Addis Ketema Woreda 13 Prosperity Party-ብልጽግና

Prosperity

05/06/2022

የዛሬው መጨለም ለነገ ብሩህ ኢትዮጵያ ማዘጋጃ ነው።

Photos from Addis Ketema Woreda 13 Prosperity Party-ብልጽግና's post 05/06/2022

"ኢትዮጵያ ህልውናዋ እና ሉዓላዊነቷ አደጋ በተጋረጠበት ጊዜ ሁሉ ችግሮቿን ለመጋፈጥ ፖሊስ ግንባር ቀደም ተሰላፊ ነበር"
- የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

ኢትዮጵያ ህልውናዋ እና ሉዓላዊነቷ አደጋ በተጋረጠበት ጊዜ ሁሉ ፖሊስ ግንባር ቀደም ተሰላፊ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተናገሩ፡፡

በመስቀል አደባባይ በተካሄደው የፖሊስ አመራርና አባላት የምስጋናና የእውቅና አሰጣጥ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰላም ጊዜ በየሰፈሩ በጦርነት ጊዜ በየግንባሩ ሰላም ለማስጠበቅ ደፋ ቀና የሚለው የፌደራል ፖሊስ ከብዙ ድል በኋል ክብረ በአሉን ለማክበር እና ተቋማዊ ስራውን ለህዝብ ለማሳየት በቅቷል ብለዋል፡፡

"ለዚህም እንኳን ደስ አላችሁ ልንላቸው ይገባል" ነው ያሉት፡፡

ኢትዮጵያ ህልውናዋ እና ሉዓላዊነቷ ለአደጋ በተጋረጠበት ጊዜ ሁሉ ፖሊስ ግንባር ቀደም ተሰላፊ ነበር ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፡፡

ሰዎች ወደ መከራ እና ግጭት ሲገቡ የሰላምን ዋጋ ቢገነዘቡም ለእናንተ ተገቢውን ክብር እምብዛም ያልሰጠን ቢሆንም ሰላም የምናድረውና ሃገራችንን ለማበልፀግ የምንጥረው እናንተን ተማምነን ነው ብለዋል፡፡

እንዲሁም የፌደራል ፖሊስ እና የሰላምና ደህንነት ተቋማት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የሚያስፈልገው የኢትዮጵያ ብልፅግና መሰረቱ ሰላም ስለሆነ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡

የብርሃንን ጥቅም የምናውቀው በጨለማ እንደሆነ ሁሉ የህግ አስከባሪዎችን ሚና የምናውቀው ሰላም እና ደህንነታችን አደጋ ላይ ሲወድቅ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፥ የሰላምን ዋጋ ብንገነዘብና ብናውቅ ለአፍታም ቢሆን ወደ ግጭት አናመራም ብለዋል።

Photos from Addis Ketema Woreda 13 Prosperity Party-ብልጽግና's post 05/06/2022

አሸባሪው ሕወሓት ከፍቶት የነበረውን ጥቃት ለመመከት የፖሊስ ሰራዊት ከመከላከያ ሰራዊት ጋር በመቀናጀት አኩሪ ገድልና ጀግንነት ፈፅሟል

አሸባሪው ሕወሓት በሰሜን ኢትዮጵያ ከፍቶት የነበረውን ጥቃት ለመመከት በተደረጉ ዘመቻዎች የፖሊስ ሰራዊት ከመከላከያ ሰራዊት ጋር በመቀናጀት አኩሪ ገድልና ጀግንነት ፈፅሟል።

'በመስዋዕትነታችን የአገራችን አንድነትና የህዝብ ሰላም ይረጋገጣል' በሚል መሪ ሀሳብ የምስጋና እና ዕውቅና መርሐግብሩ እየተካሄደ ይገኛል።

የፌዴራል ፖሊስ ሰራዊት ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ጀኔራል ደመላሽ ገብረሚካኤል 80 ዓመት የሞላው የፖሊስ ተቋም በአገር ሕልውና ዘመቻዎች ከመከላከያና ከክልሎች ፀጥታ ኃይሎች ጋር በመቀናጀት አኩሪ ገድል ፈፅሟል።

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ባደረገው ሪፎርም በአፍሪካ ቀዳሚ የሚያደርገውን የቴክኖሎጂ ትጥቅ እየታጠቀ መሆኑን፣ የወንጀል ምርመራ አቅምና ብቃቱን ማሳደጉን ገልፀዋል።

በተቋሙ ተልዕኮ የላቀ ስራ አፈፃፀም የበለጠ ለማሳደግ ዕውቅና መስጠትና ምስጋና ማቅረብ የበለጠ ሞራል ስለሚፈጥር ዓመታዊ የፖሊስ ቀን መርሐ ግብሩ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።

በዓውደ ግንባሮች ጀግንነት የፈፀሙ ከፍተኛ መኮንኖች፣ የግልና የቡድን ጀግኖችና የስራ ክፍሎች የጀግናና የላቀ ጀግና ሜዳይ እና የሰርተፊኬት ዕውቅና የሚሰጣቸው ሲሆን በጦርነቱ የተሰው አባላትም ይመሰገናሉ ነው ያሉት።

የዛሬው መርሐ ግብር ማስጀመሪያ መሆኑን ገልፀው፤ በቀጣይም በክልል ጠቅላይ መምሪያዎቹ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

በመርሐ ግብሩ የኮሞሮስ፣ ታንዛኒያ፣ የጁቡቲ፣ የደቡብ ሱዳን፣ የኬንያ ፖሊስ ተቋማት እና የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና የፖሊስ ተቋማት መሪዎችም ተገኝተዋል።

ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ

#ኢዜአ

Photos from Addis Ketema Woreda 13 Prosperity Party-ብልጽግና's post 05/06/2022

የእሁድ ገበያ /sunday market/ በመዘጋጀት የተለያዩ የፍጆታ ምርቶችና ግብይት በስፋት በመካሄድ ላይ ይገኛል

በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 በሚኪሊላንድ ኮንደሚኒየም ግቢ የእሁድ ገበያ በመዘጋጀት የተለያዩ የፍጆታ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ በመሸጥ ላይ ይገኛሉ።
የእሁድ ገበያ ዋና አላማ ህብረተሰቡ የእረፍት ቀኑን በመጠቀም በተመጣጣኝ ዋጋ የፍጆታ ምርቶችን ከአቅራቢው እንዲያገኝ በማድረግ አሁን ያለው የኑሮ ውድነትን ለመቀነስና ገበያውን ለማረጋጋት ያለመ ነው።

05/06/2022

የነገዋ ኢትዮጵያ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ኃላፊነት ናት፤

Photos from Addis Ketema Woreda 13 Prosperity Party-ብልጽግና's post 05/06/2022

የፖሊስ አመራርና አባላት የምስጋናና የእውቅና አሰጣጥ መርኃ ግብር ቅድመ ዝግጅት!!
==========
በህግ ማስከበር ፣ በኅልውና እና በሕብረ ብሔራዊ አንድነት ዘመቻዎች ወቅት ጀግንነት ለፈፀሙና የላቀ የሥራ ውጤት ላስመዘገቡ የፖሊስ አመራርና አባላት የምስጋናና የእውቅና አሰጣጥ መርኃ ግብር በመስቀል አደባባይ ከደቂቃዎች በኋላ ይጀምራል።

በመስቀል አደባባይ በሚካሄድ መርኃ ግብር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በዕለቱም የፖሊስ አመራርና አባላት የምስጋናና እውቅና አሰጣጥ መርኃ ግብር የሚካሄድ ሲሆን የፓሊስ አባላት ሙያዊ ትርዒትም የመርኃ ግብሩ ማድመቂያ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።

05/06/2022

አዲስ አበባ!!
የኢትዮጵያ ብልፅግና ተምሳሌት!!
#ሰናይ ቀን

Photos from Addis Ketema Woreda 13 Prosperity Party-ብልጽግና's post 04/06/2022

የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የተፎካካሪ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አንደኛ መደበኛ ጉባኤውን በማካሄድ በሃገር ሰላምና በህዝብ ደህንነት ዙሪያ በጋራ ለመስራት የቃል ኪዳን ሰነድ ተፈራረሙ፡፡
*********

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የሚንቀሳቀሱ 13 ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች አንድ በሚያደርጋቸው ሃገራዊ ጉዳይ ላይ ለመመካከር ታሳቢ ያደረገ የጋራ ምክር ቤት በማቋቋም ወደ ስራ የገቡ ሲሆን በዛሬው እለትም ጉባኤ በማካሄድ በጋራ ለመስራት የቃል ኪዳን ሰነድ ተፈራርመዋል፡፡

በጉባኤው ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ብርሃኑ አበራ የሃገራችን መፃኢ እድል መልካም ለማድረግ መወያየት አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው ለህዝባችን ደህንነትና ለሃገራችን ሰላም እየተሰባሰቡ መነጋገሩ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልፀዋል፡፡

የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ሙሉጌታ አበበ በበኩላቸው የዛሬው መድረክ ዋነኛ አላማው ልዩነቶቻችን እንደተተበቁ ሆነው አንድ በሚያደርጉን የሃገር ሰላምና የህዝብ ደህንነት ላይ በትብብር መስራት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ነው ብለዋል፡፡

በተለይ በሃገራችን የተጀመረው ብሄራዊ ምክክር የተሳካ እንዲሆን እያንዳንዳችን የሚጠበቅብንን ሃላፊነት መወጣት ይተበቅብናል ያሉት ደግሞ የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ወ/ሮ ትዕግስት አሰፋ ናቸው ሲል የዘገበዉ የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ገፅ ነዉ!!

Photos from Addis Ketema Woreda 13 Prosperity Party-ብልጽግና's post 04/06/2022

የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ አስተዳደር የ60 ቀናት እቅድ የ1 ወር አፈፃፀም ምክትል ከንቲባ ጃንጥራር አባይ በተገኙበት እየተገመገመ ነው፡፡
******************************

በውይይቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አባይ፣ የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሽታዬ መሃመድ እንዲሁም ሌሎች የከተማ አስተዳደሩና ክፍለ ከተማ አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡

ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት አንፃር ተስፋ ሰጭ ጅምር መኖራቸው፣ ከጓሮ አትክልት አንፃር ሰፊ መነቃቃት መኖሩ፣ አዳዲስ ፕሮጀክቶችን በማስጀመር በአጭር ጊዜ አጠናቅቆ ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግ እየተደረገ ያለው ርብርብ እንዲሁም በማዕድ ማጋራትና በቤት እድሳት ዘርፎች እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ውጤት እየተመዘገቡባቸው ነው ተብሏል።

ስለሆነም ጥንካሬዎቻችንን በማስቀጠል ድክመቶቻችንን ደግሞ አርመን ለእቅዱ መሳካት በየደረጃው ያለው አመራር በቁርጠኝነት መስራት እንዳለበት ተገልጿል፡፡

Photos from Addis Ketema Woreda 13 Prosperity Party-ብልጽግና's post 04/06/2022

እኔ ለከተማዬ ፅዳትና ውበት ባለቤት ነኝ!
************ ***
12ኛው ሳምንት ብሎክን መሠረት ያደረገው ሁሉን አቀፍ የፅዳት ንቅናቄ መርሃግብር በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ወረዳ 13 እኔ ለከተማዬ ፅዳትና ውበት ባለቤት ነኝ በሚል መሪቃል ሚኪሊላንድ ኮንዶሚኒየም ግቢ በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ።
ሁላችንም አከባቢያችን እናፅዳ
ፅዳት የትውልድ ስልጣኔ ይሁን!

Photos from Addis Ketema Woreda 13 Prosperity Party-ብልጽግና's post 04/06/2022

የኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት እድሳትና የዓድዋ 00 ፕሮጀክት ጉብኝት አካሄዱ ።

ፕሮጀክቶቹን ያስጎበኙት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በጉብኝቱ ወቅት እንደተናገሩት ምክር ቤቱ የአዲስ አበባችን የለውጥ እንቅስቃሴን ጨምሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ የብልጽግና ጉዟችንን ለማሳለጥ በክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ ሃሳብ አፍላቂነትና የተግባር አመራር ሰጪነት በሁሉም ረገድ የምናከናውናቸውን የልማት ስራዎች እየተከታተለ እንዲደግፈንና ማስተካከል የሚጠበቅብንን ጉዳዮች በማመላከት የበኩሉን አሻራ እንዲያኖር እንፈልጋለን ብለዋል ።

ኢትዮጵያ ትበለጽጋለች ስንል በነዚህ ተጨባጭ የልማት ስራዎቻችን ነው ያሉት ከንቲባ አዳነች ሩቅ ማለም ወይንም አርቆ መመልከት የሚል ስያሜ የሰጠነው ከማዘጋጃ ቤት እስከ ለገሀር ያለው የጎዳና ማስዋብ ሥራ ፤በቀላሉ የምንጓዝበትን አዲስ እይታ ፍንትው አድርጎ እንዲያስመለክት ተደርጎ የተገነባ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

ከዚህ ቀደም የከተማችንን የወደፊት ዕድገትና ተስፋ የማይመጥን ነበር ያሉት ከንቲባዋ ዛሬ ላይ ከማዘጋጃ ቤት እስከ መስቀል አደባባይ ባከናወናቸው የአካባቢ ገጽታን የማስዋብ ስራዎች ዜጎች ሲያሻቸው የሚናፈሱበትና የሚያነቡበት ሥፍራ ማድረግ ችለናል ።

የዓድዋን ታሪክ እዚህ ቦታ ሕያው አድርገን ለማስቀም እንዲቻል ገድሉን ሕያው አድርገው የሚያሳዩ ማስረጃዎቻችንን የዘርፉ ሙሁራን እያሰባሰቡ ይገኛሉ ያሉት ከንቲባ አዳነች የፓርኩ ዲዛይን የአባቶቻችንን የዓድዋ ተራራ ውጣ ውረድ እንዲያሳይ ተደርጎ እየተገነባ ያለ መሆኑን አስታውቀዋል።

04/06/2022

#ብልፅግና ፓርቲ (prosperity party) እዉነተኛ የዴሞክራሲ ስርዓትን ለመገንባት የተመሰረተ ፓርቲ!!

Photos from Addis Ketema Woreda 13 Prosperity Party-ብልጽግና's post 03/06/2022

"ጥንካሬዎችን በማስቀጠል ክፍተቶችን በመሙላት ለተሻለ ውጤት እንሰራለን!"
************************
የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ በወረዳ 13 የዘጠኝ ወር የውስጠ ፓርቲ ስራዎች አፈጻጸም ምልከታ አደረገ።
ከክፍለ ከተማው የተመደቡ የሱፐርቪዥን ቡድን አባላት በተደረገው ምልከታ አጠቃላይ በፓርቲ ዘርፎች የተፈጸሙ ተግባራትን ተመልክተዋል።
በዚህም በድክመት የተመላከቱ ጉዳዮችን ማረም እንደሚገባ እና በጥንካሬ ያሉ ተግባራትም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለባቸው የሱፐርቪዥን ቡድኑ አባላት ገልጸዋል።
ሱፐርቪዥኑ የታዩ ጥንካሬዎችን ለማጠናከርና ክፍተቶችን ለቀጣይ ለማሻሻል የሚያግዝ ነው።

Photos from Addis Ketema Woreda 13 Prosperity Party-ብልጽግና's post 03/06/2022

"ሌብነት የገንዘብ ብቻ አይደለም፤ የስራ ሰዓት ስርቆትም ሌብነት ነው" - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ሌብነት የገንዘብ ብቻ አይደለም፤ የስራ ሰዓት ስርቆትም ሌብነት ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ተናገሩ።

ወ/ሮ አዳነች በዛሬው ዕለት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የጣት አሻራ ፊርማ ስርዓትን በይፋ አገልግሎት አስጀምረዋል።

ከንቲባዋ በዚሁ ወቅት የስራ ሰዓት ሌብነትን ለመከላከል የሚያስችለውን የጣት አሻራ ፊርማ ሁሉም የአስተዳደሩ ሰራተኞች እንዲጠቀሙበት አሳስበዋል።

03/06/2022

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በዛሬው እለት ሹመቶች ሰጥተዋል::

Photos from Addis Ketema Woreda 13 Prosperity Party-ብልጽግና's post 03/06/2022

"ትምህርት ቤቴን አፀዳለሁ :ፅዱና ውብ በሆነ ከተማ እኖራለሁ"
**************************
በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ወረዳ 13 በሚገኘው አስቴር ቤተ-ፍቅር ት/ቤት ሳምንታዊው የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ።
"ትምህርት ቤቴን አፀዳለሁ :ፅዱና ውብ በሆነ ከተማ እኖራለሁ" በሚል በተካሄደው የፅዳት ዘመቻ ላይ የክፍለ ከተማና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
ግንቦት 26-2014ዓ.ም

03/06/2022

9ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔ

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 9ኛ መደበኛ ስብሰባ በ2015 የፌዴራል መንግስት በጀት ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡

የፌዴራል መንግስት የ2015 በጀት ዓመት የበጀት ዝግጅት በአስር ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ የተቀመጡ ግቦችን ከማስፈጸም አኳያ፣ የሀገር ደህንነትን ከማስጠበቅ፣ የተፈናቀሉ ዜጎችን ከመርዳትና የወደሙ መሰረተ ልማቶችን እና አገልግሎቶችን መልሶ ከማቋቋም፣ ቀጣይ የማህበራዊና የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን አቅጣጫዎችና ዓላማዎችን ማሳካት ማእከል በማድረጋ እንዲሁም የ2015-2019 የመካከለኛ ዘመን የማክሮ ኢኮኖሚና የፊስካል ማዕቀፉን መሰረት በማድረግ ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው፡፡

በዚህም መሰረት ለ2015 በጀት ዓመት ለመደበኛ ወጪ ብር 347.12 ቢሊዮን፣ ለካፒታል ወጪ ብር 218.11 ቢሊዮን እንዲሁም ለክልል መንግሥታት ድጋፍ ብር 209.38 ቢሊዮን እና ለዘላቂ የልማት ግቦች ማስፈጸሚያ ብር 12.0 ቢሊዮን የተያዘ ሲሆን አጠቃላይ የፌዴራል መንግሥት የ2015 በጀት ብር 786.61 ቢሊዮን ሆኖ ቀርቧል፡፡ ከ2014 በጀት ዓመት በጀት ጋር ሲነጻጸር የብር 111.94 ቢሊዮን ወይም የ16.59 በመቶ እድገት አሳይቷል፡፡

ምክር ቤቱም በቀረበለት የፌዴራል መንግሥት የ2015 በጀት ላይ በስፋት ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል ይጸድቅ ዘንድ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

03/06/2022

"እኛ ብልፅግናዎች ብዝሃነትን የተቀበልን፣ በአግባቡ እውቅና ሰጥተን የምንከባከብ፣ ሀገራዊ አንድነታችንን ደግሞ አጥብቀን የያዝን ነን!!" - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

03/06/2022

ለታላቅ ሀገር ታላቅ ተቋም!

Photos from Addis Ketema Woreda 13 Prosperity Party-ብልጽግና's post 02/06/2022

እንደ አዲስ ከተማ ክ/ከተማ ሲካሄድ የነበረዉ የአጠቃላይ አመራር ስልጠና ተጠናቋል!!

በ2ኛ ዙር የአመራር ግንባታ ባለፉት 4 ቀናት 'አዲስ ፖለቲካዊ ዕይታ - አዲስ ሀገራዊ እምርታ!" በሚል ርዕስ ስር በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሲሰጥ የነበረዉ የአመራር ግንባታ መድረክ ተጠናቋል።

በግንባታ መድረኩ የተለያዩ ወቅታዊ ሃገር አቀፍ እና አለም አቀፍ የፖለቲካ ርዕዮተ አለም ዕሳቤዎች ላይ አመራሩ በስፋት የተወያየ ሲሆን የህዝቡን ተጠቃሚነት በማጉላት ሁለንተናዊ ሃገራዊ ብልፅግናችንን እዉን ለማድረግ ጠንካራ ተቋምና አመራር ሰጪነትን በማጎልበት ዉጤት ተኮር ተግባራትን በትኩረት መስራት እንደሚያስፈልግ የጋራ ተግባቦትን የሚፈጥር ገንቢ ሃሳቦች የተንሸራሸሩበት እና እዉቀት የተገኘባቸዉ መሆኑም ነዉ የተገለፀዉ
-------------------
ከታች የተቀመጡት በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት የህ/ግንኙነትና ሚድያ ዘርፍ የመረጃ ገፆች ናቸዉ:-
👉Facebook:- https://www.facebook.com/addisketemap
👉Telegram:- https://t.me/joinchat/GrVqkx4WRLD1iGqG
👉Instagram:- addisketemaprosperity
👉Twitter:- https://twitter.com/PartyAddis
👉YouTube:- https://youtu.be/desLbYiqQOw
መርጠዉን አብሮነትዎን ስለገለፁልን እናመሰግናለን
#የማዕድማጋራት #ብልፅግና #ህዝባዊ

Photos from Addis Ketema Woreda 13 Prosperity Party-ብልጽግና's post 02/06/2022

ቅድምያ ለህዝባችን ተጠቃሚነት መስጠትን አጠናክረን ቀጥለናል!!

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የሶስት ፕሮጀክቶች ግንባታ ተጀመረ፡፡
============
የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ አቶ ዣንጥራር አባይ እና የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ዋና ሥ/አስፈፃሚ ወ/ሮ ሽታዬ መሐመድ
* በወረዳ 10 እፎይታ ጤና ጣቢያ አነስተኛ ገቢ ላላቸው ዜጎች በኪራይ የሚተላለፍ ቤት ግንባታ
* በወረዳ 5 አበበ ቢቂላ ስታዲየም አጠገብ የምገባ ማዕከል እንዲሁም
*በወረዳ 13 አስተዳደር የዳቦ ፋብሪካ ግንባታን የመሰረት ድንጋይ በማስቀመጥ ግንባታውን አስጀምረዋል፡፡
*********************************************
በአስቸጋሪ ኑሮ ደረጃ ውስጥ የሚገኙ ዜጎቻችንን ተጠቃሚ ለማድረግ መንግስት ከሚያደርገው ጥረት በተጨማሪ ባለሃብቶችና የግል ኩባንያዎችን ማሳተፍ ተገቢ ነው ያሉት የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አባይ ዛሬ የተጀመሩ ፕሮጀክቶች በፍጥነት ተገንብተው ለተጠቃሚዎች እንዲተላለፉ በየቀኑ ክትትልና ድጋፍ እናደርጋለን ሲሉ ገልፀዋል፡፡

የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሽታዬ መሃመድ በበኩላቸው ዛሮ በሶስት ወረዳዎች ያስጀመርናቸው ፕሮጀክቶች የ60 ቀን ሰው ተኮር ፕሮጀክት አንዱ አካል መሆናቸውን ጠቅሰው ፕሮጀክቶቹን ገንብተው ለማስረከብ ቃል የገኑ ተቋማትን አመስግነዋል፡፡

- በወረዳ 10 የሚገነባውን የጋራ መኖሪያ ቤትን፡- ኢስት አፍሪካ ሆልዲንግ የግል ኩባንያ
- በወረዳ 5 በቀን 1500 ነዋሪዎችን የሚመግብ የምገባ ማዕከልን፡- የኢትዮጵያ ወጣት ዲያስፖራ ማህበር እንዲሁም
- በወረዳ 13 በቀን 1ሚሊዮን ዳቦ የሚያመርት የዳቦ ፋብሪካን፡- ጃፋር መሃመድ የተባሉ ግለሰብ ገንብተው ለማጠናቀቅ ተስማምተው ወደ ተግባር የገቡ መሆናቸውን አስታውቀዋል ሲል የዘገበዉ የክ/ከተማዉ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነዉ።

Photos from Addis Ketema Woreda 13 Prosperity Party-ብልጽግና's post 02/06/2022

"ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነች የምትገኘዉ ስራ አበረታች እና ለበርካታ የአፍሪካ ሀገራት ተሞክሮ መሆን የሚችል ተግባር ነዉ! የአፍሪካ ሀገራት ለግብርናው ዘርፍ ትኩረት ሰጥተው ከሰሩ የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባሻገር ምርታቸውን ለውጭ ገበያ በማቅረብ ኢኮኖሚያቸውን ሊያሻሽሉ እንደሚችሉ ይሄ ምርጥ ማሳያ ነዉ!!"

:- ኦባሳንጆ

Photos from Addis Ketema Woreda 13 Prosperity Party-ብልጽግና's post 02/06/2022

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ለሥራ ጉብኝት ባሌ ሮቤ ገባ

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ለሥራ ጉብኝት ባሌ ሮቤ ገብቷል።

በጉብኝቱ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በተጨማሪ የአፍሪካ ሕብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ፣ የቀድሞ ጠቅላይ ሚስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ የዓለም ባንክ የኢትዮጵያ ተወካይ ኡስማን ዲዮን እንዲሁም የፌደራል እና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተሳታፊ ናቸው።

የልዑካን ቡድኑ በባሌ ዞን እየተከናወኑ ያሉ የግብርና ሥራዎችን ተዘዋውሮ እንደሚመለከት ከኢቢሲ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

Photos from Addis Ketema Woreda 13 Prosperity Party-ብልጽግና's post 02/06/2022

ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከዑራኤል እስከ ፑሽኪን አደባባይ የሚከናወነውን የመንገድ ዳር ማስዋብ ስራ አስጀመሩ!

ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በቂርቆስ ክ/ከተማ የሚገኘውን ከዑራኤል እስከ ፑሽኪን ያለውን መንገድ በአረንጓዴ የማስዋብ ስራ በዛሬው ዕለት አስጀምረዋል

ፕሮጀክቱ በ60 ቀናት ከሚተገበሩ ሰው ተኮር ተግባራት መካከል አንዱ መሆኑን የተናገሩት ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደዚህ ዓይነት ተግባራት ከተማዋን በማስዋብና የዜጎችን አኗኗር በመቀየር ረገድ አስተዋጿቸው ከፍተኛ ነውና በሁሉም የከተማዋ አካባቢዎች በስፋት እየተሰሩ ነው ብለዋል።

ዜጎች በንፁህና አረንጓዴ ስፍራ የመኖር መብት እንዳላቸው የተናገሩት ከንቲባዋ የከተማ አስተዳደሩም የነዋሪዎቹን ፍላጎት ለማሟላት በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው አዲስ አበባን እንደስሟ አዲስ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት መላው የከተማው ነዋሪዎች፣ ባለሀብቶችና በጎ ፍቃደኞች ከአስተዳደሩ ጎን በመቆም የበኩላቸውን አሻራ እንዲያስቀምጡ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

እንደ ስሟ አዲስና ውብ እናደርጋታለን!!

02/06/2022

"ሰላምን ለማደፍረስ በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ እርምጃ ለመውሰድ መንግስት አስተማማኝ ቁመና እና ብቃት ላይ ይገኛል።" - የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

ሰላምን ለማደፍረስ በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ እርምጃ ለመውሰድ መንግስት አስተማማኝ ቁመና እና ብቃት ላይ እንደሚገኝ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ፡፡

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አግልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ባደረጉት ቆይታ÷ ሰላምን ለማደፍረስ በሚንቀሳቀስ አካል ላይ እርምጃ ለመውሰድ መንግስት ብቁ አቋም ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡

መንግስት በትላልቅ ከተሞች ከህብረተሰቡ ጋር በርካታ ውይይቶች ማድረጉን አውስተው÷ በውይይቶቹም በየአካባቢው የሚፈጸም የተደራጀ ዝርፊያ፣ ግድያ ፣ መፈናቀል እና ስጋት ህብረተሰቡን ከፍተኛ ስጋት ላይ እንደጣለው ሕዝቡ አንስቷል ብለዋል፡፡

እነዚህን ችግሮች መንግስት በአፋጣኝ መቅረፍ እንዳለበት ህብረተሰቡ በአንድ ድምጽ ሊባል በሚችል መልኩ አጽንኦት ሰጥቶ መግለጹንም ነው ዶክተር ለገሰ የተናገሩት ፡፡

ሕግ የማስከበር ሥራው ከህብረተሰቡ የቀረበ መሆኑን የገለጹት ዶክተር ለገሰ÷ ሥራውም ከፌደራል እስከ ክልል የተቀናጀ ሆኖ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን ጨምሮ በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች ሕግ የማስከበር እርምጃዎች እየተወሰዱ እንደሆነ ነው ያነሱት፡፡

በዋነኛነት በኦሮሚያ ክልል አሸበሪው ሸኔን ማዕከል በማድረግ ከዚሁ ቡድን ጋር ትስስር ያለው የአልሸባብ የሽብር ቡድን እንደዚሁም ቀደም ብሎ ሽብርተኛው ህወሓት የፈጠራቸው ትስስሮች እና ኦሮሚያ በሚጎራበትባቸው የደቡብ፣ የሲዳማ እና የሶማሊያ አካባቢዎች ላይ ሕግ የማስከበር እርምጃው እየተወሰዱ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በሁለተኛ ደረጃ÷ በአዲስ አበባ ከተማ በጣም በከፍተኛ ደረጃ የተደራጀ፣ ለውንብድና የተሰለፈ እና ለዝርፊያ የተዘጋጀብቻ ሳይሆን በተጨባጭ ሥራ ውስጥ የገባ ኃይል መኖሩን ነው ሚኒስትሩ የገለጹት፡፡

በአማራ ክልልም በተለያዩ አካባቢዎች በክልሉ ተከስቶ በነበረው እና የሽብር ቡድኑ ህወሓት በፈጠረው ጦርነት በተለያየ ምክንያት በነፍስ ግድያ ከእስር ቤት ያመለጡ፣ የመንግስትና የግለሰብን ሀብት ዘርፈው ፍርድ ቤት ውሳኔ የሰጠባቸው እንዲሁም በተለያየ የሽፍትነት ሥራ ላይ የተሰማሩ፥ ነገር ግን እራሳቸውን ፋኖ በሚል ስም በማደራጀት ከመንግስት የጸጥታ አካል ትይዩ የተደራጁ እና ለአካባቢው ሰላምና መረጋጋት እንቅፋት የሆኑ ኃይሎችን በመለየትና በእነዚህ ቡድኖች ላይ የሕግ ማስከበር ሥራ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በዋነኛነት ቁልፍ አካባቢዎች ተብለው የተለዩ ቦታዎች ላይ በተወሰደ ሕጋዊ እርምጃ አካባቢዎቹ ነፃ መውጣታቸውንና ህዝቡም መደጋጋት መቻሉን ነው ዶክተር ለገሰ ቱሉ ከፋና ጋር በነበራቸው ቆይታ የጠቆሙት።

በዚህም ህብረተሰቡ በተጋጋ ሁኔታ ወደ ሰላማዊ ሁኔታ ተመልሶ ምርት ወደማምረት ተግባሩ እንዲገባ ሁኔታዎች እየተመቻቹ መሆናቸውን ጠቁመው÷ የምርት ግብዓቶች እንዲቀርቡ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡

ሕግና ስርዓትን በማስከበር ህብረተሰቡን ወደ ምርት ተግባር የመመለስና የህብረተሰቡን አንገብጋቢ ችግሮች መፍታት የመጀመሪያውና ትልቁ የመንግስት ሥራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

“የእኛ መንግስት የሰላም፣ የዲሞክራሲ እና የልማት መንግስት ነው” ያሉት ዶክተር ለገሰ÷ ለእዚህም ሕግ ስርዓትን የማስከበር ሥራው ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር መሆኑን በአጽንኦት አብራርተዋል፡፡

በሌላ በኩል መንግስት፥ ኢትዮጵያን ከሚያፈርሱ፣ የኢትዮጵያን አንድነት ከማይቀበሉ፣ ጽንፈኝነት እና አክራሪነት ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲጎላ ከሚሰሩ ኃይሎች እንዲሁም ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን፣ ወንድማማችነትን፣ ከማይሰብኩ ኃይሎች ጋር አብሮና ተባብሮ የማይሠራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ኅብረ ብሔራዊ አንድነት፣ወንድማማችነት፣የሕዝቦች ብልጽግና እና ክብር ፣ የሀገር ሉዓላዊነት እና አንድነት በፍጹም ለድርድር የሚቀርቡ አይደሉም ነው ያሉት።

አሁን ባለንበት ሁኔታ የመንግስት አጠቃላይ የጸጥታ መዋቅር በውስጡ የሚታዩ ችግሮችን መቅረፍ ብቻ ሳይሆን÷ ከየትኛውም አካል የሚሰነዘር ማንኛውንም ዓይነት እርምጃ የመቀልበስ የተሟላ ቁመና እና ብቃት አለው ብለዋል፡፡

“በዚህም ህብረተሰባችን ምንም ዓይነት ጥርጣሬ ሊገባው አይገባም” ሲሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አግልግሎት ሚኒስትሩ ዶክተር ለገሰ ቱሉ አስገንዝበዋል፡፡

02/06/2022

ጠንካራ ፓርቲ!
ጠንካራ ሃገር!
ሁለንተናዊ ብልፅግና

01/06/2022

" #ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!"
- ጀኔራል አበባው ታደሰ

01/06/2022

በአብሮነት እና በአንድነት የተገነባ ማህበረሰብ የሀገሩን ሉዓላዊነት አያስደፍርም።
!!

01/06/2022

የምንገነባው የኢኮኖሚ ሥርዓት መገለጫዎች:-

👉አካታችነት - INCLSUIVE
👉ፕራግማቲክ - PRAGMATIC
👉ተራማጅ - PROGRESSIVE

31/05/2022

የብልፅግና ፓርቲ ዕሴቶች:-
🇪🇹ህብረ-ብሄራዊ አንድነትን ማረጋገጥ
🇪🇹የዜጎችን ክብር ማስጠበቅ
🇪🇹ሁለንተናዊ ነፃነትን ማረጋገጥ
🇪🇹የጋራ ብልፅግናን እዉን ማድረግ

31/05/2022

የከተማችንን ልማት ሁላችንም እንደግፍ!!
"ከተማችንን በጋራ እናልማ! የከተማችንን ልማት ሁላችንም እንደግፍ! ከተማችን ስትለማ ለሁላችንም በጎ የሆነ አስተዋጽኦ አላት። ከዛም አልፎ እንደ ሀገርም፤ እንደ አህጉርም ለአለም ተቋማት መቀመጫነትም የበለጠ ምቹ ትሆናለች።"

- ክብርት ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ

31/05/2022

የኢትዮጵያ መኮንን መሆን ስታስቡ ሶስት ነገሮች ሁል ጊዜም በህሊናቹ ሊታወሱ ይገባል።
1ኛ. ጀግንነት
2ኛ. አላማ
3ኛ. የማይነጥፍ እውቀት ነው።

- ዶ/ር ዐቢይ አህመድ
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የጦር ሃይሎች ጠቅላይ አዛዥ

31/05/2022

"በፓርቲያችን ጉባኤ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን ለማሳካት እና ለህዝባችን ቃል የገባነውን ለመፈፀም በከፍተኛ የሀላፊነት ስሜት እየተረባረብን እንገኛለን፡፡"

ክቡር አቶ አደም ፋራህ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት

30/05/2022

አዲስ ንጋት #ለኢትዮጵያ !
መልካም ቀን ይሁንልዎ!!!

30/05/2022

ፊትን ወደ ትናንት አዙሮ እንዴት ነው ወደ ነገ መጓዝ የሚቻለው? በእርግጥም ለጥያቄው መልስ መስጠት ያስፈልጋል፡፡በዚህ በሰለጠነ ዘመን አብሮነታችንን ማጎልበት ሲገባን የኋላውን እያነሳን ለፀብ ከተጋበዝን መደማመጥ አቅቶን አንዳችን በሌላችን ላይ ጣታችንን የምንቀስር ከሆነ በእርግጥስ የወደፊቱ እኛነታችን ዕጣ ፈንታ ምን ሊሆን ይችላል፡፡በአንድ ጉዳይ ላይ ተቸንክረን መቆም ለውጥ አያመጣም፡፡ለውጥ ማምጣት የሚቻለው በዛሬው ልፋታችንና ድካማችን ነገን አስበን ስንሰራ መሆኑን ማሰብ ተገቢ ነው፡፡

አቅጣጫችን ወደፊት ብቻ ነው፡፡ወደ ኋላ እየተመለከቱ እርስ በእርስ መነታረክ ዛሬያችንን ያባክንብናል፡፡የህዝብ ሰላምና የሀገር መረጋጋት ግድ የማይሰጣቸው አንዳንድ ጽንፍ የረገጡ ሀይሎች ወደፊት አስቦ ሀገርን ወደ ተሻለ ከፍታ ከማሻገር ይልቅ በትናንቱ አስተሳሰባቸው ተቸንክረው ይሄው ዛሬ ድረስ በዜጎች መካከል መቃቃርን በመፍጠር ላላስፈላጊ ግጭት፣ግድያና ሞት ምክንያቶች ሆነዋል፡፡

ሕዝባችን ለሀገራዊ አንድነት፣ ለሀገር ሰላም፣ ለልማት በጥቅሉ ለሁለንተናዊ ብልጽግና እያሳዬ ያለው ፍላጎት ከጊዚያዊ ግጭቶች ይበልጥ እንደሆነ እንጂ አንሶ አያውቅም፡፡ የኢትዮጵያዊያን የመልማት ፍላጎት ከማንኛውም ከፋፋይ አጀንዳ ይበልጣል፤ይሄ ሐቅ ነው፡፡ ይሄንን ለሺህ ዓመታት ተከባብሮና ተዋዶ የኖረን ጽኑና አስተዋይ ሕዝብ ይዘን ችግሮችን እንዳይደገሙ አድርገን እንደምንፈታቸው ብልጽግና እምነቱ ከፍ ያለ ነው።

Want your organization to be the top-listed Government Service in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Videos (show all)

Website

Address

Addis Ababa
Other Political Organizations in Addis Ababa (show all)
African Union African Union
Addis Abeba
Addis Ababa, 1111

A UNITED & STRONG AFRICA

Qabsoo Bilisummaa Qabsoo Bilisummaa
Finfinne
Addis Ababa, 2560

Injifannoon Kan Abbaa dhugaati

GMN Grand Media Network GMN Grand Media Network
Addis Ababa

Manegment

Bole Wereda 1 Prosperity Party ብልጽግና Bole Wereda 1 Prosperity Party ብልጽግና
Bole Michael
Addis Ababa, G.P.O

ይህ በቦሌ ክ/ከተማ ስር በሚገኘው በወረዳ 1 ብልጽግና ፓርቲ የ?

Anwar Tuti Anwar Tuti
Somaliya
Addis Ababa, HADLIYAAAA

Addis Ketema Woreda 6 Prosperity Party-ብልፅግና Addis Ketema Woreda 6 Prosperity Party-ብልፅግና
Addis Ketema
Addis Ababa

ለሁሉም ዜጋ ብልፅግናን ለማረጋጋጥ እንሰራለን

Free state movement for Addis ababa Free state movement for Addis ababa
Addis Ababa

Political

Imala Haqaa Imala Haqaa
Addis Ababa

Kaayyoon Kenya haqaa dhokate basne baketi mulisudhaa kanafu nu hordofun haqaa cina dhabachun eru nun

Paartii Badhaadhinaa Kutaa Magaalaa Araadaa Paartii Badhaadhinaa Kutaa Magaalaa Araadaa
Belay Zeleke Street, Pissa Road
Addis Ababa, 251,56

providing facts of prosperity party

Abdallaa  Zeenu Abafogi .Follow Abdallaa Zeenu Abafogi .Follow
Jiimmaa
Addis Ababa