Lemi Kura Wereda 05 Prosperity Party-ብልፅግና

Fill the gab unfulfilled in politics!

18/06/2024

ለተሻለ ነገአችን ዛሬ እንትጋ !

አዲስ አበባ ለነዋሪዎች ጭምር አዲስ የቱሪስት መዳረሻ መሆን ጀምራለች።

አልፎ ለመሄድ ጭምር አፍንጫን መያዝ ግድ የሚሉ ፣ ለእይታ የሚቀፉ ፣ ለከተማችን ህዝብ የጤና ጠንቅ የነበሩ ሰፈሮች በለውጡ መንግስት ግብራቸው እየተለወጠ ማራኪ ገፅታን መላበስ ጀምረዋል።

ከሁሉም የከተማችን አካባቢዎች የሚገኙ ነዋሪዎች በእጅጉ እየተቀየረ የሚገኘውን የመሀል ከተማችንን ገፅታ ለመጎብኘት በየቀኑ ይጎርፋሉ ቢባል ማንም የሚመለከተው በመሆኑ ማጋነን አይሆንም።

ለአብነትም ከአድዋ ድል መታሰቢያ ጋር ተያይዞ የለማው የፒያሳ አካባቢ የህዝብ መናፈሻ ቦታ ከጠዋት እስከ ማታ ከፍ ያለ ቁጥር ባለው ሰው እየተጎበኘ የሚገኘው ንፁህ ነገር የማየት ፣ ንፁህ ነገር የማሽተት ፣ አዕምሮን ዘና የማድረግ ጥማትን ለማርካት አበረታች ጥረቶች በመጀመራቸው ነው።

የከተማ አስተዳደሩ የመዝናናት አቅም ያላቸው ከፍተኛ እና መከከለኛ የገቢ ምንጭ ያላቸው ዜጐች ብቻም ሳይሆኑ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙትም በነፃ የሚዝናኑበት እና ንፁህ አየር የሚምጉባቸውን የህዝብ መዝናኛ ፕላዛዎችን ለማበራከት በትኩረት እየሰራ ነው።

ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የስራ አዕምሮውን የሚያድስበት መዝናኛ እንዲያገኝ የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች በጥራት እና በስፋት እየተሰሩ መሆናቸውን በተለይም የኮሪደር ልማቱ እየተከናወነባቸው የሚገኙ አካባቢዎችን በመቃኘት መረዳት ይቻላል።

የኮሪደር ልማቱ በተያዘለት ዕቅድ መሰረት ህግና አሰራርን በተከተለ መልኩ የከተማችንን የከተማነት ስታንዳርድ ማሟላት ጀምሯል።

ሁሉም የልማት ተነሽዎች ከነበረበት ህይወት የተሻለ ካሳ እንዲያገኝ በማድረግ የተሰራ ሲሆን በሄዱባቸው አዲስ ሰፈሮች ያልተሟሉ አንዳንድ መሰረተ ልማቶችን ለማሟላትም በጥብቅ የአመራር ዲስፕሊን እየተመራ ጉድለቶችን ፈጥኖ የማረም ስራ እየተከናወነ ይገኛል።

የኮሪደር ልማቱ እሳትን የመሳሰሉ ድንገተኛ አደጋዎች ሲከሰቱ ለመቆጣጠር መተላለፊያ ያልነበራቸውን ፣ የተለያዩ ወንጀሎች ጭምር የሚፈፀሙባቸውን አካባቢዎች የተሟላ መሰረተ ልማት እንዲያገኙ በማድረግ ነዋሪዎችን ከስጋት ህይወት መታደግ ጀምሯል።

ህንፃዎች ከዋና መንገዶች እና ከመጋቢ መንገዶች የሚኖራቸው ርቀት ዓለም አቀፍ ስታንዳርዱን የጠበቀ እንዲሆንም በኮሪደር ልማቱ ትኩረት የተሰጠው ጉዳይ ሲሆን በተቀመጠው አቅጣጫ እና በተያዘው ዕቅድ አግባብ እየተከናወነ መሆኑን መታዘብ ይቻላል።

የኮሪደር ልማቱ በሚሰራበት አካባቢ ያሉ የወንዝ ተፋሰሶች ልማትም ተቀናጅቶ እየለማ ሲሆን በተለይም ፒያሳ እና አራት ኪሎ መካከል ላይ የሚገኘው ወንዝ ዳር እና ዳሩ የመሮጫ ትራክም ተካቶበት ካሁን በፊት ሊታሰብ የማይችል የነበረ ማራኪ ገፅታን ተላብሷል።

የከተማችን አንዱ ችግር የሆነውን ያልዘመነ የፍሳሽ አወጋገድ ለማዘመንም በኮሪደር ልማቱ ደረጃቸውን የጠበቁ የፍሳሽ ማስወገጃ መስመሮች መዘርጋታቸውም ለምንመኛት ውብ ከተማ ፅዳት መሰረት የሚጥል ነው።

የመብራት ፣ የቴሌ እና መሰል መሰረተ ልማቶችም ነገን ታሳቢ ባደረገ መልኩ በተቀናጀ አግባብ እየተሰሩ መሆናቸው ካሁን በፊት ሲያጋጥሙ የነበሩትን የቅንጅት ጉድለቶች የሚያርም ነው።

የስራ ባህል መዳበር የኮሪደር ልማቱ ስኬታማነት ሚስጢር ከመሆኑም በላይ በከተማችን በቀጣይም ለታቀዱ ታላላቅ ፕሮጀክቶች ትግበራ ልምድ የሚቀሰምበትና ተስፋ የሚጣልበት ነው።

አመራሩ፣ ኮንትራክተሩ ፣ አማካሪው እና በኮሪደር ልማቱ ላይ አሻራውን እያሳረፈ የሚገኘው ሁሉም ሰራተኛ ውሎ እና አዳሩን ልማቱ ላይ በማድረግ አንፀባራቂ ስኬት እያስመዘገቡ መሆናቸውን በማንኛውም ሰዓት ምልከታ በማድረግ ማረጋገጥ ይቻላል።

አዲስ አበባን እንደ ስሟ አበባ የማድረጉ ጉዞ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ የዲፕሎማቲክ ማዕከልነት ደረጃዋን የሚመጥን የከተማነት ስታንዳርድ እንዲኖራት ከማድረጉ ባሻገር የህዝባችንን ዘርፈ ብዙ ችግሮችም ያቃልላል።

የኮሪደር ልማታችን በአንድ በኩል የከተማችንን ህዝብ አዳጊ የመልማት ጥያቄ ትርጉም ባለው መልኩ ይመልሳል። በሌላ መልኩ ደግሞ በሂደቱ እና ከተጠናቀቀም በኋላ ለበርካታ የከተማችን ወጣቶች እና ሴቶች ቋሚ የስራ ዕድል ይፈጥራል ፤ መፍጠርም ጀምሯል።

ኢትዮጵያን የአፍሪካ ብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ አዲስ አበባን የኢትዮጵያ ብልፅግና አብነት ማድረግ በእጅጉ ወሳኝ በመሆኑ ከተማችን ያሉአትን አቅሞች ሁሉ አስተባብራ እንድትበለፅግ የህዝባችን የኑሮ ደረጃም ከፍ እንዲል ሁላችንም በጊዜአችን፣ በዕውቀታችን ፣ በገንዘባችን እና በጉልበትአችን አሻራችንን እያሳረፍን ለተሻለ ነገአችን ዛሬ እንትጋ መልዕክታችን ነው።

በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ /ፅ/ቤት

17/06/2024

አስተማማኝ ዘላቂ ሰላም የሰፈነባት ፣ የበለፀገች ኢትዮጵያን ለማረጋገጥ ለህዝባችን ተጠቃሚነት ተናጠላዊ ፍላጎቶቻችንን መስዋዕት እናድርግ !

በህብረት በቆምንበት ጊዜ ድል አስመዝግበን ታሪክ ሰርተናል። ከተናጠል ፍላጎቶቻችን ይልቅ ለብሔራዊ ክብራችን ቅድሚያ በሰጠንበት የታሪክ ምዕራፍ ሁሉ የአሸናፊነት ደማቅ ታሪክ ተጎናፅፈናል።

በዓለም አቀም ደረጃ የሚጠቀሱ ታላላቅ ስልጣኔዎች የነበሩን ፣ የዴሞክራሲ ስርዓት ከመስፋቱ በፊት አገር በቀል ስርዓትን የገነባን ፣ ተቻችሎ እና ተከባብሮ በመኖር አብነት የሆነን ፣ በየጊዜው የገጠሙንን ተግዳሮቶች በጋራ የመከትን እያልን ስለ ገናና ታሪካችን ብዙ መጠቃቀስ ብንችልም ታላቅ ነበርን ማለት ታላቅ አያደርግም ፤ ታላቅ ሆኖ መገኘት እንጂ።

ኢትዮጵያ በየዘመኑ የታሪክ ስብራቶቿን ልትጠግንባቸው የሚችሉትን መልካም አጋጣሚዎች አባክናለች። እንደ አለመታደል ሆኖ አንድነቷን እንደ ብረት ሊያጠናክርላት የሚገባው በደምና በአጥንት መስዋዕትነት የተገኘው የጥቁር ህዝቦች ሁሉ ኩራት የሆነው የአድዋ ድል አከባበር ጭምር የመሰባሰቢያ ሳይሆን የመለያያና የመገፋፊያ ምንጭ ሆኖ መቆየቱ አግራሞትን ያጭራል።

ምስጋና ለባለ ራዕይ መሪዎቻችን ይሁንና አሁን ላይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር የጥል ግድግዳ የሚፈጥርበት ምዕራፍ ተዘግቶ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በአብሮነትና በፍቅር የሚያከብርበት ብቻም ሳይሆን ድሉ ዓመቱን ሙሉ የሚዘከርበት ፣ ጥበብንና ቅርስን አጣምሮ የያዘው ፣ ከእኛ ትውልድ የታሪክ አሻራዎች ውስጥ ጎልቶ ሲጠቀስ የሚኖረው የአድዋ ድል መታሰቢያ ለከተማችንም መለያ ዓርማ ሆኗል::

በመሰባሰባችን የተገኘው ታላቁ የጥቁር ህዝቦች ድል የሆነውን የአድዋ ድልን በአድዋ ድል መታሰቢያ ተሰባስበን በድምቀት ማክበር ብቻም ሳይሆን በችግር ጊዜ ጭምር የህብረታችን ሚስጢር ተናጠላዊ ፍላጎትን ለአገራዊ ድል በማስገዛት መሆኑ በጥናትና ምርምር እየዳበረ ለትውልድ መማሪያ ዕውቀት እንደሚገበይበትም ይጠበቃል።

የለውጡ መንግስት የህዝባችንን ሉዓላዊ የስልጣን ባለቤትነት ባረጋገጠ መልኩ ነፃ ፣ ፍትሐዊ እና ዴሞክራሲያዊ በሆነ ምርጫ አገር የመምራት ሀላፊነት ስለተሰጠው የነበሩትን ውስብሰብ ችግሮች ደረጃ በደረጃ እያቃለለ እንደ አገር የነበሩብንን ስብራቶች ለመጠገን ጥልቅ ሪፎርሞችን እያከናወነ ይገኛል።

ከሪፎርም ስራዎቻችን መካከልም ነፃ እና ገለልተኛ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ተቋማትን ለመፍጠር የተደረገው አበረታች ጥረት ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ነው::

ፓርቲያችን የዴሞክራሲ ስርዓትን በፅኑ መሰረት ላይ ለመገንባት እና የፖለቲካ ባህላችን ወደ ትብብር እና ፉክክር ለማምጣት ከለውጡ ማግስት ጀምሮ የወሰዳቸው እርምጃዎች ምንጫቸው የአገራችንን ውስብስብ ችግሮች በጥልቀት ከመረዳት እና አሻግሮ ከማየት ብቃት ነው።

ነፃ እና ገለልተኛ ምርጫ ቦርድ ተቋቁሞ በአገራችን ታሪክ ሲወሳ የሚኖር ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መደረጉ ስልጣን በህዝብ ድምፅ እንጅ በሀይል የሚገኝበት የታሪክ ምዕራፍ መዘጋቱን የሚያመላክት የዛሬው ብቻም ሳይሆን የነገውም ትውልድ ብስራት ነው።

ሀገረ መንግስት ግንባታው የዕድሜውን ያህል እንዳይራመድ ተግዳሮት የነበሩ መግባባት ላይ ያልደረስንባቸውን አገራዊ ጉዳዮች በምክክር እና በውይይት ለመፍታትም ከማንኛውም አካል ጣልቃ ገብነት ነፃ የሆነ ብሔራዊ የምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ ወደ ስራ መግባቱ ይታወቃል።

ሳንግባባቸው ያደርን ሲንከባለሉ የመጡ ችግሮች ሳያንሱን ለሰላም እንምከር ፣ ለልማት እንተባበር ፣ ዴሞክራሲን እናዳብር ስንል ተቃራኒውን የሚያስቡ እና የሚተገብሩ ፅንፈኛ አካላት የሀሳብ ድርቀታቸውን ለመሸፋፈን ጥረት ቢያደርጉም ህዝባችን ምርትና ገለባውን አብጠርጥሮ የሚለይበት ጥበብ ስላለው በጊዜ ሂደት እኩይ ድርጊታቸው እየተጋለጠ የበለፀገች እና አስተማማኝ ሰላም የሰፈነባት ኢትዮጵያ ዕውን መሆኗ የማይቀር ጉዳይ ነው::

በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት
መልካም የስራ ሳምንት ይሁንላችሁ!




Addis Ababa Prosperity Party - ብልፅግና

Photos from Lemi Kura Wereda 05 Prosperity Party-ብልፅግና's post 17/06/2024

የክረምት የችግኝ ተከላ የጉድጓድ ቁፋሮ ማስጀመሪያ መረሃ ግብር ተካሄደ።

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ከወረዳ እስከ ክፍለ ከተማ ያሉ አመራሮች፥ የበጎ ፈቃድ ወጣቶች የሴፍትኔት ሰራተኞች ፥ የፅዳት ሰራተኞች እንዲሁም የሰላም ሰራዊቶች እና ሌሎችም ተሳትፈዋል።

የችግኝ ቁፋሮ መረሃ ግብሩን ያስጀመሩት የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ተስፋዬ ደንድር እንደገለፁት በዘንድሮ ዓመት በክፍለ ከተማችን 2.6 ሚሊየን ችግኝ ይተከላል ። በመሆኑም ሁላችንም እቅዱን ለማሳካት በንቃት መሳተፍ ይጠበቅበታል።

የክፍለ ከተማ ከተማ ውበተትና አረንጓዴ ልማት ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ አበበ አንሙት እንዳሉት የ2016 ዓ.ም የጉድጓድ ዝግጅት ሲካሄድ በትኩረት ባለሞያዎቹ በሚያሳዩን አቅጣጫ መሰረት መተግበር ወሳኝ ነው። ከዚህ በኃላም በየወረዳው ዛሬ የተሳተፉትን ሁሉ በማሳተፍ የጉድጓድ ዝግጅቱ በጥራት መዘጋጀት ያስፈልጋል ብለዋል።

ለሚ ኩራ ኮሚኒኬሽን
11/10/2016 ዓ.ም

Photos from Lemi Kura Wereda 05 Prosperity Party-ብልፅግና's post 16/06/2024

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1445ኛው ኢድ አልአድሀ (አረፋ በዓል) በሰላም አደረሳችሁ!

ኢድ ሙባረክ

Photos from Lemi Kura Wereda 05 Prosperity Party-ብልፅግና's post 15/06/2024

እንኳን ለ1445ኛው ዓ.ሂ ኢድ አል አድሃ/አረፋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ ኢድ አል አድሃ

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለሙስሊም ወገኖች በሙሉ እንኳን ለኢድ አል አድሃ/አረፋ በዓል አደረሳችሁ አያልኩ፣ በዓሉ የፍቅር መገለጫ፣ የሰጦታ ማበርከትና የፍቅር መስዋእትነት የተሰጠበት፣ የሚታወስበት ቀን በመሆኑ፣ ሀሉችን የከተማችን ሙስሉም ወገኖች፣ በዓሉ የሰላም፣ የመደጋገፍ፣ በአንድነት፣ በፍቅርና በደስታ የምናሳልፍበት ይሁንልን

እንኳን አደረሳችሁ፤ ኢድ ሙባረክ

አቶ ማቱሳላ አኑሎ፣ በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 05 ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ

Photos from Lemi Kura Wereda 05 Prosperity Party-ብልፅግና's post 15/06/2024

የኢድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል
የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ደንድር ባስተላለፉት መልዕክት የኢድ አል አድሀ (አረፋ ) በዓል ህዝበ ሙስሊሙ በድምቀት ከሚያከብራቸው በዓላት መካከል አንዱ ነው።

በዓሉ በምዕመናን ዘንድ ትልቅ ትርጉም ያለው ሲሆን የአንድነት እና የአብሮነት እሴቶቻችን በጉልህ የሚንጸባረቁበት በዓል በመሆኑ ህዝበ ሙስሊሙ የተራበን ማብላት፣ የተቸገረን መርዳት እንዲሁም የታረዘን ማልበስ የአረፋ በዓል ልዩ መገለጫ መሆኑን ታውቆ የሙስሊሙ ማህበረሰብ እንደ ከዚህ ቀደሙ የጋራ አንድነቱን በማጠናከር እምነቱ በሚያዘው መሰረት አቅመ ደካሞችን በመርዳት ያለውን በማካፈል በዓሉን እንዲያከብር ጥሪ አቅርበዋል።

Photos from Lemi Kura Wereda 05 Prosperity Party-ብልፅግና's post 15/06/2024

እንኳን ለ1445ኛው የዒድ አል አድሃ /አረፋ/ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

በዓሉ የወንድማማችነትና የእህትማማችነት እሴቶቻችንን የሚያጎለብት የሰላም፣ የፍቅር፣ የአብሮነት እና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።

በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ፤ ኢድ ሙባረክ

አቶ ሞገስ ባልቻ፡ የአዲስ አበባ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ

Photos from Lemi Kura Wereda 05 Prosperity Party-ብልፅግና's post 15/06/2024

"ለመላው የክ/ከተማችን የእስልምና ዕምነት ተከታዮች እንኳን ለ1445ኛው የኢድ አል አድሃ በዓል በሰላም አደረሳችሁ
በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር እና የብልፅግና እንዲሆንላችሁ እመኛለው።

በክፍለ ከተማችን በዓሉን ስናከብር እንደተለመደው በመርዳት፣ አብሮ በመብላት እና በመከባበር ሰላሙን በመጠበቅ እንዲሆን መልዕክቴን አስተላልፋለው።

አቶ ታረቀኝ ገመቹ
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ
08/10/2016 ዓ.ሞ

Photos from Lemi Kura Wereda 05 Prosperity Party-ብልፅግና's post 15/06/2024

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1445ኛው ዓ.ሂ ኢድ አል አድሃ/አረፋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ ኢድ አል አድሃ

ኢድ አል አድሃ/አረፋ በዓል፣ አላህ የሰውን ልጅ መልካምነት የፈተነበት፣ የምሰዋእትነትን ዋጋ ያሳየበት፣ የሰው ልጅ ለአምላክ ያለው ፍቅር፣ አላህም ለሰው ልጅ ያለውን ፍቅር ያሳዩበት ታለቅ በዓል ነው። በመሆኑም፣ አኛ ኢትዮጵያውያን አረስበርስ በፍቅር እየተሳሰብን ፣ ለእናት ሀገራችንና ለከተማችን፣ ለወገናችን የሚበጅ መልካም ወስዋእትነት በመክፈል ብልፅግናን መረጋገጥ ይኖርብናል፣ እያልኩ በዓሉ፣ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአብሮነት እና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።

በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ፤ ኢድ ሙባረክ

ክብርት ወ/ሮ አማኔ አማን በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ

Photos from Lemi Kura Wereda 05 Prosperity Party-ብልፅግና's post 15/06/2024

የተቋማት አፈጻጸም ድምር የአጠቃላይ ስኬቶች መሰረት ናቸዉ!

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አጠቃላይ አመራርና የአስሩም ወረዳዎች አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት የ47 ቀናት እቅድ ተግባራትን መገምገሙን ገልጿል።

በመድረኩ በዋናነት ትኩረት ተደርጎባቸው ውይይት የተደረገባቸው አጀንዳዎች መካከል
👉የስራ ዕድል ፈጠራ
👉የአርሶ አደር እና ከተማ ግብርና
👉 የክረምት በጎ ፈቃድ ስራዎችን ማጠናከር
👉የአከራይ ተከራይ ስራ ያለበት ደረጃ
👉የገቢ አሰባሰብ ያለበትን ደረጃ
👉 የECD የቀዳማይ ልጅነት ልማት
👉የአረንጓዴ አሻራ ስራ ያለበት ደረጃ
👉 የከተማ ውበት ስራ አፈፃፀም

መድረኩን የመሩት የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ታረቀኝ ገመቹ እንዳሉት በክፍለ ከተማው በእቅድ ተይዘው ወደ ተግባር ተገብቶ በመስራት በርካታ አመርቂ ውጤቶችን ማምጣት ተችሏል። በከተማ ግብርና ስራ እንዲሁም ECD ላይተመሳሳይነት ስራ አለ ሌሎቹ ጋር ከወረዳ መረዳ መለያየት ያሳያል። ይህንን ፈጥኖ ማረም በተለይ የገቢ አሰባሰብ የሁሉም አመራር የቅድሚያ ትኩረት መሆን አለባት ሲሉ ተናግረዋል። የቀጣይ አቅጣጫዎችንም አስቀምጠዋል።በተለይ ህገ ወጥነትን በመከላከል ዙሪያ የተጠናከረ ስራ መሰራት ያስፈልገዋልም ብለዋል።

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስጨንቅ ብርሃኑ አክለው እንዳሉት ወቅታዊ ተግባራትን ከመደበኛ ስራዎች ጋር በማስተሳሰር የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ እንዲሁም ከስራ ዕድል አንፃር አጣዳፊ የስራ ዕድል ፈጠራ በታቀደው መጠን ማሳካት ያሻል። የከተማ ግብርና እንደክፍለ ከተማ አጠንክሮ ከተሰራ ከተማውን የሚያረጋጋ ስራ ይጠበቃል።በጥቅሉ ሁሉንም ስራዎች በንቃት መስራት ያሻል ብለዋል።

15/06/2024

ወንድማማችነት እና እህታማማችነት ለኢትዮጵያ ብልፅግና!

ወንድማማችነትን እና እህትማማችነትን ማሳደግ ለሀገረ መንግስት ግንባታ መሰረት ነው። ሰዎች በአንድነት እና በትብብር መንፈስ ሲሰባሰቡ የሚደነቅ እመርታ ማስመዝገብ እና ፈተናዎችን በብቃት ማሸነፍ ይችላሉ።

ኢትዮጵያ ውስጥ በልዩ ልዩ ማህበረሰቦች መካከል የወንድማማችነት እና የእህትማማችነት ስሜትን ማጎልበት በተለይ ሀገሪቱ ካላት የበለፀገ የባህል ዕሴት እና ታሪክ አንፃር እጅግ ጠቃሚ ነው። ይህንን እሴቶቻችንን መቀበል ፣ መለያየትን ለመድፈን፣ መግባባትን ለማጎልበትና ለሀገር እድገት የሚያበረክተው አስተዋፅዖ ለማበርከት ይረዳል።

የተለያዩ ማህበረሰቦች የሚያጋጥሟቸውን የጋራ ተግዳሮቶች የሚፈቱ ውይይቶችን፣ የባህል ልውውጦችን እና ተነሳሽነቶችን ጨምሮ የአንድነትን ትስስር ለማጠናከር የሚደረጉ የቆዩ እሳቤዎቻችንን እያጎለበትን ልንሄድ ይገባል።

በእኛ ኢትዮጵያውያን መካከል መከባበርን፣ አብሮነትን እና መተሳሰብን ማበረታታት የሀገረ መንግስት ግንባታን በማፅናት ለዛሬና ነገዋ ኢትዬጵያ ፅኑ መሰረት የሚጥል ነው።

15/06/2024

እንኳን ለ1445ኛው ዓ.ሂ ኢድ አል አድሃ/አረፋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ ኢድ አል አድሃ

ለመላው ሙስሊም ወገኖቻችን እንኳን ለ1445ኛው ዓ.ሂ ኢድ አል አድሃ/አረፋ በዓል አደረሳችሁ እያልኩ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአብሮነት እና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።

በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ፤ ኢድ ሙባረክ

ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Photos from Lemi Kura Wereda 05 Prosperity Party-ብልፅግና's post 15/06/2024

እንኳን ለ2016 የዒድ አል አድሃ በዓል በሰላም አደረሳችሁ

ስኔ 8 ቀን 2016 ዓ.ም፣የኢድ አል አድሃ በዓል የፈተናና የመሥዋዕትነት በዓል ነው፡፡ ነቢዩ ኢብራሂም በአላህ ትእዛዝ ልጃቸውን ለመሥዋዕትነት ያዘጋጁበት፤ ጽናታቸው ተፈትኖ ያሸነፉበት በዓል ነው፡፡ ለዚህ ጽናታቸውም ከአላህ ዘንድ ምትክ በግ ያገኙበት በዓል ነው፡፡
ከዚህ በዓል የምንማራቸው ብዙ ነገሮች አሉ፡፡ ማንኛውም ፈተና በጽናት ካለፉት ዋጋው ከፈተናው በላይ መሆኑን እንማርበታለን፡፡ ልጅን ያህል ነገር እንዲሠዉ መጠየቅ ከባድ ፈተና ነው፡፡ ልጅን ለመሥዋዕትነት ማዘጋጀት ደግሞ ከባድ ጽናት ነው፡፡ ከባድ ፈተና ከባድ ቆራጥነት ይፈልጋል፡፡ ከባድ ቆራጥነት ከባድ ውሳኔን ይጠይቃል፤ ከባድ ውሳኔም ታላቅ ዋጋን ያስገኛል፡፡
ኢትዮጵያን ታላቅና የበለጸገች ሀገር ለማድረግ ስንነሣ ፈተናው ከባድ እንደሚሆን እናምን ነበር፡፡ ሳይፈቱ የተከማቹ ሀገራዊ ችግሮች አሉ፡፡ በዘመናችን የተፈጠሩ አሁናዊ ችግሮችም አሉ፡፡ እነዚህ ሁለቱን በአንድ ጊዜ መጋፈጥ ይጠይቀን ነበር፡፡ ተራራውን መጋፈጥ ሳይሆን ተራራውን ማንሣት ይጠይቀን ነበር፡፡ ይሄንን ፈተና ለመጋፈጥ ከባባድ ውሳኔዎችን መወሰን ይገባን ነበር፡፡ እንደ ልጅ የምንወዳቸውን ሰዎች፣ ነገሮች፣ ቡድኖች፣ ወዳጆችና አካሄዶች ለመሠዋት መወሰን ነበረብን፡፡ መወሰን ብቻ ሳይሆን ማድረግም ነበረብን፡፡
ነቢዩ ኢብራሂም ልጃቸው ኢስማኤልን ሳይሆን በምትኩ ከአላህ የተሰጣቸውን በግ ሠዉተዋል፡፡ የእኛ ፈተና ከዚህም የባሰ ነበር፡፡ ሀገራችን ባከማቸቻቸው ዕዳዎችና ስብራቶች የተነሣ፣ ያለን አማራጭ የራሳችንን ነገር መሠዋት ብቻ ነበር፡፡ ሀገራችንን ለማዳን፣ የሕዝባችንን ዘላቂ ጥቅሞች ለማስከበር እና ከዛሬው የተሻለ ነገን ለመፍጠር ስንል፣ ብዙ ነገሮችን ሠዉተናል፡፡
ችግሮቻችን ቀስ ብለን እንድንሄድ አይፈቅዱልንም፡፡ በጥንቃቄ እንድንሮጥ እንጂ፡፡ የልማት ጥያቄዎቻችንን ለመመለስ እንደ ሕዝብ ሁላችንም የምንወዳቸውን ነገሮች ሠዉተናል፡፡ ከምንወደው አካባቢ ወደ ሌላ ሄደናል፡፡ ትዝታዎቻችንን ሠዉተናል፡፡ የባንዳውን ጩኸት ችለናል፤ ሀገርን ለመለወጥ ስንል ቤቶቻችንና ሕንጻዎቻችን እንዲፈርሱ ፈቅደናል፡፡ የመብራትና የውኃ መጥፋትን ታገሠናል፤ የመንገድ መዘጋትንና የአካባቢ መፈራረስን ተቀብለናል፡፡ ያለ መሥዋዕትነት የሚያድግ ሕዝብ፣ ያለ መሥዋዕትነት የሚበለጽግ ሀገር የለም፡፡ የኮሪደር ልማቱን በዚህ መልኩ በመሥዋዕትነት ነው የሠራነው፡፡ ፍሬው ግን እጅግ ጣፋጭ መሆኑን አይተናል፡፡
ሰላማችንን ለማስፈን በዚሁ መንገድ ነው መቀጠል ያለብን፡፡ ነፍጥን መጣል፤ ከጫካ መውጣትና የራስን ዋሻ ትቶ ወደ መስኩ መውጣትን ይፈልጋል፡፡ የራስን ኢጎ መሠዋትን ይጠይቃል፡፡ ምቾትንና ፍላጎትን መተዉን ይፈልጋል፡፡ ከመቀበል በላይ መስጠትን ይሻል፡፡ እንደ ኢብራሂም በጣም የምንሳሳለትን ነገር ለመሠዋት መቁረጥ ይፈልጋል፡፡ ሁላችንም ለመሥዋዕትነት ከተዘጋጀን የማይሳካ የሰላም መንገድ የለም፡፡ እንደ ልጅ ያሳደግናቸው ብዙ ልማዶች፣ ጠባዮች፣ አመለካከቶች፣ ርእዮተ ዓለሞችና አካሄዶች አሉን፡፡ እነርሱን ለሀገርና ለሕዝብ ጥቅም ስንል ለመሠዋት ዝግጁ ከሆንን፣ ውጤቱ ከሰላም በላይ ነው፡፡
ምክክር የሚሳካው የተሻለ ሐሳብና የላቀ ዕውቀት በማዋጣት ብቻ አይደለም፡፡ የተሻለ ሐሳብና የላቀ ዕውቀት ስላለን ብቻ የሠመረ ውጤት አናገኝም፡፡ ሌላ ወሳኝ ነገር ይፈልጋል፡፡ እርሱም መሥዋዕትነት ነው፡፡ የራስን ፍላጎት ለመሠዋት መቻል አለብን፡፡ ለትልቅ ግብ ሲባል ይቅርብኝ ማለት አለብን፡፡ ከእኔ የተሻለ ሐሳብና ልምድ፣ ዕውቀትና ጥበብ ሊኖር ይችላል ብለን ማመንና መቀበል አለብን፡፡ ለተሻለው ሐሳብ መገዛት አለብን፡፡ ልክ ልኩን ከመንገር፤ ነጥብ ከማስቆጠር፤ ጀግና ጀግና ከመጨዋት የወጣ ትኁት ሰብእና መያዝ አለብን፡፡ ይሄ ሁሉ መሥዋዕትነትን ይጠይቃል፡፡ እንደ ነቢዩ ኢብራሂም ያሳደግናቸውን ብቻ ሳይሆን አብረውን ያደጉትን ብዙ ጠባዮች ለመሠዋት መዘጋጀትን ይጠይቃል፡፡ መሥዋዕትነት የሚከፍሉ ዜጎች በበዙ ቁጥር፣ ምክክር የላቀ ውጤት ያስገኛል፡፡
የኮሪደር ልማታችን በየከተሞቻችን እንዲስፋፋ፤ ሰላማችን የጸና እና የማይደፈርስ እንዲሆን፤ ሀገራዊ ምክክሩ ኢትዮጵያ ውስጥ ከጽንፍ እስከ ጽንፍ ተካሂዶ እንዲሳካ - ያሳደግናቸውንና ያደጉብንን አንዳንድ ነገሮች መሥዋዕት ለማድረግ እንዘጋጅ፡፡ ሐሳቦቻችን ትጥቅ ይፍቱ፡፡ ከመተኮሻ ወደ ማረሻ እንመለስ፡፡ ከጠመንጃ ወደ ማጨጃ እንዛወር፡፡ ከዲሞትፈር ወደ ምክክር እንምጣ፡፡ ከብሔር ግጭት ወደ ሐሳብ ፍጭት እንሻገር፡፡ የምንወደውን፣ የምንፈልገውንና ያሳደግነውን እንኳን ቢሆን - ለሀገር ስንል ለመሠዋት እንዘጋጅ፡፡
መልካም በዓል ይሁን፡፡

ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!

15/06/2024

ብልጽግና የብሔራዊነት ትርክትንና ሀገራዊ መግባባትን ለማጽናት እየሰራ ያለ ፓርቲ!

ብልፅግና ፓርቲ የነደፋቸው የፖለቲካ ተልዕኮና ዓላማዎች ይሳኩ ዘንድ በትኩረት ከሚሰራባቸው ጉዳዮች አንዱና ዋናው የሀገራዊ መግባባት ጉዳይ ነው። ፓርቲው ህብረ-ብሔራዊ አንድነታችንን ለማጠናከር፣ የዴሞክራሲ ስርዓት ማበብና አጠቃላይ ሀገራዊ የተረጋጋ የኢኮኖሚ ዕድገት ይመጣ ዘንድ ከነጠላ ትርክት በመላቀቅ ገዥ ብሔራዊ ትርክትን በማጽናት ሀገራዊ መግባባትን ለማዳበር በጽኑ እየሰራ ይገኛል።

በሀገራችን የተፈጠሩና እየተፈጠሩ ያሉ ችግሮች ዋነኛው መነሻቸውና አባባሽ ጉዳይ ነጠላ ትርክት መሆኑንና አንድ ሀገር የሚጸናው በአገሪቱ በተገነባው የጋራ ትርክት መሆኑን በመረዳት ሁሉም ኢትዮጵያውያን በተለይም ወጣቱ ትውልድ የተናጠል ትርክት ሰለባ እንዳይሆን ወላጆችና ማሕበረሰቡ ብዝሃነትን ማዕከል ባደረገ መልኩ ለአሰባሳቢ ትርክት ቅድሚያ በመስጠት የሚያግባባንን አሰባሳቢ የጋራ ትርክት ማጉላት ይጠበቅብናል።

ፓርቲያችን ሀገራዊ መግባባትን ለማዳበር በሚያደርገው እንቅስቃሴ ቅድሚያ ሰጥቶ ከሚሰራቸው ተግባራት አንዱ በሀገራችን የቂምና የጥላቻ ታሪክ ምዕራፍ እንዲዘጋና በብሔራዊ አርበኝነት የተገነባ ብዝሃነትን ያማከለ አካታች የፖለቲካ ስርዓት ይኖር ዘንድ ነው ።

የብልፅግና ፓርቲ በሀገራችን የምንፈጥረው የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ህብረ-ብሔራዊ አንድነትን የጠበቀና የሁሉም ማንነቶች ነፀብራቅ የሆነ፤ የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦችን ባህልና ማንነት ያከበረ መሆን እንዳለበት በጽኑ ያምናል። ለዚህም ብሔራዊ አርበኝነትን የሚያፀና አሰባሳቢ ገዥ ትርክት ወሳኝ ነው። ብሔራዊነት ስንፈልግ የምንይዘው ሳይመቸን የምንጥለው ሳይሆን ኢትዮጵያዊያን ከተቃርኖ የጠቅላይነትና የተገንጣይነት ነጠላ ትርክቶች ተላቀው ጠቃሚ የሆኑ የስልጣኔና የአብሮነት ዕሴቶቻቸውን በማዳበር የወል እውነትን በማጽናት በህብረ - ብሔራዊ አንድነት ፀንታ የምትበለጽግ የጋራ ሀገር ዕውን ማድረግ ይገባል።

Photos from Lemi Kura Wereda 05 Prosperity Party-ብልፅግና's post 15/06/2024

በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ደረጃ በአዲስ መልኩ ሲሰለጥኑ የነበሩ የሰላም ሰራዊት ዛሬ በመመረቅ ላይ በፎቶ።

Photos from Lemi Kura Wereda 05 Prosperity Party-ብልፅግና's post 15/06/2024

የኮሪደር ፅዳት ዘመቻ የወረዳ 05 ተሳትፎ በወረዳ 08 በሰሚት ተጠናክሮ ቀጥሏል

Photos from Lemi Kura Wereda 05 Prosperity Party-ብልፅግና's post 14/06/2024

የወረዳ 05 አስተዳደር ባህል ኪነጥበብና ቱሪዝም ጽ/ቤት የፎቶ አውደርእይ ፕሮግራም አካሄደ

ሰኔ 7 / 2016 ዓ.ም፣ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወሰዳ 05 በፎቶ አውደርዕይ ላይ በበጀት አመቱ በጽ/ቤቱ በኩል የተከናወኑ ተግባራትን በፎቶ አስቀኝቷል።

14/06/2024

ፓርቲያችን ብልፅግና ሃገራዊ ገዥ ትርክቶቻችንን በማፅናት ብሔራዊ አንድነትን ለመፍጠር ይተጋል!

ፖርቲያችን ብልፅግና ከሚከተላቸዉ ዋንኛው እና የመጀመሪያው በሀገር ደረጃ የጋራ የሚያደርጉንን ገዥ ትርክቶችን በመገንባት ህብረ-ብሔራዊ አንድነትን ማፅናት ነዉ።

ገዥ ትርክት ብሔራዊነትን ያማከለ
መደማመጥ የተሞላበት ከትላንት ዛሬ፣ ከዛሬ ነገ የተሻለ ልማትን የምንሰራበት የፓርቲያችንን እሴት የሚያሳካ ድል አድራጊነት ነው።

ገዥ ትርክት የጋራ የወል ታሪኮቻችንን ወይም እምነቶቻችንን በታሪክ እንድናፀና/እንድንፅፍ፣ ሁለንተናዊ ብልፅግናችንን ለማረጋገጥ አይነተኛ መሳሪያ ነው።

ሀገራችን ኢትዮጵያ በርካታ የሆኑ የጋራ ማንነት ያለን በህብረ-ብሔራዊ ወንድማማችነት እና እህትማማችነት እሳቤ የምንኖር ህዝቦች ስንሆን ብሔራዊነትን ለማፅናት እንዳንሰራ የሚያደርጉን ሀይሎች እንዳሉም ይታወቃል ። ይሁን እንጂ እኛ ኢትዮጵያውያን ከሚለያዩን ነገሮች ይልቅ አንድ የሚያደርጉን ስለሚበልጥ በብልፅግና ዕሳቤ ሆነን በርካታ የልማት ስራዎች ማጠናከር መደገፋችን አጠናክረን ቀጥለናል።

ኢትዮጵያ ውስጥ የተፈጠረው እየተፈጠሩ ያሉ ችግሮች ዋነኛው መነሻው አባባሽ ጉዳይ ነጠላ ትርክት መሆኑንና አንድ ነገር የሚፀናው በሀገሪቱ በተገነባው የጋራ ትርክት በመሆኑን በመረዳት ብዝሃነትን ማዕከል ባደረገ መልኩ ለአሰባሳቢ ትርክት ቅድሚያ በመስጠት የሚያግባባንን አሰባሳቢ የጋራ ትርክት ማጉላት ይጠበቅብናል።

ፓርቲያችን ሀገራችን ለበርካታ አመታት የምትታወቅበትን የመተባበር እና የመደጋገፍ እሴቶቻችንን ለማጎልበት በርካታ ስራዎችን እየሰራ ሲሆን የአሁኑ ዘመን ትውልድም ከፋፋይ እሳቤዎች ራሱን በማራቅ በጋራ በሚያቆሙን ገዥ ትርክቶች ላይ በማተኮር የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ሊያደርግ ይገባል።

Photos from Lemi Kura Wereda 05 Prosperity Party-ብልፅግና's post 14/06/2024

የብሔራዊነት ትርክት ለኢትዮጵያ ብልፅግና!

የብልፅግና ፓርቲ ህዝብ እና አለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ከሲዳማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ጋር በጋራ በመተባበር "የብሔራዊነት ትርክት ለኢትዮጵያ ልዕልና" በሚል መሪ ቃል ባዘጋጀው የስልጠና መድረክ የልምድ ልውውጥ ተሞክሮ ተካሂዷል።

በመርሀ ግብሩ መሰረት በአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት በህዝብ ግንኙነት እና ሚዲያ ዘርፍ በኩል የተሰሩ ስራዎች በተሞክሮነት ቀርበዋል።

የመልእክት ስርጭት ቀረፃ እና ተደራሸነት፣ ስልተቀመርን ባማከለ መልኩ የመረጀ የበላይነትን መቀናጀት፣ለማህበራዊ ሚዲያ የሚያገለግሉ የፕሮዳክሽን ስራዎች አቀራረብ ገለፃ የተደረገባቸው ነጥቦች ናቸው።

ገለፃውን ያቀረቡት የዘርፉ ሀላፊ አቶ ስዩም ከበደ ፈጠራ እና ፍጥነት፣የመረጃ ቅንጅት፣በተዋረድ የተደራጀ የግንኙነት ስርአት ለህዝብ ግንኙነት ስራ ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል።

የፓርቲያችንን ራዕይ እና ፖሊሲ ለማሳካት፣የብሔራዊነት ትርክት ግቡን እንዲመታ ለማስቻል፣በዘመናዊው የሚዲያ የትግል ሜዳ ድል አድርጎ ለመቆም ስልታዊነትን በተላበሰ አካሄድ መጓዝ እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል።

እንደ ፓርቲ የመረጃ ተደራሽነትን ማስፋት፣ተደራጅቶ ተደማሪ አቅም መፍጠር፣የተፅእኖ ፈጣሪነትን አቅም ማላቅ፣ከአጀንዳ ተቀባይነት ወደ አጀንዳ ሰጪነት መሸጋገር ለህዝብ ግንኙነት ስራችን የህልውና ጉዳይ መሆኑን ጠቅሰዋል።

እንደ ብልፅግና ፓርቲ ለህዝቡ የገባናቸውን ቃሎች በላቀ ውጤታማነት፣ ፈጠራን እና ፍጥነትን ጨምሮ ምላሽ ለመስጠት ጊዜውን የሚመጥን የህዝብ ግንኙነት ስራን መስራት አስፈላጊ መሆኑን አንስተው በዚህ ረገድ ተግባሩን በልዩ ዕቅድ ፣ በተቋም የተመራበት አግባብ አሁን ላይ በአዲስ አበባ ከተማ የተደረሰውን ውጤት እና ስራዎችን በሃሳብ የበላይነት ለህዝቡ ተደራሽ ማድረግ ተችሏል ሲሉ ገልፀዋል።

የስልጠናው ተሳታፊ የሆኑ በደቡብ ኢትዮጵያ የሚገኙ የሚዲያ ባለሙያዎች እና አመራሮች በዝርዝር የቀረቡ የልምድ እና የተሞክሮ ውጤቶችን ተግባራዊ ማድረግና የብሔራዊነት ትርክት ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት ሊደግፉ እንደሚገባ ተናግረዋል።

Photos from Lemi Kura Wereda 05 Prosperity Party-ብልፅግና's post 14/06/2024

ለሁለተኛ ምዕራፍ ፋይናንስ ተጠቃሚዎች "በቤተሰብ ደረጃ የድህነት ቅነሳ" በሚል ሀሳብ ውይይት ተደረገ

ሰኔ 7 / 2016ዓ.ም፣በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ለተጨማሪ ሁለተኛ ምዕራፍ ፋይናንስ ተጠቃሚዎች "በቤተሰብ ደረጃ የድህነት ቅነሳ" በሚል ሀሳብ ከሴፍቲ ኔት ተጠቃሚዎች ጋር እቅድ ውይይት ተደርጓል።

የፕሮግራሙ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ላይ ተገኝቶ ንግግር ያደረጉ የወረዳው ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀይሉ ተደሰ ሲሆኑ በስራና ክህሎት ጽ/ቤት በኩል ስራ የሚፈጥርላቸው አካላት በመረጡትና በሰለጠኑት ስራ ዘርፍ በመሰማራት ውጤታማ መሆን እንደሚገባቸው ገልጸው ነዋሪዎች የምግብ ዋስትናን መረጋጋት እንደሚገባቸው አያይዘውም ገልፀዋል።

የውይይት ሰነዱን ያቀረቡት የምግብ ዋስትና ተወካይ ቡድን መሪ አቶ ሀብታሙ ጎጃም ኢትዮጵያ ላይ የሚስተዋለውን የሀብት ምዝበራ ለማስቀረት ሁሉም አካል በሰለጠነው ሙያ ዘርፉ መስራት ያሰፈልጋል ከተረጂነት መንፈስ መውጣት እንደሚገባ ጠቅሰው ኢትዮጵያ " ረጂ እንጂ ተረጂ መሆን ያለበትም" ብሏል።

የኑሮ መሻሻል ባለሙያ የሆኑት አቶ ደረጄ በለጠ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ከአፍሪካ እንዲሁም ከአለም ሀገራት ቀዳሚና ለሀገራት ቀኝ ያልተገዛች ሀገር መሆኖን ገልፀው ሀገራችን አሁን ላይ ድሀ የሚለውን ስም ወደ በለፀገች ሀገርነት መቀየር ያስፈልጋል ሲሉ ገልጸዋል።

Photos from Lemi Kura Wereda 05 Prosperity Party-ብልፅግና's post 13/06/2024

እለታዊ ሰው ተኮር ስራዎችን እየገመገሙ መሄድ ለተሻለ ለውጤት ያበቃል ተባለ

በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ጠቅላላ ሰው ተኮር ስራዎችን የገመገመ ሲሆን፣ የወረዳ 05 አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ ክብርት ወ/ሮ አማኔ አማን፣ እለታዊ ሰው ተኮር ስራዎችን እየገመገሙ መሄድ ለተሻለ ለውጤት ያበቃል ሰሉ ተናግረዋል።

የተገመገሙት ሰው ስራዎች
1. የስራ እድል ፈጠራ
2. የሌማት ቱሩፋት የከተማ ግብርና
3. የቀደማዊ ልጅነት የልጆች መጫወቻ
4. አረንጓዴ ልማትና የፅዳት ስራዎች
5. ስላምና ፀጥታ ስራዎችና
6. የፓርቲ ወረጃ ማዘመን፣ ስራዎች ናቸው

አቶ ማቱሳ አኑሎ የወረዳ 05 ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ በመድረኩ፣ አመራሩ በአንድነትና በቅንጅት ስራዎችን አስተሳስሮ በሁሉም ተግባራት ውጤት ማምጣት ይጠበቅበታል ብልዋል።

Photos from Lemi Kura Prosperity Party's post 13/06/2024
Photos from Lemi Kura Wereda 05 Prosperity Party-ብልፅግና's post 12/06/2024

በአንድ ማዕከል አገልግሎት በመስጠት የባለጉዳዮች እንግልት ይቀንሳል ተባለ ።

ሰኔ 5 /2016 ዓ.ም፣ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 በዛሬው እለት የአገልግሎት አሰጣጥ በተመለከተ በአንድ ማዕከል ባለጉዳዮች በሚበዙባቸው ሴክተሮች በአንድ ላይ በመሆን በዋና ስራ አስፈፃሚ ቢሮ አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛል።

አገልግሎት አሰጣጥ በወረዳችን ዛሬ እሮብ በአንድ ማዕከል እየተሰጠ ያለ ስሆን ባለጉዳዮች የሚበዙባቸው ሰክተሮች ማለትም ዋና ስራ አስፈጻሚ የከተማ ግብርና የመሬት አስተዳደር እና ግንባታ ፍቃድ ጽ/ቤች አንድላይ በመሆን የባለጉዳዮች እንግልት እንዳይኖር በተቀናጀ መልኩ እየሰሩ መሆኑን የወረዳ 05 ዋና ስራ አስፈፃሚ ክብርት ወ/ሮ አማኔ አማን፣ ገልፀዋል።

Photos from Lemi Kura Wereda 05 Prosperity Party-ብልፅግና's post 11/06/2024

ከስራና ክህሎት ፅ/ቤት ሠራተኞች ጋር በኦዲትና ኢንስፔክሽን ዙሪያ እና የዜጎች ተጠቃሚነት ማረጋገጥ በሚያስችል ሁኔታዎች ላይ ውይይት ተደርገዋል።

በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ከስራና ክህሎት ፅ/ቤት ሠራተኞች ጋር በኦዲትና ኢንስፔክሽን ዙሪያ እና የዜጎች ተጠቃሚነት ማረጋገጥ በሚያስችል ሁኔታዎች ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ የስራ እድል ፈጠራ ስራዎች ለወረዳወሰ ነዋሪዎች ፈጣን የልማት ተጠቃሚነትን ቢሚያሳካ መልኩ መሆን እንዳለበት፣ የወረዳው ዋና ስአስፈፃሚ ክብርት ወ/ሮ አማኔ አማን ገልፀዋል።

አቶ ማቱላ አኑሎ በበኩላቸው ወረዳ 05 የስራ እድል ተግባር ስራ የተሻለ እንደሆነ አንስተው፣ የኦዲት ተግባሩም ለቀጣይ የላቀ ስራ ለመስራት ይረዳል ብልዋል

Photos from Lemi Kura Wereda 05 Prosperity Party-ብልፅግና's post 11/06/2024

የወረዳ 05 ብልፅግና ፓርቲ አባላት፣ የፓርቲው ህገ ደንብ ውይይት ተደረገ

በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር የብልፅግና ፓርቲ አባላት፣ የፓርቲው ህገ ደንብ ውይይት ለተከታታይ ቀናት የተደረገ ሲሆን፣ ውይይቱ በሴቶች ሊግ፣ በወጣቶች ሊግ፣ በቢሮና በሌሎችም ማህበራዊ መሰረት መደረጉን፣ አቶ ያሬድ ለማ፣ የወረዳ 05 ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ምክትል ኃላፊና የፖለቲካ ዘርፍ ኃለፊ ገልፀዋል።

የወረዳ 05 የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ አርጋው ከበደና የሴቶች ሊግ ሰቢሳቢ ወ/ሪት መቅደስ ሙሉ የዘርፋቸውን መህበረዊ መሰረት ህግ- ደንብ ያወያዪ ሲሆን፣ አባላት የፓርቲያችው ምንነት አውቀውና ተረድተው መንቀሳቀስ፣ መብትና ግዴታን ለይቶ ውጤታማ ስራ ለማከናወን ወሳኝ ነው ብለዋል።

Photos from Lemi Kura Wereda 05 Prosperity Party-ብልፅግና's post 11/06/2024

የተጠናከረ የሰላም ሰራዊት ለአካባቢው ሰላም!

ሰኔ 4/ 2016 ዓ.ም፣ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 በዛሬው እለት በወረዳችን የተግባር ስልጠና የወሰዱ ስሆን በስልጠናው ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ ክብርት ወ/ሮ አማኔ አማን እንደተናገሩት እናንተ በአከባቢው ሰላም ላይ ያላችው ሚና ከፍተኛ ነው ያሉት ስሆን ሳታቆራርጡ ከአከባቢው ነዋሪዎች ጋር በመሆን እንድሁም ከወረዳው አስተዳደር እና ከቀጠና ፖሊስ ኦፍሰሮች ጋር አከባቢችሁን በደንብ መጠበቅ አለባቹ ስሉ መልዕክት አስተላልፏል ።

Photos from Lemi Kura Wereda 05 Prosperity Party-ብልፅግና's post 11/06/2024

ጥራት ያለዉ የትምህርት ምዘና ስረዓት ለበለጸገ ትዉልድ ግንባታ!

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለሚገኙ የግልና የመንግስት ት/ቤቶች ለሚማሩ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች የሚሰጠው የ8ኛ ክፍል የሚኒሲትሪ ፈተና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ት/ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ፣የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ታረቀኝ ገመቹ፣የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ደንደርና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በይፋ ተጀምሯል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ እና በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ታረቀኝ ገመቹ የተመራው የከፍተኛ አመራሮች ልዑክ በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ስር በሚገኙት የጋራ ጉሪ ት/ቤት፣ኢትዮ ቻይና ት/ቤት፣እና በሻሌ ትምህርት ቤት የፈተና ጣቢያዎች ፈተና በመውሰድ ላይ የሚገኙ ተማሪዎን የፈተና አሰጣጥ ሂደት ምልከታ አድርገው ፈተናውን በይፋ ያስጀመሩ ሲሆን ሚፈተኑ ተማሪዎችንም አበረታተዋል፡፡

ልዑክ ቡድኑ ከተፈታኞች ምልከታ ጎን ለጎን በት/ቤቶች ውስጥ የተገነቡ የቅድመ መደበኛ ትምህርት የማስፋፊያ ግንባታዎችንና የከተማ ግብርና ስራዎችንም ምልከታ በማድረግ ለተሰሩት ስራዎች ያላቸውን አድናቆትም ገልጸዋል፡፡

11/06/2024

ዜና ሹመት

አቶ ሀብታሙ ሲሳይ፣ በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 05 የግንባታ ፍቃድና ቁጥጥር ፅ/ቤት ኃላፊ ሁነው ተሹመዋል። አመራሩ ቀደም ሲል በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 06 ዘርፉን ሲመሩ የነበሩ እንደነበረና አሁን በመጡበት ወረዳ የተሻለ የስራ ግዜ እንዲሆንላቸው የወረዳ 05 አስተዳደር ይመኛል።

Photos from Lemi Kura Wereda 05 Prosperity Party-ብልፅግና's post 11/06/2024

ጠንካራና ብቁ ህዝባዊ ሰራዊት ለከተማችን ፍጹም ሰላም‼️

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የሠላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ለ1ሺ አዲስ ምልምል ህዝባዊ ሠራዊት የአካል ብቃት የተግባር ስልጠና መስጠት መጀመሩን ገለፀ።

ስልጠናውን በስፍራው ተገኝተው ያስጀመሩት የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የሠላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፋኖስ ደቻሳ እንዳሉት በትላንትናው እለት በንድፈ ሀሳብ ደረጃ የወሰዱትን ሠልጣኞች ዛሬ በተግባር የሚፈፅሙበትና የራሳቸውን አልፎም የአካባቢያቸውን የሠላም የሚጠብቁበትን አቅም ለመፍጠር የሚያስችል የአካል ብቃት ስልጠና እየተሠጠ እንደሆነ ገልፀው በቀሪ ቀናትም ስልጠናው እንደሚ ቀጥል ጨምረው ገልፀዋል።

11/06/2024

በአዲሰሰ አበባ፣ በለሚ ኩራ ክ/ከተማ በአዲስ የተመለመሉ ሰላም ሰራዊት ስልጠና በኢትዮ-ቻይና ስቴድየም

Want your organization to be the top-listed Government Service in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Videos (show all)

በአዲሰሰ አበባ፣ በለሚ ኩራ ክ/ከተማ በአዲስ የተመለመሉ ሰላም ሰራዊት ስልጠና በኢትዮ-ቻይና ስቴድየም
አዲስ የተመለመሉ የሰላም ሰራዊት ስልጠና በለሚ ኩራ ክ/ከተማ' አዲስ አበባ!
በአዲስ የተመለመሉ የሰለም ሰራዊት ስልጠና በለሚ ኩራ...
በለሚ ኩራ ከ/ከተማ ሲ.ኤም. ሲ አከባቢ የኮሪደር ልማት ፅዳት ዘመቻ በቪዲዮ
'በተዛባ ትርክትና የውሸት ዜና የሚፈርስ መንግስትም ሆነ፣ የሚበተን ህዝብ የለም'! #አትዮጵያ_የሁሉም_አትዮጵያውያንና የሁሉም #ሃይማኖቶች_ሀገር ነች!
1445ኛው ኢድ አል ፈጥር  በዓል ዋዜማ በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 05፣ ሰሚት አቡበከር መስጅድ..
የ1445ኛ የኢድ አልፍጥር በዓል መክኒያት በማድረግ በለሚ ኩራ ክ/ከተማ  በወረዳ 05 የፅዳት ዘመቻ በማድረግ ላይ...መጋቢት 30/2016 ዓ.ም
የለውጡ 6ኛ አመት ምክኒያት በማድረግ፣ የድጋፍ ሰልፍ በመስቀል አደባባይ ሰልፍ...
የድጋፍ ሰልፍ በመስቀል አደባባይ ሰልፍ...
የወረዳ 05 የብልፅግና ፓርቲ አባላት ኮንፍራንስ

Telephone

Website

Address

Addis Ababa
Other Political Organizations in Addis Ababa (show all)
African Union African Union
Addis Abeba
Addis Ababa, 1111

A UNITED & STRONG AFRICA

Qabsoo Bilisummaa Qabsoo Bilisummaa
Finfinne
Addis Ababa, 2560

Injifannoon Kan Abbaa dhugaati

GMN Grand Media Network GMN Grand Media Network
Addis Ababa

Manegment

Bole Wereda 1 Prosperity Party ብልጽግና Bole Wereda 1 Prosperity Party ብልጽግና
Bole Michael
Addis Ababa, G.P.O

ይህ በቦሌ ክ/ከተማ ስር በሚገኘው በወረዳ 1 ብልጽግና ፓርቲ የ?

Anwar Tuti Anwar Tuti
Somaliya
Addis Ababa, HADLIYAAAA

Addis Ketema Woreda 6 Prosperity Party-ብልፅግና Addis Ketema Woreda 6 Prosperity Party-ብልፅግና
Addis Ketema
Addis Ababa

ለሁሉም ዜጋ ብልፅግናን ለማረጋጋጥ እንሰራለን

Free state movement for Addis ababa Free state movement for Addis ababa
Addis Ababa

Political

Imala Haqaa Imala Haqaa
Addis Ababa

Kaayyoon Kenya haqaa dhokate basne baketi mulisudhaa kanafu nu hordofun haqaa cina dhabachun eru nun

Paartii Badhaadhinaa Kutaa Magaalaa Araadaa Paartii Badhaadhinaa Kutaa Magaalaa Araadaa
Belay Zeleke Street, Pissa Road
Addis Ababa, 251,56

providing facts of prosperity party

Abdallaa  Zeenu Abafogi .Follow Abdallaa Zeenu Abafogi .Follow
Jiimmaa
Addis Ababa