Bibugn Woreda Communication Affairs Office

Bibugn Woreda Communication Affairs Office

Chokie mountain is Africa water tower

02/08/2023

"ልዩነት ያለው አካል ሁሉ ነፍጡን አስቀምጦ ወደ ውይይት ይምጣ" ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር)
የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር) በወቅታዊ ጉዳይ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫውም ባለፉት ጊዜያት ጀምሮ በክልሉ የፀጥታ ችግር አጋጥሟል ብለዋል። መንገድ በመዝጋት የሰዎችን እንቅስቃሴ በመግታት ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳት አድርሷል ነው ያሉት። ያለው ግጭት እርስ በእርስ እያገዳደለና ሰብዓዊ ኪሳራ እያደረሰ መሆኑን ገልፀዋል።
እርስ በእርስ መጠፋፋት ዘላቂ ችግር እንጂ ዘላቂ ሰላም አያመጣም ነው ያሉት። ሁሉም ለሰላም መረባረብ አለብንም ብለዋል። የክልሉ የፀጥታ መዋቅርና የሀገር መከላከያ ሠራዊት የሕግ የበላይነትን ለማስከበር እየተንቀሳቀሱ መሆኑንም አስታውቀዋል። የክልሉ ሕዝብ እየተደረገ ያለውን ሕግ የማስከበር ሂደት የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ የሚደረግ መሆኑን ማወቅ ይገባል ነው ያሉት።
የሀገር መከላከያ ሠራዊት ከሁሉም ኢትዮጵያውያን የተውጣጣ የኢትዮጵያውያን ነው ያሉት ርእሰ መስተዳድሩ መከላከያን ያለ ስሙ ስም መስጠትና መተንኮስ አግባብ አይለምም ብለዋል። የፀጥታ ችግርን በሰላማዊ መንገድ መፍታት እንደሚገባም ገልጸዋል።
የክልሉ መንግሥት ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት እየሠራ መሆኑንም አስታውቀዋል። ሁሉም ጥያቄ አለኝ የሚል ችግሮቹን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት መረባረብ አለበት ነው ያሉት።
ልዩነት ያለው አካል ሁሉ ነፍጡን አስቀምጦ ወደ ውይይት እንዲመጣ ጥሪ አቅርበዋል።
ለሰላም ዘብ በመቆም ችግሮቻችን መፍታት ይገባናል ነው ያሉት። ክልሉን ዋጋ የሚያስከፍል ችግር ከመከሰቱ አስቀድሞ ሁሉም ለሰላም መረባረብ እንደሚገባውም አሳስበዋል።
አሁን ያለው አካሄድ ክልሉን አደጋ ውስጥ የሚከት በመሆኑ የክልሉ ሕዝብ ለሰላም እንዲሠራም ጠይቀዋል። እርስ በእርስ በመገዳደል ያመጣነው ለውጥ የለምም ብለዋል።
የክልሉ ሕዝብ ለሰላም በየአካባቢው ያለውን ትንኮሳ በማስቆም ሁሉም ወደ ሰላም እንዲመጣም ጥሪ አቅርበዋል።
አሚኮ

02/08/2023

የኮሌራ በሽታ ምንነት፣ መከላከያ መንገዶች እና ጥንቃቄው
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የኮሌራ በሽታ መተላለፊያ መንገዶች፣ የሚያሳያቸዉ ምልክቶች እና የበሽታው መከላከያ መንገዶች ኮሌራ ከሰዉነት ዉስጥ ጠቃሚ ንጥረ ነገሮችንና ፈሳሽን በብዛት እና በአጣዳፊ ሁኔታ በተደጋጋሚ ተቅማጥና ትውከት በማስከተል ሰዉነትን አድርቆ #የሚገድል በሽታ ነዉ፡፡

፡-
የሰውነት ድርቀት፣
የአፍ መድረቅ፣
የአይን መሰርጎድ፣
የእንባ መድረቅ፣
የሽንት መቀነስ፣
የቆዳ መሸብሸብና አጠቃላይ የሆነ የድካም ስሜት ያስከትላል፡፡
:- በአካባቢና የግል ንጽህና መጓደል አማካኝነት ነው። ማለትም:-
• በሽታው በተበከለ ምግብና ውሃ አማካኝነት ከሰው ወደ ሰው በከፍተኛ ፍጥነት ይተላለፋል፡፡
• ንጹህ ባልሆኑ እጆች ምግብን በማዘጋጀት፣ በማቅረብና በመመገብ፣
• በበሽታ አምጪ ተህዋስያን የተበከለ የምንጭ፣ የጉድጓድ፣ የወንዝ፣ የዝናብ፣ የቧንቧና ወዘተ ውሃን መጠቀም፣
• በበሽታ አምጪ ተህዋስያን የተበከለ የውሃ ማጠራቀሚያና መገልገያ እቃዎችን በመጠቀም፣
• ክዳን የሌላቸውና ለዝንቦች የተጋለጡ የምግብ ማስቀመጫና መመገቢያ እቃዎችን በመጠቀም፣
• በበሽታ አምጪ ተህዋስያን የተበከሉ ምግቦችን፣ አትክልቶችንና ፍራፍሬዎችን በመመገብ፤ወዘተ ይተላለፋል፡

:-
• ሁልጊዜ ውሃን አፍልቶ እና አቀዝቅዞ መጠጣት ወይም በውሃ ማከሚያ ኬሚካል የታከመ ውሃ መጠቀም፤
• ምግብን በሚገባ አብስሎ በትኩስነቱ መመገብ፤
• የምግብ እቃዎችን በንጹህ ወይም በኬሚካል በታከመ ውሃ ማጠብ እና መጠቀም፣
• መጸዳጃ ቤትን አዘጋጅቶ በአግባቡ መጠቀም፤
• እጅን በሚከተሉት ወሳኝ ጊዜያት በንጹህ ውሃና በሳሙና
ሳሙና ከሌለ በአመድ በሚገባ መታጠብ፣
• ከመጸዳጃ ቤት መልስ፣
• ምግብ ከማዘጋጀት በፊት
• ምግብ ከማቅረብ በፊት፣
• ምግብ ከመመገብ በፊት፣
• ሕጻናትን ካጸዳዱ በኃላ፣
• ሕጻናትን ጡት ከማጥባት በፊት ፣
• በበሽታው ለተያዙ ሰዎች እንክብካቤ ካደረጉ በኃላ፣
• በበሽታው የሞቱ ሰዎችን አስክሬን በድንገት ከነኩ፣
• ማንኛውንም ከቤት የሚወጣ ደረቅ ወይም ፈሳሽ ቆሻሻን ውሃንና አካባቢን እንዳይበክል በአግባቡ በተመደበለት ስፍራ ማስወገድ፣
• በኮሌራ በሽታ የታመመን ሰው ልብስ በፈላ ውሃ መቀቀል ወይም በበረኪናና በልብስ ማጽጃ ሳሙና ዘፍዝፎ ማጠብ፣
• በበሽታው የተያዘን ሰው በፍጥነት ወደ ሕክምና ተቋም በመዉሰ የህክምና እርዳታ እንዲያገኝ ማድረግ ናቸው።
• የግልና የአካባቢን ንጽህና በመጠበቅ ዝንቦች እንዳይራቡ ያድርጉ፣
• ፈሳሽና ደረቅ ቆሻሻን በአግባቡ በተመደበለት ስፍራ ያስወግዱ
• ሽንት ቤት በመገንባት በአግባቡ ይጠቀሙ እንዲሁም በንጽህና ይያዙ፣
• በተቅማጥና ተውከት የተነካካ እቃን፣ ወለልና መሬትን ከማጽዳትዎ በፊት በረኪና በማፍሰስ ብክለትን ይከላከሉ።
የበሽታ ምልክት ሲታይ መከናወን ያለባቸው ተግባራት:-
- በሽታው የሰውነትን ፈሣሽና ጠቃሚ ንጥረ ነገሮችን በብዛት ከሰውነት የሚያስወጣ ስለሆነ የሚከተሉትን እርምጃዎች በፍጥነት በመውሰድ እንዲተኩ ያድርጉ።
-በመጀመሪያ ቤት ውስጥ የሚገኘውን ማንኛውም ንጽህናው የተጠበቀ ፈሣሽ የሚችሉትን ያህል ይጠጡ።
-ህይወት አድን ንጥረ ነገር ወይም ኦ.አር.ኤስ በቤት ውስጥ ካለ አንድ ፓኬት ተፈልቶ በቀዘቀዘ አንድ ሊትር ውሃ በመበጥበጥ ይጠጡ፤ የተበጠበጠ ኦ.አር.ኤስን መጠቀም የሚቻለው በተበጠበጠ በ24 ሰዓት ውስጥ ነው።
- ኦ.አር.ኤስ በቤት ውስጥ ከሌለ 8 የሻይ ማንኪያ ስኳር እና ግማሽ የሻይ ማንኪያ ጨው በአንድ ሊትር ንጹህ ውሃ በመበጥበጥ ባስቀመጥዎ ቁጥር ይጠጡ።

Photos from Bibugn Woreda Communication Affairs Office's post 01/08/2023

የክረምት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራትን በተጨባጭ የማህበረሰቡን ችግር በሚፈታ መልኩ በትኩረት እያከናወነ መሆኑን የምስራቅ ጎጃም ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ገለጸ።
*************
ሐምሌ 25/2015 ዓ.ም (ቢቡኝ ኮሙዩኒኬሽን)
የአማራ ክልል የክረምት ወጣቶች በጎ ፈቃድ የቴክኒክ ኮሚቴ ቡድን በምስራቅ ጎጃም ዞን በክረምት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎ በዝግጅት ምዕራፍና በተግባር ምዕራፍ አጀማመር በተከናወኑ ተግባራት ዙሪያ ከዞን ቴክኒክ ኮሚቴ ጋር ውይይት አካሂዷል።

የምስራቅ ጎጃም ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ሀላፊ አቶ ቢሻው ሞላ እንደገለጹት በዞኑ በ2015 ዓ.ም በክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ ወጣቶች በሚያከናውኑት ተግባር የማህበረሰቡን ችግር ሊቀርፋ የሚችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም እስካሁን ባለው 184 ቤቶች በአዲስ የመገንባት፣290 ቤቶችን የመጠገን ፣ከ98 ሚሊየን በላይ ችግኞችን የመትከል፣650 ዩኒት ደም የመለገስ እንዲሁም 98 ትምህርት ቤቶችን በመጠገን 14 ሽህ 206 ተማሪዎችን የማጠናከሪያ ትምህርት የመስጠትና 236ሽህ ብር የማሰባሰብ ተግባር ተከናውኗል፤ለዚህም ማስፈጸሚያ የሚሆን ከ3 ሚሊዮን 401 ሽህ በላይ የሚሆን በጀት የተመደበ መሆኑን መምሪያ ሀላፊው ጨምረው አስረድተዋል።

የአማራ ክልል የክረምት በጎ ፈቃድ የቴክኒክ ኮሚቴ አባላት በበኩላቸው ዞኑን ጨምረው ተዘዋውረው ምልከታ ባደረጉባቸውን ወረዳዎችና ቀበሌዎች በተከናወኑ ተግባራት ዙሪያ ተግባራቱ በበቂ እውቀትና ግንዛቤ እየተመራ መሆኑን አመላክተዋል። በዚህም እቅድ ከማቀድ ጀምሮ እቅዱን የጋራ ለማድረግ የተደረገውን ጥረት፣የተሰሩ ተግባራትንና የተሰሩ ስራዎችን በህዝብ ግንኙነት ስራ በማጀብ ለህብረተሰቡ እንዲደርስ በማድረግ፣በጀት በመመደብ፣የኮር አመራሩ ድጋፍ፣ግብረመልስ በመስጠትና በመከታተል የተከናወኑ ተግባራት በጥንካሬ አንስተዋል።

ምልከታ ካደረጉባቸው ወረዳና ቀበሌዎች አልፍ አልፎ የታቀዱ እቅዶች ጥራት መጓደል፣ሪፖርት መቆራረጥ መስተዋሉን ያመላከቱትት የክልሉ የቴክኒክ ኮሚቴ አባላት፣ችግር ፈች ድጋፍ መስጠት፣የማጠናከሪያ ትምህርት መስጠት ላይና ደም የመለገስ ተግባርን ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የክልሉ የክረምት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት የቴክኒክ ኮሚቴ አባላት ለዞኑ የሰጡትን ድጋፍ አመስግነው በክልሉ የቴክኒክ ኮሚቴ አባላት የተሰጡ አስተያየቶች ምስራቅ ጎጃምን ወደፊት እንዲራመድ የሚያስችል በመሆኑ በቴክኒክ ምክንያት የጎዳደሉ ተግባራትን ወስደን ፈጥነን እናስተካልላለን ብለዋል የምስራቅ ጎጃም ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ሀላፊ አቶ ቢሻው ሞላ።

ከምስራቅ ጎጃም ዞን ኮሙዩኒኬሽን

Photos from Bibugn Woreda Communication Affairs Office's post 01/08/2023

በወቅታዊ የሰላምና የጸጥታ ሁኔታዎች ላይ የጋራ አረዳድ በመፍጠር የተጀመረው የሠላምና የልማት ሂደቱ እንዲጠናከር መስራት ይገባል - ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር)

ከአማራ ክልል የተወጣጡ የሃይማኖት አባቶች እና የአገር ሽማግሌዎች ጋር በወቅታዊ ክልላዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር እየተደረገ ነው፡፡

ከአማራ ክልል ከሁሉም ዞኖች የተወጣጡ የሃይማኖት አባቶች እና የአገር ሽማግሌዎች በወቅታዊ ሀገራዊና ክልላዊ ፖለቲካዊ ሁኔታዎች እንዲሁም በሠላምና ፀጥታ አዝማሚያዎች ላይ በባህር ዳር ከተማ እየመከሩ ነው።

ክልላዊ ወቅታዊ ፖለቲካዊ አዝማሚያዎችን እና የሠላምና የፀጥታ ሁኔታዎችን አመላካች መነሻ ሀሳብ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር) ቀርቧል።

የውይይት መድረኩ በወቅታዊ የሰላምና የጸጥታ ሁኔታዎችና አዝማሚያዎች ላይ የጋራ አረዳድ በመፍጠር የተጀመረው የሠላምና የልማት ሂደቱ እንዲጠናከር ፋይዳዉ የጎላ መሆኑ መሆኑ ተገልጿል።

በሰላም እና በውይይት እንጂ በጦር መሳሪያ የተፈታ ችግር አለመኖሩ የተገለጸ ሲሆን የአማራ ክልል ህዝብ ጦርነት ሳይሆን ልማት የሚሻ ህዝብ በመሆኑ ልማቱን ይበልጥ በማተኮር የህዝቡት ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባልም ተብሏል።

መረጃው : የአማራ ኮሙኒኬሽን ነው።

Photos from Bibugn Woreda Communication Affairs Office's post 01/08/2023

በትራፊክ አደጋ ምክንያት የተዘጋዉ መንገድ ተከፍቷል።

እስካሁን በአደጋዉ የ2 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት የደረሰባቸዉ ተጎጅዎች ወደደብረ ማርቆስ ሪፈራል ሆስፒታል ተልከዋል።

በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ቀበሌ 12 ልዩ ቦታው ጨሞጋ ድልድይ ላይ ከየጁቤ ህዝብ አሳፍሮ ሲመጣ የነበረ ኮድ( 3 ) 10464 የሆነ የህዝብ ኤፍ ኤስ አር ተሽከርካሪ ከጭነት አይሱዙ ጋር በመጋጨቱ ምክንያት የጭነት አይሱዙዉ ተሽከርካሪ ጨሞጋ ወንዝ ውስጥ በግምት 10 ሜትር በመግባቱ መዘጋቱ ይታወሳል።

ነገር ግን ከተማ አስተዳደሩ ባደረገዉ ጥረት መንገዱ ለትራንስፖርት ክፍት ሆኗል።

01/08/2023

የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና መሰጠት ጀመረ
************************

የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና በዛሬው ዕለት በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መሰጠት ጀምሯል።

በዩኒቨርስቲዎች የሚሰጠው ፈተና እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም እንደሚቆይ የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

ሚኒስቴሩ ለተማሪዎቹ መልካም የፈተና ጊዜ ተመኝቷል።

የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ 21 ቀን 2015 መሰጠቱ ይታወቃል።

በዘንድሮው 12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና በአጠቃላይ 868 ሺህ 74 ተማሪዎች ፈተናውን ይወስዳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ከትምህርት ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

31/07/2023

በምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ የ2015/16 የመኸር ምርት ዘመን የስንዴ ሰብል ክልላዊ የዘር መርኃ ግብር እየተካሄደ ነው።
ሐምሌ 24/2015 ዓ.ም (ቢቡኝ ኮሙኒኬሽን) በዞኑ በምርት ዘመኑ በሠብል ከሚለማው 607 ሺህ ሄክታር ማሳ 68 በመቶ በኩታ ገጠም አሠራር የሚለማ ሲኾን 212 ሄክታር በስንዴ ሰብል ይሸፈናል ተብሏል።
በዛሬው ክልላዊ የስንዴ ዘር መርኃ ግብር በዞኑ ከ5 ሺህ 2 መቶ በላይ ሄክታር ማሳ በስንዴ ሰብል እንደሚሸፍን ከዞኑ ግብርና መመሪያ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በአማራ ክልል በተያዘው የመኸር ወቅት በሠብል ለመሸፈን ከታቀደው 5 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ውስጥ እስካሁን 3 ነጥ 5 ሚሊዮን ሄክታሩ በዘር መሸፈኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገልጿል።
በመርሐ ግብሩ የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ፣ የዞንና የወረዳ የሥራ ኀላፊዎች እና የዘርፉ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

31/07/2023

እንደ ሕዝብ ለመጽናት እንደሀገር ለመኖር የዉስጥ ሰላም የወል ሀሳባችን እና የጋራ መግባቢያችን ሊሆን ይገባል።
*********
ሀገር ማለት የሰዉ ልጆች ማኅበራዊ ስሪት ነዉ። ይህ ማኅበራዊ መስተጋብር በዜጎች መካከል በሚፈጠር ተፈጥሯዊም ሆነ ሰዉ ሰራሽ ልዩነት ዉስጥ በሚፈጠር የተቃርኖ ስንጥቅ የሚሰፋዉ እና የሚደፈርሰዉ በሰላም እጦት ነዉ። ይህ ሁኔታ ሰላም የሰዉ ልጆች የእለት ከእለት ኑሮ ዉስጥ በአጽንዖት ከሚፈልጉት አንኳር ጉዳይ አንደኛዉና ብቸኛዉ መፍትሄ መሆኑን ያስረዳናል።
በዘልማድ ሰላም ከዉስጥ የሚመነጭ መሆኑን ባለመረዳት አንዳንዶቻችን አንጋጠን ሰላምን ከኛ ዉጭ እንናፍቃለን። አለፍ ሲልም ሀሳብን ወደ ጠረጴዛ ከማምጣት ይልቅ ወደ አክሳሪ እና ከፋፋይ ግጭት እንወስደዋለን። ያኔ የሰላም አየር ከባለቤቱ ይርቃል፤ አብሮነት ይናጋል፤ አንድነት ይኮሰምናል።
ሰላም በናፍቆት ወይም በመሻት አይመጣም ይልቅ ከራስ የሚጀምር አልፎም ለሌሎች የሚተርፍ ሰዋዊ እሳቤ ነዉ። በግርግር ወይም በብጥብጥ ዉስጥ ሰላምን መፈለግ ደመናን እነደመጨለፍ ይቆጠራል። በልዩነት እና በግጭት የሚገኝ ሰላም፣ የሚጸና አንድነት እና የሚቆም ሀገር የለም። የሚመለስ የክልሉ ህዝብ ፍላጎትና ጥያቄም አይኖርም። ፍላጎቶቻችንና ጥያቄዎቻችን ሁሉ የሚመለሱት በሰላማዊ ትግልና በሰላም ብቻ ነው።
እንደ ሀገርም ሆነ እንደ ክልል አልፎ አልፎ የሚፈጠሩ የከረሩ ልዮነቾችን ምክንያት አድርጎ እየጎላ የመጣዉ መጠራጠር እና አለመተማመን ሰላምን የሩቅ አገር አድርጎብናል። የዚህ ፈተና እያደገ መምጣት ደግሞ ሰላምን ከራስ የሚመነጭ ሳይሆን ከሌሎች የሚቸረን አድርገን በማሰባችን ነዉ።
እንደ ህዝብ አንድ ሆኖ ሰላም፣ ዲሞክራሲ እና ልማት ለማምጣት ከዉስጥ የጀመረ ሰላም ብቸኛዉ ጋሻ ነዉ። ሰላም ሲኖር አንድነት፣ ፍቅር፣ ደስታ፣ እድገትና ልማት ተከታትለዉ ይመጣሉ።
የተለያዬ አሰላለፍ ውስጥ የገባ ማህበረሰብ ወይም ህዝብ የተሰናኘ የህዝብ አቅም ኑሮት ችግሮችን በአሸናፊነት መሻገር እንደማይችል የምንረዳበት ጊዜዉ አሁን ነዉ።
ስለሆነም እንደ ህዝብ ለመጽናት እንደሀገር ለመኖር ሰላም የወል ሀሳባችን እና የጋራ ቋንቋችን ሊሆን እንደሚገባ በመገንዘብ ለሰላም እና ለዉይይት በራችን ክፍት አድርገን ለጋራ ሰላማችን ዘብ በመሆን እንድ ሆነን በአንድ በመቆም በጋራ መስራት ለነገ የማይባል ተግባር መሆኑን ልንረዳ ይገባል።
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ

Photos from Bibugn Woreda Communication Affairs Office's post 30/07/2023

በቢቡኝ ወረዳ "የጋራ መነሻና መዳረሻ ካበጀን ከአሸናፊነት መንገድ ላይ እንገናኛለን!" በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የሰላም ኮንፈረንስ እንደቀጠለ ነው።
===================================
ሐምሌ 23/2015 (ቢቡኝ ኮሙኒኬሽን) በምስራቅ ጎጃም ዞን በቢቡኝ ወረዳ "የጋራ መነሻና መዳረሻ ካበጀን ከአሸናፊነት መንገድ ላይ እንገናኛለን!" በሚል መሪ ቃል በወቅታዊ የሰላምና ደህንነት ስራዎች ላይ የተጀመረው የሰላም ኮንፈረንስ በየቀጠናው ተጠናክሮ ቀጥሏል።

በመድረኩ ላይ የተሳተፉ አካላት የቀበሌ አመራሮች፣ የፀጥታ መዋቅሮች፣ የወረዳ ም/ቤ/ት አባላት፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሃገር ሽማግሌዎች፣ የመንግስት ሰራተኛ የሴክተር ተጠሪዎች፣ የወጣቶችና የሴቶች አደረጃጀት መሪዎችና ሌሎች ተፅዕኖ ፈጣሪ ባለድርሻ አካላት በመድረኩ ተሳትፈዋል።



" !!"

30/07/2023

ከምስራቅ ጎጃም ትምህርት መምሪያ የተሰጠ መረጃ !!

በደረሰዉ የመኪና አደጋ ጉዳት የደረሰበት ተማሪ የለም፤ ሁሉም ተማሪዎች ወደ መፈተኛ ዩኒቨርሲቲ ገብተዋል።

የሁለተኛው ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናቸውን ለመፈተን ወደሚፈተኑበት ዩንቨርስቲ እየተጓጓዙ መሆኑ ይታወቃል ።

ይሁንም እንጅ የእናርጅ እናጋውጋ ተማሪዎች እየተጓጓዙ እያሉ አንድ ሚኒባስ ተሽከርካሪ መንገድ ስቶ በመግባቱ የመገልበጥ አደጋ የተከሰተ ቢሆንም በተማሪዎቻችን ላይ የተፈጠረ ምንም አይነት ጉዳት አለመኖሩን እየገለጽን አሽከርካሪዎች የተጣለባችሁ ኃላፊነት ከባድ ነውና በጥንቃቄ በማሽከርከር ለፈተና ሂደቱ ስኬታማነት ድርሻችሁን እንድትወጡ ከአደራ ጋር አሳስባለሁ !!

አቶ ጌታሁን ፈንቴ
የምስራቅ ጎጃም ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ

መረጃው: የምስ/ጎጃም ዞን ኮሙኒኬሽን ነው።

30/07/2023

በቢቡኝ ወረዳ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ወደ መፈተኛ ዩኒቨርሲቲ ደብረ ማርቆስ ሽኝት ተደረገላቸው።
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ሐምሌ 23/2015 (ቢቡኝ ወረዳ ኮሙኒኬሽን) በምስራቅ ጎጃም ዞን በቢቡኝ ወረዳ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ወደ መፈተኛ ዩኒቨርሲቲ ደብረ ማርቆስ ሽኝት ተደረገላቸው።

እንደ ወረዳችን በትምህርት ዘመኑ ትምህርት ክፍል ወ=320 ሴ=357 ድ=677 ተማሪዎች በመንግት ሲሆኑ በግል ደግሞ ወ=102 ሴ=126 ድ=228 ለፈተና ዝግጅት በማድረግ ወደ ፈተና ጣቢያ ጉዞ አድርገዋል፤ አሸኛኘትም ተደርጎላቸዋል።
መልካም ጉዞ!
መልካም ፈተና ! እንዲሆንላቸው እንመኛለን።

#ቢቡኝ

Photos from Bibugn Woreda Communication Affairs Office's post 29/07/2023

ከ53 ሚሊዮን 338 ሺህ 3 መቶ 85 ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የቢቡኝ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት ገለጸ።
=================================
ሐምሌ 22/2015 ዓ.ም (ቢቡኝ ኮሙዩኒኬሽን) በምስራቅ ጎጃም ዞን የቢቡኝ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አስማረ ከበደ እንደገለጹት በ2015 በጀት ዓመት ከንግድ፣ ከእርሻ እና ከሌሎች አገልግሎት 54 ሚሊዮን 749 ሺህ 8 መቶ 32ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ እስከ ሰኔ 30/2015 ዓ.ም ድረስ 53 ሚሊዮን 338 ሺህ 3 መቶ 85 ነጥብ 87 ብር ወይም የእቅዱን 97 ነጥብ 42 በመቶ መሰብሰብ ተችሏል ብለዋል።

ኃላፊው አያይዘውም ገቢው ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 13 ሚሊዮን 624 ሺህ 6 መቶ 74 ነጥብ 58 ብር ብልጫ እንዳሳየ አመላክተዋል፡፡

አቶ አስማረ አክለውም ይህ ውጤት ሊመዘገብ የቻለበት ምክንያት ዋና ዋናዎቹ :-
👍ሰፋ ያለ የግንዛቤና የክትትል ስራዎችን መስራት በመቻሉ
👍የሴክተር አመራሩ፣ ማኔጅመንት እና አጠቃላይ ሰራተኛው የመፈፀም አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱ (ተቋማዊ የታክስ ሰራዊት መፍጠር በመቻሉ)
👍ከአጋርና ባለድርሻ አካላት ጋር ያለን ቅንጅታዊ አሰራር እየተሻሻለ መምጣቱ ፣
👍በየደረጃው እስከ ቀበሌ ድረስ ያለው አመራር ክትትልና ድጋፍ ጠንካራ መሆኑ
👍 ወረዳው ሊያመነጨው የሚችለውን ሀብት ለይቶ መስራት በመቻሉ
👍የአገልግሎት አሰጣጣችንን ለማሻሻል ጥረት መደረጉ፣
👍የግብር ከፋዩ ግንዛቤና ፍላጎት እየተሻሻለ በመምጣቱ እንደሆነ ገልፀዋል።

👍 በተያዘው 2016 በጀት ዓመት በተጠናቀቀው ዓመት የነበሩ ጥንካሬዎችን በማስቀጠል፣ ጉድለቶችን በማረም ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ ለመሰብሰብ በትኩረት እንደሚሰራ አቶ አስማረ ከበደ ተናግረዋል።

" !!"

Photos from Bibugn Woreda Communication Affairs Office's post 29/07/2023

የምስራቅ ጎጃም ዞን አልማ ማስተባበሪያ በ2015 በጀት ያከናወናቸዉ ወርቃማ ተግባራት

መረጃው: የምስ/ጎጃም ኮሙኒኬሽን ነው።

Photos from Bibugn Woreda Communication Affairs Office's post 29/07/2023

~~ገቢያችን ለልማታችን ለዕድገታችን~~ !
=============================
➡️ግብር በዜጎች መካከል ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል እንዲኖር የማይተካ ሚና አለው፡፡
➡️ የምስራቅ ጎጃም ዞን ገቢዎች መምሪያ ባለፉት አራትና አምስት አመታት ወጭውን በገቢ የመተካት አቅምን ለማሳደግ ሁሉንም የገቢ አርእስቶች አሟጦ በመጠቀም የተጀመረው ጅማሮ እጅግ አበረታች ነበር፡፡

✅ ለዚህ ደግሞ ማሳያው ፍትሃዊ የግብር አሰባሰብ ስርዓት በመዘርጋት ዜጎች በተለይም የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች በአንድ ጀንበር ግብራቸውን እንዲከፍሉ የተደረገው ጥረት ጥሩ ማሳያ ነው፡፡

የዞናችን የግብር አሰባሰብ ሲታይ ከጊዜ ወደ ጊዜ እድገት እያመጣ የዜጎች የመክፈል ፍላጎች መሻሻል እያሳዬ ነው፡፡
📲 ለአብነት ከንግዱ ማህበረሰብና ከልዩ ልዩ አርዕስቶች
✔ በ2011 ዓም ደብረ ማርቆስ ከተማን ጨምሮ ከመደበኛ ገቢና የከተማ አገልግሎት አገልግሎት 818 ሚሊዬን 333ሽ 673 ብር የተሰበሰበ ሲሆን
✔ በ2012 ዓም 1ቢሊዬን 002 ሚሊዬን 718ሽ 071 ብር
✔ በ2013 በጀት አመት 1ቢሊዬን 351 ሚሊዬን 682ብር 485 ብር መሰብሰብ ተችሏል፡፡
✔ በ2014 በጀት አመት ደብረማርቆስ ከተማ አስተዳደር ወደ ሪጂኦ ፖሊታንትነት በማደጉ ከእርሱ የሚሰበሰበው ቢቀርም ዞኑ የገቢ ማግኛ ዘዴዎችን አፈላልጎ ለመጠቀም ባደረገው ጥረት 1 ቢሊዬን 365 ሚሊዬን 309ሽ 056 ብር መሰብሰብ ችሏል፡፡
✔ በዚህ አመት ደግሞ በዚህ አመት 1 ቢሊዮን 725 ሚሊዮን 599ሽ 973 ብር መሰብሰብ ተችሏል፡፡
✔ በዚህ አመት የተሰበሰበው ከባለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር 360 ሚሊዮን 290ሽ 918 ብር ብልጫ ማስመዝገብ ተችሏል፡፡
📲ከመሬት መጠቀሚያ ግብር አንጻር ሲታይ፦

✔ በ2011 በጀት አመት 32 ሚሊዬን 571ሽ 143 ብር የተሰበሰበ ቢሆን የማይከፍሉ አካላትን በማጥናት በተሰራው ስራ በ2015 በጀት አመት 40 ሚሊዬን 644 ሽ 107 ብር መሰብሰብ ተችሏል፡፡

በአጠቃላይ እንደ ምስራቅ ጎጃም ዞን የገቢዎች መምሪያ ከዓመት ዓመት የጥራትና የዕድገት አቅሙን በማሻሻል የተጀመረውን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማሳካት እየሠራ ይገኛል ።

Photos from Bibugn Woreda Communication Affairs Office's post 28/07/2023

!
በቢቡኝ ወረዳ ሲካሄድ የዋለው የሰላም ኮንፈረንስ እንዳስደሰታቸው የውይይቱ ተሳታፊዎች ገለፁ።
==================================

ሐምሌ 21/ 2015 ዓ.ም (ቢቡኝ ኮሙኒኬሽን) በምስራቅ ጎጃም ዞን በቢቡኝ ወረዳ ሲካሄድ የዋለው የሰላም ኮንፈረንስ እንዳስደሰታቸው የውይይቱ ተሳታፊዎች ገለፁ።

የውይይቱ ተሳታፊ የነበሩት መ/ጌታ ጥበቡ አንተነህ የነበረው ውይይት ከላይ እስከታች ድረስ ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ማሳተፍ በጣም ያስደስታል። ዛሬ የተወያየንበት ብቻ በቂ ስላልሆነ በቀጣይም እስከ ጠቅላላ ህዝቡ ምክክክር ያስፈልገዋል፤ አሁን ላይ አንድነት ስለሌለን ስለተነጣጠልን እንጅ አንድ ከሆን #ተሰሚነት ይኖረናል ከዚህ በኋላ አንዱ አንዱን መግደል ይብቃ የመንግስት አካላት ከወረዳ ጀምሮ በተለይም የክልሉ መንግስት የህዝቡን ጥያቄ ይዞ መፍታት አለበት ብለዋል።

በተመሳሳይ አቶ ደሴ አንተነህ የዛሬው የወረዳ ኮንፈረንስ በጣም ጠቃሚ ነበር የተሰነደው ሰነድ በጣም ጥሩና ህዝባችንን አሻጋሪ የሚያስደስት ነው። ሁሉንም ተሳታፊ አካላትና የወረዳው ብሎም የዞኑ መንግስት ምስጋና ይገባቸዋል፤ ከዚህ ወርደንም ለህዝባችን እናስተምራለን ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ሌላኛው አስተያየት ሰጭ አቶ አበበ ካሳ ሲሆኑ የነበረው የሰላም ኮንፈረንስ ከመቸውም በላይ የላቀና #ለሰላማችን የሚበጅ ሲሆን ለወጣቱም ፣ለአዛውንቱም ሆነ ለሴቱ ሰላም አስፈላጊ ነው። ይህ የሰላም ኮንፈረንስ ለሌላው ማ/ሰብም ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል።

የመጨረሻው አስተያየት ሰጭ አቶ ስናማው ልመንህ ሲሆኑ የዛሬው ኮንፈረንስ በጣም ደስ የሚልና ከቤታችን ሆነን የምናስበው አንድ የሚያደርገን ልዩ ኮንፈረንስ ነው። ነገም ይሄ ኮንፈረንስ እስከ ህዝቡ ድረስ መውረድ አለበት ብለዋል።

ሁሉም አስተያየት ሰጭዎች መንግስት ህግ ማስከበር ላይ መጠንከር እንዳለበትና ይህንን ሰላማችንን አጠናክረን ልማታችንን ማስቀጠል ይኖርብናል ብለዋል።

!

ቢቡኝ ድጎ ጽዮን

Photos from Bibugn Woreda Communication Affairs Office's post 28/07/2023

የመጀመሪያው የዙር የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና ሰላማዊ ሁኖ እንዲጠናቀቅ የድርሻችሁን የተወጣችሁ አካላት በነበራችሁ የስራ ትጋትና የባለቤት ስሜት በእጅጉ ኮርተንባችኋል፤ እናመሰግናለን።
አቶ ጌታሁን ፈንቴ
የምስራቅ ጎጃም ዞን የትምህርት መምሪያ ኃላፊ

የምስራቅ ጎጃም ዞን የትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ጌታሁን ፈንቴ የመጀመሪያው የዙር የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና በሰላም መጠናቀቅን ምክንያት በማድረግ የምስጋና መልእክት በማህበራዊ ትስስር ገጻቸዉ አስተላልፈዋል።

✅ የመልዕክቱ ሙሉ ቃል እንደሚከተለዉ ቀርቧል።

የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሃገር-አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና በሁለት ዙር በዩንቨርስቲዎች እየተሰጠ መሆኑ ይታወቃል። በዚህም መሰረት ከ14,279 በላይ የሚሆኑት የዞናችን የ12ኛ ክፍል ማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች በባህርዳር፤ በመካነሰላምና በደብረማርቆስ ዩንቨርስቲዎች ተመድበው ከሀምሌ 19-21/2015 ዓ.ም ለተከታታይ ሶስት ቀናት የተሰጠውን የማህበራዊ ሳይንስ ፈተና በመልካም ስነ-ምግባር አጠናቀዋል።

የባለፈው ዓመት ችግር እንዳይደገምና የፈተና ሂደቱ እንዳይታወክ የተሰራው ጠንካራ የቅድመ-ዝግጅት ስራ እና የባለድርሻ አካላት የትብብርና የቅንጅት ስራ ፈተናው በሰላም እንዲጠናቀቅ ምክንያት ሁኗል። የተማሪዎቻችንን ውጤትና ስነ-ምግባር ለማሻሻል በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ተግባራትም እጅግ መልካም ነበሩ። የቅድመ ዝግጅት ስራ በአግባቡ መስራት ለተግባር ምዕራፍ ስራው ስኬታማነት ቁልፍ መንደርደሪያ መሆኑንም በዚህ ዓመት በተሰጠው የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ፈተና አፈጻጸም ማረጋገጥ ችለናል።

የፈተና ሂደቱ እጅግ ሰላማዊና የተረጋጋ እንዲሁም የተሻለ ልምድ የተወሰደበትም ነበር። ተማሪዎቻችንን ከቀለም ትምህርት በዘለለ በስነ-ምግባር ማነጽ ቁልፍ ተልዕኮ ተደርጎ ሲሰራ በመቆየቱ የተሻለና ተደማሪ ስኬት ታይቶበታል። እንደነዚህ አይነት ተግባራት በሃገር አቀፍ ፈተና ብቻ ሳይሆን በክፍል ምዘናዎችና አጠቃላይ በመማር ማስተማር ሂደቱ ተጠናክረው የሚቀጥሉ ይሆናል።

የመጀመሪያው ዙር ተፈታኝ ተማሪዎቻችን የፈተና ሂደት ሰላማዊ ሁኖ እንዲጠናቀቅ ሌት ከቀን ያለመታከት የተጋችሁ የፈተና አስፈጻሚዎች፤ የዩንቨርስቲ አመራሮችና የግብረሃይል አባላት፤ ለፈተና ስራው የተመደባችሁ የጸጥታ አባላትና አመራሮች፤ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ተጠሪ መ/ቤት ሰራተኞችና የተሽከርካሪ ባለቤቶች እንዲሁም አሽከርካሪዎች ፤ በየደረጃው የምትገኙ አመራሮች፤ የተማሪዎችን እውቀትና ስነምግባር ለማስተካከል ሌት ከቀን የደከማችሁ ውድ መምህራንና የትምህርት አመራሮች፤ የመልካም ስነ-ምግባር ባለቤት በመሆን አደራችሁን የተወጣችሁ ውድ ተፈታኝ ተማሪዎችና ወላጆች፤ በጥቅሉ የፈተና ሂደቱ ሰላማዊ ሁኖ እንዲጠናቀቅ ድርሻችሁን የተወጣችሁ አካላት በሙሉ በነበራችሁ የስራ ትጋትና የባለቤት ስሜት በእጅጉ ኮርተንባችኋል፤ ምስጋናችንም በእጅጉ ከፍ ያለ ነውና በዞናችን የትምህርት ማህበረሰብ ስም ከልብ እናመሰግናችኋለን።

ለትውልድ ማሰብ፤ ለሃገር ግንባታ መጨነቅ፤ ለጋራ ተልዕኮ በጋራ መረባረብና ባለቤት ሁኖ ያለድካም መታከት፤ መደማመጥና ተቀናጅቶ መስራት በእጅጉ የታየበት የፈተና አፈጻጸም ነበር። ይህ መልካም አፈጻጸም ቀጣይ ከሀምሌ 25-28/2015 ዓ.ም በሚሰጠው ሁለተኛው ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተናም ከመጀመሪያው ዙር ባደገ መልኩ እንደሚፈጸም በመተማመን ለተፈታኝ ተማሪዎቻችን በሙሉ መልካም የፈተናና ጊዜ እንዲሆንላቸው እመኛለሁ።
" በጋራ ጥረታችን ወደ ቀደመ ከፍታችን !!"

Photos from Bibugn Woreda Communication Affairs Office's post 28/07/2023

በቢቡኝ ወረዳ ሲካሄድ የዋለው ተጠናቀቀ።
==============================
ሐምሌ 21/2015 (ቢቡኝ ኮሙኒኬሽን) በምስራቅ ጎጃም ዞን በቢቡኝ ወረዳ የሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት አስተባባሪነት " #የጋራ መነሻና መዳረሻ ካበጀን ከአሸናፊነት መንገድ ላይ እንገናኛለን!" በሚል መሪ ቃል ሲካሄድ የዋለው የሰላም ኮንፈረንስ ተጠናቀቀ።

የሰላም ኮንፈረንሱ ተሳታፊዎችም የምስ/ጎጃም ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ቢሻው ሞላ፣ የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ አለባቸው ሽታ እና የወረዳችን ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ጌታ ይዘንጋው በተገኙበት የሃይማኖት አባቶች፣ ታዋቂ የሃገር ሽማግሌዎች፣ የዕድር መሪዎች፣ የት/ት ባለድርሻ አካላት፣ ደንብ ፀሃፊዎች፣ የዕቁብ ዳኞች፣ ወጣቶች፣ የፀጥታ ማኔጅመንት አባላት፣ የወረዳ አመራሮች እና ሌሎች ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ተሳትፈዋል።

በውይይቱ በወረዳችን ብሎም በክልላችን #ሰላም እንዲረጋገጥ ሁሉም የድርሻውን በመወጣት የተጀመረውን የኢኮኖሚያዊ፣ የፖለቲካዊና የማህበራዊ ለውጦችን ለማፅናት ያለመ ነበር።

በመጨረሻም የቀጣይ የመንግስትን አቅጣጫ በማስቀመጥና መድረኩ ሲጀመርም ሆነ ሲጠናቀቅ በሃይማኖት አባቶች የተከፈተ እና የታሰረ ከመቸውም በላይ ሰላም ወዳዱን ተሳታፊ ባለድርሻ አካላት ያረካና ያስደሰተ ሆኖ ስምምነት ላይ በመድረስ ተጠናቋል።

" !"

ቢቡኝ ድጎ ጽዮን

Photos from Bibugn Woreda Communication Affairs Office's post 28/07/2023

በአማራ ክልል እስካሁን 1 ሚሊየን ኩንታል በላይ የዩሪያ ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ተሰራጭቷል
***
በአማራ ክልል የዩሪያ ማዳበሪያን ለአርሶ አደሩ በፍትሃዊነት የማሰራጨት ስራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል፡፡
የቢሮው ምክትል ሃላፊ አቶ አጀበ ስንሻው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷በክልሉ የሚገኙ አርሶ አደሮች የዩሪያ ማዳበሪያ ፍላጎት 4 ነጥብ 1 ሚሊየን ኩንታል በላይ ነው፡፡
ይሁን እንጂ ለክልሉ አጠቃላይ የተገዛው የዩሪያ ማዳበሪያ መጠን 2 ነጥብ 3 ሚሊየን ኩንታል ብቻ መሆኑን ነው የተናገሩት፡፡
ከተገዛው የዩሪያማዳበሪያ ውስጥም 1 ነጥብ 3 ሚሊየን ኩንታሉ ወይም 75 በመቶ የሚሆነው ወደ ክልሉ ተጓጉዞ መድረሱን አቶ አጀበ አረጋግጠዋል፡፡
እስካሁን ድረስም በክልሉ ለሚገኙ አርሶ አደሮች 1 ሚሊየን ኩንታል በላይ የዩሪያ ማዳበሪያ መሰራጨቱን ጠቁመዋል፡፡
በቀጣይ ቀሪውን የዩሪያ ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማሰራጨት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
በስርጭት ሒደቱ ላይ የሚያጋጥሙ ሕገ ወጥ ድርጊቶችን ለመከላከልም በየደረጃው ግብር ሃይል ተቋቁሙ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ህብረተሰቡም ህገ ወጥ የዩሪያ ማዳበሪያ ስርጭት በሚመለከትበት ጊዜ በአካባቢ ለሚገኙ የጸጥታ አካላት እንዲጠቁም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ዘገባው የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ነው።

Photos from Bibugn Woreda Communication Affairs Office's post 28/07/2023

በቢቡኝ ወረዳ መካሄድ ጀመረ።
==============================
ሐምሌ 21/2015 (ቢቡኝ ኮሙኒኬሽን) በቢቡኝ ወረዳ የሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት አስተባባሪነት " #የጋራ መነሻና መዳረሻ ካበጀን ከአሸናፊነት መንገድ ላይ እንገናኛለን!" በሚል መሪ ቃል የሰላም ኮንፈረንስ መካሄድ ጀመረ።

የሰላም ኮንፈረንሱ ተሳታፊዎችም የምስ/ጎጃም ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ቢሻው ሞላ እና የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ አለባቸው ሽታ በተገኙበት የሃይማኖት አባት፣ ታዋቂ የሃገር ሽማግሌዎች፣ የዕድር መሪዎች፣ የት/ቤት ወመህ አካላት፣ ደንብ ፀሃፊዎች፣ የዕቁብ ዳኞች፣ ወጣቶች፣ የፀጥታ ማኔጅመንት አባላት፣ የወረዳ አመራሮች እና ሌሎች ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ተሳታፊ ሆነዋል።

በውይይቱ በወረዳችን ብሎም በክልላችን ሰላምን እንዲረጋገጥ ሁሉም የድርሻውን በመወጣት የተጀመረውን የኢኮኖሚያዊ፣የፖለቲካዊና የማህበራዊ ለውጦችን ለማፅናት ያለመ ነው።

በመጨረሻም የቀጣይ አቅጣጫ እንደሚሰጥ ይገመታል፤ ዝርዝር መረጃውን እየተከታተልን የምናደርሳችሁ ይሆናል።

" !"

ቢቡኝ ድጎ ጽዮን

Photos from Bibugn Woreda Communication Affairs Office's post 27/07/2023

የቢቡኝ ወረዳ አስተዳድር ልማት ዕቅድ የ2016 ዕቅድ ዝግጅትን አስመልክቶ ኦረንቴሽን አካሄደ።
=================+=================
ሐምሌ 20/2015 ዓ.ም (ቢቡኝ ኮሙኒኬሽን) በምስራቅ ጎጃም ዞን የቢቡኝ ወረዳ አስተዳድር ልማት ዕቅድ የ2016 ዓ.ም ዕቅድ ዝግጅትን አስመልክቶ ኦረንቴሽን አካሄደ።

ለበጀት ዓመቱ ዕቅድ ዝግጅት ኦረንቴሽን የወረዳው የሴክተር መ/ቤት ኃላፊዎችና የዕቅድ ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ባለሙያዎችበሙሉ ተሳትፈዋል።

ከላይ ጀምሮ በተዋረድ በመጣው አዲስ ዕቅድ መሰረት የተከለሰ የአስር ዓመት ዕቅድ እና የ2016 በጀት ዓመት የአንድ ዓመት ዕቅድ በተሰጠው ኦረንቴሽን መሰረት ታቅዶ ወደ ስራ እንደሚገባ አቅጣጫ በማስቀመጥ ተጠናቋል።

Photos from Bibugn Woreda Communication Affairs Office's post 27/07/2023

ጮቄ ተራሮችን ይጎብኙ። ጎጃም፤ አማራ/ኢትዮጵያ
Visit Choke Mountains, Gojjam, Amhara/Ethiopia

Photos from Bibugn Woreda Communication Affairs Office's post 27/07/2023

ምስራቅ ጎጃም ዞን አስተዳደር፣ ምስራቅ ጎጃም ዞን ጤና መምሪያና ሸበል በረንታ ወረዳ በበጀት አመቱ ዜጎችን ከዐይነስውርነት በመታደግ በክልል ደረጃ በተካሄደ ውድድር 1ኛ በመውጣታቸዉ የዋንጫና የቁሳቁስ ተሸላሚ ሆኑ፡፡

ዞኑ አንደኛ በመውጣት ተሸላሚ የሆነው በአንድ ዓመት ውስጥ 13ሽ 874 ሰዎችን ከዓይነ ስውርነት በመታደጉ በክልል ደረጃ በተካሄደ ውድድር 1ኛ በመውጣቱ ነው፡፡

የምስራቅ ጎጃም ዞን ሽልማት የተበረከተለት ትራኮማን በመከላከልና መቆጣጠር ሥራው የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን ለመገምገምና በቀጣይም በሽታውን ለማስወገድ በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ክልል አቀፍ የምክክር መድረክ በባሕር ዳር በተካሄደበት የማጠቃለያ ስነ ስርዓት ላይ ነው፡፡

የምስራቅ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አያሌው የትራኮማ በሽታን ከዞኑ ነጻ በማድረግ ዜጎችን ከዓይነ ስውርነት ለመታደግ ሌትና ቀን የሰሩ አካላትን አመስግነዋል፡፡ አቶ አብርሃም በመልእክታቸው ይህ ተግባር ተወዳድሮ አንደኛ ከመውጣት በላይ በዓይነ ስውርነት የሚሰቃዩ ዜጎችን ቀዶ ጥገና በማድረግ ከአይነ ስውርነት በመታደግ ብርሃን እንዲያገኙ ማድረግ የሚሰጠው የህሌና እርካታ ይበልጣል ብለዋል፡፡

በዚህ ስራ የተሳተፉ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና ባለሙያዎች አስተዳደሩ በእጅጉ ያመሰግናል ያሉት አቶ አብርሃም በቀጣይ ትራኮማን ለማስወገድ ለምንሰራው ስራ ሁሉም አካል ርብርብ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ለስራችን መሳካት በጤናው ዘርፍ ያሉ አመራሮችና ባለሙያዎች በተጨማሪ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ጥብቅ ክትትልና ድጋፍ እንዲሁም የአጋር አካላት ሚና ከፍተኛ ነበር ያሉት የምስራቅ ጎጃም ዞን ጤና መምሪያ ሃላፊ አቶ መልካሙ ጌትነት በበጀት አመቱ በተደረገ ርብርብ 13ሽ 874 ሰዎችን ከዓይነ ስውርነት መታደግ መቻላቸውን ተናግረዋል፡፡

በዚህ ስራ በርካቶች እንዲሳተፉበት አድርገናል ያሉት አቶ መልካሙ የታካሚ ልየታ በሚካሄድበት ወቅት ከፍተኛ እርብርብ ያደረጉ የምስራቅ ጎጃም ህዝብ፣የመንግስት ሰራተኛ፣ጤና ባለሞያዎች፣በየደረጃው ያሉ አመራሮች እና አጋሮች ከፍተኛ ምስጋና አቅርበው በቀጣይ በሽታው የዞኑ ህዝብ የጤና ችግር ከማይሆንበት ደረጃ ለማድረስ በሚደረገው ትግል የሚጠበቅብንን እንድንወጣ በማለት ጠንካራ ጥሪ አቅርበዋል።

✅ምስራቅ ጎጃም ዞን አስተዳደር 1ኛ በመውጣት
✔ ዋንጫና ሰርተፍኬት
✅ ምስራቅ ጎጃም ዞን ጤና መምሪያ 1ኛ በመውጣት
✔ ዲስክቶፕ ኮምፒዩተር፣ ✔ ኤልሲዲ✔፣ ፎቶ ኮፒ ማሽን
✅ ሸበል በረንታ ወረዳ 1ኛ በመውጣት
✔ ዲስክቶፕ ኮምፒዩተር፣
✔ ኤልሲዲ✔፣
✔ ፎቶ ኮፒ ማሽን፣
✔ ሰርተፍኬት ተሸላሚ ሲሆኑ ከዞኑ

✅ 3 ትምህርት ቤቶች እያንዳንዳቸው ሰርትፍኬትና 2000 ሊትር የሚይዝ ሮቶ እና 4 የዓይን ቆብ ቀዶ ህክምና ባለሞያዎች ከ16-12ሽ ብር ሽልማት ተበርክቷል፡፡

ምስራቅ ጎጃም ዞን አስተዳደር፣ ምስራቅ ጎጃም ዞን ጤና መምሪያና ሸበል በረንታ ወረዳ በበጀት አመቱ ዜጎችን ከዐይነስውርነት በመታደግ በክልል ደረጃ በተካሄደ ውድድር 1ኛ በመውጣታቸዉ የዋንጫና የቁሳቁስ ተሸላሚ ሆኑ፡፡

ዞኑ አንደኛ በመውጣት ተሸላሚ የሆነው በአንድ ዓመት ውስጥ 13ሽ 874 ሰዎችን ከዓይነ ስውርነት በመታደጉ በክልል ደረጃ በተካሄደ ውድድር 1ኛ በመውጣቱ ነው፡፡

የምስራቅ ጎጃም ዞን ሽልማት የተበረከተለት ትራኮማን በመከላከልና መቆጣጠር ሥራው የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን ለመገምገምና በቀጣይም በሽታውን ለማስወገድ በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ክልል አቀፍ የምክክር መድረክ በባሕር ዳር በተካሄደበት የማጠቃለያ ስነ ስርዓት ላይ ነው፡፡

የምስራቅ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አያሌው የትራኮማ በሽታን ከዞኑ ነጻ በማድረግ ዜጎችን ከዓይነ ስውርነት ለመታደግ ሌትና ቀን የሰሩ አካላትን አመስግነዋል፡፡ አቶ አብርሃም በመልእክታቸው ይህ ተግባር ተወዳድሮ አንደኛ ከመውጣት በላይ በዓይነ ስውርነት የሚሰቃዩ ዜጎችን ቀዶ ጥገና በማድረግ ከአይነ ስውርነት በመታደግ ብርሃን እንዲያገኙ ማድረግ የሚሰጠው የህሌና እርካታ ይበልጣል ብለዋል፡፡

በዚህ ስራ የተሳተፉ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና ባለሙያዎች አስተዳደሩ በእጅጉ ያመሰግናል ያሉት አቶ አብርሃም በቀጣይ ትራኮማን ለማስወገድ ለምንሰራው ስራ ሁሉም አካል ርብርብ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ለስራችን መሳካት በጤናው ዘርፍ ያሉ አመራሮችና ባለሙያዎች በተጨማሪ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ጥብቅ ክትትልና ድጋፍ እንዲሁም የአጋር አካላት ሚና ከፍተኛ ነበር ያሉት የምስራቅ ጎጃም ዞን ጤና መምሪያ ሃላፊ አቶ መልካሙ ጌትነት በበጀት አመቱ በተደረገ ርብርብ 13ሽ 874 ሰዎችን ከዓይነ ስውርነት መታደግ መቻላቸውን ተናግረዋል፡፡

በዚህ ስራ በርካቶች እንዲሳተፉበት አድርገናል ያሉት አቶ መልካሙ የታካሚ ልየታ በሚካሄድበት ወቅት ከፍተኛ እርብርብ ያደረጉ የምስራቅ ጎጃም ህዝብ፣የመንግስት ሰራተኛ፣ጤና ባለሞያዎች፣በየደረጃው ያሉ አመራሮች እና አጋሮች ከፍተኛ ምስጋና አቅርበው በቀጣይ በሽታው የዞኑ ህዝብ የጤና ችግር ከማይሆንበት ደረጃ ለማድረስ በሚደረገው ትግል የሚጠበቅብንን እንድንወጣ በማለት ጠንካራ ጥሪ አቅርበዋል።

✅ምስራቅ ጎጃም ዞን አስተዳደር 1ኛ በመውጣት
✔ ዋንጫና ሰርተፍኬት
✅ ምስራቅ ጎጃም ዞን ጤና መምሪያ 1ኛ በመውጣት
✔ ዲስክቶፕ ኮምፒዩተር፣ ✔ ኤልሲዲ✔፣ ፎቶ ኮፒ ማሽን
✅ ሸበል በረንታ ወረዳ 1ኛ በመውጣት
✔ ዲስክቶፕ ኮምፒዩተር፣
✔ ኤልሲዲ✔፣
✔ ፎቶ ኮፒ ማሽን፣
✔ ሰርተፍኬት ተሸላሚ ሲሆኑ ከዞኑ

✅ 3 ትምህርት ቤቶች እያንዳንዳቸው ሰርትፍኬትና 2000 ሊትር የሚይዝ ሮቶ እና 4 የዓይን ቆብ ቀዶ ህክምና ባለሞያዎች ከ16-12ሽ ብር ሽልማት ተበርክቷል፡፡
East Gojjam Communication

27/07/2023

"በአማራ ክልል በአንድ ዓመት ውስጥ 60 ሺህ ሰዎችን የዓይን ቆብ ቀዶ ጥገና ሕክምና ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል" ዶክተር መልካሙ አብቴ
ባሕር ዳር: ሐምሌ 20/2015 ዓ.ም (ቢቡኝ ኮሙኒኬሽን) ትራኮማን በመከላከልና መቆጣጠር ሥራው የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን ለመገምገምና በቀጣይም በሽታውን ለማስወገድ በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ክልል አቀፍ የምክክር መድረክ በባሕር ዳር እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ በምክትል ርእሰ መሥተዳደር ማዕረግ የማኅበራዊ ዘርፍ ክላስተር አስተባባሪ ስዩም መኮንን ጨምሮ የአማራ ክልል ጤና ቢሮ፣ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎችና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶችና የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።
የክልሉ ጤና ቢሮ ኀላፊ ዶክተር መልካሙ አብቴ እንደተናገሩት በጤናው ዘርፍ ሰፊ ሥራ እየተከናወነ ነው። በተለይም የትራኮማ በሽታን በክልሉ ነጻ ለማድረግ ከካርተር ሴንተርና ሌሎችም አጋር አካላት ጋር የሚደረገው ርብርብ አበረታች ነው ብለዋል።
ቢሮ ኀላፊው እንዳሉት በዚህ አንድ ዓመት 60 ሺህ ሰዎችን የዓይን ቆብ ቀዶ ጥገና አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል። ከዓይን ጤንነት ጋር በተያያዘ 21ሺህ 45 ሰዎች የዓይን ቆብ ቀዶ ጥገና ተሠርቶላቸዋል ነው ያሉት። ከለጋሽ አካላት እስከ ሚመለከታቸው አካላት ላደረጉት አስተዋጽኦ ምሥጋናቸው አቅርበዋል።
ካርተር ሴንተር የትራኮማ በሽታን ከአማራ ክልል ሙሉ በሙሉ ለማስወገድ በሚያስችል ኹኔታ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሠራ ነው ያሉት ደግሞ በካርተር ሴንተር የአማራ ክልል ኀላፊ ፈጠነ ምሕረቱ ናቸው።
ኀላፊው እንዳሉት በክልሉ 62 ወረዳዎችን ከትራኮማ ነጻ በማድረግ ከመድኃኒት እደላ ውጭ ማድረግ ተችሏል ብለዋል። ኀላፊው በሽታው ከክልሉ እስኪጠፋ ድረስም ካርተር ሴንተር ከክልሉ መንግሥት ጋር በጋራ ይሠራል ብለዋል።
ኃላፊው አሁንም በክልሉ ከ70 እስከ 80 ሺህ የሚደርሱ ሰዎች የትራኮማ ሕክምና እንደሚያስፈልጋቸው ነው የተናገሩት።
በመድረኩ የተገኙት የካርተር ሴንተር የትራኮማ መቆጣጠር ፕሮግራም ዳይሬክተር ኬሊ ካልንኽን በአማራ ክልል ትራኮማን የመከላከል ሥራው ስኬታማ ነው ብለውታል። በተለይም ከአጋር አካላት ጋር የተደረገው ቅንጅታዊ አሥራር በየትኛውም ዓለም እና በሀገሪቱም በየትኛውም ክልል ያልታየ የመከላከልና የመቆጣጠር፣ የሕክምና አገልግሎት ነው ብለዋል።
በምክትል ርእሰ መሥተዳደር ማእረግ የማኅበራዊ ዘርፍ ክላስተር አስተባባሪ ስዩም መኮንን በመድረኩ እንደተናገሩት ትራኮማን ለመከላከል የሚያስችል ውሳኔ ላይ መድረስ ከቻልን በቀላሉ የምንከላከለው ነው ፣በችግር ላይ ተኹኖም የታዩት ጅምሮች ለስኬት የሚያበቁ ናቸው ብለዋል።
አቶ ስዩም የትራኮማ በሽታን ለመከላከልና ለማስወገድ ለንጹሕ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ተደራሽነት ቆርጠን መነሳትና የማኅበረሰብን ግንዛቤ ማሳደግ ላይ ሁሉም በኃላፊነቱ ልክ እንዲሠራ አሳስበዋል።
ልንከላከለው በምንችለው ቀላል በሽታ ኅብረተሰቡ ለዓይነ ሥውርነትና በኢኮኖሚም ለመዳከም እንዲበቃ ኾኗል፣ይህ የክልሉን ሕዝብ የማይመጥን ነው ብለዋል። የተጀመረው ርብርብ ተጠናክሮ ከቀጠለ ከፍተኛ ለውጥ ማምጣት ይቻላል፣ በቅርብ ዓመታትም ከትራኮማ በሽታ ነጻ የኾነ ክልል መፍጠር ይቻላል ነው ያሉት።

27/07/2023

"በማንነታችን ላይ ዳግም ለአፍታ እንኳን ተዘናግተን የተራዘመ መከራ እና ባርነት ለመቀበል ፍጹም አንፈቅድም" ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ
ሁመራ: ሐምሌ 20/2015 ዓ.ም (ቢቡኝ ኮሙኒኬሽን) የግማሽ ምዕተ ዓመት ገደማ ሴራ እና ተንኮል መጋለጫ፣ የሩብ ምዕተ ዓመት አምባገነናዊ አገዛዝ መሸኛ፣ የሦስት አስርት ዓመታት የጨለማ ጉዞ ምዕራፍ መቋጫ እና የአዲሱ ትውልድ የነጻነት አደራ ርክክብ ትናንት በቅርቡ የተስተዋለ ክስተት ነበር፡፡ እልፎች ማንነታችን ይከበር ብለው አደባባይ ድረስ ዘልቀው በመውጣት የከበረ መስዋዕትነት ሲከፍሉ ከተፈጥሯዊ ነጻነት ባሻገር የጠየቋቸው እና ለትግል የሚያበቁ አያሌ ምክንያቶች ነበሯቸው፡፡
ማኀበረሰባዊ ማንነትን የሚያስቀጥል ትግል ደግሞ በትውልድ ቅብብሎሽ መካከል የሚጸና የነጻነት መርከብ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ ለማንነት መከበር በሚደረግ ትግል ውስጥ ውስኖች እንደ አብሪ ኮከብ ጎልተው ቢታዩም የትግሉ ባለቤት እና ሞተር ግን ሕዝብ መኾኑ አይካድም፡፡ የወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት እና ራያ ሕዝብ የዘመናት የነጻነት ትግል መልህቅ በታሪክ አጋጣሚ በአዲሱ ትውልድ መዳፍ ውስጥ ገብቷል፡፡
የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ በጀቱ የሕዝብ ቁጭት እና ብሶት ነው ያሉት በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ምክትል አሥተዳዳሪ እና የሰላም እና ጸጥታ መምሪያ ኅላፊ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ናቸው፡፡ የወልቃይት ወረዳ በቅርቡ ያስገነባቸውን የተለያዩ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች አጠናቆ አስመርቋል፡፡
በምረቃ ሥነ-ሥርዓተ ላይ የተገኙት የዞኑ ምክትል አሥተዳዳሪ እና የሰላም እና ጸጥታ መምሪያ ኅላፊው ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብን ለዘመናት ሞት፣ ስደት እና እንግልት ከዳረጉት የህወሐት ፖለቲካዊ ሸፍጦች መካከል አንዱ ፍትሐዊ የልማት ተጠቃሚነት አለመኖር እንደነበር አንስተዋል፡፡
ለዘመናት በማንነቱ ምክንያት ፍትሐዊ ልማት ናፍቆት የኖረ ሕዝብ በጥረቱ የሠራውን የመሰረተ ልማት ግንባታዎች በማየት ትናንት የበደሉን ሁሉ ሊሸልሙን እና ሊያመሰግኑን በተገባ ነበር ብለዋል፡፡
ወልቃይት ጠገዴ በርካታ የመልማት ጸጋዎች እና አቅሞች ያሉት አካባቢ ነው፡፡ ነገር ግን ባለፉት ሦስት አስርት ዓመታት በህወሃት አምባገነናዊ የጭቆና አገዛዝ ውስጥ እንዲቆይ በመገደዱ ለከፋ ሰብዓዊ፣ ምጣኔ ሀብታዊ እና ማኀበራዊ ስብራቶች እንዲዳረግ አድርጎት እንደቆየ ኮሎኔል ደመቀ አንስተዋል፡፡ የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ በተለያዩ የትግል ስልቶች እና አማራጮች የተጫነበት የባዕድ ማንነት እንደማይገልጸው ተናግሯል፡፡ ነገር ግን የነበረው ሥርዓት ነባር ባለእርስቶችን አፈናቅሎ የእኔ ነው የሚለውን ማኀበረሰብ ማጽናት በመኾኑ የሕዝብን ጥያቄ በኃይል ለማፈን ብዙ እርቀት ተጉዞ ነበር፡፡
የወልቃት ወረዳ ማዕከል የኾነችው ወፍ አርግፍ ከተመሠረተች አያሌ ዓመታትን ብታስቆጥርም ይህ ነው የሚባል የመሠረተ ልማት ግንባታ የላትም፡፡ ኮሎኔል ደመቀ እንደሚሉት በከተማዋ መካከል አልፎ የሚሄደው የአስፓልት መንገድ የተሠራበት ዓላማ ግልጽ ቢኾንም ወፍ አርግፍን ሳይነካ እንዲያልፍ ለማድረግ የተሠራውን ሴራ ሕዝብ ያውቀዋል ብለዋል፡፡ በሕዝብ እምቢተኝነት መንገዱ በከተማዋ መካከል አልፎ እንዲሄድ ቢገደዱም፡፡
ኮሎኔል ደመቀ የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ሕዝብ የነበረውን መዋቅራዊ ሴራ በሚገባ ተረድቷል ነው ያሉት፡፡ “የማንንም ርስት አልፈን አልነካንም፤ ያስመለስነውም ለረጂም ጊዜ ታግለንና መስዋእትነት ከፍለን ማንነታችንን ነው” ብለዋል፡፡ የትግራይ ሕዝብ የወልቃይትን እውነት መመስከር እንዳለበትም ነው የተናገሩት፡፡
የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ሕዝብ እና አሥተዳደር አሁን በሙሉ አቅሙ ልማት ላይ ነው፡፡
"ከማንም ጋር ግጭት አንፈልግም በማንነታችን ላይ ግን ዳግም ለአፍታ እንኳን ተዘናግተን የተራዘመ መከራ እና ባርነት ለመቀበል ፍጹም የማንፈቅድ መኾኑን ሊታወቅ ይገባል" ብለዋል የሰላም እና ጸጥታ መምሪያ ኅላፊው፡፡
የትግራይ ጊዜያዊ አሥተዳደር በሀገረ አሜሪካ ገብቶ የሚነዛውን የሃሰት ፕሮፖጋንዳ እየሰማን ነው ያሉት ኮሎኔል ደመቀ የትግራይ ሕዝብ በውሸት መመራት ይበቃኛል ማለት አለበት ነው ያሉት፡፡
የኢትዮጵያ ሕዝብ የትግራይ መገናኛ ብዙኀኖች ሳይቀር የሚሰብኩትን እና የሚጎስሙትን የጦርነት ነጋሪት ሊገነዘበው እንደሚገባም ኮሎኔል ደመቀ ተናግረዋል፡፡
ህወሃት አካባቢውን የግጭት ቀጠና ለማድረግ የሚሠሩትን ዘርፈ ብዙ ሙከራ በሚገባ እናውቃለን ነው ያሉት ኮሎኔል ደመቀ። የተለየ ሃሳብ እና ፍላጎት ያለው ሁሉ ሃሳቡን አደባባይ አውጥቶ ይሞግት፤ ሃሳብ ያሸነፍል ወይም ይሸነፋል፡፡
ይሁን እንጅ ውስጥ ለውስጥ መሄድ እና የአካባቢውን ሕዝብ ዳግም ያማያባራ ዋጋ ለማስከፈል የሚደረግ የትኛውም አይነት እንቅስቃሴ ተገቢነት የለውም ብለዋል፡፡

26/07/2023

"አሚኮ ባለፉት ዓመታት በሀገር አቀፍ ደረጃ የራሱን አሻራ ያሳረፈ፣ የራሱ ቀለም ያለው፣ ለኅብረተሰብ ለውጥ የሚተጋ ተቋም ነው" የአሚኮ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሙሉቀን ሰጥዬ
ሐምሌ 19/2015 ዓ.ም (ቢቡኝ ኮሙኒኬሽን) አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ወደ አዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግረውን የመዋቅር ለውጥ አካሂዷል። አዲሱን መዋቅር የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈጉባኤ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች፣ የአሚኮ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት፣ የሚዲያ ባለሙያዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት አስተዋውቋል።
"አሚኮ ወደ አዲስ ምዕራፍ" በሚል የተዋወቀው አዲሱ መዋቅር ላለፉት ጊዜያት ከአማራ ምሁራን መማክርት ጋር በጋራ ሢሠራ ነው የቆዬው።
የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሙሉቀን ሰጥዬ ባስተላለፉት መልእክት ተቋሙ ጊዜውን በሚዋጅ መልኩ ከአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት ወደ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በአዋጅ መቀየሩን አስታውሰዋል። ተቋሙ የመለያ ቀለሙንም አሻሽሏል፣ ሁለተኛ የቴሌቪዥን ቻናል ከፍቷል፣ ደሴ ላይ ዘመናዊ የሚዲያ ተቋም እየገነባ ነው፣ አዲስ አበባ ላይ አስተዋፅኦውን ማሳደግ የሚያስችለው ቦታ ተቀብሏል ነው ያሉት።
አሚኮ የውስጥ ገቢውን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሳደገ መኾኑንም ተናግረዋል። በነበረው የወረራ ጦርነት ወልድያና ደሴ ላይ የሚገኙ ቅርንጫፎቹ ሙሉ ለሙሉ ወድመው እንደነበር ያስታወሱት ሥራ አስፈፃሚው የደሴን ስቱዲዮ ባለ አቅም ወደ ሥራ እንዲገባ መደረጉን ነው የተናገሩት።
አሚኮ በሀገር አቀፍ ደረጃ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሚዲያ መኾኑንም ገልጸዋል።
ተቋሙን የሚደግፉ የክልል መሪዎች፣ የሥራ አመራር የቦርድ አባላት እንዳሉትም ገልጸዋል። አሚኮ ወደ አዲስ ምዕራፍ የተሸጋገረበት ዋናው ዓላማው ለሕዝብ የሚሠራ፣ ጠንካራና መፍትሔ አመላካች የሚዲያ ተቋም ለመገንባት መኾኑን አንስተዋል።
በአንድነት ከሠራን የጠንካራ ተቋም መሠረት እንጥላለን፣ በቀጣይም ጠንካራ ተቋም ለትውልድ እናስተላልፋለን ነው ያሉት።
ባለፉት ዓመታት በሀገር አቀፍ ደረጃ የራሱን አሻራ ያሳረፈ፣ የራሱ ቀለም ያለው፣ ለኅብረተሰብ ለውጥ የሚተጋ ተቋም መኾኑንም ገልጸዋል።
ተቋሙ የተከማቸ ትልቅ ተቋማዊ እሴት እንዳለውም ተናግረዋል። ተቋሙ ለሕዝብ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ለውጦች መትጋት እንደሚገባውም ተናግረዋል። የሚገጥሙ ፈተናዎችን በጋራ ኾኖ ማለፍ እንደሚገባም ገልጸዋል።
ዋና ሥራ አስፈፃሚው አሚኮ ወደ አዲስ ምዕራፍ እንዲሸጋገር የክልሉ መንግሥት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል። ለአሚኮ ሥራ አመራር ቦርድ አባላትና ለአማራ ምሁራን መማክርት ላደረጉት አስታውጽዖም ምሥጋና አቅርበዋል ሲል የዘገበው አሚኮ ነው።

26/07/2023

"የክልሉ መንግሥት አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽንን ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ይደግፋል" አቶ ግዛቸው ሙሉነህ
********
ሐምሌ 19/2015 ዓ.ም (ቢቡኝ ኮሙኒኬሽን) አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ወደ አዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግረውን የመዋቅር ለውጥ አካሂዷል።
አዲሱን መዋቅር የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የአሚኮ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት፣ የሚዲያ ባለሙያዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት አስተዋውቋል።
የክልሉን መንግሥት ወክለው መልእክት ያስተላለፉት የአማራ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ግዛቸው ሙሉነህ አሚኮ ከትንሽ ነገር ጀምሮ ታላቅ ተቋም መኾን የቻለ መኾኑን ገልጸዋል።
ያለንበት ዓለም ተለዋዋጭ በመኾኑ የሚዲያ ተቋማትም ጊዜውን የሚመጥን ለውጥ እንደሚያስፈልጋቸው ነው የተናገሩት።
የክልሉ መንግሥት አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ለክልሉ አስፈላጊ መኾኑም በማመን በትኩረት እንደሚደግፍ ገልጸዋል። የክልሉ መንግሥት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ድጋፉን እንደሚቀጥልም አስገንዝበዋል።
ሚዲያው እንዲያድግ የሥራ አመራር ቦርዱ በትኩረት መሥራቱንም አስታውሰዋል። አሚኮ ከሌሎች ሚዲያዎች ጋር ተወዳዳሪ እንዲኾን ሥራዎች ሲሠሩ መቆዬታቸውን ነው የገለጹት።
አሚኮ የክልሉን ሕዝብ አንድነት የማጠናከር፣ የክልሉን ሕዝብ በሌሎች ሕዝቦች ዘንድ በትክክለኛው ማንነቱ እንዲታወቅ የማድረግ ሥራ የመሥራት ኃላፊነት አለበት ነው ያሉት።
ችግሮችን ያገናዘበ እና ችግሮችን በትጋት የመወጣት ኃላፊነት እንዳለበትም ነው የገለጹት። የተቋሙ አዲስ መዋቅር በተገቢው እንዲተገበር የክልሉ መንግሥት ድጋፍ እንደሚያደርግም ተናግረዋል ያለው አሚኮ ነው።

Photos from Bibugn Woreda Communication Affairs Office's post 26/07/2023

"ማዕድን አዲስ የንጋት ተስፋ ለዞናችን"!

እጅግ ውድና የከበሩ ማዕድናት መገኛ ምስራቅ ጎጃም ዞን 👇👇👇

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሚወጡ ጥናቶች የምስራቅ ጎጃም ዞን አስተዳዳር ከሰብል ልማት በተጨማሪ በማዕድን ሀብቱ ዘርፈ ብዙ ዕምቅ ሀብት ያለው መሆኑ እየታወቀ የመጣ ዞን ነዉ፡፡

መምሪያዉ ራሱን ችሎ ከተቋቋመ የአንድ አመት ብቻ እድሜ ያለዉ ቢሆንም ዉጤታማ ስራ እየሰራ ነዉ። ከተሠሩ ስራዎች በጥቂቱ ፦

✅ ለዞናችንን በክልል ደረጃ የተሰጡ ፈቃዶች👎
👉 የስሚንቶ ምርመራና ማምረት ፈቃድ የወሰዱ ብዛት 5
👉 ከፍተኛ ደረጃ ጥቁር ድንጋይ ጠጠር ማምረት ፈቃድ የወሰዱ ብዛት 16
👉 የግራናይት ምርመራና ማምረት ፈቃድ የወሰዱ ብዛት 114 የማምረት ፈቃድ የወሰዱ 64
👉 እምነበረድ ምርመራና ማምረት ፈቃድ የወሰዱ ብዛት 12 የማምረት ፈቃድ የወሰዱ 3
👉 የጅብሰም ማምረት ፈቃድ የወሰዱ ብዛት 21
👉 ሲሊካ ላንድ ማምረት ፈቃድ የወሰዱ ብዛት 3 ናቸው፡፡
✅ በ2015 በተሰበሰበ የማዕድን ሃብት መረጃ ውስጥ ዋና ዋናዎቹ👎
➡️ የኢንደስትሪ ማዕድናት 👇
✔ ግራናይት፣
✔ የኖራና የሲሚንቶ ድንጋይ፣
✔ የጀሶ ድንጋይ፣
✔ ሸክላ አፈር፣
ሲሊካ ላንድ
➡️ የኮንስትራክሽን ማዕድናት 👇
✔ አሸዋ ድንጋይ ፣
✔ ሰሌክትድ ማቴሪያል
➡️ ብረት ነክ ማዕድናት የሚገኙባቸው ወረዳዎች👇
✔ እነብሴ ሳር ምድር፣
✔ እናርጅ እናውጋ፣
✔ ሸበል በረንታ
➡️ የጅኦተርማል የማዕድን ውሃክምችት
✔ በደብረ ኤልያስ ወረዳ

ከ2011 እስከ 2015 ድረስ ባለው ጊዜ በዘርፉ በባህላዊና በአነስተኛ 1282 ፈቃድ ተሰጥቷል፡፡

👉 በዚህም በባህላዊ 13ሽ 317 በአነስተኛ 2ሽ 280 ወጣቶች የስራ እድል ተፈጥሮላቸዋል፡፡
👉 ፈቃድ ከተሰጣቸው ውስጥ 2468 የሚሆኑ በባህላዊና በአነስተኛ ደረጃ ፈቃዳቸውን ጨርስው ፈቃዳቸው እንዲሰረዝ ተደርጓል፡፡
👉 በማእድን ዘርፍ 47 ሚሊዬን 039ሽ 745 ብር ገቢ መሰብሰብ ተችሏል፡፡

ዛሬም ላይ በህግ ማዕቀፎች መሠረት ልዩ ልዩ ማዕድናት እየተጠኑ ይገኛሉ ።

"ማዕድን አዲስ የንጋት ተስፋ ለዞናችን"!

Videos (show all)

በቢቡኝ ወረዳ የ2015  የት/ት አጀማመር በደመቀ ሁኔታ ተጀመረ።===================================መስከረም 09/2015 ዓ.ም (ቢቡኝ ኮሙኒኬሽን) በምስራቅ ጎጃም ዞን ...

Website