Teppi Town Gov't Communication Affairs Office

Teppi Town Gov't Communication Affairs Office

We work for update information

Photos from Teppi Town Gov't Communication Affairs Office's post 24/07/2024

ሐምሌ 17/2016 ዓ.ም

በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻልና የትምህርት ስብራትን ለመጠገን በተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየታዩ ነው_ ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር)

"የተማረ ትውልድ ለሁለንተናዊ ብልፅግና" በሚል መሪ ቃል የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ የ2017 የትምህርት ዘመን የዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች የንቅናቄ መድረክ በታርጫ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ የተገኙ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻልና የትምህርት ዘርፍ ስብራትን ለመጠገን በተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየታዩ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የህብረተሰብ ተሳትፎ ለትምህርት ዘርፍ ልማት ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነ ያብራሩ ርዕሰ መስተዳድሩ ህብረተሰቡ ለትምህርት ዘርፍ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ ልቀጥል ይገባልም ብለዋል።

በዘርፉ የባለድርሻ አካላት አስተባባሪነትና በህብረተሰቡ የነቃ ተሳትፎ የመማሪያና ማስተማሪያ መፅሃፍትን ለማሳተም በልዩ ትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

የመምህራንን አቅም ለማጎልበትና መሠረታዊ ጥያቄዎችን ለመፍታት የክልሉ መንግስት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛልም ብለዋል።

ተማሪዎች በራስ መተማመንን በመፍጠር በስነ ምግባር የታነፁ፣ በእውቀትና ክህሎት የዳበሩ ልሆኑ እንደሚገባም ተብራርቷል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ አልማው ዘውዴ በበኩላቸው የክልሉን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ በትምህርት ልማት ስራዎች ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

የፖለቲካ አመራር ቁርጠኛነት ለትምህርት ዘርፍ ልማት ውጤታማነት እጅግ ወሳኝ እንደሆነም አቶ አልማው አብራርተዋል።

የትምህርት ጥራት ያለ መምህር ብቃትና ቁርጠኛነት የሚሳካ አይደለም ያሉት አቶ አልማው በክልሉ የመምህራንን አቅም ለማጎልበት የተለያዩ ስራዎች እየተከናወነ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

በታርጫ ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው በዚሁ የንቅናቄ መድረክ የክልሉን ርዕሰ መስተዳድር ጨምሮ የክልል፣ የዞኖች፣ የወረዳዎችና የከተማ አስተዳደሮች የመንግስትና የፓርቲ የስራ ሀላፊዎች፣ የዘርፉ ባለድርሻ አካላትና ጥሪ የተደረገላቸው አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ ሲል የዘገበው የክልሉ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ነው።

Photos from Teppi Town Gov't Communication Affairs Office's post 23/07/2024

"በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ ድንገተኛ የመሬት ናዳ አደጋ የበርካታ ዜጎቻችንን ሕይወት ቀጥፏል። በደረሰው አስከፊ ጉዳት የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን እገልጻለሁ።

አደጋውን ተከትሎ የፌዴራል የአደጋ መከላከል ግብረ-ሀይል በአካባቢው ተሰማርቶ የአደጋውን ጉዳት ለመቀነስ ርብርብ እያደረገ ነው።"

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Photos from Teppi Town Gov't Communication Affairs Office's post 23/07/2024

ሐምሌ 16/2016 ዓ.ም

ምክር ቤቱ 17.6 ቢሊዮን ብር በጀት አፀደቀ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ለ2017 በጀት አመት ዕቅድ ማሳኪያ የ17 ቢሊዮን 622 ሚሊየን 88ሺህ 4 መቶ 2 ብር በጀት አፅድቋል።

በጀቱ ለምክር ቤቱ ቀርቦ ምክክር እና ውይይት ከተደረገ በኋላ ነው በሙሉ ድምፅ የፀደቀው።

የመንግሥት ግምጃ ቤት፣ የውስጥ ገቢ፣ ከውጭ እርዳታ፣ ከዘላቂ የልማት ግቦችና ሌሎች የገቢ ምንጮች በጀቱ ይገኛል ነው የተባለው።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ እንደገለፁት፤ በጀቱ ከአምናው በጀት ጋር ስነፃፀር የ4.1 ቢሊዮን ብልጫ ወይም የሳላሳ በመቶ ዕድገት አለው ነው ያሉት።

በጀቱ ውስን ነው፤ የህብረተሰቡ የመልማት ፍላጎት ደግሞ ከፍ ያለ በመሆኑ በጀቱን በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባም አሳስበዋል ሲል መረጃውን ያገኘነው ከደሬቴድ ነው።

Photos from Teppi Town Gov't Communication Affairs Office's post 23/07/2024

ሐምሌ 16/2016 ዓ.ም

በ2016 በጀት ዓመት የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ የልማት ስራዎች ተሰርተዋል። ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ

ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ከምክርቤቱ አባላት ለተነሱላቸው አስተያየቶችና ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል ፡፡

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክርቤት 6ኛ ዙር 3ኛ ዓመት 6ኛ መደበና ጉባኤ በሁለተኛው ቀን ውሎ በተነሱ የአስፈጻሚ ተቋማት አፈጻጸም ሪፖርት ላይ በተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል ፡፡

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ከምክርቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ በግብርና ልማት ስራዎች ፣በንጹህ መጠጥ ውሃና መስኖ ተቋማት ግንባታ፣በሌማት ትሩፋት ስራዎችና በቡና ልማት ስራዎች ላይ ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል ፡፡

የግብርና ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ አኳያ በክልሉ የአፈር ማዳበሪያ አጠቃቀም ከጊዜ ወደ ጊዜ መሻሻሎች የታዩበት መሆኑንና ከዚህም ጋር ተያይዞ የአፈር ማዳበሪያ ሽያጭ ገንዘቦች ወደ አካውንት ከማስገባት አንጻር ያሉ መሰረታዊ ችግሮች ሊቀረፉ እንደሚገባ በምላሻቸው አስታውዋል ፡፡

በክልሉ ተከስቶ የነበረውን የሰላምና ጸጥታ ሁኔታ ወደ አስተማማኝ ደረጃ ማድረስ መቻሉን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ ቀጣይነት ባለው መልኩ ተጠናክሮ ይሰራበታል ብለዋል ፡፡

በገቢ አሰባበሰብ፣በስራ ዕድል ፈጠራ ስራዎችና በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሮች የሚያበረታታ ስራዎች ተከናውነዋልም ብለዋል ፡፡

በክልሉ የወባ በሽታ ስርጭት በህብረተሰቡ ላይ አሁንም ከፍተኛ ጫና ማሳደሩን ቀጥሏል ያሉት ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ችግሩን ለመቅረፍ ከፌደራል መንግስት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል ፡፡

ከመድሀኒት አቅርቦት ጋር በተያያዘ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ ማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎትን የማስፋት ጉዳይ ትኩረት የሚሰጠው ተግባር በመሆኑ ህብረተሰቡ በዚህ በመሳተፍ ህክምና ወጪውን በመቀነስ ጤናውን እንዲንከባከብ ምክርቤት አባላት ድርሻቸውን እንዲወጡም ጠይቀዋል ፡፡

በክልሉ የተጀመረውን የብሔረሰቦችን ባህል ፣ቋንቋ፣ታሪክና ወግ ለማልማት የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ከቋንቋ ተናጋሪ ብሐረሰቡ ተወላጆች ጋር በቀራረብ አጠናክሮ የማስቀጠል ስራ ይሰራልም ብለዋል ፡፡

በክልሉ ብሔራዊ ፓርኮች ለምተው እንደሚገኙ ያብራሩት ርዕሰ መስተዳድሩ አዳዲስ ፓርኮችን ከልሎ ለማልማት ሰፊ ጥናት የሚፈልግ በመሆኑ ከህብረተሰቡ ጋር በመወያየትና በመግባባት በጥንቃቄ በጥናት ላይ የተመረኮዘ ምላሽ መስጠት ተገቢ መሆኑን አብራርተዋል ፡፡

በመንገድና ድልድይ መሰረተ ልማቶች የማስፈጸም አቅም እየጎለበተ መምጣቱን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ የህብረተሰቡን ፍላጎት የተሟላ ለማድረግ የተጀመረውን የህብረተሰብ ተሳትፎ አጠናክረነረ እናስቀጥላለን ብለዋል ፡፡

በመደመር ትውልድ በተገኘ ሀብት በክልሉ 6 ቤተ መጻህትን ለመገንባት ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በዘንድሮ ዓመት በቦንጋ ከተማ መጀመሩና ይህም በሂደት በሌሎቹ ተጠናክሮ እንደሚሰራም አብራርተዋል ፡፡

በከተሞች የሚስተዋለውን ህገ ወጥ የመሬት ወረራ ለመከላከል በተደረገው ስራ መሻሻሎች መኖራቸውን በማመላከት ህገ ወጥነትን ለመከላከል የሚሰራው ስራ ተጠናክሮም ይቀጥላል ብለዋል ፡፡

ግንባታቸው የተጓተቱ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት እንደየችግራቸው ስፋት እየታየ ምላሽ የመስጠት ሂደቱ ተጠናክሮም ይቀጥላል ሲሉ አብራርተዋል ፡፡

በአርብቶ አደሩ አካባቢ የፍትሐዊነት ተጠቃሚነትን ከማረጋገጥ አንጻር የ

Photos from Teppi Town Gov't Communication Affairs Office's post 23/07/2024

ሐምሌ 16/2016ዓ/ም

የከተማችን ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር "የቴክኖሎጂ አጠቃቀማችንን ለማሻሻል የመኸር ምርትና ምርታማነትን እናሳድጋለን "ብለዋል።

በቴፒ ከተማ ግብርና ደን- አካባቢ ጥበቃ ህብረት ሥራ ልማት ጽ/ቤት የ2016 ዓ/ም እቅድ የአፈፃፀም ግምገማና 2017 ዓ/ም የመኽር እቅድ ዙሪያ ከባለድርሻ አካለት ጋር የንቅናቄ መድረክ ተካሄደ።

መድረኩን የከፈቱት ግብርና ደን-አካባቢ ጥበቃ ህብርት ሥራ ጽ/ቤት ኃለፍ አቶ አድሱ ሸዋ መክፈቻ ንግግር ሲያደረጉ እንዳሉት በመኸር እርሻ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል በማድረግ ከአርሶ አደሩ ጎን በመሆን ምርትና ምርታማነትን ለማረጋገጥ እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

በቀጣይ ሰራ ዘመን ስኬታማ ለማድረግ በከተማችን ላይ ያሉ ገበሬዎች በቴክኖሎጂ በማዘመን የተለያዩ ሰብሎችን በትንሽ ቦታ ላይ ብዙ ሰብሎች በማምረት ተጠቃሚነት እናረጋግጣለን ብለው የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሻሻል የተቀመጠውን የምርታማነት ግብ ማሳካት ዋነኛ ዓለማ እንደሆነ ገልፀዋል።

የቴፒ ከተማ ከንቲባ ተወካይና የሠላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ደረጄ አዝመራው እንዳሉት በግብርና ዘርፍ በሀገራችን እና በከተማ ኢኮኖሚ የጎላ አሰተዋጽኦ ያለው ዘርፍ በመሆኑ በመኽር ወቅት ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በልዪ ትኩረት ሊሰራ ይገባል ብለዋል ።

ግብርና ደን-አካባቢ ጥበቃ ህብርት የሥራ ሂደቱ ባለሙያ የሆኑት አቶ መልካሙ ተሰማ ሰነድን ሲያቀርቡ እንዳሉት 2016ዓ/ም በመኽር ዕቅድ ወቅት ጥንካሬዎች በማጠናከር ጉድለቶችን በማስተካከል 2017 ዕቅድ ተዘጋጅቶ አጠናክርን መቀጠል እንደሚገባ አቀርበዋል።

የቴክኖሎጂ አጠቃቀም በማሻሻል ማሳደግ፤ በኩታ ገጠም የአመራር ዘዴን ተግባራዊ በማድረግ የሜካናይዘሽን አመራረት በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን መጨመር ፤ የድህረ ምርት ቴክሎጅ አጠቃቀም በማሻሻል የምርት ብክለት ለመቀነስ ይርዳል ብለዋል ።

በመቀጠልም የ2017 ዕቅድ ግቦችን ለማሳካት የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን በብቃት መሥራት ፤ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ችግሮችን መፍታት (የአቅርቦትና አጠቃቀም ችግር እንዲፈታ ተቀናጅቶ መሥራት) ፤ የባለሀብቱን ተሳትፎ ማሳደግ ፤ የኤክስቴንሽን አገልግሎት ተደራሽነት ማሻሻል ፤ የአርሶ አደር ማሰልጠኛ ማዕከል ሰርቶ ማሳያ ስራዎችን ማከናወን ፤ የቅድመና ድህረ ምርት አያያዝ እና አጠቃቀም ማሻሻል ፤ የመልካም ተሞክሮዎች የመለየት፤ የማስፋፋት ሰራ መሰራት እንዳለብን ገልፀዋል ።

2016ዓ/ም 55.5 ሄክታር ታዕቅዶ አፈፃፀም 48.5 ሄክታር መሠራት ተችሎል በ2017ዓ/ም 221 ሄክታር ለመስራት ታቅዶል ብለዋል ።

በሸካ ዞን ግብርና ደን- አካባቢ ጥበቃ የእርሻና ህብርት ሥራ የዘርፋ ኃለፋ አቶ ሽመልስ ካሣ እንዳሉት አርሶ አደሮች ተጠቃሚ ሁሉም ባለ ድርሻ አካለት በመቀናጀት መሰራትና ምርትንና ምርታማነትን ለመጨመር የሚያስችል የከተማችን ህብረተሰብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ የተለያዩ የቴክኖሎጂና የዘር አቅርቦት የዘር አመራጥ ወደ ውጭ ምንዛሬ የሚያሰገኙ ምርቶች ለይቶ በስፋት በመስራት የከተማችን የመሠረተ ልማት ችግሮችን ማሻሻል እንችላለን ብለው የዕለቱ የንቅናቄ መድረክ ተቋጭቷል ።

Photos from Teppi Town Gov't Communication Affairs Office's post 22/07/2024

ሐምሌ 15/2016 ዓ.ም

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክርቤት 6ኛ ዙር 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 6ኛ መደበኛ ጉባኤ መካሄድ ጀምሯል።

በጉባኤው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ምክርቤት ዋና አፈጉባኤ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ በተገባደደው 2016 በጀት ዓመት ምክር ቤቱ በህገ መንግስቱ የተሰጠዉን ሀላፊነት ለመወጣት በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል።

ከአቻ ክልሎች እንዲሁም ከተወካዮች ም/ቤትና ከፌደሬሽን ምክር ቤት ጋርም ተግባራትን በቅንጅት ማከናወን መቻሉን አፈጉባኤው ተናግረዋል።

በ6ኛ ዙር 3ኛ የስራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባኤ በም/ቤቱ በተቀመጡ አቅጫጫዎች ላይም በትኩረት ለመስራት ጥረት መደረጉንም አፈጉባኤ ወንድሙ ኩርታ ተናግረዋል ፡፡

በዚህም አንዳንድ የአስፈጻሚ ተቋማት ከክልሉ ም/ቤት ጋር በቅንጅት ለመስራት ያደረጉት ጥረት የሚበረታታ ነበርም ብለዋል፡፡

በሕገ-መንግስቱ በተቀመጠው ስልጣን መሠረት ምክር ቤቱ ጉባኤዎችን ማካሄድ፣ የአስፈፃሚ ተቋማትን የዕቅድ አፈፃፀም መገምገም፣ ግብረ-መልስ የመስጠት፤የመስክ ምልከታ ማድረግ፤ የሕዝብ አስተያየት መሰብሰቢያ መድረኮችን በመፍጠር ሲሰራ መቆየቱንም ጨምረው ገልጸዋል ።

በከክልሉ በሚዘጋጁ ረቂቅ አዋጆች ላይ ግብዓት በማሰባሰብ፣ የም/ቤቶችን የጋራ ምክክር ፎረም በማካሄድና ለቀጣይ የተሻለ አሰራር ለመዘርጋት በአመራሩና በባለሙያዎች የልምድ ልዉዉጦች መደረጋቸውንም አብራርተዋል፡፡

የክልሉ ም/ቤት 6ኛ ዙር 3ኛ የስራ ዘመን 6ኛ መደበኛ ጉባኤያው ለተከታታይ ቀናት የሚቆይ መሆኑን በመጠቆም በሚቀርቡ የም/ቤቱ አጀንዳዎች ላይ ጥልቅ ዉይይትና ምክክር በማድረግ ቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ የክልሉን ህዝብ ዉክልና በአግባቡ በመወጣት ህገ መንግስታዊ ተልዕኳቸውን እንዲወጡም አፈጉባኤ ወንድሙ ኩርታ አሳስበዋል ሲል የዘገበው የክልሉ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ነው።

Photos from Teppi Town Gov't Communication Affairs Office's post 21/07/2024

ሐምሌ 14 / 2016 ዓ.ም

የድሩማን ኮሌጅ በቴፒ ካምፓስ በአራቱም የትምህርት መስኮች ለ5ኛ ዙር ጊዜ ያሰለጠናቸውን 268 ተማሪዎችን በደረጃ አራትና በደረጃ ሁለት በዛሬው ዕለት አስመርቋል ።

በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የዱሩማን የኮሌጅ ቴፒ ካምፓስ ዋና ዲን አቶ አድሱ አዘነ እንዳሉት ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመንግስት የግል ድርጅቶች ኃላፋዎች ጥሪ የተደረገላችሁ እንግዶች ክቡራንና ክቡራን የዱሩማን ኮሌጅ እጩ ተመራቂ ተማሪዎች የተማሪ ወላጆች በምርቃቱ ሰነ-ሰርዓት የተገኛችሁ እንግዶች በመጀመሪያ የአክብሮት ሠላምታና ምስጋናቸውን አቅርቧል ።

ክቡራን እጩ ተመራቂዎች ተማሪዎች በኮሌጁ ባሳለፉት ለሦስት ተከታይ አመታት ቆይታ በሰልጠና ሂደቱ በቂ የሆና ዕውቀትና ክህሎት እንዳገኛችሁ እናምናለን ፣ በመሆኑም የትምህርት መሠረታዊ ዓላማው የአስተሳስብ፤ የአመለካከትና የባህሪ ለውጥ ማምጣት መሆኑን አውቃችሁ ሥራ የሚሰራ ሰነ - ልቦናችሁን እራሳችሁን በማዘጋጀት ቤተሰቦቻችሁንና መንግስት በቁርጠኝነት እየሰራ ባለው ሀገራችን ከድህነት ጎዳና የሚላቀቅበት ተግባር ለይ እየ እራሳችሁን አሻራ ማሳረፍ እንደሚገባችሁ በትህትና ገልፀዋል ።

አክለውም ተመራቂ ተማሪዎችም ኮሌጅ የቀሰሙትን ዕዉቀት ቀጣይነት ያለው ተግባራዊ በማድረግ የቤተሰባቸውንና የማህበረሰቡን ችግር መፋታት መቻል እንዳለባቸው መልክታቸው አስቀምጠዋል ።

በዱርማን ኮሌጅ በዘንድሮው ተመራቂ ተማሪዎች በአራቱም የትምህርት መስኮች ማለትም
1ኛ በአካውንቲንግ በደረጃ ሁለት፤ በደርጃ አራት 66 ተማሪዎች
2ኛ በሰው ኃብት አሰተዳደር አሰ/ር በደረጃ ሁለት፤ በደርጃ አራት 66 ተማሪዎች
3ኛ በአይሲቲ በደረጃ ሁለትና በደርጃ አራት 86 ተማሪዎች
4ኛ በእጽዋት ሳይንስ በደረጃ ሁለት፤ በደርጃ አራት 50 ተማሪዎችን በጠቅላላ በአራቱም የትምህርት መሰኮች በ2016ዓ/ም የተመረቁ ተማሪዎችን 268 በዛሬው ዕለት አስመርቋል ።

በምርቃት ሰነ ሰርዓቱ የተገኙት የሸካ ዞን የቴፒ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዋና ፕሬዘዳንት አቶ ተካልኝ ሻወኖ ፤ የሸካ ዞን ኢ/ሥራ / ክህሎት ኃለፋ አቶ አማኑኤል ግርማ፤ የሸካ ዞን የቴፒ ከተማ ዋና ከንቲባ ወንድሙ ግርማ ከፋተኛ ውጤት ያሰመዘገቡ ተማሪዎችን ሽልማት ሰር ሰርዓት አድርገው

በቀጣይ በ2017 ዓ/ም የትምህርት ዘመን ተማሪዎች የኮሌጅ አስተማሪዎች የተሻሻለ የመማር ማሰተማር ዘዴዎችን በመጠቀም ጥሩ ውጤቶችን ማስመዝገብ እንዳለባቸው አሰቀምጠው የዕለቱ የምርቃት ፕሮግራም አጠናቀዋል ።

Photos from Teppi Town Gov't Communication Affairs Office's post 19/07/2024

ሐምሌ 12/2016 ዓ.ም

የቴፒ ከተማን ዕድገት ለማፋጠን ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቁርጠኝነት አንዲሰሩ ጥሪ ቀረበ።

የሸካ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ
የከተሞች ፈርጅ ለውጥ ጥናት ዙሪያ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በቴፒ ከተማ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል።

በመምሪያዉ የከተሞች አደረጃጀት ዘርፍ ቡድን መሪ አቶ ቢሻው ኪታሞ በከተሞች ፈርጅ ለውጥ ጥናት ዙሪያ የተዘጋጀውን ሰነድ አቅርበዉ ምክክር ተደርጎበታል።

የሸካ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ሀላፊ አቶ ሸሎ አዴሎ በበኩላቸዉ የቴፒ ከተማን ደረጃ በማሻሻል የፈርጅ ለውጥ ለማምጣትእንዲቻል በተቀናጀ መልኩ በተግባር የተደገፈና በመረጃ የተደራጀ ሥራ መሥራት አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል።

የቴፒ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ወንድሙ ግርማ ሁላችንም በተሰማራንበት የሥራ መስክ የድርሻችን በመወጣት ለከተማዋ ዕድገት ብሎም ፈርጅ ለውጥ በቁርጠኝነት መሥራት ይገባናል ብለዋል።

አክለዉም የከተማዉን ህዝብና ባለሀበቶችን በሙሉ በማሳተፍና በመንግስት ደረጃ የማስተባበር ሥራ መሥራት እንዲሁም ድጋፍ ማደረግ ከተቻለ ከተማውን ማደግ ወዳለበት ፈርጅ ላይ ማድረስ የሚቻል መሆኑን ተናግረዋል።

ከተሳታፊዎች መካከል አንዳንዶቹ በሰጡት አስተያየት የከተማዋን ዕድገት ለማፋጠንና ለፈርጅ ለዉጥ የሚያስፈልጋትን መስፈርቶች እንዲታሟላ በቁጭት የድርሻቸዉን ለመስራት ዝግጁ መሆናቸዉን ተናግረዋል።

Photos from Teppi Town Gov't Communication Affairs Office's post 18/07/2024

ሐምሌ 11/2016 ዓ.ም

በሸካ ዞን የተለያዩ የሚዲያ አማራጮችን ተደራሽነት ለማስፋት የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለጸ

የሸካ ማህበረሰብ ቴሌቪዥን ቦርድና የደቡብ ሬዲዮና ቴለቪዥን ድርጅት ማሻ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸዉን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል።

የሸካ ዞን የሚዲያ ተደራሽነት ጥያቄ ምላሽ ሳያገኝ ለዘመናት ከቆዩ የሀገራችን ጥቂት ዞኖች አንዱ ነው።

ሆኖም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የሚዲያ ተደራሽነት ችግር ለመቅረፍ በየደረጃዉ ያሉ ባለድርሻ አካላት በሰጡት ቁርጠኛ አመራርና ድጋፍ ችግሩ እየተቀረፈ ነው ለዚህም ማሳያ አሁን በሥራ ላይ የሚገኘዉ የማሻ ቅርንጫፍ ኤፍ ኤም ተጠቃሽ ነው።

አሁንም በዞኑ የሚዲያ አማራጮችን ይበልጥ ለማስፋትና የሸካ ማህበረሰብ ቴለቪዥን ቦርድ አቋቁሞ የቴሌቪዥን ዜናና ፕሮግራም ስርጭት ለመጀመር የሚያስችለዉን ተግባር እያከናወነ ይገኛል።

በዛሬዉ ዕለትም ቦርዱ ከደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ማሻ ቅርንጫፍ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችለዉን ስምምነት ተፈራርሟል።

የመግባቢያ ሰነዱ የሸካ ማህበረሰብ ቴሌቪዥን ለጊዜዉ የአየር ሰዓት ከደቡብ ሬድዮና ቴለቭዥን ድርጅት ተከራይቶ በሚሰራበት፣ አስፈላጊዉ የሰዉ ኃይልና ግብዓቶች በሚመለከትና ተያያዥ ለሥራዉ ስኬት አጋዥ የሆኑ ጉዳዮችን አካቷል።

በቀጣይም በጋራ ለመስራት የሚያስችለዉን የመግባቢያ ሰነድ የሸካ ማህበረሰብ ቴሌቪዥን ቦርድ ሰብሳቢና የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ እና የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ማሻ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ አቶ ታምሩ ጎዱ ተፈራርመዋል።

የዘገበው የሸካ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ነው።

Photos from Teppi Town Gov't Communication Affairs Office's post 18/07/2024

ሐምሌ 11/2016 ዓ.ም

በሸካ ዞን የቴፒ ከተማ ምክር ቤት ባካሄደው 2ኛ ዙር 11ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አካሂዷል።

ምክር ቤቱ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ የቴፒ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ ሹመት አፅድቋል።

የቴፒ ከተማ ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ጥላሁን ዳቃ በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለፁት ምክር ቤቶች መደበኛ ጉባኤ ከመካሄዱ በፊትም ሆነ መደበኛ ጉባኤ ከተካሄደ በኋላ አስቸኳይ ውሳኔ የሚሹ ጉዳዮች ሲኖሩ ምክር ቤት አባላትን አስቸኳይ ጉባኤ በመጥራት ውሳኔዎችን ያስተላልፋሉ ብለዋል።

በምክር ቤቱም የቴፒ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ ሆነው የተሾሙትን የአቶ ያሬድ ለገሰን የትምህርት ዝግጅትና አገልግሎት አዲስ የተሾሙት የቴፒ ከተማ ከንቲባ አቶ ወንድሙ ግርማ ለምክር ቤቱ አቅርበው ምክር ቤት አባላትም ሹመቱን ያፀደቁ ሲሆን አቶ ያሬድ ለገሰም በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው ቃለ መሃላ ፈፅመዋል።

Photos from Teppi Town Gov't Communication Affairs Office's post 18/07/2024

ሐምሌ 11/2016 ዓ.ም

የቴፒ ከተማ ምክር ቤት ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ የከተማውን ከንቲባ ሹሟል

በሸካ ዞን የቴፒ ከተማ ምክር ቤት ባካሄደው 2ኛ ዙር 11ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አቶ ወንድሙ ግርማን የከተማው ከንቲባ አድርጎ ሹሟል።

ከንቲባውን በዕጩነት ያቀረቡት የሸካ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አአቶ ዘርሁን አንደሞ የዕጩውን የትምህርት ደረጃና የስራ ልምድ በተመለከተ ለምክር ቤቱ በዝርዝር አቅርበዋል።

አዲስ የተሾሙ ከንቲባን በተመለከተ የምክር ቤቱ አባላት አስተያየት ከሰጡ በኋላ በሙሉ ድምፅ አፅድቀዋል።

አዲስ የተሾሙት ከንቲባም በምክር ቤቱ ፊት ቃለ መሃላ ፈፅመዋል።

አዲሱ ከንቲባ አቶ ወንድሙ ግርማ ከቀድሞው ከንቲባ አቶ ዮሐንስ በንዲ ጋር ርክክብ አድርገዋል።

Photos from Teppi Town Gov't Communication Affairs Office's post 17/07/2024

ሐምሌ 10/2016 ዓ.ም

ከተሞች ለጎብኝዎች ምቹ ለነዋሪዎች ተስማሚ ሰው ወዶና ፈቅዶ የሚዝናናባቸው ከተሞች ለማድረግ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የደን፣አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ቢሮ እየሰራ እንደሚገኝ ገለፀ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የደን፣አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ቢሮ የደረቅ ቆሻሻ ማስወገጃ /ደስት ቢን/ለሸካ ዞን ቴፒ ከተማ ማዘጋጃ ቤት አስረክቧል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የደን፣አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ኢንጂነር አስራት ወልደ ማርያም እንደተናገሩት ቢሮው በክልሉ የተፈጥሮ ሀብቶችንና ፀጋዎችን አደጋ ሳይደርስባቸው ተጨማሪ የልማት ሥራዎችን በማከናወንና ሚዛኑን ጠብቆ እንዲሄድ በማድረግ እንዲሁም ከተሞችን ለነዋሪው ምቹ የማድረግ ሥራ እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

አክለውም እንደ ተቋም ዜጎች ንፁህ፣ ምቹ አካባቢ ላይ የመኖር ህገ-መንግስታዊ መብታቸውን ለማስከበር ተቋማዊ በሆነ መልኩ ለመምራት ይገባልም ብለዋል።

በሌላ በኩል በከተሞች ባህሪ ውስብስብነት ከህዝብ ቁጥር መጨመርና ፍላጎት እያደገ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ በቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ላይ ባለሀብቶችና የተለያዩ ተቋማት ትኩረት እንዲሰጡ ከማስቻልም አንፃር ቢሮው የበኩሉን ድርሻ ለመወጣትና በዚያው ልክ የድጋፍ ክትትልና ቁጥጥር ሥራዎችን በማድረግ ከህግ ያለፈ ጉዳይ ካለ ህግ የማስከበር ሥራ እንደሚሰራም ተናግረዋል።

ዶክተር ኢንጂነር አስራት ወልደ ማርያም አክለውም የደረቅ ቆሻሻ ማስወገጃ /ደስት ቢኖችን/ በክልሉ በ6ቱም ዞኖች ለማሰራጨት ዝግጅት መደረጉን ገልፀው በዛሬው ዕለትም በሸካ ዞን ለቴፒ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤት
ማስረከባቸውን ተናግረዋል።

በተያያዘም የተሰሩ የቆሻሻ መስወገጃ ደስት ቢኖች ለታለመላቸው ዓላማ እንዲውሉ አሳስበው ሁሉም ዜጋ ኃላፊነቱን ወስዶ ደረቅ ቆሻሻዎችን በአግባቡ እንዲያስወግድና ሁሉም መስሪያ ቤቶች፣ የክልሉን አርአያ ተከትለው በየዓመቱ የዕቅድና የበጀት አካል በማድረግ በትኩረት መሥራት እንዳለባቸውና የአካባቢ ጥበቃ ጽህፈት ቤትም በአግባቡ ተግባራዊ መደረጉን ክትትል እንዲያደርግ አሳስበዋል።

በሌላ በኩል ሆቴሎችና አገልግሎት መስጫ ተቋማትም በአካባቢያቸው የሚፈጠሩ ቆሻሻዎችን ማከማቸት የሚችል መሰል የቆሻሻ መስወገጃ ደስት ቢኖችን ማዘጋጀት እንዳለባቸው ገልፀው ማዘጋጃ ቤቱና የከተማ አስተዳደሩ ህብረተሰቡን የማንቃት ሥራ እንዲሰሩም አሳስበዋል።

በመጨረሻም ድጋፉ በየዓመቱ አቅም በፈቀደ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን ገልፀው ቢሮው የክልሉ ከተሞችን ለጎብኝዎች ምቹ ለነዋሪዎች ተስማሚ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራ ቃል ገብተው ለተግባሩ ስኬትም አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የደን፣አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ቢሮ ምክትል የቢሮ ኃላፊ አቶ ደምሴ ደንቦ በበኩላቸው "ብክለት ይብቃ ውበት ይንቃ " በሚል መሪ ቃል እንደ ክልል የአካባቢ ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ገልፀዋል።

አክለውም በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች በተፈጥሮ አረንጓዴ እንደሆኑ ቢታወቅም በከተሞች ከፕላስቲክና መሰል ቆሻሻዎች ጋር ተያይዞ እንዳይቆሽሹና እንዳይበከሉ እየተሰራ መሆኑን ገልፀው በቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ላይ ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ እንዲከናወን በክልሉ በ6 መቶ ሺህ ብር ወጪ የቆሻሻ ማስወገጃ ደስት ቢን መዘጋጀቱን ተናግረዋል።

የቴፒ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ያሬድ ለገሰ ቢሮው ያደረገውን ድጋፍ አመስግነዋል።

Photos from Teppi Town Gov't Communication Affairs Office's post 15/07/2024

ሐምሌ 8/2016 ዓ.ም

ችግኞችን መትከል ብቻ ሳይሆን በአግባቡ ተንከባክቦ ማሳደግ ላይ ትኩረት እንዲደረግ ተጠየቀ።

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ቤቴል ሲኖዶስ የኪ ፕሪስቢተሪ የቴፒ ማህበረ ምዕመናን የአቮካዶ ችግኞችን በቴፒ ከተማ ተክለዋል።

በቴፒ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ፅዳትና ውበት አረንጓዴ ልማት ሥራ ሂደትና በከተማ ግብርና ጽህፈት ቤት አስተባባሪነት የቤተክርስቲያኗ ምዕመናን በዛሬው ዕለት በቤተክርስቲያኗ ቅጥር ግቢና ከቤተክርስቲያናኗ ውጪ የአቮካዶ ችግኝ ተክለዋል።

በችግኝ ተካላ ላይ ያገኘናቸው የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ቤቴል ሲኖዶስ የኪ ፕሪስቢተሪ የቴፒ ማህበረ ምዕመናን አገልጋይ ቄስ ደበበ ወልደ ጊወርጊስ እንደገለፁት ቤተክርስቲያኗ ለምዕመናን የወንጌል አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ የተለያዩ ማህበራዊና የልማት ሥራዎችን በማከናወን ሀገራዊ ግዴታዋን እየተወጣች መሆኗን ተናግረዋል።

አክለውም እንደሀገር የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል የተያዘውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አንድ አካል የሆነውን የችግኝ ተከላ የቤተክርስቲያኗ ምዕመናን በማሳተፍ በከተማ ውስጥም ይሁን ከከተማ ውጪ ባሉ አጥቢያ ቤተክርስቲያን የተለያዩ የጥላ ዛፎችንና ለምግብነት የሚውሉ ችግኞችን እየተከለች መሆኑን ተናግረዋል።

ያነጋገርናቸው የቤተክርስቲያኗ አገልጋይና ምዕመን አቶ ዋለ አያሌው እንዳሉት ችግኝ መትከል ለመጪው ትውልድ ማሰብና ለጋራ ጥቅም መሆኑን በማሰብ እንደ ምዕመን የራሳቸውን አሻራ ማስቀመጣቸውን ተናግረዋል።

አክለውም በቀጣይ ቤተክርስቲያኗ ከመንፈሳዊ አገልግሎት ጎን ለጎን እንደሀገር የተያዘውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ምዕመኑን በማሳተፍ ለማስቀጠል በትኩረት እንደሚሰራ ገልፀዋል።

በተያያዘም የቴፒ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ፅዳትና ውበት አረንጓዴ ልማት ሥራ ሂደትና የቴፒ ከተማ ግብርና ጽህፈት ቤት ላደረጉላቸው የችግኝ ድጋፍ አመስግነው በቀጣይም አጋርነታቸው እንዳይለያቸው ጠይቀዋል።

የቴፒ ከተማ ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አዲሱ ሸዋ በከተማው ከተለያዩ ተቋማት በተገኘው የችግኝ ድጋፍ በጽህፈት ቤታቸውና በቴፒ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ፅዳትና ውበት አረንጓዴ ልማት ሥራ ሂደት አስተባባሪነት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በተለያዩ ተቋማት ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ገልፀው ከነዚህ ተቋማት መካከልም የኃይማኖት ተቋማትም የሚጠቀሱ መሆናቸውን አንስተዋል።

አክለውም በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን ለቴፒ መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያንም የአቮካዶ ችግኝ ድጋፍ መደረጉንና በምዕመናን መተከሉን አመስግነው ችግኞችን ከመትከል ባለፈ እንክብካቤ እንዲደረግላቸው ጠይቀዋል።

Photos from Teppi Town Gov't Communication Affairs Office's post 14/07/2024

ሐምሌ 7/2016 ዓ.ም

የትምህርት ጥራትን ለማስመዝገብ የግል የትምህርት ተቋማት አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑ ተገለፀ።

የአዘነ ውቤ መታሰቢያ አካዳሚ የ2016 ዓ.ም የቅድመ መደበኛ ተማሪዎችን በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ ሁለገብ አዳራሽ አስመርቋል።

የአዘነ ውቤ መታሰቢያ አካዳሚ ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ አቶ ተሾመ ታከለ በምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ ተገኝተው እንደገለፁት ዓለም አሁን ላይ የደረሰበትን የሥልጣኔ ደረጃ ላይ ለመድረስ የትምህርት ዘርፉ የተጫወተው ሚና የጎላ መሆኑን ገልፀዋል።

አክለውም የአዘነ ውቤ መታሰቢያ አካዳሚ በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ ላይ ትውልድን ከመዋለ ህፃናት ጀምሮ በሥነ ምግባር፣ በዕውቀትና በክህሎት በመቅረፅ በትምህርት ቤቱ የሚማሩ ተማሪዎችም የተሻለ ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑንም ተናግረዋል።

በተያያዘም በከተማው የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ በፕሮጀክት በመቅረፅና በዘርፉ የማስፋፊያ ግንባታ በመገንባት የትምህርት አሰጣጥ ሂደቱን የበለጠ ለማሻሻል እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

በሌላ በኩል በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ሰርቪስ/School Bus/ ግዥ በመፈፀምና ወደ ከተማው በማስመጣት ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ትምህርት አሰጣጡን ለማሳደግ እየሰራ መሆኑንም አክለዋል።

በተሰማሩበት የትምህርት ዘርፍ ስኬታማ እንዲሆኑ እገዛ ላደረጉላቸው የመንግስት መስሪያ ቤቶች፣ የግል ድርጅቶችና ግለሰቦች ምስጋና አቅርበዋል።

የቴፒ ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ ተወካይ አቶ አብረሃም ወንድማገኝ እንደገለፁት የትምህርት ጥራትን ለማስመዝገብ የግል የትምህርት ተቋማት አስተዋጿቸው የጎላ መሆኑን ገልፀው በተለይ በዞናችን ቴፒ ከተማ ላይ አዘነ ውቤ መታሰቢያ አካዳሚ የተሻለ ውጤት እያስመዘገበ የመጣ የግል የትምህርት ተቋም መሆኑን ተናግረዋል።

አክለውም በከተማችን በትምህርት ዘርፉ የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ ላደረጉት ጥረትና አሁንም የትምህርት ተደራሽነትን ለማሳደግ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ለሚገኙት የተቋሙ ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ አቶ ተሾመ ታከለንና የትምህርት ቤቱ መምህራንን አመስግነው ተቋሙ ከዚህ የበለጠ እንዲሰራ ወላጆችና አጋር አካላት ድጋፍ ሊያደርጉ ይገባልም ብለዋል።

የትምህርት ቤቱ የቅድመ መደበኛ ርዕሰ መምህርት ሚስ መስታወት ገላሳ እንደገለፁት ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 2016 ዓ.ም ላለፋት 3 ዓመታት ያስተማራቸውን ወንድ 70 ሴት 51 በድምሩ 121 ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት ማስመረቁን ገልፀዋል።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ሀገራዊ አንድነትን፣ አብሮነትን፣ መቻቻልና ብዝሃነትን የሚያንፀባርቁ አስናኝና አስተማሪ የሆኑ ግጥሞች፣ ጭውውቶች፣ መነባንቦች፣ ድራማዎች፣ መዝሙሮች፣ ሽለላና ፉከራዎች፣ ባህላዊና ዘመናዊ ውዝዋዜዎች በትምህርት ቤቱ ተማሪዎች ቀርበዋል።

በመጨረሻም በትምህርት ቤቱ ከ6ኛና ከ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ውጪ ከቅድመ መደበኛ እስከ 7ኛ ክፍል ያሉና በትምህርታቸው ባስመዘገቡት ውጤት ከ1ኛ እስከ 3ኛ ደረጃ የወጡ ተማሪዎች ሠርተፍኬትና የተለያዩ ሽልማቶች ተበርክቶላቸዋል ።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተማሪ ወላጆች፣ ከተለያዩ ተቋማት የመጡ የክብር እንግዶች፣ የትምህርት ቤቱ መምህራን፣ ተማሪዎችና የአስተዳደር ሠራተኞች ተገኝተዋል።

Photos from Teppi Town Gov't Communication Affairs Office's post 13/07/2024

ሐምሌ 6 ቀን 2016 ዓ.ም

በቴፒ ከተማ የሰፈነዉ ሰላም ዘላቂ እንዲሆን አሁንም ቅንጅታዊ አሰራር በየደረጃዉ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ተባለ።

የቴፒ ከተማ ፖሊስ ከ15 ዓመት በላይ ሙያዊ ሥነ ምግባርን ጠብቀዉና መስዋዕትነት ከፍለዉ በአካባቢዉ ሰላም እንዲሰፍን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ለሰሩ የፖሊስ አባላት የሜዳሊያ ፣ የምስጋና፣ የምስክር ወረቀት ብሎም የማዕረግ ሽልማት መርሃ ግብር በቴፒ ከተማ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት አካሂዷል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሸካ ዞን ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኮማንደር አስታወሰኝ አይሞ ፖሊስ ከሚያከናዉናቸዉ በርካታ ተግባራት መካከል ወንጀልን መከላከልና የህብረተሰቡን ሰላም መጠበቅ ዋነኛዉ መሆኑን ጠቁመዋል።

በዚሁ ረገድ የቴፒ ከተማ ፖሊስ አባላት ከሌሎች የጸጥታ አካላት ጋር በአካባቢዉ ሰላም እንዲሰፍን ላደረጉት ተጋድሎ የምስጋና፣ የሰርትፍኬትና የሜዳሊያ ሽልማት መዘጋጀቱ በፖሊስ ተቋም ከሚሰጡ 3 ዓይነት የሽልማት ደረጃዎች አንደኛዉ መሆኑን አዉስተዋል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ክቡር አቶ መሰለ ከበደ በበኩላቸዉ የፖሊስና የጸጥታ አባላት ከራሳቸዉ ይልቅ ለህዝብ ሰላምና ደህንነት ሲሉ በበርካታ ተግዳሮት ዉስጥም ሆነዉ ለህዝብ ቅድሚያ ሰጥተዉ የሚሰሩ ህዝባዊ ሰራዊት መሆናቸዉን ተናግረዋል።

አክለዉም ለህዝቡ ሰላም አካላቸዉንና ህይወታቸዉን ጭምር የሚከፍሉ መሆናቸዉን ገልጸዉ ይህ ዓይነቱ መርሃ ግብር መካሄዱ ደግሞ ለቀጣይ ይበልጥ ተነቃተዉ እንዲሰሩ አጋዥ ነዉ ብለዋል።

በመርሃ ግብሩ ከተሳተፉት መካከል አንዳንዶቹ በሰጡት አስተያየት በተለያዩ ወቅቶች በቴፒ ከተማ የተፈጠረዉን ሰዉ ሰራሽ የጸጥታ ችግር ለመፍታት ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር መስዋዕነት ለከፈሉ በህይወት ለለሉና አሁን በሥራ ላይ ለሚገኙ የፖሊስ አባላቶች ምስጋና አቅርበዋል።

በቀጣይም በቴፒ ከተማ የሰፈነዉን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ ቅንጅታዊ አሰራርን በየደረጃዉ ማጠናከር እንደሚገባም አንስተዋል።

በመድረኩ የተገኙት የሸካ ዞን፣ የቴፒ ከተማና የኪ ወረዳ አመራሮች ባለፉት ጊዜያት በሸካ ዞን በተለይ በቴፒ ከተማና የኪ ወረዳ የተፈጠረዉን የጸጥታ ችግር ለመቅረፍ በቅንጅት መሰራቱን አስታዉሰዉ አሁንም ቅንጅታዊ አሰራር በየደረጃዉ አጠናክሮ ለማስቀጠል ይሰራል ብለዋል።

በኘሮግራሙ ማጠቃለያ መልዕክት ያስተላለፉት የሸካ ዞን መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አለማየሁ ዓለሙ በዞኑ የመጣዉ ሰላም ዘላቂ እንዲሆን ሁሉም የራሱን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት አሳስበዋል።

አያይዘዉም የፖሊስ ተቋም ጊዜዉ የሚፈልገዉን አገልግሎት ቅንነት በተላበሰ መልኩ ማስቀጠል እንዳለበት የገለጹት አቶ አለማየሁ ዓለሙ ወንጀልን ለመከላከል ሁሉም ከፖሊስ ጎን እንዲቆም አሳስበዋል።

በመርሃ ግብሩ ከ20 ዓመት በላይ ላገለገሉ የቴፒ ከተማ ፖሊስ አባላት ሜዳሊያ ሽልማት የተበረከተላቸዉ ሲሆን ለሌሎችም እንደየአገልግሎት መጠናቸዉ የምስክርና የምስጋና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

Photos from Teppi Town Gov't Communication Affairs Office's post 13/07/2024

ሐምሌ 6 ቀን 2016 ዓ.ም

የቴፒ ከተማ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ከ15 ዓመት በላይ ላገለገሉ የፖሊስ አባሎች የሜዳሊያ፣ የምስክር ወረቀትና የማዕረግ ሽልማት አሰጣጥ ኘሮግራም በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ እያካሄደ ነዉ።

የመርሃ ግብሩ ዓላማ በተለያዩ ወቅቶች በቴፒ ከተማ በተፈጠረዉ ሰዉ ሰራሽ የጸጥታ ችግር ምክንያት ከተለያዩ የጸጥታ አካላት ጋር መስዋዕት ከፍለዉ ሰላሙን ለመለሱና እየሰሩ ለቆዩት የፖሊስ አባሎች የምስጋና፣የሜዳሊያ ፣ የምስክር ወረቀትና የማዕረግ ሽልማት ለማበርከት ነዉ።

በመርሃ ግብሩ ላይ ከፌደራል፣ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፣ ከሸካ ዞን፣ ከቴፒ ከተማና ከየኪ ወረዳ የተዉጣጡ ከፍተኛ አመራሮችና ተጋባዥ እንግዶች እየተሳተፉ ነዉ።

Photos from Teppi Town Gov't Communication Affairs Office's post 12/07/2024

ሐምሌ 5/2016 ዓ.ም

የቴፒ ከተማ ገቢ አሰባሰብን ከስኬት ለማድረስ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ እንዲያደርጉ ተጠየቀ።

የቴፒ ከተማ የ2016/17 የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች የግብር መክፈያ መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት በቴፒ ከተማ ተካሂዷል።

በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የቴፒ ከተማ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ዋሲሁን አውሎ እንደተናገሩት ቴፒ ከተማ የራሷን ወጪ በራሷ ገቢ የምትሸፍን ከተማ በመሆኗና በየደረጃው ህዝቡ የሚያነሳውን የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በሁሉም የገቢ አርዕስቶች ገቢ መሰብሰብ ይገባል ብለዋል።

አክለውም የገቢ አሰባሰቡን ውጤታማ ለማድረግ የባለድርሻ አካላት ቁርጠኝነት፣ ርብርብና ቅንጅት የሚጠይቅ በመሆኑ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል ።

በተያያዘም አቅምን አሟጦና በቁርጠኝነት መሥራት ከተቻለ ካለፉት ዓመታት የተሻለ ገቢ መሰብሰብ እንደሚቻል ጠቁመዋል።

በሌላ በኩል የተሰበሰበውን ገቢ በቁጠባና በአግባቡ ለታለመለት ዓላማ መዋል እንዳለበትም አክለዋል።

የቴፒ ከተማ ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ መሠረት ተስፋዬ በበኩላቸው የአንድ ሀገር ዕድገት የሚለካው ከዜጎች በሚሰበሰበው ገቢ በሚሰራው ልማት በመሆኑ ሁሉም ዜጋ ግብርን በአግባቡና በታማኝነት መክፈል እንዳለበት አሳስበዋል።

የቴፒ ከተማ ገቢዎች ባለስልጣን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ተወካይ አቶ ሙሉዓለም ጣሰው እንደገለፁት በየዓመቱ በሚሰራው የገቢ አሰባሰብ ሥራ ድጋፍ የሚያደርጉ አካላትን አመስግነው ዘንድሮም የተለመደውን እገዛ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

አክለውም የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች ከሐምሌ 1 እስከ ሐምሌ 30/2016 ዓ.ም ግብር የሚሰበሰብ መሆኑን ገልፀው አሁን ላይ የግብር ከፋዩን እንግልት፣ መጨናነቅና የጊዜ ብክነት ለማስቀረት ግብር ከፋዩ ባሉበት ቦታ ላይ ሆነው ግብራቸውን በቴሌ ብር እንዲከፍሉ መመቻቸቱን ተናግረዋል።

በተያያዘም በግብር አከፋፈል ሂደቱ ላይ የግብር ከፋዩ ስምና የሚጠቀምበት የስልክ ቁጥር የራሱ መሆን እንዳለበት አሳስበው ምናልባት የንግድ ፈቃዱ ስምና የስልክ ቁጥር የማይገናኝ ከሆነ የቴፒ ከተማ ገቢዎች ባለስልጣን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በአካል በመገኘትና በማስተካከል ግብራቸውን በወቅቱ እንዲከፍሉ አሳሰበዋል።

Photos from Teppi Town Gov't Communication Affairs Office's post 12/07/2024

ሐምሌ 05 ቀን 2016

አካባቢን ማጽዳትና የበጎ አድራጎት ሥራ በሁሉም ዘንድ እንደ ባህል ሊዳብር ይገባል ተባለ።

የወባ ወረርሽኝን ለመከላከል የሚደረገዉን ጥረት ለመደገፍ በበጎ ፈቃደኝነት የጽዳት ዘመቻ በቴፒ ከተማ አያከናወኑ መሆናቸዉን ከሚዛን አማን ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የመጡ ተማሪዎችና መምህራን ገለጹ።

የጽዳት ዘመቻዉን ያስጀመሩት የቴፒ ከተማ የመንግስት ተጠሪ አቶ ዋሲሁን አውሎ አሁን ላይ እንደ ሀገር እየተሰራ ያለውን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መነሻ በማድረግ በቴፒ ከተማ በርካታ የበጎ ፈቃድ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልፀዋል።

አክለውም ከቤንች ሸኮ ዞን የሚዛን አማን ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጤና ሳይንስ ተማሪዎች በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ ተገኝተው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አንድ አካል የሆነውን የጽዳት ዘመቻ በማድረጋቸው አመስግነው ይህ ዓይነቱ የበጎ ሥራ የሁለቱን ዞኖች የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱን የበለጠ የሚያጠናክር በመሆኑ ሌሎችም የእነርሱን ፈለግ ተከትለው በጎ ማድረግን ባህል እንዲያደርጉ ጥሪ አስተላልፈዋል።

በጽዳት ዘመቻዉ ከተሳተፉ የሚዛን አማን ጤና ሳይንስ ኮለጅ ተማሪዎች መካከል የፋርማሲ ተማሪ ተግባሩ ፈቀደና የነርሲግ ተማሪ እያሱ ሙሴ በቴፒ ሆስፒታል ለተግባር የህክምና ልምምድ ከመጡበት ጊዜ ጀምሮ በበጎ ፈቃደኝነት በየሳምንቱ ዓርብ ቀን የጽዳት ዘመቻን በከተማዉና በሆስፒታሉ ቅጥር ግቢ እያከናወኑ እንዳሉ ተናግረዋል።

የሚዛን አማን ጤና ሳይንስ ኮሌጅ መምህር ጋሻዉ ተመስገን በበኩላቸዉ በቴፒ ሆስፒታል ባለፈዉ አንድ ወር ጊዜ በተግባር የህክምና ልምምድ ላይ ተማሪዎቹ በቆዩበት ወቅት በሆስፒታሉም ሆነ በከተማዉ ለወባ መራቢያ ምቹ የሆኑ ቦታዎችን የማዳፈንና የማፋሰስን ሥራ በየሳምንቱ እያከናወኑ እንዳሉ ተናግረዋል።

የጽዳቱ ዓላማም በህብረተሰቡ ላይ ጫና እያሳደረ ያለዉን ወባ ለመከላከልና ህብረተሰቡ በዘላቂነት አካባቢዉን እንዲያጸዳ አርአያነት ያለዉ ተግባር ለማሳየት ነዉ ብለዋል።

በቀጣይም በሚኖራቸዉ የተግባር ልምምድ ቆይታ ውስጥ የጽዳት ዘመቻዉን አጠናክረዉ እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።

Photos from Teppi Town Gov't Communication Affairs Office's post 11/07/2024

ሐምሌ 4/2016 ዓ.ም

በሸካ ዞን የከተሞችን ዕድገት ለማፋጠን ህብረተሰቡን አሳትፎ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባ ተገለጸ።

የዞኑ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ የ2016 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም በቴፒ ከተማ በገመገመበት ወቅት ነው ይህ የተገለጸው።

የሸካ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸሎ አዴሎ በመድረኩ ባደረጉት ንግግር በዞኑ ውስጥ የሚገኙ ማዘጋጃ ቤቶች እንዲሁም በየደረጃው ያሉ የባለድርሻ አካላት በከተሞች ዕድገት ዙሪያ የሚሰሩ ስራዎችን በቁርጠኝነት ሊተገብሩ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

በዞኑ በሁሉም አካባቢዎች የከተሞችን ዕድገት ለማፋጠን ህብረተሰቡን አሳትፎ በቁርጠኝነት የመስራት ሂደት የተሻለ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።

በመምሪያው በ2016 በጀት ዓመት በመሬት ልማት ማኔጅመንት፣ህብረተሰብ ተሳትፎ፣በአረንጓዴ ልማት፣በመሰረተ ልማት አፈጻጸም በመሳሰሉ ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት በዝርዝር ቀርቧል፡፡

በሌላ በኩል የውይይቱ ተሳታፊዎች በቀረቡ ሪፖርቶች ዙሪያ አስተያየት የሰጡ ሲሆን የታዩ ጠንካራ አፈጻጸሞች እንዲሁም በቀጣይ ማሻሻል ያለባቸውን መለየት የቻሉ መሆኑን ተናግረው በቀጣይ የጋራ ርብርብ በማድረግ ለመስራት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል፡፡

በመጨረሻም የ2017 በጀት ዓመት ዋና ዋና ጠቋሚ ዕቅድ ቀርቦ ውይይት ከተደረገበት በኋላ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሶ መድረኩ መጠናቀቁን የዘገበው የሸካ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ነው፡፡

Photos from Teppi Town Gov't Communication Affairs Office's post 11/07/2024

ሐምሌ 3/2016 ዓ/ም

በቴፒ ከተማ የፈርጅ ለውጥ ጥናት ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በቴፒ ከተማ ተሰጠ።

በሸካ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ አዘጋጅነት በተሰጠው ስልጠና የቴፒ ከተማን ፈርጅ ለውጥ ጥናት በማድረግ የከተማውን ኢኮኖሚያዊ ፤ ማህበራዊ ፤ ፖለቲካዊ ዕድገት ለማምጣትና የህብረተሰቡን ተሳትፎ ለማሳደግ ታሳቢ ያደረገ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ እንደሆነ ተጠቁሟል ።

የተዘጋጀውን የስልጠና ሰነድ ያቀረቡት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የከተሞች አደረጃጅት ዳይሬክተር አቶ ዘሪሁን ፀጋዬ እንደገለፁት የመብራት ፤ የንፁህ የመጠጥ ውሃ ፣ አዳዲስ የመንገድ ዝርጋታና አጠቃላይ አገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን ሁለንተናዊ ርብርብ እንደሚያስፈል ተናግርዋል ።

አክለውም የከተማ ኢኮኖሚዊ እንቅስቃሴ፣ የባህልና ቱሪዝም ማዕከል ፤የንግድና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ፤ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማፋጠን የህብረተሰቡን ቁርጠኝነት ያስፈልጋልም ብለዋል ።

በመድረኩ የተገኙት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የከተሞች ፕላን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ፀጋዬ ሀይሌ እንዳሉት የከተማውን የእድገት ደረጃ የሚመጥን የፈርጅ ለውጥ በማድረግ ብቁ ፣ተወዳዳሪና ለነዋሪዎች ምቹ ከተማ በመፍጠር የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ነው ብለዋል ።

አንድንድ የመድረኩ ተሳታፊዎች እንድሉት የትኛውም የከተማ ልማት ዙሪያ የሚደረገው ውይይት የከተማን ገጽታ በሚቀይር መልኩና ከህዝቡ ተጠቃሚነት አንጻር መሆኑ ታሳቢ በማድረግና ህዝቡ የፈረጅ ለውጥ ጥናት ለማምጣት ኢንቨስትመንትን ማሳደግ ፤ማበረታታት ፤የማዘጋጃ ቤቶችን መልሶ የማደራጀት ስራዎችን ማጠናከር ይገባል ብለዋል።

በመጨረሻም የቴፒ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ኃላፋ አቶ ሸሎ አደሎ እና የቴፒ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ደመላሽ ገዳ በመድረኩ ማጠቃለያ እንገለፁት በከተማው ፈርጅ ለውጥ ጥናት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫው በቀጠይ ለሁሉም ባለ ድርሻ አካለት በትኩረት እንደሚሰጥ ገልፀዋል ።

በተያያዘም በከተማው ለኢንቨስትመንትና ለተለያዩ አገልግሎቶች የተሰጡ ቦታዎች ግንባታቸው ተጠናቀው አገልግሎት እንዲሰጡና ከተማውን በሚመጥን ደረጃ የመልሶ ማልማት ሥራ ከባለድርሻ አካላት ጋር በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

07/07/2024

ሰኔ 30/2016 ዓ.ም

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቁን የሸካ ዞን ትምህርት መምርያ አስታወቀ።

የሸካ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን አለሙ አጠቃላይ ስለፈተናው አሰጣጥ መግለጫ ሰጥተዋል።

የ2016 የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመስጠትና የተማሪዎች ውጤት እንዲሻሻል ተማሪን በዕውቀት፣ በክህሎትና በቴክኖሎጂ እንዲበቃ የተለያዩ ተግባራት ሲሰራ መቆየቱንና የማጠናከሪያ ትምህርቶች ከሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመቀናጀት መሰጠቱን ጠቅሰው የቅድመ ፈተና ዝግጅት የተሻለ መሆኑን ጠቁመዋል።

በትምህርት ዘመኑ በማህበራዊ ሳይንስ 1121 ተማሪዎች በተፈጥሮ ሳይንስ 524 ተማሪዎች አጠቃላይ 1663 ተማሪዎች በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ካምፓስ ፈተናውን እንደሚፈተኑ ገልጸዋል።

በዚህ መሰረትም ሰኔ 30 እስከ ሀምሌ 1/2016 ዓ.ም ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡበት ሆኖ ለማህበራዊ ሳይንስ ከሐምሌ 6 እስከ 7 2016ዓ.ም ፣ ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ደግሞ ከሐምሌ 9 እስከ 11 ቀን 2016 ዓ.ም
በዩኒቨርሲቲ ውስጥ ፈተናው የሚሰጥ መሆኑን ጠቁመዋል።

ተፈታኞች ወደ መፈተኛ ቦታቸው ሲመጡ ለፈተናው የተፈቀዱና የተከለከሉ ነገሮችን በማጤን ለራሳቸውና ለፈተናው ደህንነት ትኩረት በመስጠት እንዳለባቸው ጠቁመዋል።

ስለሆነም ተፈታኞች እና የሚመለከታቸው ሁሉ ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ አገልግሎቱ አቶ መስፊን አሳስበዋል።

የተሻሻለ ውጤት የሁሉም የትምህርት ባለድርሻ አካላት ድምር ውጤት በመሆኑ የጋራ ርብርብ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል ።

የዘገበው የሸካ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ነው።

Photos from Teppi Town Gov't Communication Affairs Office's post 07/07/2024

ሰኔ 30/2016 ዓ.ም

"ሠላም ለሁሉም ሁሉም ለሠላም" በሚል መሪ ቃል ሀገር አቀፍ የሠላም ሩጫ በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ ተካሄደ ።

በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የሸካ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ዓማየሁ ዓለሙ የጋራ ቤታችን የሆነችውን ሀገራችንን ለማፅናት በጋራ ለሰላም መስራት አለብን ብለዋል።
ሰላምን የበለጠ ለማጽናት በሩጫ መሃል አብሮነታችንንና ለማጠናከር ታስቦ መሠናዳቱን ተናግረዋል።

የሸካ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የዞኑ ስፖርት ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢ አቶ በላቸዉ ጋራ ይህ ሩጫ የሚደረገዉ ትልቅ ትርጉምና ቦታ ተሰጥቶት ነዉ ብለዉ አሁን እንደ ሀገር አሁን ካለንበት ሁኔታ እንዲንወጣ ሰላምና አብሮነትን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አንስተዋል።

በዞኑ ከዓመታት በፊት የነበረዉ የጸጥታ ችግር ተፈትቶ ሰላም እንዲሰፍን ያደረጉ በየደረጃዉ ያሉ ባለ ድርሻ አካላትና መላዉ የዞኑ ነዋሪ አሁንም የሰላሙን ዘላቂነት ለማረጋገጥ የሰላሙ ባለቤት እኔ ነኝ በሚል መርህ ተግቶ እንዲሰሩ አሳስበዋል።

በዉድድሩ በሴቶች 1ኛ ሮዛ ማሩ፣ 2ኛ መዲና ሙሳ ፣ 3ኛ ዲቦራ አስራት እንዲሁም በወንዶች 1ኛ ወጣት መሃሪ ሻምበል፣
2ኛ ሀፊዝ አባወሊ ፣ 3ኛ ሰብረዲን ይማም በመዉጣት የሜዳሊና የሰርትፍኬት ሽልማት ተበርክቶላቸዉ ።

በማጠቃለያው የሸካ ዞን ሰላም ጸጥታና ምሊሻ መምሪያ ሀላፊ አቶ ዘርይሁን እምሩ ሰላምን ለማጽናት ከዚህ መርሃ ግብር ባሻገር ሁሉም በትኩረት እንዲሠራ አሳስበዉ ለዉድድሩ ስኬት ለሠሩ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

Photos from Teppi Town Gov't Communication Affairs Office's post 06/07/2024

ሰኔ 29/2016 ዓ.ም

ችግኞችን መትከል ብቻ ሳይሆን በተገቢዉ በመከባከብ ለቀጣይ ትዉልድ ለማሸጋገር ሁሉም በትኩረት ሊሰራ ይገባል ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ መቱ አኩ አሳሰቡ።

በክልሉ ሸካ ዞን ቴፒ ከተማ ክልል አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ የክረምት ችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ ኘሮግራም ተካሂዷል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የሸካ ዞን ግብርና አካባቢ ጥበቃና ህብረት ሥራ መምሪያ ሀላፊ አቶ አእምሮ ደሳለኝ እንደ ሀገር አየተከናወነ ባለዉ የአረንጓዴ አሻራ ተግባር ዞኑም በትኩረት እየሰራ መቆየቱን አንስተዉ ባለፈው ዓመት 9 ሚሊዮንበላይ ችግኞች መተከላቸዉን አስታዉሰዋል።

በዘንድሮ የክረምት አሬንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በዞን ደረጃ 10 ነጥብ 4 ሚልዮን በላይ ችግኞችን ለመትከል የታቀደ ሲሆን እስካሁን ባለዉ 6 ሚሊዮን ያህሉ ተተክሏል ብለዋል።

የቴፒ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ደመላሽ ገዳበበኩላቸዉ እንደ ሀገር የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም ከተጀመረበት አንስቶ እስካሁን ለውጦች መምጣቱን ገልፀው ይሄው ፕሮግራም ዘንድሮም የሚቀጥል ሲሆን በዚህ ዓመት የተለያዩ ፋይዳ ያላቸዉ የዛፍ ችግኞችና አትክልቶች ይተከላሉ ብለዋል።

የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ላይ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ መቱ አኩ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ የምንተክለው ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለመጪዉ ትውልድ በማሰብ ጭምር ነዉ ብለዋል።

አክለውም የዛሬው የክረምት ችግኝ ተከላ በክልሉ በ4ቱም ክላስተር ከተሞች በተመሳሳይ እየተከናወነ መሆኑን ገልፀው መትከል ብቻም ሳይሆን የተከልነውን ተንከባክበን ማሳደግ ይገባናል ብለዋል።

በቴፒ ከተማ ሰላም ቀበሌ ዉስጥ ባለፈዉ ዓመታት የተተከሉ ችግኞች በጥሩ የጽድቀት ደረጃ ላይ እንዲገኙ ለሰሩ አካላት በሙሉ ምስጋና አቅርበዋል።

በቀጣይም አሁን የተተከሉ ችግኞች ጸድቀዉ ለተፈለገዉ ዓላማ እንዲዉሉ ሁሉም በሀላፊነት አንዲንከባከበዉ አሳስበዋል።

በተከላ መርሃ ግብሩ ላይ የክልል፣የሸካ ዞን፣ የቴፒ ከተማና የኪ ወረዳ ከፍተኛ አመራሮች፣ የጸጥታ አካላትና የሰላም ቀበሌ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።

Photos from Teppi Town Gov't Communication Affairs Office's post 05/07/2024

ሰኔ 28/2016 ዓ.ም

"በጎነት ለአብሮነት እና ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የ2016 ዓ.ም የቴፒ ከተማ የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሂዷል።

የቴፒ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ደመላሽ ገዳ
እንደገለፁት የባለፈው ዓመት ጠንካራ አፈፃፀሞችን አጠናክሮ የማስቀጠልና ክፍተት የታየባቸው ዘርፎችን በመለየት የተሻለ የበጎ ሥራ ለመስራት ቅድመ ዝግጅት መደረጉን አንስተዋል።

አክለውም በዘንድሮው የበጎ ፈቃድ ተግባር የተለያዩ ባለሀብቶችን፣ ከተለያዩ ተቋማት የመጡ ወጣቶችንና ነዋሪዎችን በማሳተፍ የበጎ ሥራ ይሰራልም ብለዋል።

በመቀጠልም የቴፒ ከተማ ሴቶች ወጣቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ጽህፈት ቤት የወጣቶች ማካተት ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ አቶ ሰይድ መሐመድ የ2015 ዓ.ም የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አፈፃፃምንና የ2016 ዕቅድ አቅርበዋል።

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራዎች አቅመ ደካሞችን ከመደገፍ ባለፈ በመንግስትና በህዝብ ከሚወጡ ወጪዎች ማዳን ያስችላል ብለዋል።

አክለውም በ2015 ዓ.ም በቴፒ ከተማ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን አፈፃፀሞችን ሲያቀርቡ እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ ከ12 የስምሪት መስኮች 9 መስኮችን ማሳካት ተችሏል ብለዋል።

ለአብነትም በጤናው ዘርፍ፣ በትምህርት ዘርፍ፣ በአረንጓዴ አሻራ፣ በማዕድ ማጋራት፣ የአቅመ ደካሞችና አረጋዊያን ቤት የመሥራትና የመጠገን እና የትምህርት ቂሳቁስ ድጋፍ መደረጉንና ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች መከናወናቸውን ገልፀዋል።

አክለውም በ2016 ዓ.ም የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በ12 የስምሪት መስኮች 10 ሺህ 2 መቶ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችን በማሳተፍ ከ6 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በላይ የሚሆን የበጎ ፈቃድ ተግባር ለማከናወን መታቀዱን ተናግረዋል።

በተያያዘም በሚቀጥሉት የክረምት ወቅት
የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር፣ ድጋፍ የሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎችን መደገፍ፣ የሰላምና ፀጥታ ስራዎች፣ የትምህርትና ስልጠና አገልግሎት፣ የጤና አገልግሎት፣ መሰረተ ልማቶችን ማጠናከር እና ማልማት፣የመንገድ ትራፊክ ደህንነት አገልግሎት፣ የአካባቢ ጥበቃና እንክብካቤ፣ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች፣ ፆታዊ ጥቃትና ትንኮሳን መከላከል፣ የስብዕናግንባታ ስራዎችና የወጣት ማዕከላትን ማጠናከር፣ ህገ-ወጥ የሰዎችን ዝውውርን መከላከል፣ የሙያ አገልግሎቶችን ለመስጠት ታቅዷል ብለዋል።

አንዳንድ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት መልካም ነገር ለማገኘት ለሰዎች መልካም ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል።

አክለውም የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶችን በሁሉም መስኮች በአግባቡ በመለየት ሁሉንም ህብረሰብ በማሳተፍና ተግባራዊ በማድረግ ከልብ በመነጨ መንፈስ አቅመ ደካሞችን ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እንዲሰራ ጠይቀዋል። በተያያዘም በጤናው ዘርፍ በትኩረት መሥራት እንደሚገባ አንስተው በጎ ለማድረግም ዝግጁ መሆናቸውን ጭምር ገልፀዋል።

የቴፒ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ደመላሽ ገዳ፣ የቴፒ ከተማ የመንግስት ተጠሪ አቶ ዋሲሁን አውሎ እና የቴፒ ከተማ ሴቶች ወጣቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ታሪኳ ይርሲ መድረኩን በጋራ በመሩበት ወቅት እንደተናገሩት በጎ ማድረግ በመንፈሳዊም ሆነ በዓለማዊ ህይወታችን ተቀባይነት ያለው፣ በወቅት ያልተገደበ የሁል ጊዜ ተግባራችን በማድረግ እንደ ባህል እንዲለመዱ ጥሪ አቅርበዋል።

አክለውም የበጎ ተግባሮቻችን እንዲሳኩ በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባም አሳስበዋል።

በመጨረሻም በሠላም ቀበሌ የአንድ አቅመ ደካማ ቤት የማስጀመር ሥራና የቤት መሥሪያ ቁሳቁስ ርክክብ ተካሂዷል።

05/07/2024

ሰኔ 28/2016 ዓ.ም

"የሠላም ባለቤት እኔ ነኝ" በሚል መሪ ቃል ሰኔ 30/2016 ዓ.ም በቴፒ ከተማ የሠላም ሩጫ ይካሄዳል።

በሸካ ዞን ሠላም ፀጥታና ሚሊሻ መምሪያ እና በሸካ ዞን ባህል ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ አዘጋጅነት ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓ.ም ከጧቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በቴፒ ከተማ የሚካሄደው ሩጫ መነሻውን የቀድሞ የቴፒ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ፊት ለፊት በማድረግ በአየር ሜዳ ዙሮ ፍፃሜውም የቀድሞ የቴፒ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ፊት ለፊት እንደሚሆንና አጠቃላይ ርዝመቱ ከ3 እስከ 5 ኪሎ ሜትር እንደሚሸፍንና በውድድሩም 1 ሺህ 5 መቶ ሯጮች እንደሚሳተፉ ከውድድሩ አዘጋጆች የተገኘው መረጃ ያስረዳል።

የሠላም ሩጫው ዓላማ ያደረገው በሀገራችን በተለይም በዞናችን እየተገኘ ያለውን አንፃራዊ ሠላም ወደ ዘላቂና አዎንታዊ ሠላም ለማሸጋገር ዜጎች በአገረ መንግስት ግንባታ ሂደት የራሳቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ማስቻል ነው።

በውድድሩም ከ1ኛ እስከ 3ኛ ለሚወጡ ተወዳዳሪዎች የገንዘብ፣ የሜዳሊያና የሰርተፍኬት ሽልማት እንደሚሰጥ ከዝግጅት ኮሚቴው የተገኘው መረጃ ያስረዳል።

በመሆኑም ማንኛውም ሠላም ወዳድ የከተማችን ነዋሪ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ የሚፈልግ ቴፒ ከተማ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽህፈት ቤት በአካል ተገኝቶ መመዝገብ እንደሚችልም ተገልጿል።

Videos (show all)

ቀን 28/01/2015 ዓምከተለያዩ አከባቢዎች ሚዛን ቴፒ ዩንቨርስቲ ቴፒ ጊቢ         የተመደቡ የ1ኛ ዙር የዩንቨርስቲ መግቢያ ፈተና ተፈታኞች በሰላም ቴፒ ጊቢ ገብተዋል።በዩንቨርስቲው የ...

Website