eyoba360
Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from eyoba360, Education, .
15/04/2021
"የኮቪድ-19 ክትባትን ለማግኘት ምንም ዓይነት የኮቪድ 19 ቅድመ ላብራቶሪ ምርመራ ማድረግ አያስፈልግም" - ጤና ሚኒስቴር
የጤና ሚኒስቴር ዛሬ ምሽት ባሰራጨው መልዕክት የኮቪድ-19 ክትባት መርሃ ግብር በታቀደው መሰረት በመላው ኢትዮጵያ መሰጠት መቀጠሉን ገልጿል።
እስካሁን ባለው ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ የጤና ባለሙያዎች ተከትበዋል።
እድሜያቸው ከ 65 ዓመት በላይ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች እና ከ55-64 ዓመት ሆነው የሚታወቅ ተጓዳኝ የጤና ችግር ያለባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ከመጪው ሰኞ ጀምሮ የኮቪድ 19 ክትባትን ማግኘት ይጀምራሉ፡፡
ጤና ሚኒስቴር ክትባቱን ለመውሰድ የኮቪድ- 19 የቅድመ ላብራቶሪ ምርመራ ያስፈልጋል እና ሌሎች ክትባቱን በተመለከተ የሚነገሩት ነገሮች ማህበረሰቡ ትክክል እንዳልሆኑ በመገንዘብ የክትባቱን እንዲወስድ ፥ ከአላስፈላጊ ወጪ አልፎም ከሚፈጠረው ትርምስ እንዲሁም አካላዊ ንክኪ እንዲቆጠብ ብሏል።