምና የተሻለ ዉጤት ለማምጣት አመራርም ባለሙያም ትኩረት ሰጥተው እየተገበረ እንደሚገኝ አክለዋል።

በማስጀመሪ መርሃግብር ላይ የተገኙት የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር ዝናቡ ወልደ (ዶ/ር) በዞኑ ባለዉ ዉሃ ገብ በሆነ በሁሉም አከባቢዎች ላይ የበጋ የመስኖ ስራ የምከናወን መሆኑን ገልፀው በተያዘዉ የመስኖ ሰንዴ እንደ ዞን ከ300 ሄ/ር በላይ መሬት በስንዴ ሰብል የማሸፈን ሲሆን ከዚህም ጎንለጎን በሁለቱም በበጋም በመደበኛም መስኖ 10 ሺህ ሄ/ር መሬት ለህብረተሰቡ በአጭር ጊዜ ውስጥ ደርሰው አርሶአደሮች ልመግቡ የሚችሉ የጓሮ አትክልትና ለሎች ሰብሎች ላይ በልዩ ትኩረት ተሰጥተዉ እየተሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል።

የዞኑ ም/አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ ዕጩ ዶ/ር ታጠቅ ዶሪ ሁላችንም በዚህ በበጋ ወቅት ያለንን የዉሃ ሀብት በአግባቡ ተጠቅመን ባለን መረት፤ በየጓሮአችን በኩታገጠም በአንድነት መንፈስ ኑሮአችንን በማሻሻል የኢኮኖሚን ችግር በመቅረፍ ከሌላ ቦታ የሚመጣውን እዚሁ በማምረት ከራሳችን አልፎ ለአከባቢ ገበያ የሚበቃ ሀብት በማመንጨት ከዕዳ ወደ ሚንዳ መሸጋገር እንችላለን ሲሉ ገልጸዋል።

የራጴ ወረዳ ም/አስተዳዳሪና የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አማኑኤል ወርቁ ወጣቶች አሁን ያለዉን ሀገራዊም ሆነ አከባቢያዊ ወቅታዊ ሁኔታዎችን ተገንዝቦ ያለዉን ሀብት ተጠቅመው ምንዳ ማመንጨት እንድችሉ ለማድረግ እንደ ወረዳ የመንግስት የወል መሬቶችን ለተደራጁ ወጣቶች ለግብርና ልማት አሳልፎ በመስጠት የዘር፣ የግብዓትና የባለሙያ ድጋፍችን በማድረግ መኸርም በበጋም መስኖ ስራዎች ላይ በንቃት በማሳተፍ ሀብትን ማፍራት በሚችሉበት ሁኔታ በማመቻቸት ስራ ላይ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል።

አዝመራ ላይ አግኝተነው ያነጋገርናቸው ለመስኖ ስንደ ስራ በኩታገጠም የተደራጁ ወጣቶችና አርሶአደሮች በበኩላቸው መንግስት ላደረገላቸው የመሬት፣ የዘርና የግብዓት ድጋፍ አመስግነው በቀጣይ የተሻለ ማምረትና ሀብት ማመንጨት እንድንችል መንግስት በተለያዩ በግብርና ተክኖሎጂ ድጋፎችን አጠናክሮ እንድቀጥል እንፈልጋለን ሲሉ ጠይቀዋል ሲል የጌዴኦ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ከስፍራው ዘግቧል።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 25/12/2023

ራዕያችን የኢትዮጵያን ተስፋ ለማረጋገጥ የሚያደናቅፍ ሳይሆን የሚያፀና ሊሆን ይገባል -
አቶ ኃይለማርያም ተስፋዬ

#ታኅሳስ 15/2016 ዓ.ም

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዲላ ማዕከል ለሚገኙ የብልፅግና ፓርቲ አባል ለሆኑ የመንግሥት ሠራተኞች "ከዕዳ ወደ ምንዳ!" በሚል ርዕስ እየተሠጠ የነበረው የአቅም ግንባታ ስልጠና ዛሬ ተጠናቋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደንና አካባቢ ጥበቃ ቢሮ ኃላፊ የሆኑት አቶ ግዛቴ ግጄ '' የሠላም ባህልንና አመለካከትን መገንባት'' በሚል ርዕስ የቀረበውን ሰነድ ሰፊ ገለፃ ያደረጉ ሲሆን ከሰልጣኙ ለተነሳው ሀሳብ ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት አጠናቀዋል።

የማጠቃለያ መድረኩን የመሩት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይለማርያም ተስፋዬ የሀገራችንን ሁለንተናዊ የብልፅግና ጉዞ ለማረጋገጥ አባሉ የፓርቲውን አላማ በመረዳትና በመገንዘብ የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ ይገባል ብለዋል።

ሠላም ለሁሉም የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች መሠረት መሆኑን አቶ ሀይለማርያም ገልፀው በሠላም አጀንዳ ላይ በጋራ መክሮ የጋራ መግባባት ላይ መድረስና በጋራ አቋም ለሀገር ጥቅም መጠበቅና ለሠላም መረጋገጥ እጅ ለእጅ ተያይዞ መረባረብ ወቅቱ የሚጠይቀው ቁልፍ ተግባር መሆኑን አስምረውበታል።

በስልጠናው የተዳሰሱ ጉዳዮች ተጨማሪ ግንዛቤዎችን ፈጥሯል ያሉት አቶ ኃይለማርያም ያሉንን አቅሞች አሟጠን በመስራት በሀብት የበለፀገች ሀገር ልንፈጥር ይገባል ብለዋል።

ዘገባውን ያደረሰን የክልሉ ግብርና ኮምኒኬሽን ነው።

Follow us፦ https://www.facebook.com/profile.php?id=61551118559109

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 25/12/2023

ለጌዴኦ ዞን ማዕከል ፐብልክ ሰርቫንት ሲሰጥ የቆየ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተጠናቀቀ

#ታህሳስ 15/2016 ዓ/ም

በጌዴኦ ዞን ለዞን ማዕከል "ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል ሀሳብ ለብልጽግና ፓርቲ አባል የመንግስት ሰራተኞች ለአራት ተከታታይ ቀናት ሲስጥ የቆየው አቅም ግንባታ ስልጠና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ።

ስልጠናው የዳሰሳቸው ዋና ዋና ሀሳቦች ሀብትና ብልጽግናን መፍጠርና ማስተዳደር፣ገዥ ትርክት ግንባታ፣ አገልጋይና ስልጡን ፐብልክ ሰርቪስ እና የሠላም ባህል ግንባታ የሚሉ ነበሩ።

በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር) እና የጌዴኦ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪ ክቡር አቶ አበባየሁ ኢሳያስ ተገኝቶ ከየቡድኑ ለተነሱ ዋና ዋና ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥቷል።

በማጠቃለያው ዋና አሰተዳዳሪው እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ ሀብት መረዳት እና ማስተዳደ፣ አርሶ አደሩ በበቂ እና በጥራት እንዲያመርት እና የዋጋ ንረት የመቆጣጠር ድርሻውን እንዲወጣ ማስቻል ከፐብልክ ሰርቫንቱ የሚጠበቅ በመሆኑ ከዚህ ስልጠና መልስ ቁርጠኛ በመሆን ፐብልክ ሰርቫንቱ ውጤት ማስመዝገብ ይጠበቅበታል ብለዋል።

ዋና አስተዳዳሪው አክለውም ስናገሩ የሠላም እሴት ግንባታ ጉዳይ ሀገርን የመጠበቅ የህልውና ጉዳይ እና ለአፍታ እንኳ መዘናጋት የሌለብን ጉዳይ ነው ካሉ በኃላ የሠላም ግንባታ የውስጥ ሠላም ከመጠበቅ የሚጀምር ስለሆነ እያንዳንዱ አካል የግሉን ሠላምና የአካባቢውን ሠላም መጠበቅ ይኖርበታል ብለዋል።

የመንግስት ዋና ተጠሪው በማጠቃለያ ወቅት እንደተናገሩ ፐብልክ ሰርቫንቱ በስልጠናው ያገኘውን ዕውቀት በየተሰማራበት ሙያ በተጨባጭ ወደ ተግባር በመቀየር የሕዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መትጋት እንደሚገባው አበክረው ጠይቀዋል።

አቶ አበባየሁ አክለውም ስልጠናው በሀገሪቱ የተጀመረውን የለውጥ፣ የዕድገትና የብልፅግና ጉዞ ለማሳካት አቅም የሚሆን አባል እንዲፈጠር ዕገዛው የጎላ ነው ብለዋል።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 25/12/2023

የራጴ ወረዳ ፐብልክ ሰርቫንት ከስልጠናው በኋላ በወረዳው እየተከናወነ ያለዉን የልማት ስራዎችንና ታርካዊ ቦታዎችን እየጎበኙ ነው

#ታህሳስ 15/2016 ዓ.ም

"ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል መሪ ቃል ለ4 ተከታይ ቀናት ስልጠናዉን የወሰዱ የአቅም ግንባታ ሰልጣኞች ዛሬ በወረዳ እየተከናወነ ያለዉን የልማት ስራዎችንና ታርካዊ ቦታዎችን እየጎበኙ ይገኛሉ።

በጎብኝት መርሃግብሩ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልደ (ዶ/ር) ጨምሮ፣ የዞን፣ የወረዳ ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች እና የስልጠና ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።

በጉብኝት ወቅት በወረዳው እየተከናወነ ያለዉን የግብርና ልማት ስራዎች ማብራርያ የሰጡት የወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታምራት ደልቦ በሁሉም ዘርፎች በተለይም በግብርና ስራዎች በበጋ ስንደና ገብስ አመርቂ ዉጤት እየተመዘገበ ያለበት መሆኑን ገልፀው ሰልጣኞች ባገኙት ሰልጠና መነሻ በተሰማሩበት ሙያ የተሻለ ዉጤት ለማስመዝገብ በትኩረት መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልደ (ዶ/ር) ለሰልጣኝ ጎብኝዎች ባስተላለፉት መልዕክት ሁሉም ሰልጣኞች ባገኙት ስልጠና መሠረት በአንድነት ለራሳቸው ብቻ ሳይሆን ለሌላ ማህበረሰብ ክፍል የሚተርፍ ሀብት ማመንጨት መቻል አለባችሁ ስሉ ተናግሯል።

ሰልጣኞቹ በወረዳው በተለያዩ ቀበለያት በኩታገጠም እየለማ ያለዉን የግብርና ልማት ስራዎች መካከል በላባ ጋሻ ቀበሌ ከ70 ሄ/ር በላይ በኩታ ገጠም እየለማ ያለዉን የገብስ ማሳ ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱ የተሳተፉት ሰልጣኞች፣በወረዳዉ ውስጥ እየተሰራ ባለው የግብርና ልማት ስራዎች መደሰታቸውን ገልጸዉ በስልጠናው ያገኙትን ክህሎት በተግባር በመታገዝ ወደ ውጤት ለመቀየር መሠረት የሚጥል መሆኑ ተናግሯል ሲል የጌዴኦ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ከስፍራው ዘግቧል።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 25/12/2023

ለፐብልክ ሰርቫንት እየተሰጠ የሚገኘው ስልጠና ዛሬም ቀጥሏል።

#ታህሳስ 15/2016 ዓ.ም

ከዕዳ ወደ ምንዳ በሚል መሪ ሀሳብ ለሲቪል ሰርቫንት የምሰጠው ስልጠና ዛሬም ቀጥሎ ውለዋል ።

በጌዴኦ ዞን በሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም በዞን ማዕከል ፐብልክ ሰርቫንት ስልጠና ቀጥሎ እየተካሄደ የሚገኝ ሲሆን "የሠላም ባህልና አመለካከት የመገንባት የመምራት ክህሎት" በምል ርዕስ ላይ ያጠነጠነ ሰነድ ቀርቦ በውይይት እየዳበረ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል።

ከዕዳ ወደ ምንዳ በሚል መሪ ቃል ስልጠና ለተከታታይ ለሶስት ቀናት ቆይቶ ዛሬ የመጨረሻ ቀኑን የያዘው ስልጠና ሀብትን መፍጠር ፤ገዢ ትርክት ፤ስልጡን ሲቪል ሰርቫንት እና የሠላም ፋይዳና ግንባታ በዋና ዋና ርዕሶች ለይ ነው ስልጠና እየተሰጠ ያለው ።

24/12/2023

ብልጽግና ፓርቲ የሀገሪቱን አቅሞች በመጠቀም ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ የጀመረውን ውጤታማ የአመራርነት ሚና አጠናክሮ ይቀጥላል - አቶ አደም ፋራህ

#ታህሳስ 14/2016 ዓ/ም

ብልጽግና ፓርቲ የሀገሪቱን አቅሞች በመጠቀም ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ የጀመረውን ውጤታማ የአመራርነት ሚና አጠናክሮ እንደሚቀጥል የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንትና የዋና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የገበታ ለሀገር ኮይሻ ፕሮጀክት አካል የሆነውን የጨበራ የዝሆን ዳና ሎጅ ትላንተ መርቀው ከፍተዋል።

በምረቃ መርኃ ግብሩ ላይ የተገኙት የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንትና የዋና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ፤ ኢትዮጵያ ብዙ አቅም ቢኖራትም ወደ ልማት መለወጥ ላይ ውስንነቶች መኖራቸውን ተናግረዋል።

ለዚህም በየአከባቢው ያሉ አቅሞችን በአግባቡ አይቶ፣ አቅሞችን ወደ ተጨባጭ ኃብት በመቀየር የሕዝብን ተጠቃሚነት ከማረጋግጥ አኳያ የአመራር ውስንነት ዋነኛው ምክንያት መሆኑን አንስተዋል።

በተለይም የመሪዎች የኃሳብ አመንጪነት እንዲሁም የማስፈጸም አቅም አናሳ እንደነበር ጠቅሰዋል።

በሌላ በኩል በመሠረታዊ ጉዳዮች ላይ መግባባት አለመፈጠሩን ተከትሎ በሚነሱ ግጭቶች የሚመጣ የፖለቲካ አለመረጋጋት ጸጋዎችን ለመጠቀም አዳጋች እንደነበር አንስተዋል።

የብልጽግና ፓርቲም በሀገሪቱ በተለያዩ ሥፍራዎች ያሉ አቅሞችን አሟጦ ለመጠቀም አመራሩ ሚናውን እንዲወጣ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ውጤታማ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

ከዚህ አንጻር በተለይም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኃሳብ አመንጪነት ትላንት የተመረቀው የጨበራ የዝሆን ዳና ሎጅ ጨምሮ ሌሎች የልማት ሥራዎች ተጠቃሽ መሆናቸውን ነው የገለጹት።

ጎን ለጎንም በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ለማምጣትና ሀገሪቱ ያሏትን እምቅ አቅሞች እንድትጠቀም በተለይም በሀገራዊ ምክክሩ አማካኝነት ልዩነቶች እንዲፈቱ ያላሰለሰ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

በኢትዮጵያ እየተተገበሩ ያሉ ፕሮጀክቶች የኃሳብ ኃይል ምን ያክል ወሳኝ እንደሆነ ትምህርት የሚወሰድባቸው መሆናቸውን ገልጸዋል።

በተለይም የተፈጥሮ ጸጋዎችን ለሀገሪቱ የብልጽግና ጉዞ እንዴት መጠቀም እንደሚገባ ትልቅ ማሳያዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል።

በሌላ በኩል ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ እንዲሁም በከፍተኛ የጥራት ደረጃ እንዴት ማጠናቀቅ እንደሚቻል የፕሮጀክት አመራር ጥበብን የተማርንባቸው ናቸው ሲሉም ተናግረዋል።

እነዚህ ፕሮጀክቶች በሕዝብ ተሳትፎ የተገነቡ መሆናቸውን ጠቅሰው በቀጣይም ሕዝቡን በሁሉም ደረጃ በማሳተፍ የሕዝቡን ተጠቃሚነትና የሀገሪቱን ብልጽግና ለማረጋገጥ የታያዙ ውጥኖች እውን እንዲሆኑ ይሰራል ብለዋል።

በመሆኑም በቀጣይም የብልጽግና ፓርቲ የአገሪቱን አቅሞች በመጠቀም ሀገሪቱን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ የጀመራቸውን ውጤታማ የአመራርነት ሚና አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 23/12/2023

"የተከልኩትን ችግኝ እንከባከባለሁ"በሚል መሪ ቃል የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ሀገር አቀፍ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት መርሀ ግብር ማስጀመሪያ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል።

#ታህሳስ 13/2016 ዓ/ም

በመርሀ ግብሩ ላይ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንቶች ወጣት ፈዲላ ቢያ እና ወጣት አባንግ ኩመዳንን ጨምሮ የሊጉ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ሀላፊዎች ተገኝተዋል።

የበጎ ፍቃድ አገልግሎቱ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ወጣት እንዲሳተፍበትና በክረምት ወራት የተተከሉ ችግኞች ይፀድቁ ዘንድ የሚደረገው እንክብካቤ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተጠቅሷል።

በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር አሁን ላይ ሀገራችንን በአለም ምሳሌ እንድትሆን ጭምር ያደረጋት ተግባር ነው።

ወጣቱ የህብረተሰብ ክፍልም ይህንን እምርታ ለማሳደግ ሀላፊነት እንዳለበትና በችግኝ ተከላ ወቅት ያሳየውን ውጤት በእንክብካቤውም ሊደግመው እንደሚገባ በመርሀ ግብሩ ላይ ተገልፇል።

በተለይም ለፍራፍሬነት እና ለምግብነት የሚውሉ ችግኞችን በመንከባከብ እንደ ሀገር ያለንን የምግብ አቅርቦት ላይ ጭማሪ ማድረግ እንደሚቻል እና ለወጣቶችም የስራ እድል የሚፈጥር ሀሳብ እንደሆነ በሊጉ አመራሮች ተብራርቷል።

የሀገራችንም ወጣቶች ይህንን በጎ ሀሳብ ተረድተው የበኩላቸውን አስተዋፆ እንዲያበረክቱ ተጠይቋል።

ከበጎ ፍቃድ መርሀ ግብሩ ጎን ለጎን በሆሳእና ከተማ የስራ እድል የተፈጠረላቸው ወጣቶች እንቅስቃሴን ምን እንደሚመስል በወጣት አመራሮች ተጎብኝቷል።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 22/12/2023

የ አ ቋ ም መ ግ ለ ጫ

በጌዴኦ ዞን የተካሄደው ልዩ የይቅርታና የአንድነት የምክክር መድረኩ የተቋጨው ጉባኤው ባለ አምስት ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት እና አሁን ዞኑን ፊት ሆነው እየመሩ ያሉትን አስተባባሪዎችን ስለ ልዩ ዝግጅቱ በማመስገን ነበር

የአቋም መግለጫ

የጌዴኦ ዞን ሕዝብ ለህዝብ የምክክር፣ የእርቅና አንድነት ጉባዔ "ዞናዊ የአንድነት ምዕራፍ ለእድገትና ብልጽግና" በሚል መሪ ቃል ታህሳስ 12/2016 ዓ/ም በጌዴኦ ዞን አስተዳደር አስተባባሪነት በተካሄደው በአንድ ቀን የምክክር መድረክ ላይ የተገኘን እኛ የፌዴራል፣ የክልል፣ የዞን የከተማና የወረዳ አመራሮች፣ የቀድሞ የጌዴኦ ዞን አስተዳዳሪዎች፣ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት፣ የአባገዳ ካቢኔ አባላት፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሰባቱ ጎሳ ተወካዮች እና ከተለያዩ ማህበረሰብ ክፍሎች የተወከልን የሚከተለውን ባለ አምስት ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥተናል።

↪ምክክር ስር የሰደዱ ዞናዊ አለመግባባቶችን፣ እንዲሁም ከወቅታዊና ተጨባጭ ሁኔታ አንፃር የተዛቡ መስተጋብሮችን ማረሚያና መፍቻ ተመራጭ ዘዴ መሆኑን በመገንዘብ ለዞናችን አንድ ወጥ ሀሳብ እና ሁሉንም ወገን የሚያግባባ የጋራ አንድነት በዘላቂነት የሚያስቀጥል ተቋምና ተቋማዊ አሰራር መፍጠር አማራጭ የሌለው ውሳኔ ስለሆነ ሁላችንም ያላንዳች ልዩነት ይህንን መድረክ እስከ ሕዝብ ለማድረስ በጥብቅ ለመፈጸምና ለማስፈጸም ቃል እንገባለን።

↪የማራኪ አሴት ባለቤት ትልቅና አኩሪ ታርክ ያለው ህዝባችን ፥ ዘመናዊ ትምህርት ከመጀመሩ በፊት ሀገር በቀል እውቀትና ጥበብ ይዞ የመጣውን ሀብት አስጠብቆ በመሄድ እና ተሻጋሪ የሆነ አንድነት በመፍጠር ኢኮኖሚያዊ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ልማት ከማረጋገጥ አኳያ ያሉብንን ውስንነቶች አርመን የህዝባችንን ልማትና እኩልነት ለማረጋገጥ ቃል እንገባለን፤

↪ስለጌዴኦ ህዝብ ታታሪነትና ጥንካሬ ለመግለጽ ተራራማውን መልክዓ ምድር ለኑሮ ምቹ አድርጎ በባህላዊ አስተራረስ የጥምር እርሻ ከትውልድ ትውልድ እንዲዘልቅ ከማድረግ ጎንለጎን በቅርቡ የተባበሩት መንግስታት የትምህር፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት UNESCO የተመዘገበው የጌዴኦ መልክዓ ምድር በቀጣይ የዞናችን የቱሪስት መዳረሻ በማድረግ የወጣቱን ሥራ አጥነት በሚቀርፍ አኳኋን ለመስራት ቃል እንገባለን፤

↪አለማቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የአሁኑንና የወደፊቱን እምቅ ሀብት በቂ እውቀት ኖሮት በዚህ የሚያፍር ሳይሆን የሚኮራ ስሙ የተከበረ የአለም ዜጋ ለመባል ብቃት ያለው በልዩ ልዩ ስፖርት አይነቶች፣ በሳይንሳዊ ፈጠራዎች፣ በስነ ጥበብ፣ በሙዚቃና ተቆጥሮ በማያልቅ ሌሎች የሙያ መስኮች የተካኔ ስለ ድሞክራሲያዊ እሴቶች ሁለንተናዊ ትርጉም ከፍተኛ ግንዛቤ ያለው ባህላዊ ሀብቶቻችን በደስታ አይን ማየት ብቻ ሳይሆን የበለጠ ለማበልጸግ የምጥር ቀጣይ የኢኮኖሚ እድገትና ማህበራዊ ልማት ለማምጣት በጎ ፍቃድ ብቻ ሳይሆን ችሎታና ራዕይ ያለው ትውልድ ማነጽ የሚችል የትምህርት ስርዓት በተቀናጀና በተደራጀ አግባብ በጋራ ለመፈጸም ቃል እንገባለን፤

↪የህዝባችንን ታርክና ታላቅነት ያገናዘበ ብዝሃነትን ማለትም የፆታ፣ የዕድሜ፣ የሐይማኖት፣ የፖለቲካና ወ ዘ ተ አካታች በሆነ አግባብ ዞናዊ የምክክር ጉባዔ የተዛቡ አተያዮችን ማረምና ማስተካከል በሚያስችል አኳኋን ሁሉ አቀፍ እርቀ ሰላም በተሳካ መልኩ ፈጽመን አንድነታችን በጋራ ስለማጽናታችን ቃል ገብተናል።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 22/12/2023

Haranga gargar hedheeke garin uudendaax mari'e telcho arfaasa 12/2016 G.W Gede'iinxe Zoonne'n Dillike qachchanni assendeen

12/2016 G.W

Tinni mari'e assendeek olma Gede'iinxxa zoone akeekeexx ta'axxe yannanni gargar gargar hexxeexxe bogiinxxe kutuwwa'n hujettenni iima hexxeexxe akeekissanona ta'axxe yannanni Zoone akeekkatte'n iima hexxexxe akeekissano iittan saxxemaxxe saddeeta woga'aa gadoome arda akeeke abagada Danboobna ta'axxe yannanni arda akekkanneek abagada Bifoomi afemmeexxe odonniten

Mari'e tennek umi yaadina weli'aan wel gattowaali hiyyati mittunte duudhedhdhate kaddawoda akkeekatike barro'ni eggennatina kadde haakkitik wel kajeela yookin kajjo hexxo'aa danddettamaxxe aada no'oxxishan kajjot henne haanjinne yookin jijjirensha iyedaga dandeena gonphphanaxxee gattowaaliiti weli fayya hasissamaxxeeten hiyyeen Gede'iinxxe zoonek illichi galchanji Dokteer Zinaabu Wolde

Tenne mari'eni jajaba Gede'iink dhot dhot meyakina labak ittan lubbot mageninba'a me'iteexxe akekkisannox minink haduwi afemeex kokessende'een

okkone woda wel froomati ittan gattowaalii adhdhat wel'aan wel hanqalfat aba gadake albi eedo qulummatina ajajjenshat arda akeekkate'e kako aangeexxi eeba adhdhineen ittan fakkataak qephin looliin qicon muuxendeechin uduma faci'etike seerin qunqumendaaxxe kade'ex egge'nende'een

Muuxxamakenni ulfininika gicana badhaas olminaan sanfeexx ardakee ergatemeeke Zoonetixx galcha badhaaseen

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 22/12/2023

በጌዴኦ ዞን በሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ሁለተኛ ቀኑን የያዘ የፐብልክ ሰርቫት እና የነዋሪ አባላት የስልጠና መርሃ ግብር ዛሬም በተሳካ ሁኔታ ቀጥሏል

#ታህሳስ 12/2016 ዓ/ም

በጌደኦ ዞን በሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች "ታላቁን ገዢ ትርክት መፍጠር" በሚል አብይ ሀሳብ በሀገር ደረጃ በተዘጋጀ ሰነድ ላይ በጥልቀት ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 22/12/2023

ሁለተኛ ቀኑን የያዘ የፐብልክ ሰርቫት እና የነዋሪ አባላት የስልጠና መርሃ ግብር ዛሬም በተሳካ ሁኔታ ቀጥሏል

#ታህሳስ 12/2016 ዓ/ም

በጌደኦ ዞን በዞን ማዕከል በሦስቱም ማህበራዊ መሠረት "ታላቁን ገዢ ትርክት መፍጠር" በሚል አብይ ሀሳብ በሀገር ደረጃ በተዘጋጀ ሰነድ ላይ በጥልቀት ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 22/12/2023

ሀገር ወደፊት የሚጓዘው ጥላቻን በይቅርታ በማሸነፍ በመሆኑ ፣ ይህንኑ ተግባር አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ፦የጌዴኦ ዞን የቀደሞ እና የአሁኑ መሪዎች

#ታህሳስ 12/2016 ዓ/ም

ሀገር ወደፊት የሚጓዘው ጥላቻን በይቅርታ በማሸነፍ በመሆኑ ፣ ይህንኑ ተግባር በማጠናከር ሀገርን እና ህዝብን ማስቀጠል ይገባል ሲሉ የጌዴኦ ዞን የቀደሞ እና የአሁኑ መሪዎች ገልጸዋል ።

በጌዴኦ ዞን ላለፉት 33 አመታት የዞን ዋና አስተዳዳርነት ጨምሮ በተለያዩ የስልጣን እርከን ያገለገሉ አመራሮች እና አባገዳዎች የአንድነት፣ የእርቅና የይቅርታ መርሃግብር በዲላ ከተማ እያካሄዱ ይገኛል ።

የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ ዶ/ር በወቅቱ እንደገለፁት ጥላቻ ከትንሽ ነገር ተነስቶ ቤተሰብን ከመጉዳት ባለፈ በሀገር ላይ አደጋን የሚደቅን ነዉ ብለዋል ።

የአንድነትና ይቅርታ ለሀገር ያለዉ አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ያስረዱት ዝናቡ ወልዴ ዶ/ር ሀገርና ትውልድን ለማስቀጠልና ነገን የተሻለ ህይወት ለመምራት ከጥላቻ ስሜት መውጣት አማራጭ የለሌው ምርጫ መሆኑን ጠቁሟል።

ለዚህም ጥላቻን በይቅርታ በመተካት ሀገርን እና ህዝብን የምናስቀጥልበት ወቅት አሁን ነው ሲል አስገንዝቧል።

ይህንኑ ስራ አጠናክሮ ለማስቀጠል እንዲቻል የአንድነት፣ የእርቅና የይቅርታ መርሃግብር መዘጋጀቱ የጎላ ሚና መኖሩን አስተዳዳሪዉ የገለፁት ።

በመርሃ ግብሩ የቀድሞ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪዎች ፣በተለያዩ የስልጣን እርከን እያገለገሉ ያሉ አመራሮች፣ የቀድሞ እና የአሁኑ አባ ገዳ እንዲሁም የአባጋዳ የካብኔ አባላት መገኘታቸውን የጌዴኦ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ዘግቧል ።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 21/12/2023

በጌዴኦ ዞን በሁሉም መዋቅሮች እና በዞን ማዕከል እየተሰጠ ያለው የፐብልክ ሰርቫንት እና የነዋሪ አባላት ስልጠና ዛሬ በቡድን ውይይት ቀጥሎ እየተካሄደ ይገኛል።

#ታህሳስ 11/2016 ዓ/ም

የከተማ አስተዳደሮች እና ወረዳዎች የቡድን ስልጠና በፎቶ

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 21/12/2023

በጌዴኦ ዞን በሁሉም መዋቅሮች እና በዞን ማዕከል እየተሰጠ ያለው የፐብልክ ሰርቫንት እና የነዋሪ አባላት ስልጠና ዛሬ በቡድን ውይይት ቀጥሎ እየተካሄደ ይገኛል።

#ታህሳስ 11/2016 ዓ/ም

21/12/2023

ብሔራዊነት የሕዝቦችን የጋራ ጉዳይ ማጉላት ነው፡፡

#ታህሳስ 11/2016 ዓ/ም

ብሔራዊነት የሕዝቦችን የጋራ ጉዳይ ማጉላት ነው፡፡ በአንድ ሀገር ውስጥ የኖርን፣ ለአንድ ሀገር እኩል ዋጋ የከፈልን ነን ብሎ ያስባል፡፡ በዚህች ሀገር የመጡ ዕድሎችንና መከራዎችን እኩል ተጋርተናል ብሎ ያምናል፤ እኩል የሀገር ባለቤቶች ነን ብሎ ይቀበላል።

ቢጻፍም ባይጻፍም፤ ቢነገርም ባይነገርም ለኢትዮጵያ ታሪክ የየራሳችንን አስተዋጽኦ ያደረግን፤ የባህል፤ የእምነት፤ የቋንቋ፤ የአስተሳሰብ ልዩነቶችን የምናከብር ነን ብሎ ይቀበላል፡፡

ልዩነቶቻችን ግን አንድነታችንን ወደ መከፋፈል የማይወስዱብን፤ አንድነታችንም ማንነታችንን የማያጠፋብን፤ ዛሬን አጥብቀን የምንሠራ፤ ነገን በርትተን የምንገነባ ሕዝቦች ነን ብሎ ያስባል፡፡

ብሔራዊነት በሀገራችን ለሚገኙ ሁሉም ብሔር፤ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ዕውቅና የሚሰጥ ካላቸው የትሪክ ትሥሥር፤ የጋራ ጥቅምና የጋራ ተስፋ በመነሳት፤ በፈቃደኝት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ህብረትና ትብብር ሊኖሪቸው ይገባል የሚል አስተሳሰብ ነው፡፡

ብሔራዊነት ብዝኃነትን ሳይክድና ሳይደፈጥጥ የህብረትን አስፈላጊነትና ጥቅም አጽንኦት የሚሰጥ፤ የቋንቋና የባህል ልዩነቶችንም የሚያከብር አካሄድ ነው፡፡ ብሔራዊነት ለጋራ ዓላማና ግብ አብረን መቆም፤ አብረን መሥራት እንዳለብን፤ እጣ ፈነታችን እጅጉን የተቆራኘ በመሆኑ መደጋገፍ፤ መተጋገዝ እንደሚገባን የሚያስገነዝብ ትርክት ነው፡፡

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 20/12/2023

ኮቾረ ወረዳ በሚቀጥሉት 4 ቀናት "ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል ርዕስ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለፐብልክ ሰርቫንት ለሚሰጠው ስልጠና ኦሬንቴሽን ተሰጥቷል።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 20/12/2023

ዲላ ዙሪያ ወረዳ በሚቀጥሉት 4 ቀናት "ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል ርዕስ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለፐብልክ ሰርቫንት ለሚሰጠው ስልጠና ኦሬንቴሽን ተሰጥቷል።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 20/12/2023

ራጴ ወረዳ በሚቀጥሉት 4 ቀናት "ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል ርዕስ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለፐብልክ ሰርቫንት ለሚሰጠው ስልጠና ኦሬንቴሽን ተሰጥቷል።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 20/12/2023

ዲላ ከተማ አስተዳደር በሚቀጥሉት 4 ቀናት "ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል ርዕስ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለፐብልክ ሰርቫንት ለሚሰጠው ስልጠና በየማህበራዊ መሠረቱ ኦሬንቴሽን ተሰጥቷል።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 20/12/2023

በጌዴኦ ዞን ማዕከል ለሚገኙ ፐብልክ ሰርቫንት ለሚቀጥሉት አራት ቀናት" ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል መሪ ስልጠና እንደሚሰጥ ተገለጸ፤

#ታህሳስ 10/2016 ዓ/ም

በጌዴኦ ዞን ማዕከል ለሚገኙ ፐብልክ ሰርቫንት ለሚቀጥሉት አራት ቀናት" ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል መሪ ስልጠና እንደሚሰጥ ተገለጸ፤

ይህም የተገለጸ ዛሬ በጌዴኦ ዞን ባህል አዳራሽ ለሰልጣኞቹ ኦሬንቴሽን በተሰጠበት ወቅት ነው።

ኦሬንቴሽን መድረኩን በንግግር የከፈቱት የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ ዶ/ር ዝናቡ ወልዴ እንደገለፁት ስልጠናው ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት እና የሠላም እሴቶችን ለማሳደግ ጉልህ ሚና የሚጫወት በመሆኑ ሰልጣኞች በጥብቅ ድስፕሊንና በነቃ ተሳትፎ ድሞኪራስያዊ በሆነ መንገድ ስልጠናውን እዲከታተሉ አደራ ብለዋል።

አጠቃላይ የስልጠናውን ሂደት ያብራሩት የጌዴኦ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪ የተከበሩ አቶ አበባየሁ ኢሳያስ እንደገለፁት ስልጠናው መንግስታዊ ተግባራት ከመወጣት ባሻገር በግል ሕይወት ጭምር ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ገልጾ ሰልጣኞች በትኩረት እንዲከታተሉ ጠይቀዋል።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 20/12/2023

ገደብ ከተማ በሚቀጥሉት 4 ቀናት "ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል ርዕስ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለፐብልክ ሰርቫንት ለሚሰጠው ስልጠና ኦሬንቴሽን ተሰጥቷል።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 20/12/2023

ገደብ ወረዳ በሚቀጥሉት 4 ቀናት "ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል ርዕስ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለፐብልክ ሰርቫንት ለሚሰጠው ስልጠና ኦሬንቴሽን ተሰጥቷል።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 20/12/2023

ጨለለቅቱ ከተማ አስተዳደር ለሚቀጥሉት አራት ቀናት "ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል ርዕስ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሚሰው ስልጠና ኦሬንቴሽን ተሰጥቷል።

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 20/12/2023

ይ/ጨፌ ወረዳ በሚቀጥሉት 4 ቀናት "ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል ርዕስ ለሚሰጠው የፐብልክ ሰርቫንት ስልጠና ኦሬንተሽን ተሰጥቷል

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 20/12/2023

ወናጎ ወረዳ ለምቀጥሉት አራት ቀናት የሚሰጥ "ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል ርዕስ የፐብልክ ሰርቫንት ስልጠና ኦሬንቴሽን በዛሬው ዕለት ተሰጥቷል

Photos from የጌዴኦ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት - Gedeo Zone Prosperity Party Office's post 20/12/2023

በጌዴኦ ዞን በይ/ጨፌ ከተማ ''ከዕዳ ወደ ምንዳ'' በሚል ርዕስ በከተማ ደረጃ ለሚሰጠው ስልጠና የኦሬንተሽን መድረክ ለፐብልክ ሰርቫንት አባላት ተሰጠ።

ይ/ጨፌ ከተማ:ታህሳስ 10/2016 ዓ.ም በጌዴኦ ዞን በይ/ጨፌ ከተማ ''ከዕዳ ወደ ምንዳ'' በሚል ርዕስ ሀገር አቀፍ መድረክ በከተማ ደረጃ ለሚሰጠው ስልጠና የኦሬንተሽን መድረክ ተካሂዷል።

በኦሬንተሽኑ መድረክ ላይ የተገኙት የይ/ጨፌ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ብዙአየሁ ታደሰ እንደገለፁት በሀገር አቀፍ ደረጃ በአራት ዙሮች ለአመራሮች ስልጠና መሰጠቱን ገልጸው ለአምስተኛ ዙር በየደረጃው ለሚገኙ በሁሉም ግንባር ለምገኙ አመራርና አባባሎች እንዲሁም ለቀጠና አመራሮች እና አባላት እንደምሰጥ ገልጸዋል ስልጠናው በተለያዪ 4 ርዕሶች ከታህሳስ 11-14/2016ዓ/ም እንደምሰጥ አክለዉ ገልጸዋል።

አቶ ብዙአየሁ አክለውም እንደተናገሩት የሀገራዊ ገዥ ትርክት እሳቤን በየደረጃው ለሚገኙ የፓርቲው አመራሮችና አባላት በማስረፅ የተጀመረውን የሀገረ መንግስት ግንባታና ሀገራዊ መግባባትን ከዳር ማድረስ ያስፈልጋል ብለዋል።

አቶ ታደለ ጥላሁን የይ/ጨፌ ከተማ ከንቲባ እንደገለጹት በየደረጃው የሚገኙ የፓርቲው አመራሮችና አባላት ስልጠናውን በተቀመጠው ጊዜ ሰለዳ መሠረት በጥብቅ ዲስፕሊን በአግባቡ መሰልጠን እንዳለባቸው አሳስበዋል።

በኦሬንተሽን መድረክ ላይ የከተማ አስተባባሪ አካል የከተማው አጠቃላይ አመራሮች ሁሉም የፐብልክ ሰርቫንት አባላት ናየደቡብ ራድዮና ተለቭዥን ድርጅት አባላትተሳታፊ ሆነዋል።
ዘገባው የይ/ጨፌ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ነው፡፡

Videos (show all)

ፕሮጀክቶች ተመርቀዋል
ሰው ተኮር ተግባራችንየመጨረሻው #ክፍል
ሰው ተኮር ተግባራችንክፍል-3
ሰው ተኮር ሥራዎቻችን ክፍል-2
ብልጽግና ፓርቲ ሰው ተኮር ፓርቲ ነው ሲባል በምክንያት ነው!!💚💚 ክፍል-1
የጠቅላይ ሚንስተር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ድንቅ ንግግር በ20ኛው የተባበሩት መንግሳት ድርጅት እንዱስትሪ ልማት ድርጅት ጉባዔ ላይ

Telephone