የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር /ኢመማ/ Ethiopian Teachers Association /EI/

BETTER EDUCATION FOR BETTER WORLD!

08/10/2024

እንኳን ለአለማቀፉ የመምህራን ቀን October 5 አደረሳችሁ!!

October 5 በመላው አለም በመምህራንና ሙያው ዙሪያ የሚያጠነጥኑ መርሀ_ግብሮችን በማካሄድና ለመምህራን እውቅናና ሽልማት በመስጠት ይከበራል።

የዘንድሮው ማለትም 2024 የመምህራን ቀን የሚከበረው "VALUING TEACHER VOICES: TOWARDSA NEW SOCIAL CONTRACT FOR EDUCATION" በሚል መሪ ቃል ነው።

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር በአሉን ከመስከረም 30-ጥቅምት 1/2017 ዓ.ም ድረስ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በሚገኙበት ጥናትና ምርምር ኮንፈረንስን ጨምሮ በልዩ ልዩ መርሀ_ግብሮች ከድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር ያከብራል።

27/09/2024
17/09/2024

የሀዘን መግለጫ

በሕዝብ ተሳትፎ፣ በአካዳሚክ ውጤታቸው እና በምርምር መሪነት ብዙ ዓለም እና አገር አቀፍ ሽልማቶች እና የወርቅ ሜዳሊያዎች ባለቤት የነበሩት ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ከዚህ ዓለም በሞት በመለየታቸው የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር በመላው የኢትዮጵያ መምህራን ስም ጥልቅ ሃዘኑን ይገልፃል።

የደርግ መንግሥት ወድቆ በኢህአዴግ አስተባባሪነት በተቋቋመው የሽግግር መንግሥት ወቅት የኢፌዴሪ ትምህርት ሚንስቴር ም/ሚንስትር የነበሩት ፕሮፌሰር በየነ ኢመማ ዳግም እንዲደራጅ ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል።

በወቅቱ በማህበሩ ውስጥ ስለነበረው ክፍፍል የማህበራችን የ70 ዓመት ታሪክ ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀው መፅሐፍ ውስጥ በቃለ_መጠይቅ እውነታውን ተናግረው በፅሁፍ ሰፍሯል። ለማህበሩ ስላበረከቱት አስተዋጾኦ ኢመማ ዘወትር ሲያስታውሳቸው ይኖራል።

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለሥራ ባልደረቦቻቸው መጽናናትን ይመኛል።

Photos from የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር /ኢመማ/ Ethiopian Teachers Association /EI/'s post 16/09/2024

በትምህርት ዓለም አቀፍ አፍሪካ ለምስራቅ አፍሪካ መምህራን ማህበር (ዞን አምስት) ስርዓተ ጾታ ተጠሪዎች የተዘጋጀው የ3 ቀናት የአቅም ግንባታ ስልጠና (ከመስከረም 6-8/2017ዓ.ም) በኬንያ ናይሮቢ ሳፋሪ ክለብ ሆቴል ተጀምሯል።

ስልጠናው በአፍሪካ እና ዓለም አቀፍ ጉባኤ የተወሰኑ እና ከስምምነት የተደረሰባቸው ጉዳዮች እንዲሁም በስራ ቦታ የሚደርስ ጥቃትን ለመከላከል በዓለም ሥራ ድርጅት በፀደቀው ኮንቬንሽን 190 ላይ ማህበራት እያከናወኑ ባሉት ተግባር ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል።

Photos from የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር /ኢመማ/ Ethiopian Teachers Association /EI/'s post 01/09/2024

ከነሐሴ 23-25/2016 ዓ/ም በአዲስ አበባ ስካሄድ የነበረው 33ኛ ሀገር አቀፍ የትምህርት ጉባኤ ተጠናቀቀ።

ጉባኤው ነሐሴ 23/2016 ዓ.ም በሁለቱ ዘርፎች ማለትም በሲቪል ሰርቪስ ዩንቨርስቲ የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ እና በኢንተርኮንትነንታል አዲስ በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የተናጠል ውይይት ተጀምሯል።

የኢመማ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ተከፋፍለው በሁለቱም ዘርፎች ላይ የተሳተፉ ከመሆኑም በላይ የየክልል መምህራን ማህበራት ኘሬዝዳንቶች ተሳትፈዋል።

የሁለቱ ዘርፎች የጋራ መድረክ ከነሐሴ 24-25/2016 ዓ.ም የተካሄደ ሲሆን የት/ት ሴክተር ዓመታዊ አፈጻጸም ቀርቦ ተመክሮበታል።

የኢመማ የትምህርት ሥራ እንቅስቃሴ እና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች እንዲሁም በቀጣይ ትኩረት ሊደረግባቸው የሚገቡ ጉዳዮች ትኩረት እንዲደረግባቸው በአጽንኦት ቀርቧል።

በአጠቃላይ ጉባኤው የማህበሩ ንቁ ተሳትፎ የጎላበትና የተሳካ መድረክ ነበር።

Photos from የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር /ኢመማ/ Ethiopian Teachers Association /EI/'s post 24/08/2024

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ስራ አስፈፃሚዎች እና ሰራተኞች "የምትተክል ሀገር የሚያፀና ትውልድ!" በሚል መሪ ቃል የሚከናወነውን የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር በሸገር ከተማ አስተዳደር ፉሪ ክ/ከተማ በገዳ ፋጂ ወረዳ በመገኘት አከናወኑ።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ለመላው ኢትዮጵያውያን "600 ሚሊዮን ችግኝ በአንድ ጀምበር" የመትከል መርሀ-ግብር ያስተላለፉትን ሀገራዊ ጥሪ በመቀበል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መምህራን ማህበር እና የክፍለ ከተማ የማህበሩ ስራ አስፈፃሚዎች፣ መምህራንና የወላጅ ተማሪ መምህር ህብረት አመራሮች የተሳተፉበት የአረንጓዴ አሻራ የማኖር ፕሮግራም ላይ ተሳትፈዋል።

ይህንን መርሀ-ግብር ያዘጋጀውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መምህራን ማህበርን በመላው መምህራን ስም የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር አመስግኗል።

19/08/2024

ፈትህ ለተማሪና ሕፃን ሄቨን !

ሰሞኑን በባህርዳር ከተማ በአንዲት ከ2ኛ ክፍል ወደ 3ኛ ክፍል ተዛውራ አስነዋሪ ድርጊት ተፈጽሞባት ሕይወቷ ባለፈ ህፃን አሳዛኝ ጉዳይ ሰምተናል።

እንዲህ ዐይነቱ አስነዋሪ ድርጊት የሴት ተማሪዎች ተሳትፎ ላይ እንቅፋት ከመሆኑም በላይ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት በመሆኑ የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር እያወገዘ ማስተማሪያ በሚሆን መልኩ ፍትህ እንዲሰጥ እየጠየቅን ለቤተሰቦቿና ወዳጅ ዘመዶቿ መጽናናትን እንመኛለን።

10/08/2024

አንኳን ደስ አላችሁ!

አትሌት ታምራት ቶላ 2:06:26 በሆነ ሰዓት የኦሎምፒክ ክብረወሰንን አሻሽሎ በ33ኛው የፓሪስ ኦሎምፒክ ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ በማስገኘቱ የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር እንኳን ደስ አላችሁ ይላል።

Photos from የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር /ኢመማ/ Ethiopian Teachers Association /EI/'s post 03/08/2024

በቅድመ ጉባኤ መድረክ በከፍተኛ ትምህርት፣ በነባር ሕዝቦች የትምህርት አቅርቦት መብትና በሴት መምህራን ኮከስ የተጀመረውና ከሐምሌ 22-26/2016 ዓ/ም በአርጀንቲና ቦኖስ አይረስ ሲካሄድ የነበረው 10ኛው የትምህርት ዓለምአቀፍ ጉባኤ(Education International) በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።

ጉባኤው በበርከታ ጉዳዮች ላይ ለአብነት በመምህራን የኑሮ ሁኔታና ሙያውን እያጋጠመ ባለው ፈተና እንዲሁም ሙያውን አስመልክቶ በተባበሩት መንግሥታት በተቋቋመው የከፍተኛ ፓናል ምክረ-ሀሳቦች፣ በትምህርት ጥራትና ፋይናንስ አቅርቦት፣ በከፍተኛ ትምህርት መምህራን መብትና አካዳሚ ነጻነት፣ በዓለም እየተካሄዱ ባሉ ጦርነቶችና ግጭቶች ምክንያት እየደረሱ ባሉ ሁለንተናዊ ጉዳቶች፣ በሴት መምህራን መብትና ተሳትፎ፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎትና ተያያዥ ጉዳዮች፣ በአየር ንብረት ለውጥ፣ በዴሞክራሲ መብቶች ላይ እየደረሰ ባለው ጥቃት ...ወዘተ ጉዳዮች ላይ መክሮ አቋም ወስዷል፤ አቅጣጫም አስቀምጧል።

በጉባኤው ላይ ከተለያዩ የዓለም ሀገሮች የተወጣጡ ከ1200 በላይ ተሳታፊዎች የተገኙ ሲሆን ከሀገራችን ኢትዮጵያ የኢመማ ኘሬዝደንት ዶ/ር ዮሐንስ በንቲ፣ የኢመማ ም/ኘሬዝደንት አቶ ሽመልስ አበበ፣ የኢመማ ም/ዋና ፀሐፊና የሥርዓተ ፆታ ተጠሪ ወ/ሮ ደስታዬ ታደሰና ከአዲስ አበባ የማህበሩ ኘሬዝደንት አቶ ድንቃለም ቶለሣ ተሳትፈዋል።

በጉባኤው ላይ በርካታ ዓለምአቀፍ ተቋማት በአካል ተገኝተው ወይም በርቀት በቪዲዮ የድጋፍና የአጋርነት መልዕክት አስተላልፈዋል።

በተደረገው ምርጫም የማህበራችን ኘሬዝዳንት ዳግም የትምህርት ዓለምአቀፍ ሥራ አስፈፃሚ ቦርድ አባል ሆነው ተመርጠዋል። ይህ ለማህበራችንም ሆነ ለሀገራችን ከፍተኛ ጠቀሜታና ትርጉም እንዳለው ይታመናል።

Photos from የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር /ኢመማ/ Ethiopian Teachers Association /EI/'s post 31/07/2024

የትምህርት ዓለም አቀፍ 10ኛ (The 10th Education International World Congress)ጉባኤ በአርጄንቲና ቦነሳይረስ ይካሄዳል።

ጉባኤው ሰኞ July 29/2024 በታላቅ ድምቀት የተከፈተ ሲሆን በ27/7/2024 የነባር ህዝቦች የትምህርት መብት ላይ ውይይት ተደርጎ በጉባኤው እንዲፀድቁ የውሳኔ መነሻ ሃሳቦች ከተለያዩ አገራት ቀርቧል።

በራስ ቋንቋ አለመማር፣ስርዓተ ትምህርቱ የነባሩን ሕዝብ ባህልና ወግ አሳድጎ ለትውልድ ማስተላለፍ አለመቻልና በበቂ በጀት ያልተደገፈ መሆኑ እንደ ተግዳሮት ተነስቷል።

23/07/2024

የሀዘን መግለጫ

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በተከሰተው የመሬት ናዳ በደረሰው የዜጎቻችን ሞት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልፃል።

ጉዳት ለደረሰባቸው ቤተሰቦችም መጽናናትን ይመኛል።

ሀምሌ 16/2016 ዓ.ም

Photos from የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር /ኢመማ/ Ethiopian Teachers Association /EI/'s post 22/07/2024

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር የ2ኛው የአቢሲኒያ ኢንዱስትሪ ሽልማት የወርቅ ደረጃ ተሸላሚ ሆነ።

ማህበራችን ላለፉት 76 አመታት በከፍተኛ ውጣ ውረድ ውስጥ ሆኖ ላበረከተው አስተዋፅኦ ለተቋሙ የወርቅ ዋንጫ፣ ለዶ/ር ዮሐንስ በንቲ የከፍተኛ አመራር የላቀ አፈፃፀም የኮርዶን ኒሻን እና የክብር ዲፕሎማ ፣ ለሁለት መካከለኛ አመራሮች የከፍተኛ አፈፃፀም የክብር ኒሻንና እና ሰርተፍኬት እንዲሁም ለሌሎች 10 ሰራተኞች የምርጥ አፈፃፀም የወርቅ ሜዳሊያና ሰርተፍኬት ተሸልመዋል።

የሽልማት ስነስርአቱ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን እና በሀገሬ ቴሌቪዥን የቀጥታ ስርጭት ያገኘና እጅግ ደማቅ የነበረ ሲሆን የቀድሞ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንትና የአቢሲኒያ የኢንዱስትሪ ሽልማት ድርጅት የበላይ ጠባቂ ዶ/ር ሙላቱ ተሾመን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች የተገኙበት ነበር።

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ባገኘው በዚህ ሽልማት የተሰማውን ደስታ እየገለፀ ለመላው አባሎቻችን እና አጋሮቻችን እንኳን ደስ አላችሁ እያለ የማህበሩንና የመምህራንን የሀገር ባለውለታነት ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሽልማት ያበቃውን የአቢሲንያ የኢንዱስትሪ ሽልማት ድርጅት ሊያመሰግን ይወዳል።

08/07/2024

የአዲስ ዘመን ጋዜጣ የሰኔ 30/2016 ዓ.ም ዕትም በርዕሰ አንቀፅ አምዱ "ክብር ለመምህራን !!" በሚል ርዕስ የሚከተለውን ፅሁፍ ይዞ ወጥቷል...

08/07/2024

ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ስለ መምህራን ያደረጉትን ንግግር አስመልክቶ የማህበራችንን አሰተያየት አዲስ ዘመን ጋዜጣ በሰኔ 29/2016 ዓ.ም ዕትም ...

04/07/2024

ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር አብይ አህመድ በዛሬው የፓርላማ ውሏቸው
"ኢትዮጵያ የቆመችው በአርሶ አደር፣ ወታደር እና መምህራን ውለታ ነው" ብለዋል።

የአርሶ አደሩን ሕይወትም ለማሻሻል በርካታ ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑን ተናግረዋል ፡፡

ነገር ግን መምህር እና ወታደር ለሀገር ከሚከፍሉት ውለታ ባሻገር የሚከፈላቸው ዋጋ እዚህ ግባ የሚባል አይደለም በማለት ተናግረዋል፡፡

በቀጣይ የመምህራንን ሕይወት ለማሻሻል የሚረዱ ሥራዎች እየተሠሩ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሚያበረክቱት አስተዋጽኦ ግን ኢትዮጵያ ታመሠግናቸዋለች ብለዋል፡፡

Photos from የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር /ኢመማ/ Ethiopian Teachers Association /EI/'s post 27/06/2024

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር GO PUBLIC FUND EDUCATION!! የተሰኘውን አለማቀፍ ዘመቻ በአዲስ አበባ ኢንተርኮንቲኔንታል አዲስ ሆቴል ሰኔ 20/2016 ዓ.ም በድምቀት አስጀመረ።

የዘመቻው ዋና አላማ መንግስታት ለትምህርት ትኩረት ማድረግ እንደሚገባቸው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እ.አ.አ. መስከረም 2022 ባደረገው ጉበኤ ያስቀመጠውን አቅጣጫ ተከትሎ በሀገራችንም ይሄው ተግባራዊ እንዲሆን መልዕክት ለማስተላለፍ ነው።

በዚህ ዘመቻ የማስጀመሪያ ስነ_ስርአት ላይ የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴን ጨምሮ ከጠቅላይ ሚንስትር ፅ/ቤት፣ እና ከተለያዩ የሚንስቴር መስሪያ ቤቶች ተወካዮች ፣ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ መምህራን፣ ተማሪዎች፣ የተማሪ ወላጆች ማህበር፣ የልማት አጋር ድርጅቶች፣ የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች ፣ የትምህርት አለማቀፍ አፍሪካ አህጉር ዳይሬክተር፣ የማእከላዊ ፅ/ቤቱ ስራ አስፈፃሚዎችን ጨምሮ የሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የማህበር አመራሮችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው የትምህርት ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

ይህ የህዝብ ፈንድ ለትምህርት ዘመቻ ከ 11ኛው የትምህርት ጥራት ኮንፈረንስ ጋር አብሮ የተካሄደ ሲሆን ሦስት የምርምር ስራዎች ቀርበው ከፍተኛ ውይይት ተካሂዶባቸዋል።

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ይህ በአይነቱ የተለየ ዘመቻ እንዲሳካ እገዛ ላደረጉት ሁሉ በተለይም ዘመቻውን በገንዘብ የደገፈውን ትምህርት አለማቀፍን Education International ሊያመሰግን ይወዳል።

GO PUBLIC FUND EDUCATION !!

የህዝብ ፈንድ ለትምህርት!!

26/06/2024

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ከሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳዳሮች ለተውጣጡ የማህበር አመራሮች እና ለማዕከላዊ ፅ/ቤቱ ስራ አስፈፃሚዎች በተግባቦትና ዘመቻ ክህሎት ( communication and campaign skills) ዙሪያ በአዲስአበባ ኢንተርኮንቲኔንታል ሆተል ስልጠና ሰጠ።

ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የማህበሩ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዮሐንስ በንቲ ሲሆኑ የስልጠናው ዋና አላማ በነገው ዕለት ማለትም ሰኔ 20/2016 ዓ.ም ቅድሚያ ትምህርት GO PUBLIC FUND EDUCATION !! በሚል መሪ ቃል ለሚደረገው የትምህርት ንቅናቄ እንዲያግዝ ነው ብለዋል።

ስልጠናውን የሰጡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህርና ከፍተኛ ተመራማሪና በኢትዮጵያ መምህራን ማህበር የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች መምህራን ማህበር ፕሬዘዳንት የሆኑት ዶ/ር በፍቃዱ ዘለቀ ናቸው። ስልጠናው አሳታፊ የነበረ ሲሆን ከተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ቀርበዉ ዉይይት ከተደረገባቸው በኋላ በነገው ዕለት ሰለሚደረገው ዘመቻ ተግባራዊ ልምምድ በማድረግ ተጠናቋል።

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ይህንን ስልጠና በገንዘብ ድጋፍ ያደረገውን የትምህርት አለማቀፍ Education International ፣ ስልጠናውን ላስተባበሩት የማህበሩ ስራ አስፈፃሚዎች እና ስልጠናውን ለሰጡት ዶ/ር በፍቃዱ ዘለቀ ምስጋናውን ያቀርባል።

GO PUBLIC FUND EDUCATION !!
ቅድሚያ ትምህርት!!

16/06/2024

ለእስልምና ኃይማኖት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለኢድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል አደረሳችሁ !!
የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር

19/05/2024

በተለያዩ ምክንያቶች የሚከሰቱ የመምህራን ዕጥረትን ለመቅረፍ ተተኪ መምህራንን የማፍራት ስራው ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተገለፀ።

12/05/2024

የመቀሌ ከተማ አስተዳደር ትናንት ለ19 የመምህራን ማኅበራት የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታዎችን እንደሰጠ የክልሉ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

የከተማዋ አስተዳደር ትናንት በእጣ ባከፋፈላቸው የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታዎች፣ ከ350 በላይ መምህራን ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተገልጿል።

የከተማዋ አስተዳደር ከትግራዩ ጦርነት በፊት ለመምህራን ማኅበራት የቤት መስሪያ ቦታዎችን የሰጠ ሲሆን፣ ትናንት መሬት የተረከቡት በጦርነቱ ምክንያት ሳይረከቡ የቀሩ ማኅበራት እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል።

Photos from የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር /ኢመማ/ Ethiopian Teachers Association /EI/'s post 18/04/2024

የትግራይ ክልል መምህራን ማህበር በአክሱም ከተማ ያካሄደውን 33ኛ መደበኛ የምክር ቤት ስብሰባውን ባለ 11 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቀቀ።

በኢትዮጵያ መምህራን ማህበር የትግራይ ክልል መምህራን ማህበር 33ኛ መደበኛ ምክር ቤት ስብሰባውን ከሁሉም ወረዳዎች የምክር ቤት አባላት፣ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ኪሮስ ግዑሽ፣ የክልሉ ት/ቢሮ የመምህራን ልማት ዴስክ ተወካዮችና የኢመማ ተወካዮች በተገኙበት በአክሱም ከተማ ሮማዳዕ ሆቴል ሚያዚያ 6/2016 ዓ.ም አካሂዷል። ምክር ቤቱ የ2015 ዓ.ም የስአኮ እና ኦዲት እቅድ አፈፃፀም ገምግሟል።

የትግራይ ክልል ላለፉት ሶስት ዓመታት በጦርነት ውስጥ በነበረበት ወቅት በመምህራን እና በክልሉ ትምህርት ላይ የደረሰው ጉዳት ላይ ተውያይተዋል። በተለዩ አጀንዳዎችም ማለትም:-
1/በማህበሩና አባላት መካከል ያለው ግንኙነት
2/በቀጣይ ከኢመማ ጋር ያላቸው ግንኙነት፣ ፈሰስ አሰባሰብና አላላክና የህንፃ ግንባታ
3/የክልሉ አጠቃላይ ትምህርት ያለበት ሁኔታና የትምህርት ጥራት፣ ትምህርት ቤቶችን መልሶ ስለማደራጀትና ወደ ትምህርት ገበታ ያልተመለሱ ተማሪዎችን መመለስ
4/መሪ ተመሪነትን በተመለከተ በኢመማ መተዳደሪያ ላይ የተገለፁትን ማክበር
5/ከጦርነቱ በኋላ ወደ ስራ ከተመለሱበት ጊዜ ጀምሮ ያልተከፈለ የ5 ወር ደመወዝ እና
6/ማህበሩን ለረጅም ዓመት ያገለገሉና በጡረታ ለተሰናበቱ እውቅና መስጠት ነበር፤ አጀንዳዎቹም በተያዘላቸው ፕሮግራም ውይይት ተደርጎባቸው ባለ 11 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል።

Want your organization to be the top-listed Non Profit Organization in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Videos (show all)

በተለያዩ ምክንያቶች የሚከሰቱ የመምህራን ዕጥረትን ለመቅረፍ ተተኪ መምህራንን የማፍራት ስራው ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተገለፀ።
"የዓለም መምህራን ቀን”፣ በየዓመቱ በአውሮፓውያኑ ጥቅምት 5 ቀን ተከብሮ ይውላል። የተመድ የትምህርት የሳይንስ እና ባህል ድርጅት(UNESCO) በተደነገገው በዚህ ቀን፣ የመምህራን አስተዋፅኦ...
የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዮሐንስ በንቲ በትምህርት ጥራት ዙሪያ ከኢቲቪ ዳጉ ፕሮግራም ጋር ቆይታ አድርገዋል።
የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር አዲስ የሚያሰራው ህንፃ ዲዛይን ፅንሰ_ሀሳብመዝሙር በድሬዳዋ መምህራን... ምስጋናችን ከፍ ያለነው።ኢመማ
የአለም መምህራን ቀንን ምክንያት በማድረግ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዳጉ ፕሮግራም ከአቶ ሽመልስ አበበ የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ም/ፕሬዚዳንትና አቶ ታረቀኝ ኃይሌ የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ...
የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ነሀሴ 25/2014 ዓ.ም በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ ለሚድያ የሰጠው መግለጫ ከፍተኛ ሽፋን እያገኘ ነው
ለመላው የእስልምና ዕምንት ተከታይ ወገኖቻችን እንኳን ለ1443ኛው ኢድ አል-ፈጥር በዓል አደረሳችሁ።የተከበራችሁ የኢመማ አባላትና አመራሮች ሰኞ ሚያዚያ 24/2014 ዓ.ም ከቀኑ 6:30-7:3...
የትምህርት ጥራት መጓደል መንስኤዎችን በተመለከተ ከኢትዮጵያ መምህራን ማህበርና ትምህርት ሚንስቴር ጋር የተደረገ ቃለ -ምልልስ በኢሳት ቴሌቪዥን
የድሬዳዋው ተማሪ ከባጃጅ ሾፌርነት እስከ ኤር ባስA 350 ም/አብራሪነት፣ የቀድሞው መምህር የአሁኑ ጋዜጠኛ የዮናስ ተማሪ የነበረ ኡመር ዱዋሌ ታሪክ...  የተማሪዎች ስኬት የመምህራን ጥረት ...

Telephone

Address


Addis Ababa
13205
Other Nonprofit Organizations in Addis Ababa (show all)
Noble Cause Elder Care and Support Noble Cause Elder Care and Support
Office Addis Ababa
Addis Ababa, P.O.BOX21261,CODE1000

We are working for/with the most poorest and potentialy vulnerable elders in Ethiopia!

Rotaract Club of Keroggie Rotaract Club of Keroggie
Bole Subcity, Woreda 03, Zewdu Gessese Bldg, House No. 2414/2nd Foor
Addis Ababa

We are visionary, committed and disciplined young Ethiopians passionate to make a positive difference in the lives of our fellow citizens and the humanity through community service...

Rotaract Club of SOLYANA Rotaract Club of SOLYANA
Addis Ababa

Rotaract Club of Solyana is one of the 16 clubs in Ethiopia, and has been running since 2007 as a partner in service of Rotary International

Rotaract club of Ra'ey Rotaract club of Ra'ey
Addis Ababa

RAC Ra'ey is a rotaract club with members of different professions and knowledge in Ethiopia working for the realization of Ethiopia's visions VISION IN ACTION!

Strong Hearts International Strong Hearts International
Nifas Silk Lafto Sub City, Kore Mekanissia Area
Addis Ababa

We are a 501c3 non profit organization, our mission is to bring about transformation from the insideo

AIESEC in Ethiopia AIESEC in Ethiopia
EiABC, Dej. Baltcha Aba Nefso Street
Addis Ababa

Welcome to the AIESEC in Ethiopia Official Fan Page! AIESEC is the World's largest student‐run organi

The School of St Yared, Ethiopia The School of St Yared, Ethiopia
Opposite French Embassy
Addis Ababa

The School of St Yared opened in 2009 with the aim of offering a top class education to talented, imp

The Ethiopian Film Initiative The Ethiopian Film Initiative
Addis Ababa

Empowering Ethiopian filmmakers

Life4all Life4all
Addis Ababa
Addis Ababa, 41303

Great Commission Ministry Ethiopia on the journey of spiritual movement every where is impacting stu

Goh Bedembia Charitable Association Goh Bedembia Charitable Association
Addis Abeba
Addis Ababa, FUTUREPARK

Goh Be Dembia Charitable Association

Cancer Care Ethiopia Cancer Care Ethiopia
Ambo Street, Melka Gefersa
Addis Ababa, 10620,ADDISABABA

This is page of cancer care ethiopia. Updates about works will be presented here.