ኬር አውድ ፕሬስ Kere-Awed Press
የጉራጌን ባህል የማስተዋወቂያ እና በተለያዩ ጠቃሚ ጉዳዮ ዙሪ
አዝናኝ ፈጠራ😁
በሠላም ዋሉ!
በጉራጌ ዞን ከ18ሺህ በላይ ህጻናት ለምግብ እጥረት መጋለጣቸው ተነገረ
።።።
የምግብ እጥረት ችግር የገጠማቸው ህጻናቱ በአሁኑ ሰዓት ለተለያዩ ተላላፊ በሽታዎች እየተጋለጡ ይገኛሉ ነው የተባለው።
የጉራጌ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ አየለ ፈቀደ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደተናገሩት፣ በዞኑ ለምግብ እጥረት ችግር የተጋለጡትን ህጻናት ልየታ በማድረግ ድጋፍ እየተደረገላቸው ይገኛል።
ከምግብ እጥረት ጋር በተያያዘም በአሁኑ ሰዓት 36 ህጻናት ለበሽታ መጋለጣቸውን ነው ሃላፊው የተናገሩት።
በዞኑ እየተስተዋሉ ያሉ የድንገተኛ ወረርሽኝ አደጋዎች በአፋጣኝ ለመከላከል ኮሚቴ ተቋቁሞ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
በምግብ እጥረት ምክንያት ትውልዱ የከፋ ችግር ላይ እንዳይወድቅ ሁሉም ድጋፍ እንዲያደርግም ጠይቀዋል።
በዞኑ በአሁን ሰዓት ድንገተኛ በሽታዎች፣ የኮሌራና የወባ በሽታዎች እና በስነ ምግብ እጥረት ሊከሰቱ የሚችሉ በሽታዎች ለመከላከል ሰፊ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ሃላፊው ተናግረዋል።
ምንጭ፡- ETHIO FM 107.8
ምድረ-ከብድ (ከባድ ስፍራ)
***
በየዓመቱ ጥቅምት 5 በርካታ ቁጥር ያላቸው የኦሮቶዶክስ ዕምነት ተከታዮች ወደ ምድረ ከብድ አቦ ገዳም መንፈሳዊ ጉዞ በማድረግ የአቡነ መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ ክብረ በዓል ይታደማሉ፡፡ ይህ ጥንታዊ ገዳም በጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ከአዲስ አበባ በ122 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ ከጢያ ትክል ድንጋይ መካነ ቅርስ አቅራቢያ ይገኛል፡፡ ጻድቁ አቡነ መንፈስ ቅዱስ በጾምና ፀሎት መንፈሳዊ ተጋድሎ አድርገው በዚሁ ገዳሙ እንዳረፉ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡
#በደምሰው በንቲ
የአረቅጥ ሀይቅ የቱሪስት መዳረሻነት የሚጨምር ሎጅ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
***
በጉራጌ ዞን አረቅጥ ሀይቅን ለመጎብኘት የሚመጡ ቱሪስቶችን አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ የተገነባው ሙሉወርቅ ሎጅ ተመረቀ።
ሎጁ 221 ሚሊዮን ብር ፈሰስ ተደርጎበታል።
በወረዳው ከ14 ሄክታር በላይ ሰብል በግሪሳ ወፍ መጠቃቱ ተገለፀ
****
የሶዶ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት እንዳስታወቀው በወረዳው በሰባት ቀበሌያት 14.5 ሄክታር ሰብል በግሪሳ ወፍ ተጠቅቷል።
''ሴራና'' ፊልም በሴራና አዳራሽ ሊመረቅ ነው
፡፡፡፡፡፡
የጉራጌ ባህል ላይ ትኩረቱን ያደረገው ''ሴራና'' የተሰኘው ፊልም በቡታጅራ ከተማ ሴራና አዳራሽ መስከረም 5 2016ዓ.ም ይመረቃል።
የፊልሙ ደራሲ ዘሪሁን ደነቀ እንደሆነ ከዘቢደር ቲዩብ ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል።
https://www.youtube.com/watch?v=nxlWASxJRRo
//ውሎ// "ከአሜሪካ ተመልሼ ሀገሬ ላይ ወጣት ገበሬ ሆኛለሁ" በረከት የምሩ /እሁድን በኢቢኤስ/ An infotainment program on Sunday afternoon with EBS’ own Asfaw Meshesha , Mekdes Debesay, Lula Gezu, Kalkidan Girma, Lea Samuel & Tinsae Berhane . It includ...
የእኛ ሰው በቡዳፔስት ሃንጋሪ
ተፈጥሮን የመንከባከብ ባህል ያለው ህዝብ!
Not only impressive, but it also highlights a dedication to environmental conservation.
አትሌት ጥላሁን ሀይሌ በቡዳፔስቱ የአትሌቲክስ ውድድር ያለመሰለፉ ብዙዎችን እያነጋገረ ነው
….
አትሌት ጥላሁን በ5 ሺ ሜትር ወንዶች ባስመዘገበው ምርጥ ሰአት ኢትዮጵያን እንዲወክል ወደ ሀንጋሪ ቡዳፔስት በውድድሩ እንዳይሳተፍ ተደርጓል።
በ10 ሺ ሜትር ተካፍሎ አራተኛ የወጣውን በሪሁ አረጋዊ በድጋሚ ለማሳተፍ ሲባል በ5 ሺ ሜትር ወንዶች ጥላሁን ሀይሌ እንዲቀነስ መደረጉ የስፖርት ቤተሰቡን አሳዝኗል።
ጎጎት ለጉራጌ አንድነት እና ፍትሕ ፓርቲ የጉራጌ የክልል አደረጃጀት ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጠው ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አቤቱታ አስገባ
የአቤቱታው ዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
ዳሙ ገነት
ሃምሳ ብር ህይወት ቀጠፈ
DW
ሃምሳ ብር ህይወት ቀጠፈ | DW | 24.07.2023 "ጥቂት እንደተጓዝን ተሸከርካሪውን በማቆም እኔም ሆንኩ ሌሎች መንገደኞች ደንግጠን ወረደን መሮጥ ጀመርን ፡፡ በዚህ ሁኔታ ውስጥ እሱን በጥይት መትተው ጣሉት"
ጉቦ የለመዱት ትራፊክ ፖሊሶች ነፍስ ወደ ማጥፋት ተሽጋገሩ
፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ባለፈው ዓርብ (ሐምሌ 14/2015 ዓ.ም) ተሳፋሪ ጭኖ ከአዲስ አበባ ወደ ቡታጅራ በመጓዝ ላይ እያለ በትራፊክ ፖሊስ አባላት የተጠየቀውን ጉቦ አልሰጥም በማለቱ የ33 ዓመቱ ሳሙኤል መረተ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የትራፊክ ፖሊስ አባላት በጥይት ተደብድቦ ተገደለ፡፡ የሟች ቤተሰቦች ፍትህ እየጠየቁ ነው፡፡
ዶቼቬለ እንደዘገበው ተጠርጣሪዎቹ በህግ ቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
የኦነግ ሽኔ ታጣቂዎች ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኘው የጉራጌ ዞን ውስጥ ሰርገው ገብተው ጥቃት መፈጸም እንደጀመሩ የመረጃ ምንጮቻችን ጠቁመዋል
፡፡፡፡፡፡፡፡
የኦነግ ሽኔ ታጣቂዎች በጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ሱተን እና አማውቴ ላሊጌ ተብለው የሚጠሩ አካባቢዎች እንዲሁም ወልቂጤ ሰርገው ገብተው የጸጥታ ኃይሎች ላይ እና ሰላማዊ ሰዎች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት መፈጸማቸው የመረጃ ምንጮቻችን ያመለክታሉ፡፡
የቀንድ ከብት የጫነ ተሽከርካሪ አስቁመው ተሽከርካሪውን እንዳቃጠሉና በተጠቀሱት አካባቢዎች ቅኝት ሲያደርግ የነበረ የጸጥታ ኃይል የጫን ተሽከርካሪ ላይም ጥቃት እንደፈጸሙ ተጠቁሞዋል፡፡ በጥቃቱ ምን ያህል ሰው እንደተጎዳ የመረጃ ምንጮቻችን ያሉት ነገር የለም፡፡
ታጣቂዎቹ በዞን ውስጥ መመሸጋቸውም ተገለጾአል፡፡
Photo credit: Ethiopia Insight
[የትራንስፖርት ታሪፍ ጉዳይ]
አንድ ሰው ከአዲስ አበባ ጢያ-ሱተን-ቡኢ-ኬላ መሄድ ቢፈልግ የቡታጅራን ሂሳብ ከፍሎ እንዲወርድ ይደረጋል።
ይህ አነስተኛ የገቢ አቅም ላለው ሰው ከባድ ነው።
ለ80 ኪሎ ሜትር 250 ብር?
ቢያንስ ቡኢ ወይ ኬላ ከተማ የራሳቸው ታሪፍ (መስፈርቱን የሚያሟሉ ይመስለኛል ) ሊወጣላቸው ይገባል።
: S**o Lema
``ባከቶ፣
ይበሎት ዬከቶ``
ማለት ምን ማለት ነው?
ት/ቤቱ ከ300ሺህ ብር በላይ ግምት ያላቸው የተለያዩ ማጣቀሻ መጻህፍት እና ኮምፒውተር ድጋፍ ተደረገለት
:::::::
የሶዶ ቡኢ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የቀድሞ ተማሪዎችና ወዳጆች ህብረት የአዲስ አበባ ኮሚቴ አባላት ከ100ሺህ ብር በላይ ግምት ያላቸው ማጣቀሻ መጻሕፍት እና በ200ሺህ ብር 15 DELL Core I3 ኮምፒውተር በተሰበሰበው ገንዘብ ግዢ በመፈጸም ለሶዶ ቡኢ ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት አስረከበዋል።
አማውቴ!
ታዳጊ ማዘጋጃ ቤት እንዲሆን ከተፈቀደ ወዲህ የልማት ጅምሮቹ የሚበረታታ ነው፡፡ ቦታው ለማታውቁት ዳዮ አቦ ቤተክርስቲያን አካባቢ ይገኛል፡፡ ከአዲስ አበባ በቀጥታ የህዝብ ትራንስፖርት የሚመደብለት በተሬ ከተማ ወይም በጢያ ከተማ በኩል ከአዲስ አበባ የሚያገናኝ መንገድ አለው፡፡
የክስታኒኛ መዝገበ-ቃላት መግዛት ይፈልጋሉ?!
።።።።።፡።።።
የክስታኒኛ ቋንቋን ለማሳደግ ከተሰሩ ስራዎች ውስጥ ዋነኛው የመዝገበ ቃላት ዝግጅት ነው። መዝገበ ቃላቱን ያልገዛችሁ በመግዛት ለቋንቋችን ዕድገት አስተዋጽኦ ብታደርጉ መልካም ነው። የት እንደሚሸጥ በ0938407116 ደውላችሁ መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ።
ደስታ ጋርመንት የሚባል ድርጅት 340 ሙሉ የስፓርት ትጥቅ ለጢያ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ድጋፍ አደረገ::
# Gordena Media
የዎስጠደ
ያማተ…
የዎስጠደ-የሙሽሪት ሽኝትና በቀጣይ ለትዳር የሚታጭ ሰው ማብሰሪያ ስነስርዓት “የዎስጠደ” በክስታኔ ጉራጌ ዘንድ የሠርግ ዕለት ሙሽሪት ከተሸኘች በኋላ የሚከናወን ስነስርዓት ነው፡፡ ሴቶች የዛፍ ቅጠል ይዘው “የዎሰጠደ ያማተ” እያሉ ጨፍረው ስጦታ የሚጠይቁበት .....
ስራ መስራት ብቻ ሳይሆን አካባቢያቸውንም መንከባከብ ያውቁበታል-My ጉራንስ ፒውፕል
የእርዳታ ጥሪ🚨
🇪🇹🇪🇹🇪🇹
ወ/ሮ ሉሊት ጌታሁን ትባላለች፤ በቡታጅራ ከተማ የሲቪል ሰርቪስ ፅ/ቤት ሰራተኛ ነች።
የማህፀን ካንሰር ስላጋጠማት በአስቸኳይ የህክምና ክትትል እንድታደርግ በሀኪሞቿ ተነግሯታል።
ወ/ሮ ሉሊት የህክምናውን ወጪ የመሸፈን አቅም ስለሌላት የእኛ ድጋፍ ትሻለች።
ሉሊትን መደገፍ ለምትፈልጉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት
1000056870095 ሉሊት ጌታሁን ወይም በእህቷ
የዳሽን ባንክ አካውንት 5026903600006 ጥበቧ ጌታሁን ገንዘብ ማስተላለፍ ትችላላችሁ።
ውቢቷ ቡታጅራ
ባህላዊ እና ዘመናዊ የቤት አሰራር የተጣመሩበት
ምድረከብድ
ምድረከብድ የተገኛችሁ የኬርአውድ ቤተሰቦች የዛሬው የአቡዬ ዓመታዊ ክብረበዓል የሚገልጹ ምስሎች ካላችሁ በአስተያየት መስጫው ላይ አስቀምጡልን።
https://www.youtube.com/watch?v=GOo4GeJH0iI
ጉዞ ወደ ክስታኔዎች መንደር አጭር ቆይታ በጉራጌዎች መንደር-መስቀል በጉራጌ -አዳብና
[እሰይ ነጋ]
ፕሮፌሰር ብርሀኑ ላይ ትንሽዬ ቂም ቋጥሬ ነበር፡፡ ይህም ከተለየ የፖለቲካ አመለካከት የመነጨ ወይም ከገዢው ፓርቲ ጋር አብሮ በመስራቱ ምክኒያት ሳይሆን፡~
ታስታውሱ እንደሆን ለውጡ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ወደ ሀገር ቤት ገብተው ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል እንዲያካሂዱ ሲፈቅድና ግንቦት ሰባትም በዚህ ጥሪ መሰረት ወደ ሀገር ቤት ሲገባ ብርሀኑ ነጋ በቦሌ አየር ማረፊያ በተደረገላቸው አቀባበል አንድ ልቤን የነካ ንግግር ለጋዜጠኞች ተናግረው ነበር፡፡ “ከዚህ በኋላ በሰፊው መስራት የምፈልገው በወጣቱ ላይ ነው፡፡ ወጣቱ ሞራሉ ላሽቋል፣ ስነምግባር ጠፍቷል፣ የሀገር ፍቅር የሌለው ሀላፊነት የማይሰማው ሆኗል፡፡ ስለዚህ በወጣቱ ላይ አተኩሬ መስራት እፈልጋለሁ” ሲሉ ተናግረው ነበር፡፡
እውነት ልንገራችሁ በዚያ በፖለቲካ ወሬዎች ብቻ በተጨናነቀ ወቅት፣ በዚያ በዘርና በብሄር ክፍፍሉ እንደ ብረት ግሎ መቅለጥ በጀመረበት ወቅት ብርሀኑ ነጋ አንድ የሀገር ስብራት አንጓ መዞ “ወጣቱን ማከም እፈልጋለሁ” ብሎ ሲናገር ፍጹም የተለየ ስሜት ነበር የተሰማኝ፡፡ ስለ ክልል፣ ስለ ብሄር፣ ስለ መገንጠል፣ ስለ ምርጫና ስልጣን እየተፎከረ ወደ ሀገር በሚገባበት በዚያ የእብጠት ዘመን ይህን ታላቅ አላማ አንግቤ ነው ወደ ሀገር የተመለስኩት ሲል ስሰማው ነፍሴ በሀሴት ለምልማ ነበር፡፡
ይሁንና ቀን እያለፈ ቀን እየተተካ ሲሄድ ፕሮፌሰር ብርሀኑን በገባው ቃል ዙሪያ ፈልጌ አጣሁት፡፡ ይህንንም ይዤ በየጊዜው እወቅሰው ገባሁ፡፡ ..........
እነሆ ዘንድሮ ቃሉን በተግባር ተርጉሞ አየሁት፡፡ “ሌብነት እስካልተያዙ ድረስ ስራ ነው” የሚል መሪ በነበረባት ሀገር ተወልደው ያደጉ ልጆች ስርቆትን እንደ ስራ እያሰቡ የፈተናን ስርቆት እንደ መለማመጃ ቆጥረውት ያዳበሩትን የሞራል ዝቅጠት አፈራርሶ ልጆች በራሳቸው ተማምነው መስራትን፣ አውቆ መፈተንን፣ በእውቀት መመዘንን፣ በሁለት እግር መቆምን እንዲያውቁ ለማስቻል ብዙ የተባለለትን የብሄራዊ ፈተና አዘምኖ ለትውልዱ ደርሶ አየሁ፡፡ እነሆ ብርሀኑ ነጋ ! እሰይ ነጋ!!!
Tadele
Click here to claim your Sponsored Listing.
Videos (show all)
Category
Website
Address
Addis Ababa
Addis Ababa, 1874
Kida Digital Solutions is a full-service digital marketing agency.
Addis Ababa
welcome to our official page. In this page you will learn more about content marketing and advertisi
Bole
Addis Ababa
ሽያጭዎን ለማሳደግ ከእኛ ጋር ይስሩ፡፡ ለመሸጥ የፈለጉትን እቃ ወይም አገልግልዎት እኛ ለትክክለኛ ደምበኛ በተመጣጣኝ ዋጋ እናስተዋዉቅልዎታለን ፡፡
Addis Ababa
Social media is the ultimate equalizer. It gives a voice and a platform to anyone willing to engage. Amy Jo Martin Amy Jo Martin
Addis Ababa
Addis Ababa, 1000
A leading digital marketing agency in Ethiopia, dedicated to helping small businesses and individuals
Addis Ababa
Social Media Marketing Agency -Facebook,IG Ads -Youtube,tiktok ads -Social media automation -web devt