EAS-Ethiopian Accreditation Service

Ethiopian National Accreditation Office

ENAO was established as an autonomous federal government office having its own legal personality.

EAS was established as an autonomous federal gov’t office having its own legal personality will offer accreditation services on a national & Intern' basis for conformity assessment bodies.. The mandate of ENAO is to accredit, by formal third-party recognition, the competence of Conformity Assessment Bodies (CABs) to perform specific activities, such as test, calibrations, certifications or inspect

05/05/2024

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለፋሲካ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ።
የኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት።

Photos from EAS-Ethiopian Accreditation Service's post 27/04/2024

ሀገር አቀፍ የጤና አገልግሎት አክሪዲቴሽን ፕሮግራም ፍኖተ ካርታ ይፋ ተደረገ
ሚያዝያ 19 ቀን 2016 ዓ.ም
*************************************************
የሃገራችን የጤና ፖሊሲን ትግበራ ለማረጋገጥ የሚያስችለው የአክሪዲቴሽን ፍኖተ ካርታ መዘጋጀቱ እንዲሁም የጤና ኢኖቬሽን መመሪያ እና የጤና አመራር ፕሮግራም መዘጋጀቱ የጤናው ስርአት ወደፊት ያራመደ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በመርሃ ግብሩ መክፍቻ ንግግራቸው ገልጸዋል፡፡
ተቋሞቻችን በሃገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሃገራት ዘንድ ተቀባይነት እንዲኖራቸው ለማስቻል የአክሪዲቴሽን ፍኖተ ካርታን ተግባራዊ ለማድረግ የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ቁርጠኝነት ይጠያቃል ያሉት ዶ/ር መቅደስ፤ የፍኖተ ካርታው መዘጋጀት እንደ ሃገር በጤናው ዘርፍ ልንደርስበት ያሰብነውን ግብ ለማሳካት የሚያገለግል መሳሪያ መሆኑንም አጽእኖት ሰጥተዋል፡፡
ፍኖተ ካርታው የልህቀት ማእከል ለመሆን አለማ ያላቸው የጤና ተቋማት መስፈርት እንደሚሆን የጠቆሙት ሚኒስትሯ፤ አክሪዲቴሽን ከሃገር ባለፈ አለም አቀፍ መስፈርቶችን እዲያካትት ጤና ሚኒስቴር ድጋፍ እና ክትትል ያደርጋል ብለዋል፡፡
አክሪዲቴሽን ቅንጦት ሳይሆን የህብረተሰብን ጥያቄ እና የጤና ሚኒስቴር ምላሽ የመስጠት አቅምን ማሳያ ግዴታ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ በመድረኩ ያስረዱ ሲሆን፤ ፍኖተ ካርታው መዘጋጀቱ የባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ እና በማስተባበር፤ አገልግሎት፣ ስልጠና እና ጥናትና ምርምርን እንደሚያቀናጅ ተናግረዋል፡፡
የሃገራችን የጤና አገልግሎት በአደጋ የማይበገር እንዲሆን ለማድረግ ያለንን ቁርጠኝነት ያረጋገጠ መሆኑን የኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ቦንሳ ባይሳ ገልጸው፤ በተለይም በገጠር የሚገኙ ዜጎች ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ማግኘታቸውን ለማረጋገጥ እንደሚረዳም አክለዋል፡፡
የኢትዮጵያ የጥራት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር በበኩላቸው፤ የሚመሩት ኢንስቲትዩት ከጥራት ተቋማት አንዱ መሆኑን በመግለጽ፤ በጤናው ዘርፍ ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎትን ለማረጋገጥ የደረጃዎች ሚና ከፍተኛ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
አክሪዲቴሽን የዜጎችን ፍላጎት ከሟሟላት ባለፈ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እንዳለው የግል ጤና ተቋማት ፌደሬሽን ምክትል ፕሬዘዳንት ዶ/ር ግርማ አባቢ ያስረዱ ሲሆን፤ ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት መኖሩ ዜጎች ለህክምና ወደ ውጭ ሃገራት በመጓዝ ላላስፈለጊ ወጪ እንዳይዳረጉ እንዲሁም ለጎረቤት ሃገራት አገልግሎት በማቅረብ የገቢ ምንጭ እስከመሆን ይደርሳል ብለዋል፡፡
የፍኖተ ካርታው መዘጋጀቱ ትምህርት እና ስልጠና ባለስልጣን ከጤናው ሴክተር ጋር በትብብር ለመስራት የሚችልበትን መንገድ ያደላደለ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤ ናቸው፡፡
የአክሪዲቴሽን ፕሮግራም ፍኖተ ካርታው በጤና ሥርዓት ኢኖቬሽንና ጥራት ሥራ መሪ ስራ አስፈፃሚው ዶ/ር አባስ ሐሰን ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን በመርሃ ግብሩ የክልል ጤና ቢሮ የስራ ሃላፊዎች፣ ባለድርሻ አካላት፣ የግል እና የመንግስት የጤና ተቋማት አመራሮች እና የአጋር ድርጅቶች ተወካዮች ተሳትፈዋል።
የዜናው ምንጭ፡ ጤና ሚኒስቴር ፌስቡክ ገጽ

Photos from EAS-Ethiopian Accreditation Service's post 26/04/2024

የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ
ሚያዝያ 18 ቀን 2016 ዓ.ም
*************************************
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸሙን በአዳማ ከተማ ገመገመ፡፡ በመድረኩ ላይ በመገኘት የአገልግሎቱ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን አንዱዓለም መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
አገልግሎቱ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የስራ አፈጻጸም በርካታ ተግባራትን ማከናወኑን በመግለጽ በቀጣይ ሶስት ወራት የበጀት ዓመቱን ግብ ለማሳካት የአገልግሎቱ የሥራ ኃላፊዎች እና ሰራተኞች ስራዎቻቸውን በከፍተኛ ተነሳሽነት እንዲፈጽሙ አሳስበዋል፡፡
የአገልግሎቱ የስትራቴጂክ ጉዳዮች ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዋለልኝ አድማሱ የዐገልግሎቱን የዘጠኝ ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበው በተሳታፊዎች ውይይት ተካሂዷል፡፡
በውይይቱ ላይ ከሰራተኞች የተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች እንዲሁም የቀጣይ የአገልግሎቱ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ቦንሳ ባይሳ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል ፡፡
በተመሳሳይ በአክሪዲቴሽን አገልግሎት አፈጻጸም እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ለተሳታፊዎች ተጨማሪ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ባለፉት ዘጠኝ ወራት በህክምና ላቦራቶሪ፣ በፍተሻ ላቦራቶሪ ፣ በምርት ሰርቲፊኬሽን እና በኢስፔክሽን ወሰኖች ለኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ለህንድ ሰርቲፊኬሽን ተቋምን ጨምሮ ለበርካታ ድርጅቶች የአክሬዲቴሽን አገልግሎትን ተደራሽ ማድረግ ችሏል፡፡

23/04/2024

አክሬዲቴሽን የሕዝብ አገልግሎት ሰጭ ተቋማትን ለማዘመን ይረዳል!!!
ሚያዝያ 15 ቀን 2016 ዓ.ም
***********************************************************
አክሬዲቴሽን በሕዝብ አገልግሎት ሰጭ ድርጅቶች ውስጥ የጥራት መሻሻልን ለመተግበር ይረዳል። ድርጅቶች የአክሬዲቴሽን እውቅና መስፈርቶችን ሲያሟሉ የአሰራር ሂደቶቻቸውን፣ አገልግሎቶቻቸውን እና አጠቃላይ አፈፃፀማቸውን እንዲያሳድጉ ያደርጋል፡፡ በሌላ በኩል ድርጅቶች የአክሬዲቴሽን አገልግሎቱ ተጠቃሚ ሲሆኑ የበለጠ ተጠያቂነትን እና ግልፅነትን በመፍጠር የተቀመጡ ደረጃዎችን በማክበር ለባለድርሻ አካላት የላቀ ብቃት እና ኃላፊነት የተሞላበት አገልግሎት እንዲያቀርቡ ያደርጋል፡፡ በዚህ መልካም ስምና ዝናናን እንዲጎናጸፉ በማድረግ ለአንድ ሃገር ያላቸውን አበርክቶ በላቀ ብቃት እንዲያሳኩ ይረዳቸዋል፡፡
የአክሬዲቴሽን አገልግሎት ድርጅቶች በተለያዩ ዘርፎች ካሉ ቁልፍ አጋሮቻቸው ጋር ያላቸውን ግንኙነት ያጠናክራል፡፡
አክሬዲቴሽን ድርጅቶች በማስረጃ ላይ የተመሰረቱ አሰራሮችን እንዲጠቀሙ ያበረታታል። እንዲሁም ድርጅቶች በጥናት ላይ የተመሰረቱ አካሄዶችን ወደ ፕሮግራሞቻቸው እና አገልግሎቶቻቸው ለማካተት ጥረት እንዲያደርጉ በማገዝ ወደ ተሻለ ውጤት እንዲሸጋገሩ ከፍተኛ ዕድል ይፈጥራል።
አክሬዲቴሽን ድርጅቶች የሀብት አጠቃቀምን እንዲያሳድጉ ይረዳል።የተቀመጡ ደረጃዎችን በመከተል ሃብቶችን በብቃት በመመደብ ጥቅም ላይ እንዲያውሉ ያስችላቸዋል።
አክሬዲቴሽን ለህዝብ አገልግሎት ድርጅቶች ቀጣይነት ያለው መሻሻል፣ ተጠያቂነት እና ጠንካራ የማህበረሰብ አጋርነት ማዕቀፍ እንዲተገብሩ በማድረግ ለተሻለ አገልግሎት እና ለሚያገለግሉት ደንበኛ ውጤት የሚያበረክት ጠቃሚ ሂደት ነው።
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት
ስልክ 0116671269
የፌስ ቡክ ገጽ EAS-Ethiopian Accreditation Service
ድረ-ገጽ www.eas-eth.org

22/04/2024

አክሬዲቴሽን እና የቱሪዝም ኢንዱስትሪ
ሚያዝያ 11 ቀን 2016 ዓ.ም
*******************************************************************
የቱሪዝም አክሬዲቴሽን የቱሪዝም ንግዶችን እና የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ደረጃዎችን ጥራት ለማሻሻል ይረዳል፡፡ አክሬዲቴሽን ስለ ቱሪዝም ምርት ህጋዊነት እና ጥራት ለተጠቃሚዎች እምነት ይሰጣል።
ጥራት ያለው የቱሪዝም አክሬዲቴሽን የቱሪዝም ንግድ በአገልግሎት፣ በደህንነት፣ በኢንሹራንስ፣ በማስታወቂያ ልምዶች፣ በአደጋ አስተዳደር እና በቢዝነስ ስራዎች ከደንበኞች ከሚጠበቀው በላይ በማድረግ እርካታን ለማሳደግ ይረዳል ፡፡ አክሬዲቴሽን የቱሪዝም አሰራርን በማሻሻል በዘርፉ ለተሰማሩ ባለሃብቶች የተሻለ የገበያ ዕድል እንዲፈጥሩ ይረዳቸዋል፡፡ አክሬዲቴሽን ቀጣይነትና ዘላቂነት ያለው የቱሪዝም ዘርፍን በማጠናከር በብሔራዊ ፓርኮች እና በባህር ፓርኮች ውስጥ ላሉ የቱሪዝም ኦፕሬተሮች በአካባቢ፣ በባህላዊ፣ በማህበራዊ እና በንግድ ንግድ ስራዎች ላይ ዐትኩረው በመስራት የብዝሃ ህይወት፣ የአካባቢ እና የመስህቦች ጥበቃን አካቶ በመስራት ሃገራዊ ፋይዳውን ለማሳደግ ያስችላል ።
አገራችን ኢትዮጵያ በቱሪዝም ዘርፉ የተሻለ ተጠቃሚ ለመሆን የሚያስችሉ ብዙ የቱሪስት መስህቦች፣ፓርኮች እና መዝናና ማዕከሎች በመገንባት ወደስራ እንዲገቡ በማድረግ ላይ ትገኛለች፡፡ ለአብነትም የአንድነት ፓርክ፣እንጦጦ ፓርክ፣አላላ ኬላ፣ወንጪ፣ጎርጎራ እና ሌሎችም በርካታ ፓርኮች ለቱሪዝም ኢንዱስትሪው ዘርፍ ፋይዳቸው የጎላ ነው፡፡ ከዘርፉ የላቀ ተጠቃሚነትን እውን ለማድረግ የአክሬዲቴሽን ሚና ከፍተኛ በመሆኑ የሌሎች ሃገራትን ልምድ በመቅሰም ታሳቢ ተደርጎ ቢሰራ የላቀ ውጤት ለማግኘት ይረዳል፡፡
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት
ስልክ 0116671269
የፌስ ቡክ ገጽ EAS-Ethiopian Accreditation Service

Photos from EAS-Ethiopian Accreditation Service's post 20/04/2024

ኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት የአሰሰሮች ካሊብሬሽ አካሄደ
ሚያዝያ 12 ቀን 2016 ዓ.ም
********
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት የአሰሰሮች ካሊብሬሽ በአዳማ ከተማ አካሄደ።
በመድረኩ ላይ የተገኙት የአገልግሎቱ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን አንዱዓለም ባስተላለፉት መልዕክት የአክሬዲቴሽን አገልግሎትን በአገራችን ተደራሽ ለማድረግ የአሰሰሮች ሚና የማይተካ መሆኑን ገልጸው በአሰስመንት ሂደት ሊታዩ የሚችሉ ክፍተቶችን በመለየት ቀጣይ ስራዎቻችንን ይበልጥ የተሻለና ተደራሽ ለማድረግ መድረኩ እንደሚረዳ ለተሳታፊዎች አብራርተዋል። አገልግሎቱ በአፍሪካ የአክሬዲቴሽ ትብብር በዓለም አቀፍ እውቅና ባገኘባቸው ወሰኖች የሚሰጣቸውን የአክሬዲቴሽን አገልግሎት አጠናክሮ ለማስቀጠል በርካታ ተግባራትን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በቅርቡ በሚኒስትሮች ም/ቤት የጸደቀው የአገልግሎቱ ረቂቅ ደንብ በቀጣይ አገልግሎቱ ለሚሰራቸው ስራዎች ፋይዳው የጎላ መሆኑን ጨምረው አብራርተዋል።
በአደጋ ስጋት ስራ አመራር ላይ በአገልግሎቱ የጥራት ስራ አስኪያጅ በአቶ ዘውዱ አየለ ገለጻ ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።
በተሳታፊዎች ከአስተዳደር እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ ለቀረቡ ጥያቄዎች በም/ዋና ዳይሬክተሩ ማብራሪያ ቀርቦ መድረኩ ተጥናቋል። በመድረኩ ላይ 61 የአገልግሎቱ ሰራተኞች እና አሰሰሮች ተሳትፈዋል ።

16/04/2024

አክሬዲቴሽን የትምህርት ስርዓታችንን ለማጠናከር
ሚያዚያ 3 ቀን 2016 ዓ.ም
**********************************************
አክሬቴሽን የትምህርት ጥራትን ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋፅዖ የሚያደርግ ወሳኝ ሂደት ነው። አክሬዲቴሽን የትምህርት ተቋማት ማሟላት ያለባቸውን ግልጽ ደረጃዎች ያስቀምጣል። እነዚህ ደረጃዎች ሥርዓተ ትምህርትን፣ የመምህራን ብቃትን፣ የተማሪ ድጋፍ አገልግሎቶችን እና መገልገያዎችን ጨምሮ የተለያዩ ገጽታዎችን ይሸፍናሉ። እነዚህን መመዘኛዎች በማክበር ጥራትን ለማስጠበቅ ተቋማት ተጠያቂ ይሆናሉ። አክሬዲቴሽን ወጥና ቀጣይነት ያለው የትምህርት አሰጣጥ ሥርዓት መሻሻል ባህልን ያበረታታል። ተቋሞች ፕሮግራሞቻቸውን፣ የማስተማር ዘዴዎቻቸውን እና የተማሪ ውጤቶቻቸውን በየጊዜው እንዲገመግሙ ያደርጋል። የማሻሻያ ቦታዎችን እንዲለዩ እና የትምህርት ጥራትን ለማሳደግ ለውጦችን እንዲተገብሩ ያደርጋል። አክሬዲቴሽን ከሌሎች ተቋማት በመጡ ባለሙያዎች የአቻ ግምገማን ተግባራዊ እንዲያደርጉ በማድረግ ክፍተቶችን ይለያል። እነዚህ የውጭ (ከተቋሙ ውጭ የሆኑ) ገምጋሚዎች ጠቃሚ ግንዛቤዎችን እና ምክሮችን ይሰጣሉ። ተቋማቱ እርስበርስ ከሚያደርጉት ምርጥ ተሞክሮ በመማር ጉድለቶችን ይፈታሉ። አክሬዲቴሽን የአንድን ተቋም ተዓማኒነት እና መልካም ስም ያሳድጋል። አንድ ተቋም ዕውቅና ሲሰጥ ለተማሪዎች፣ ለቀጣሪዎች እና ለሕዝብ እውቅና የሰጣቸውን የጥራት ደረጃዎች ማሟላቱን ያሳያል። ይህ ተዓማኒነት ተማሪዎችን የትምህርት ተቋማትን እንዲመርጡ ያደርጋቸዋል፡፡ አክሬዲቴሽን የትምህርት ተቋማት በተማሪዎች የትምህርት ውጤቶች ላይ እንዲያተኩሩ ያደርጋል። ይህም ተማሪዎች የተወሰኑ የትምህርት ዓላማዎችን እንዳሳኩ ያደርጋቸዋል።
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት
ስልክ 0116671269
የፌስ ቡክ ገጽ EAS-Ethiopian Accredidation Service
ድረ-ገጽ www.eas-eth.org
ኢ-ሜል [email protected]

Photos from FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)'s post 12/04/2024

የሚኒስትሮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ብሔራዊ አክሬዲቴሽን ጽሕፈት ቤትን ለማቋቋም የቀረበ ረቂቅ ደንብ ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው ብሔራዊ የአክሬዲቴሽን ስርዓት በመገንባት የሀገር ውስጥና የውጪ ንግድ እንዲቀላጠፍ፣ የሕብረተሰቡ ጤናና ተጠቃሚነት እንዲሁም የአካባቢ ደህንነት እንዲጠበቅ ብሎም ፍትሐዊ የግብይት ስርዓት እንዲሰፍን በሚያስችል መልኩ ተቋሙን የሚያጠናክር ረቂቅ ደንብ ህኖ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡

09/04/2024

ለመላዉ የእስልምና ተከታዮች በሙሉ እንካን ለኢድ-አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡ የኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት

04/04/2024

አክሬዲቴሽን ለማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ…
መጋቢት 26 ቀን 2016 ዓ.ም
***********************************************
አክሬዲቴሽን በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ውስጥ እውቅና ጥራትን፣ ተቀባይነትን እና ቅልጥፍናን በማረጋገጥ ረገድ ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
አክሬዲቴሽን በማኑፋክቸሪንግ የኢንዱስትሪ ዘርፍ አምራቾች ትክክለኛውን የጥራት እና የእሴት ሚዛን በመጠበቅ ምርቶቻቸው ደንቦችን ፣ ደረጃዎችን እና ዝርዝር መግለጫዎችን መሰረት በማድረግ እንዲያመርቱ በማድረግ በደንበኞቻቸው ዘንድ ተፈላጊ ለመሆን ያስችላቸዋል፡፡
አክሬዲቴሽን አምራቾች ውጤታማ ሂደቶችን ለማረጋገጥ እና በማምረት ሂደት ሊፈጠሩ የሚችሉ ስህተቶችን ለመቀነስ ያግዛል፡፡
እንዲሁም አክሬዲቴሽን አምራቾች ጥራት ያላቸውን ምርቶች በማቅረብ የደንበኞችን ፍላጎቶች እና የቁጥጥር መስፈርቶች ለማሟላት ያስችላል፡፡ በዚህም የምርት ጥራትን አስተማማኝ ሆኖ ለደንበኞች እንዲደርስ ይረዳል፡፡
በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማሩ አምራቾች አክሬዲቴሽን አገልግሎት በመጠቀም በዓለም ገበያ ብቁ ተወዳዳሪ ለመሆን ያስችላቸዋል፡፡
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልገሎት
ስልክ 0116671269
የፌስ ቡክ ገጽ EAS-Ethiopian Accreditation Service
ድረ-ገጽ WWW.eas-eth.org

02/04/2024

አክሬዲቴሽን የድርጅቶች አፋጻጸምን ያሳድጋል
መጋቢት 24 ቀን 2016 ዓ.ም

አክሬዲቴሽን አፈጻጸምን ለማሻሻል ኃይለኛ አንቀሳቃሽ ሲሆን የአመራር ስትራቴጂው ዋነኛ አካል በመሆን የድርጅቶች ባህል የማጠናከር አቅም አለው። እንደ የጥራት ማረጋገጫ ዘዴ እና የጥራት ማሻሻያ ዘዴ በድርጅቶች ጥቅም ላይ ይውላል። የጥራት ማረጋገጫ እና የጥራት መሻሻል በቅርበት የተሳሰሩ ሲሆኑ የአፈፃፀም ክፍተቶችን ለማስወገድ አክሬዲቴሽን እጅግ ጠቃሚ ነው፡፡ በዚህም ድርጅቶች የጥራት ማረጋገጫ አፈጻጸማቸውን ከደንበኞች እርካታ ጋር በማነጻጸር የጥራት ማሻሻያ እንዲተገብሩ በማድረግ በተከታታይ ዕድገት በማስመዝገብ ድርጅቶች ወደፊት እንዲራመዱ ያደርጋል።
አክሬዲቴሽን ለድጅቶች ደንበኞች እንክብካቤ አወንታዊ ተሞክሮ አስተዋፅዖ በማድረግ ከደንበኞች አኳያ መልካም አፈጻጸም እንዲኖራቸው ያደርጋል ። አወንታዊ የተጠቃሚ ተሞክሮን መግለጽ እና መግለጽ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች በመደበኛ ልማት ውስጥ ንቁ ተሳትፎ ካላደረጉ በእውቅና መመዘኛዎች ውስጥ በትክክል መፍታት አይቻልም። አክሬዲቴሽን ደረጃዎች እና የእውቅና አሰጣጥ ሂደት አቀራረብ በእያንዳንዱ የምርትና አገልግሎት አሰጣጥ ሁኔታ ውስጥ ያለ እውነታ መርህ በማድረግ ድርጅቶች ሁሉን አቀፍ የተሻለ አፈጻጸም እንዲኖራቸው በማድረግ ውጤታማነታቸውን ያሳድጋል፡፡
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት
ስልክ 0116671269
የፌስ ቡክ ገጽ EAS-Ethiopan Accreditation Service
ድረ-ገጽ www.eas-eth.org

01/04/2024

አክሬዲቴሽን እንደ ስጋት ቅነሳ ስትራቴጂ
መጋቢት 23 ቀን 2016 ዓ.ም
*****************************************************
የአክሬዲቴሽን እውቅና ማግኘት ውጤታማ የአደጋ ቁጥጥር እና ቅነሳ መሰረት ይፈጥራል። የአክሬዲቴሽን አሰጣጥ ደረጃዎች እና የዳሰሳ ጥናት ሂደት አንድ ድርጅት ትክክለኛ እና ሊከሰቱ የሚችሉ አደጋዎችን በመለየት እና በመገምገም እንዲሁም ክስተትን ለመከላከል እና ለመቀነስ የሚያግዙ ተግባራትን በመተግበር ሂደት ተከትሎ የሚሰጥ ነው ። አንድን ድርጅት ከተዛባ ክስተት በኋላ ምላሽ ከመስጠት ወደ ቀጣይነት ያለው ንቁ የአደጋ አስተዳደር አካሄድ ለማሸጋገር አክሬዲቴሽን ሚናው የጎላ ነው፡፡
እንዲሁም በኢንሹራንስ ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ድርጅቶች በብሔራዊ የአክሬዲቴሽን ሰጪ አካል ዕውቅና ከተሰጣቸው አስተማማኝ የሆነ የስጋት ቁጥጥር ተግባራት ለማከናወን የሚያስችል ጠንካራ መሠረተ ልማት እንዳለው ይወሰዳል። በሌላ በኩል በአክሬዲቴሽን ሂደት አልፈው እውቅና ያገኙ የኢንሹራንስ ድርጅቶች ደንበኞች ለኢንሹራንስ ባላቸው አስተማማኝ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ቁጥጥር ስርዓት መሰረት የሚከፍሉት ዓመታዊ ክፍያ መጠን ከሌሎቹ ተመሳሳይ አክሬዲት ካልሆኑ ደንበኞች ጋር ሲነፃፀር ዝቅተኛ ይሆናል። ይህ ማለት አክሬዲቴሽን ድርጅቶች ጠንካራ የስጋት አስተዳደርን በመተግበር ወጪን ለመቀነስ እና ውጤታማነትን ለማሳደግ ያግዛል፡፡
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልገሎት
ስልክ 01166771269
ፌስ ቡክ ገጽ EAS-Ethiopian Accryditation Service

29/03/2024

ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ጠንካራ የጥራት መሰረተ ልማትን በመገንባት ከቀዳሚዎቹ ተርታ ተሰለፈች
መጋቢት 20 ቀን 2016
****************************************
መንግስት ከፍተኛ በጀት በመመደብ የጥራት መሰረተ ልማት ግዙፍ ተቋማትን መገንባት፣ የአቅም ግንባታ ስራዎችን እንዲሁም የአሰራር ስርዓትን ዝርጋታ ልዩ ትኩረት በመሰጠት ኢትዮጵያ ጠንካራ የጥራት መሰረተ ልማት ከገነቡ 6 የአፍሪካ አገራት አንዷ መሆን መቻሏን የጥራት መሰረተ ልማትና ማረጋገጫ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ እንዳለው መኮንን መግለጻቸውን ከንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የማህበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘ መረጃ አመልክቷል ፡፡
የብሔራዊ የጥራት መሰረተ ልማት ተቋማት የቢሮ እና የላብራቶሪ ግንባታ በመገባደድ ላይ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው ጠቁመዋል፡፡
ከጥራት መሰረተ ልማት ተቋማት መካከል የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ባለ 6 ወለል ሕንጻ የቢሮ ግንባታ በመጠናቀቅ ላይ በመሆኑ ለደንበኞቹ የሚሰጣቸውን የአክሬዲቴሽን አገልግሎት እንደሚያሳልጥ ይጠበቃል፡፡ ይህ አገልግሎቱ በአፍሪካ ካሉ ጥቂት የአክሬዲቴሽን ተቋማት ቀዳሚ ያደርገዋል፡፡
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን በሕክም ላቦራቶሪ፣በፍተሻ ላቦራቶሪ ፣በካሊብሬሽን ላቦራቶሪ ፣ ሰርተፊኬሽን እና በኢንስፔክሽን ዓለም አቀፍ እውቅና ያለው የአክሬዲቴሽን አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት
ስልክ 0116671269
የፌስ ቡክ ገጽ EAS-Ethiopian Accreditaton Service
ድረ-ገጽ WWW.eas-eth.org

27/03/2024

አክሬዲቴሽን እና ተጠያቂነት /Accreditation and Accountability/
መጋቢት 18 ቀን 2016 ዓ.ም
******************************************
አክሬዲቴሽን ከ100 ዓመታት በፊት በአሜሪካ ዩኒቨርስቲዎች እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተገነባ እና በዋናነት የትምህርት ደረጃዎችን የተከተሉ ትምህርት ቤቶችን ለመለየት በፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ የጥራት ማረጋገጫ ዘዴ ነው። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ አክሬዲቴሽን ግብአቶችን ብቻ ማዕከል ካደረገ እንቅስቃሴ ወደ በጥናት ላይ የተመሰረተ የተቋም ውጤታማነት አጠቃላይ ግምገማ ስርዓት ገብቷል። ይህም አክሬዲቴሽን የተስማሚነት ምዘና ተቋማት የተወሰኑ ተግባራትን ለማከናወን መቻላቸውን በመገምገም የ3ኛ ወገን የብቃት ማረጋገጫ እውቅና በመስጠት የምርትና አገልግሎት ጥራትን ለማረጋገጥ ይሰራል፡፡
ተጠያቂነትም ተቋማት ለደንበኞቻቸው የሚያቀርቧቸው ምርትና አገልግሎቶች መሻሻል እና የተቀመጡ መስፈርቶች ማሟላታቸውን ማረጋገጫ እንዲያቀርቡ ያደርጋል። አክሬዲቴሽን ተጠያቂነትን ለመወጣት ዋና መሳሪያ ሆኖ ያገለግላል፡፡
አክሬዲቴሽን እና በተጠያቂነት መሻሻልን ለማምጣት የታቀዱ እቅዶችን ማዘጋጀት እና መተግበርን ይጠይቃሉ፤ ግልጽነት፣ ተደራሽነት፣ እና የመረጃ አጠቃቀም ላይ ትልቅ ዋጋ ትኩረት ይሰጣሉ፤ ውጤታማነትን ለማሳደግ በተወሰነ ደረጃ የማሻሻያ እቅድ አፈፃፀም የውጭ ክትትልን ይጠቀማሉ፡፡
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት
ስልክ 0116671269
የፌስ ቡክ ገጽ EAS-Ethiopian Accreditation Service
http://xn---www-zpsx1e4dqr.eas-eth.org/

26/03/2024

አክሬዲቴሽን የጤና እንክብካቤ ጥራት ዋስትና
መጋቢት 17 ቀን 2016 ዓ.ም
*****************************************************
አክሬዲቴሽን ብቃት ባላቸው የውጭ አቻ ገምጋሚዎች/External Assossers/ ግምገማን የሚያካትት ወሳኝ የግምገማ ሂደት ሲሆን የጤና አገልግሎት ሰጭ አካላትን ከደህንነት እና ከጥራት ደረጃዎች ጋር መጣጣምን ይገመግማሉ። እንዲሁም አስተማማኝ እና ከፍተኛ ጥራት ያለው የጤና እንክብካቤን የሚያበረታቱ ቀጣይነት ያለው የጥራት ማሻሻያ ስልቶች እንዲውሉ ያስችላል፡፡
ይህም የጤና እንክብካቤ ተቋማት የተወሰኑ መመዘኛዎችን እንደሚያሟሉ እና ያለማቋረጥ ለላቀ ስራ መጥራታቸውን ያረጋግጣል።
አክሬዲቴሽን የጤና እንክብካቤ ጥራትን በማሻሻል ረገድ ተመራማሪዎች እና ፖሊሲ አውጪዎች የጤና አጠባበቅ እውቅና ፕሮግራሞች የጤና አጠባበቅ አገልግሎቶችን ጥራት ለማሳደግ እና ለጤና አጠባበቅ ድርጅቶች የተሻለ አጠቃላይ አፈፃፀም እንዲኖራቸው አስተዋፅኦ እንዳላቸው ግንዛቤ ይፈጥራል፡፡ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የጤና አጠባበቅ ድርጅቶች እና ተመራማሪዎች በሆስፒታል ውስጥ ባሉ የዕውቅና መርሃ ግብሮች ውጤታማ ትግበራ እና ዘላቂነት ቁልፍ ጉዳዮችን ግምት ውስጥ ማስገባት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ያደርጋል፡፡
የአክሬዲቴሽን አካላት በውጫዊ ጥራት ማሻሻል ላይ ወሳኝ ሚና ይጫወታሉ፡፡ የህግ አውጭ ግዴታዎች፣ የቁጥጥር መስፈርቶች፣ የገበያ ፍላጎቶች እና የጤና እንክብካቤ አቅራቢዎች የጥራት ማሻሻያ ጥረቶች በሁሉም የአክሬዲቴሽን አካላት በኩል በጤና አጠባበቅ ጥራት ማረጋገጫ ላይ አስተዋፅዖ ያደርጋሉ።.
አክሬዲቴሽን አውዳዊ ምክንያቶች እና አተገባበር በተመለከተ የኖርማላይዜሽን ሂደት ንድፈ ሃሳብ የአክሬዲቴሽን አተገባበር ላይ ተጽእኖ ሊሳድሩ በሚችሉ ጉዳዮች ላይ ግንዛቤዎችን ይሰጣል። ትኩረቱ ብዙውን ጊዜ በእውቅና አሰጣጥ ሂደት ላይ ያተኮረ ቢሆንም፣ ለጤና ባለሙያዎች ሚና፣ የተሳትፎ ስልቶች እና ስለ ዕውቅና ግቦች እና ጥቅሞች ግልጽ ግንኙነት ትኩረት ይሰጣል።
አክሬዲቴሽን የጤና አጠባበቅ ጥራትን ለመገምገም እና ለማሻሻል እንደ ጠቃሚ መሳሪያ ሲሆን የጤና አጠባበቅ ሥርዓቶችን በማሻሻል የላቀ የአገልግሎት ደረጃን በማረጋገጥ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ውጤታማ የታካሚ እንክብካቤ ተግባራዊ ያደርጋል፡፡
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት
ስልክ ቁጥር 0116671269
የፌስ ቡክ ገጽ EAS-Ethiopian Accreditation Service

25/03/2024

አክሬዲቴሽን የጨርቃጨርቅ ምርቶች ጥራትን ያረጋግጣል
መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ.ም
******************************************
የጨርቃጨርቅ ሰርተፊኬሽን ለጨርቃ ጨርቅ ምርቶች ወይም የተወሰኑ ደረጃዎችን ለሚያሟሉ ሂደቶች የተሰጠ መደበኛ እውቅና ሲሆን በጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ ውስጥ ጥራትን፣ ዘላቂነትን እና ተገዢነትን በማረጋገጥ ረገድ ወሳኝ ሚና ይጫወታሉ።
የሰርተፊኬሽን አካላት እውቅና ካላቸው የአክሬዲቴሽን አካላት የእውቅና ሂደቶችን በማከናወን እና አክሬዲት በመሆን የጨርቃጨርቅ ምርቶችን ለሚያመርቱ ድርጅቶች የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎት ይሰጣሉ።
የአክሬዲቴሽን እውቅናው የሰርተፊኬሽን አካላት በተቀመጡ መስፈርቶች እንዲሰሩ፣ ስህተቶችን ነቅሰው እንዲያርሙ እና የጨርቃጨርቅ ፋይበርን ውስጣዊ እሴትን እንደሚጠብቁ ማረጋገጫ ሲሆን ይህም በተጠቃሚዎች ላይ እምነት እንዲፈጠር ያደርጋል።
የሰርተፊኬሽን አካላት በአቅርቦት ሰንሰለቱ የአካባቢ ፣ የማህበራዊ እና የእንስሳት ደህንነት ያረጋግጣሉ፡፡
በጨርቃ ጨርቅ ምርቶች ውስጥ ኩባንያዎች እና ሸማቾች እንደ ኦርጋኒክ እና እንደገና ጥቅም ላይ የዋሉ ያሉ የዘላቂነት ጥያቄዎችን እንዲያረጋግጡ ያስችላቸዋል።
የጨርቃጨርቅ ሰርተፊኬሽን የጥራት ደረጃዎችን መከበራቸውን ያረጋግጣሉ፣ የደንበኞችን እምነት ያሳድጋሉ እንዲሁም በጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ ውስጥ ዘላቂ አሰራር እንዲኖር አስተዋፅዖ ያደርጋሉ።
የኢትዮያጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት
ስልክ 0116671269
የፌስ ቡክ ገጽ EAS-Ethipian Accreditation Service
ድረ-ገጽ WWW.eas-eth.org

20/03/2024

ዓመታዊ መደበኛ የተሽከርካሪ ቁጥጥር ዓለም አቀፍ መስፈርቶች በጥቂቱ
መጋቢት 11 ቀን 2016 ዓ.ም
*************************************
የኢንስፔክሽን ምርመራ ለሚያደርጉ አካላት የተሸከርካሪን እንዲሁም ለተለያዩ የፍተሻ ዓይነቶችን በዓለም አቀፍ ደረጃ ISO / IEC 17020: 2012 መስፈርትን መሰረት በማድረግ ይሰራሉ።
የኢንስፔክሽን አካላቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያለው አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን የኢንስፔክሽን እውቅና ከአክሬዲቴሽን አገልግሎት ሰጭ ተቋም ማግኘት የሚጠበቅባቸው ሲሆን በድርጊታቸው ነፃ እና ገለልተኛ መሆናቸውን ማሳየት አለባቸው። እንዲሁም የኢንስፔክሽን ውጤቶችን ምስጢራዊነት ማረጋገጥ የሚጠበቅባቸው ሲሆን ውጤታማ ድርጅታዊ አወቃቀሮች ፣ የአስተዳደር ስርዓቶች ፣ እውቀት ያላቸው ብቁ ባለሙያዎች ሊኖራቸው ይገባል።
ምርመራ ለማድረግ በቂ መገልገያዎች እና መሳሪያዎች ፤ተከታታይነት ያለው ውጤት ለማግኘት የፍተሻ አካላት ደረጃቸውን የጠበቁ ዘዴዎችን እና ሂደቶችን መከተል ፤ዓምታዊ የተሽከርካሪ ምርመራ ኢንክከሽን በዓለም አቀፍ ደረጃዎች መስፈርት መሠረት ማከናወን፤ ይጠበቅባቸዋል።
ኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት
ስልክ 0116671269
የፌስ ቡክ ገጽ EAS-Ethiopian Accreditation Service
ድረ-ገጽ WWW.eas-eth.org

19/03/2024

የአፍሪካ አክሬዲቴሽን ትብብር (AFRAC)
መጋቢት 10 ቀን 2016 ዓ.ም
*********************************************
የአፍሪካ አክሬዲቴሽን ትብብር የአክሬዲቴሽን አገልግሎት አካላት ሰጪ እና ባለድርሻ አካላት ማህበር በመሆን እ.ኤ.አ በ2010 የክፍለ-አህጉራዊ አክሬዲቴሽን ትብብር በመሆን የተመሰረት ትብብር ነው።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያለው የጋራ እውቅናን ለማስቀጠል በአፍሪካ አክሬዲቴሽን ውስጥ አቅምን ለመገንባት መተባበርን ተልዕኮው በማድረግ ይሰራል ።
የአፍሪካ አክሬዲቴሽን ትብብር ዋና አላማ ለኢንዱስትሪ እና ለንግድ የዕውቅና ድጋፍ መስጠት ሲሆን ለሕዝብ ጤና እና ደህንነት እንዲሁም ለአካባቢ ጥበቃ አስተዋጽኦ ያደርጋል።
የአፍሪካ አክሬዲቴሽን ትብብር አባላት በብሔራዊ መንግሥቶቻቸው በይፋ እውቅና አግኝተው የሚሰሩ ሲሆን የተስማሚነት ምዘና አገልግሎት የሚያካሂዱ ድርጅቶችን ከዓለም አቀፍ ደረጃዎች መሰረት አገልግሎት እንዲሰጡ ያደርጋሉ።
የአፍሪካ አክሬዲቴሽን ትብብር በአፍሪካ እክሬዲቴሽን ውስጥ አቅምን ለመገንባት ይተጋል። ዋና ትኩረቱ ከዓለም አቀፍ ደረጃዎች ጋር የሚጣጣም የጋራ ስምምነትን መተግበር ሲሆን በተያያዘም ትብብርን በማጎልበት፣ በአፍሪካ ውስጥ የእክሬዲቴሽን ሂደቶችን ታማኝነት እና አስተማማኝነት ለማሳደግ ያለመ ትብብር ነው።

ኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት
ስልክ 0116671269
የፌስ ቡክ ገጽ EAS-Ethiopian Accreditation Service
ድረ-ገጽ WWW.eas-eth.org

Photos from EAS-Ethiopian Accreditation Service's post 15/03/2024

የካቲት 20 ቀን 2016 ዓ.ም አዲስአበባ
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በልዩ ልዩ መስኮች ዓለም አቀፍ እውቅና አገኘ፡፡
የ ዓለም አቀፍ አክሬዲቴሽን ፎረም (IAF) በምርት ሰርቲፊኬሽን product certification-ISO/IEC17065(12 February 2024) እንዲሁም የዓለም አቀፍ አክሪዲቴሽን ላብራቶሪ ትብብር (ilac)
• በ Testing ISO/IEC 17025-20 October 2017
• በ Testing ISO 15189-28 October 2017
• በ Inspection ISO/IEC 17020 -23 October 2019
• በ Calibration ISO/IEC 17025-13 February 2024
የእዉቅና ምስክር ወረቀት አግኝቶል፡፡

15/03/2024

የሶፍትዌር አልሚዎች
መጋቢት 06 ቀን 2016 ዓ.ም
*******************************
የሶፍትዌር ልማት ኩባንያ ማግኘት ከሚገባቸው በጣም አስፈላጊዎቹ የISO ሰርተፊኬቶች መካከል የመረጃ ደህንነት ISO/IEC 27001 እና የጥራት ስራ አመራር ISO 9001 ተጠቃሽ ናቸው።
በመረጃ ደህንነት ላይ ያተኮሩ የዓለም አቀፍ ደረጃዎች ስብስብ አካል የሆነው “ISO/IEC 27001” ሰርተፊኬት ዕውቅና ማግኘት ይጠበቅባቸዋል። አላማው ጠቃሚ መረጃን በአስተማማኝ ሁኔታ ለመያዝ፣ ለማከማቸት እና ለመጠበቅ የሶፍትዌር ልማት ድርጅቶችን ግልጽ የሆነ ማዕቀፍ ማቅረብ ነው። ይህ በተለይ ለሶፍትዌር ኩባንያዎች ብዙውን ጊዜ ሚስጥራዊነት ያለው መረጃ ስለሚያስተናግዱ እና መረጃቸው በእነሱ ላይ ደህንነቱ የተጠበቀ መሆኑን ለደንበኞቻቸው ማረጋገጥ ስለሚያስፈልጋቸው በጣም አስፈላጊ ነው።
ISO 9001 ጥራት በማረጋገጥ ላይ የሚያተኩር ሲሆን የISO 9001 መስፈርቶችን የሚያከብሩ ኩባንያዎች እና አጋሮቻቸው ለደንበኞች ጥራት ያላቸው ምርቶችን እና አገልግሎቶችን ያለማቋረጥ የማቅረብ ችሎታቸውን እንዲያሳዩ ያግዛቸዋል። ISO 9001 መስፈርቶች እንደ የድርጅቱ አውድ ፣ አመራር ፣ እቅድ ፣ ድጋፍ ፣ አሠራር ፣ የአፈፃፀም ግምገማ እና መሻሻል ባሉ ጥቂት ቁልፍ ቦታዎች ላይ ኩባንያዎቹ እንዲያተኩሩ በማድረግ ውጤታማ እንዲሆኑ ያደርጋል።
ኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት
ስልክ 0116671269
የፌስ ቡክ ገጽ EAS-Ethiopian Accreditation Service
ድረ-ገጽ WWW.eas-eth.org

13/03/2024

የሥራ አካባቢ ጤንነትና ደህንነት ሥራ አመራር ሥርዓት አስፈላጊነት
መጋቢት 04 ቀን 2016 ዓ.ም
***************************
የሥራ አካባቢ ጤንነትና ደህንነት ሥራ አመራር ሥርዓት መተግበር በስራ ቦታ ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን ለመቀነስ እና ለሙያ ጤና እና ደህንነት ቁርጠኝነትን ለማሳየት ለሚፈልጉ ድርጅቶች ከፍተኛ ጠቀሜታ ይሰጣል።
የሥራ አካባቢ ጤንነትና ደህንነት ሥራ አመራር ሥርዓት የሙያ ጤና እና ደህንነት አደጋዎችን ለመቆጣጠር ዓለም አቀፍ እውቅና ያለው ማዕቀፍ ተግባራዊ የሚያደርግ ሲሆን ድርጅቶች አደጋዎችን ስልታዊ በሆነ መልኩ እንዲገመግሙ እና የአደጋ መከላከያ እርምጃዎችን እንዲተገብሩ ያስችላቸዋል። ይህም በስራ ቦታ ላይ ጉዳቶችን፣ በሽታዎችን እና አደጋዎችን ይቀንሳል።
ለውጭ ባለድርሻ አካላት ድርጅቱ የሰራተኛ ጤና እና ደህንነት ለማረጋገጥ ቁርጠኛ መሆኑን በማሳየት መልካም ስምን ለመገንባት ያግዛል።እንዲሁም የኢንሹራንስ አረቦን ሊቀንስ የሚችል፣ ንቁ የአደጋ አያያዝን ያበረታታል።
የአደጋ ጊዜ ዝግጁነት እና ምላሽ ፕሮቶኮሎችን በመተግበር ከደህንነት ስጋቶች እና ቀውሶች ድርጅታዊ የመቋቋም አቅምን ያጠናክራል።
የዕቅድ ማዕቀፍ ሥርዓት ያለማቋረጥ በማሻሻል እና በሳደግ የረጅም ጊዜ ሠራተኛ ጤና እና ደህንነት አፈጻጸምን ያሳድጋል።
የሥራ አካባቢ ጤንነትና ደህንነት ሥራ አመራር ሥርዓት ድርጅቶች ሰራተኞቻቸውን በተሻለ ሁኔታ እንዲጠብቁ እና የሙያ ጤና እና ደህንነት አደጋዎችን ለመከላከል የሚስችል በመሆኑ በዓለም ዙሪያ አስፈላጊ ያደርገዋል።
ኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት
ስልክ 0116671269
የፌስ ቡክ ገጽ EAS-Ethiopian Accreditation Service
ድረ-ገጽ WWW.eas-eth.org

12/03/2024

የሥራ አካባቢ ጤንነትና ደህንነት ሥራ አመራር ሥርዓት ሰርተፊኬሽን
መጋቢት 03 ቀን 2016 ዓ.ም
******************************************
የሥራ አካባቢ ጤንነትና ደህንነት ሥራ አመራር ሥርዓት ሰርተፊኬሽን ለሙያ ጤና እና ደህንነት ሥራ አመራር ሥርዓት መስፈርቶችን ዓለም አቀፍ ደረጃ ተገባራዊ ለማደረግ ይረዳል። የሥራ አካባቢ ጤንነትና ደህንነት ሥራ አመራር ሥርዓት ለድርጅቶች አደጋዎችን ለመቆጣጠር እና የባለሙያን የሥራ አካባቢ ጤናና ደህንነትን ለማረጋገጥ የሚረዱ አፈጻጸምን ለማሻሻል ማዕቀፍ ያቀርባል።
የሥራ አካባቢ ጤንነትና ደህንነት ሥራ አመራር ሥርዓት ፖሊሲ፣ ዓላማዎች፣ እቅድ፣ ትግበራ፣ አሠራር፣ ኦዲት እና ግምገማ መስፈርቶችን ያስቀምጣል። ዋና ዋና ነገሮች የአመራር ቁርጠኝነትን፣ የሰራተኛ ተሳትፎን፣ የአደጋን መለየት እና የአደጋ ግምገማ፣ የህግ እና የቁጥጥር አሰራር፣ የአደጋ ጊዜ እቅድ፣ የአደጋ ምርመራ እና ቀጣይነት ያለው መሻሻል ያካትታሉ።
ISO 45001 የጤና እና የደህንነት ስጋቶችን ስልታዊ በሆነ መንገድ ለመቆጣጠር የዕቅድ ተግባር የእርምጃ ዘዴ ይጠቀማል። በሁሉም መጠኖች ድርጅቶች ላይ የሚተገበር ሲሆን ከሌሎች የሥራ አመራር ሥርዓት ደረጃዎች ጋር በመጣመር ሥራ ላይ ሊውል ይችላል።
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት የሥራ አካባቢ ጤናና ደህንነት ሥራ አመራር ሥርዓት ሰርትፊኬሽን አገልግሎትን የሚሰጥ ሲሆን የአምራች ኢንዱስትሪዎች እና አገልግሎት ሰጭ አገልግሎቱን በመጠቀም የምርትና ምርታማነታቸውን ለማሳደግ ይችላሉ።
ኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት
ስልክ 0116671269
የፌስ ቡክ ገጽ EAS-Ethiopian Accreditation Service
ድረ-ገጽ WWW.eas-eth.org

11/03/2024

የአክሬዲቴሽን ኢኮኖሚያዊ እንድምታ
መጋቢት 02 ቀን 2016 ዓ.ም
********************************************
አክሬዲቴሽን በአገር ውስጥ ኢኮኖሚ እና በአለም አቀፍ ንግድ ላይ ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
ለሀገር ውስጥ ኢኮኖሚ
አክሬዲቴሽን ንግዶች እና ድርጅቶች የቁጥጥር እና የህግ ኃላፊነቶችን እንዲያሟሉ ይረዳል። ከሰው ጤና፣ ከአካባቢ ጥበቃ እና ከሌሎች ወሳኝ አካባቢዎች ጋር በተያያዙ ውሳኔዎች ላይ እርግጠኛ አለመሆንን ይቀንሳል።
የንግድ አጋሮችን አስተማማኝነት እና የብቃት በማረጋገጥ ዕውቅና በመስጠት የተረጋጋና የበለፀገ የሀገር ውስጥ ገበያ እንዲኖር አስተዋጽኦ ያደርጋል።
ዓለም አቀፍ ንግድ
እውቅና መስጠት በሸቀጦች እና አገልግሎቶች ጥራት እና ደህንነት ላይ እምነትን በመስጠት ዓለም አቀፍ ንግድን ያመቻቻል።
አገሮች በዓለም አቀፍ ገበያ እንዲሳተፉ የሚያስችል የጋራ ስምምነት ያላቸው ዝግጅቶችን እንዲያደርጉ ይረዳል።
ገዢዎች እና ሻጮች የድንበር ተሻጋሪ ግብይቶችን በማበረታታት በተረጋገጠ የተስማሚነት ምዘና መረጃ ላይ እምነትን ይፈጥራል።
አክሬዲቴሽን ጥራትን ማረጋገጥ ብቻ ሳይሆን ለኢኮኖሚ ዕድገት፣ ለፈጠራ እና በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ ለመስጠት ወሳኝ አንቀሳቃሽ መሳሪያ ነው።
ኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት
ስልክ 0116671269
የፌስ ቡክ ገጽ EAS-Ethiopian Accreditation Service
ድረ-ገጽ WWW.eas-eth.org

Photos from EAS-Ethiopian Accreditation Service's post 08/03/2024

አገልግሎቱ 113ኛውን የሴቶች ቀን በዓልን አከበረ
“ሴቶችን እናብቃ፤ልማትና ሰላምን እናረጋግጥ”
የካቲት 29 ቀን 2016 ዓ.ም
********************************************
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ113 በኢትዮጵያ ለ48ኛ ጊዜ የሚከበረውን የሴቶች ቀን በዓልን “ሴቶችን እናብቃ፤ልማትና ሰላምን እናረጋግጥ” በሚል መሪ ቃል በአዳማ ከተማ አከበሩ፡፡
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን አንዱዓለም በበዓሉ ላይ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ሴቶች በእናትነት ሚናቸው የላቁ መሆናቸውን በመግለጽ ከግል ሕይወታቸው አስተማሪ የሆነ መረጃን ለተሳታፊዎች አጋርተዋል፡፡ ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ለተሳታፊዎች እንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
በበዓሉ ላይ በሀገራችን በዘመናቸው ታላላቅ ታሪክ የሰሩ በርካታ ሴቶች ላይ መረጃ የሚሰጥ ገለጻ በአገልግሎቱ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቡድን መሪ በወ/ሮ አዜብ ሰለሞን ለተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን በተመሳሳይ ሙስናና ብልሹ አሰራር በሴቶች ላይ የሚሳድርው ማህበራዊ ችግርና መፍትሄው ላይ ያተኮረ ገለጻ በአገልግሎቱ የስነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ሥራ አስፈጻሚ በአቶ ታከለ ደርሶ ቀርቧል፡፡
በሌላ በኩል የአገልግሎቱ የ2016 በጀት ዓመት የስምንት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም በአገልግሎቱ የዕቅድና ስትራቴጂክ ጉዳዮች ሥራ አስፈጻሚ በአቶ ዋለልኝ አድማሱ ቀርቦ ውይይት ተደጓል፡፡
ውይይቱን አቶ ወንድወሰን አንዱዓለም በመምራት ተቋማችንን ውጤታማ ለማድረግ ሁሉም የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች በትጋት መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡

Photos from EAS-Ethiopian Accreditation Service's post 07/03/2024

ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም የሚከበረው የዓለም አክሬዲቴሽን ቀን በዓል ትኩረቶች
የካቲት 28 ቀን 2016 ዓ.ም
*********************************************
የዘንድሮው የዓለም አክሬዲቴሽን ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ከቴክኖሎጂ እስከ መጓጓዣ፣ ከዘላቂነት እስከ ደህንነት በማካተት እስከ ፈጠራ ድረስ የተለያዩ የህይወት ዘርፎችን በመቅረጽ ረገድ በዓለማችን ለውጥ ለማምጣት የአክሬዲቴሽን ሚና የጎላ መሆኑን በማስገንዝብ ላይ ትኩረት ያደርጋል።የዓለም አቀፍ አክሬዲቴሽን ፎረም እና የዓለም አቀፍ የላብራቶሪ አክሬዲቴሽን ትብብር አክሬዲቴሽን የፈጠራ ቴክኖሎጂዎችን ማዳበር እንዴት እንደሚያስችል እና እነዚህን ቴክኖሎጂዎች ለማቀናጀት እና ለማስፋት እንዴት እንደሚያመቻች በተለይ በኢንዱስትሪዎች እና በአቅርቦት ሰንሰለቶች ትክክለኛነት፣ ደህንነት እና ጥራት ወሳኝ ሁኔታዎችን ይቃኛል። የሳይበር ደህንነትን እና ግላዊነትን መደገፍን ጨምሮ በዲጂታል ቴክኖሎጂዎች ላይ እምነትን በማሳደግ የአክሬዲቴሽን ሚና ላይ በበዓሉ ትኩረት ካገኙ ጉዳዮች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። እንዲሁም አክሬዲቴሽን ዘላቂነትን እንዴት እንደሚደግፍ፣ ነጋዴዎች እና ሸማቾች በመረጃ ላይ የተመሰረተ ምርጫ እንዲያደርጉ ማገዝን ያካትታል። በተለያዩ አካባቢዎች የዓለም አቀፍ አክሬዲቴሽን ፎረም የአክሬዲቴሽን ዝግጅት ስምምነቶች(MLA) እና የዓለም አቀፍ የላብራቶሪ አክሬዲቴሽን ትብብር የጋራ እውቅና ዝግጅት ስምምነቶች (MRA) ድርጅቶች ከጂኦግራፊያዊ እና የኢንዱስትሪ ድንበሮች እንዲሻገሩ ለማስቻል ወሳኝ ሚና ይጫወታሉ።ይህ ጭብጥ ከብዙ የተባበሩት መንግስታት የዘላቂ ልማት ግቦች (SDGs) በተለይም SDG 2 (ዜሮ ረሃብ) ፣ SGD 6 (ንፁህ ውሃ እና ሳኒቴሽን)፣ SDG 7 (ተመጣጣኝ እና ንጹህ ኢነርጂ)፣ SDG 9 (ኢንዱስትሪ፣ ፈጠራ እና መሠረተ ልማት)፣ SDG 11 (ዘላቂ ከተሞች እና ማህበረሰቦች)፣ SDG 16 (ሰላም፣ ፍትህ እና ጠንካራ ተቋማት) እና SDG 17 (የግቦቹ አጋርነት) ጋር ይዛመዳል።
ስልክ 0116671269
የፌስ ቡክ ገጽ EAS-Ethiopian Accreditation Service
ድረ-ገጽ WWW.eas-eth.org

Photos from EAS-Ethiopian Accreditation Service's post 06/03/2024

የአቅም ግንባታ እና የንብረት አያያዝ ላይ ትኩረት ያደረገ ስልጠና ተሰጠ
የካቲት 27 ቀን 2016 ዓ.ም
********************************************
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ለአሽከርካሪዎችና የሪከርድና ማህደር ሰራተኞች የአቅም ግንባታ እና የንብረት አያያዝ ላይ ስልጠና ሰጠ።
በስልጠናው ላይ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ቦንሳ ባይሳ እንዲሁም የአገልግሎቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን አንዱዓለም በመገኘት መልዕክት አስተላልፈዋል።
አገልግሎቱ ዓለም አቀፍ ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ የሚሰራ በመሆኑ አሽከርካሪዎች የተቋሙ አምባሳደሮች በመሆን በኃላፊነት ስሜት እንዲያገለግሉ ዋና ዳይሬክተሩ አሳስበዋል።
በተመሳሳይ የተቋሙ ውጤት የሁሉም ሰራተኞች የጋራ ድምር ውጤት መሆኑን የገለጹት የአገልግሎቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን አንዱዓለም አሽከርካሪዎች የእጃቸው የያዙዋቸውን ተሽከርካሪዎች ደህንነት የመጠበቅና አገልግሎት የመስጠት የህግና የሞራል ባላደራዎች መሆናቸውን አስገንዝበዋል።

05/03/2024

የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት
ማስታወቂያ
የካቲት 26 ቀን 2016 ዓ.ም
*****************************************************
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 195/2003 የተቋቋመ መንግስታዊ ተቋም ሲሆን የዓለም አቀፍ ዕውቅና ባገኘባቸው በህክምና ላብራቶሪ ፣ በፍተሻ ላብራቶሪ፣በካሊብሬሽን ላብራቶሪ፣ በምርት ሰርተፊኬሽን ፣ በጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ሰርትፊኬሽን እና በኢንስፔክሽን አክሬዲቴሽን ለተስማሚነት ምዘና እና ለህክምና አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ብቃታቸውን በማረጋገጥ ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው የ3ኛ ወገን የላቀ የብቃት ማረጋገጫ ምስክርነት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ አገልግሎቱ በአፍሪካ የአክሬዲቴሽን ተቋማት በቀዳሚዎቹ ተርታ ካሉ 7 ተቋማት አንዱ ሲሆን የሕብረተሰቡን ጤና እና ደህንነት ለማስጠበቅ ፣የአካባቢ ደህንነትን ለማረጋገጥ እንዲሁም ፍትሃዊ የግብይት ሥርዓትን ለማስፈን የበኩሉን አስተዋጽኦ በማበርከት ላይ ይገኛል። እንደአብነትም የኢትዮጰያ አየር መንገድ ለመንገደኞቹ የሚያቀርበውን ምግብ ደህንነትን ለማረጋገጥ የሚያስችለውን የማይክሮ ባዮሎጂ ላብራቶሪ አክሬዲት ማድረግ፣ የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልን የተለያዩ የህክምና ላብራቶሪዎች አክሬዲት ማድረግ እንዲሁም ለኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዝና ድርጅት በፍተሻ ላብራቶሪ፣በኢንስፔክሽን እና በሰርቲፊኬሽን የአክሬዲቴሽን እና ለተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎችና ለግል ድርጅቶች የአክሬዲቴሽን አገልግሎት ሰጥቷል።
“በአንድ ጊዜ ፍተሻ በአንድ አክሬዲቴሽን በሁሉም ቦታ ተቀባይነትን ያገኛሉ!!!”
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት

04/03/2024

በኢንስፔክሽን እና በሰርተፊኬሽን ላይ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ
የካቲት 25 ቀን 2016 ዓ.ም
*****************************************************
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በኢንስፔክሽን እና በምርት ሰርተፊኬሽን ደረጃዎች ፅንሰ ሃሳብ ፣ መስፈርቶች እና አስፈላጊነታቸው ላይ ትኩረት ያደረገ ከየካቲት 19-22/2016 ዓ.ም ለ5 ቀናት በሃዋሳ ከተማ ሴንትራል ሃዋሳ ሆቴል ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡
ስልጠናው በኢንስፔክሽን እና በሰርተፊኬሽን ወሰኖች ላይ ለተሳታፊዎች ግንዛቤ የፈጠረ ሲሆን ተሳታፊዎች የወከሏቸው ድርጅቶች በቀጣይ በተለያዩ ወሰኖች ላይ የአክሬዲቴሽን አገልግሎት ተጠቃሚ በመሆን ምርትና አገልግሎቶቻቸውን በዓለም አቀፍ ገበያዎች ተወዳዳሪ ለማደረግ እንደሚያግዛቸው ይጠበቃል።
በሌላ በኩል ከመንግስት ተቋማት የተሳተፉ የስራ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ከጥራት ጋር ተያይዞ የሚደረጉ የቁጥጥር ስራዎችን ለማጠናከር ስልጠናው ጠቃሚ መሆኑን ተገልጿል።
በስልጠናው ላይ ከሀዋሳ እና ሌሎች ከተሞች ከ16 ተቋማት የተውጣጡ በኢንስፔክሽን፣ በምርት ሰርተፊኬሽን፣ በጥራት ፍተሻ እና ቁጥጥር ማረጋገጥ ዘርፍ ላይ የሚሰሩ ከአምራች ኢንዱስትሪዎች ፣ ከአገልገሎት ሰጭ ተቋማት እንዲሁም የቁጥጥር ስራ የተሰማሩ ከመንግስት ተቋማት የተውጣጡ በአጠቃላይ 32 የስራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።

Photos from EAS-Ethiopian Accreditation Service's post 01/03/2024

“ዓድዋ የጥቁር ሕዝቦች ድል” በሚል መሪ ቃል128ኛው የዓድዋ ድል በዓል ተከበረ
“አንድ ጊዜ ሳይሆን ልሙት እንደገና፣
ለሀገሬ አንድ ሞት አይበቃትምና“
የካቲት 22 ቀን 2016ዓ.ም
**************************************************
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት እና የኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች በጋራ 128ኛውን የዓድዋ ድል በዓል አክብረዋል።
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ቦንሳ ባይሳ እና የኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ መዓዛ አበራ በበዓሉ ላይ በመገኘት የዳቦ ቆረሳ አከናውነዋል።
በበዓሉ ላይ ገለጻ ያቀረቡት የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን አንዱዓለም የዓድዋ ድል በዓል የራሱ የሆነ ቋሚ መታሰቢያ ያልነበረው ቢሆንም ዘንድሮ ለድሉ የሚመጥን የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየምን በመገንባት 128ኛውን የዓድዋ ድል በዓል “ዓድዋ የጥቁር ሕዝቦች ድል!” በሚል መሪ ቃል በልዩ ሁነትና ድምቀት እየተከበረ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
በሀገር ተከብሮና ታፍሮ በነፃነት ከመኖር በላይ ክብር እንደሌለ የገለፁት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ለሀገር ክብርና ነጻነት መሞትም የዜግነት ታላቅ ግዴታና የሚያኮራ ተግባር እንደሆነ ገጣሚ ዮፍታሄ ንጉሴ “አንድ ጊዜ ሳይሆን ልሙት እንደገና፣ ለሀገሬ አንድ ሞት አይበቃትምና“ በማለት ሊቁ የተቀኙትን ለተሳታፊዎች አብራረተዋል።
የአድዋ ድል ኢትዮጵያውያን ብሔራቸው፣ ቋንቋቸው፣ ኃይማኖታቸው፣ ባህላቸውና ሌሎች ልዩነቶች ሳያግዷቸው ፤ሴት ወንድ፣ መሪ ተመሪ፣ ልጅ አዋቂ፤ ከሀገሪቱ አራቱም ማዕዘናት ተሰባስበው መስዋዕትነት በመክፈል የተጎናፀፉት ታላቅ ድል መሆኑን አቶ ወንድወሰን አክለዋል።
በበዓሉ ላይ ገለጻውን ተክትሎ የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ቦንሳ ባይሳ እና የኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ መዓዛ አበራ ከተሳታፊው ጋር ውይይት አድርገዋል።
የአድዋ ድል ፅኑ እውነትን እና እምነትን ባነገቡ አባቶቻችን መስዋዕትነት የተገኘ ብሄራዊ ኩራታችን መሆኑን በመረዳት አንድነታችንን በማጠናከር ለቀጣይ ስራችን መጠቀም እንዳለብን ተሳታፊዎች ገልፀዋል።
በማጠቃለያ ላይ አገራችን የሕዳሴ ግድብ ፣ የባህር በር የማልማት እና ሌሎች ታላላቅ የልማት ፕሮጅክቶችን እውን በማድረግ የተሻለች ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስረክብ መስራት እንደሚገባ ወ/ሮ መዓዛ አበራ ገልፀዋል።
አክለውም የሥራ ሃላፊዎቸና ሰራተኞች ከኪራይ ሰብሳቢነትና ብለሹ አሰራር ነፃ በመሆን ብሎም በመከላከል በአገልጋይነት ስሜት በመስራት ሃገርን ማፅናት እንዳለባቸው አሳስብዋል።
በተመሳሳይ በዓሉ ክብሩን በሚመጥን መልኩ ለትውልድ ለማስተላልፍ በጠቅላይ ሚኒስትሩ መሪነት የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም መገንባቱን የገለፁት አቶ ቦንሳ ባይሳ ለዚህም መሪዎቻችንን ማመስገን ይገባል ብለዋል።
የወጪ ንግዳችንን በማሳደግ አገርን ማበልጸግ የሚቻለው የምርትና አገልግሎት ጥራትን ማስጠበቅ ሲቻል መሆኑን በመግለፅ ተቋሞቻችን የምርት ጥራት ፍተሻ አሰራርን በጥንቃቄ መከወን እንደሚገባቸው አሳሰበዋል።

Want your business to be the top-listed Gym/sports Facility in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Videos (show all)

የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎትማስታወቂያየካቲት 26 ቀን 2016 ዓ.ም*****************************************************የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት...
እውቅና የተሰጣቸው ተቋማት! Fana News.
ትኩረት - በህክምና ላብራቶሪዎች ውስጥ የሚፈጠሩ ስህተቶች
የቀን 7 ሰዓት ቢዝነስ ዜና…ጥር 06 2015 ዓ.ም
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን  አገልግሎት እንደሃገር የመጀመሪያውን የምርት ሰርተፊኬሽን እና በግሉ ዘርፍ የካሊብሬሽን ላብራቶሪ ጨምሮ ለኢንስፔክሽን ለህክምናና ለፍተሻ ላብራቶሪ አጠቃላይ ለ11   ...
ENAO Director General Mr. Araya Fesseha presented keynote speech on Higher Education Curriculum Accreditation Forum Host...
#2 WAD2021-France: Delivering confidence in cloud computing services - COFRAC
#1: WAD 2021 - Meeting the needs of people - Accreditation Supporting the implementation of SDGs
WAD2021
Ethiopian Broadcasting Corporation News on ENAO -Accreditation services
Accreditation - Adding Value to Supply Chains
Its all about ISO & Conformity(Accreditation) to the standards !

Address


Ring Road
Addis Ababa
3898

Other Addis Ababa gyms & sports facilities (show all)
St.George FC Supporter's Page St.George FC Supporter's Page
Kebele 05 Bulding # 096
Addis Ababa

The St. George Club was brought into existence December 1936. If questions like when, where and by w

Addis Ababa Hash House Harriers a.k.a AAHHH a.k.a A2H3 Addis Ababa Hash House Harriers a.k.a AAHHH a.k.a A2H3
Hilton Hotel
Addis Ababa, ADWAAVENUE

The Addis Hash, the highest Hash in Africa (2500 m.), runs every Saturday afternoon, rain or shine, outside the city of Addis Ababa. We meet at 2:00pm at the Hilton Hotel parking l...

Great Ethiopian Run Great Ethiopian Run
Haile Grand, Korebtama Haile Building #2, Room 403
Addis Ababa

🏃🏾 Make running a lifestyle for everyone 🏃🏾‍♀️ 🌍 Biggest road race in Africa🏅 🔗 Be part of the family 👇 https://linktr.ee/greatethrun

Inter Sport Inter Sport
P. O. Box 12878
Addis Ababa

Inter Sport is National Weekly sport news paper which gives coverage for local and international sport events. Especially Football and Athletics. The Newspaper exists since 23 Jan ...

market pulse market pulse
Adisabebe Bola
Addis Ababa, 777692

all sport

Belete bele Belete bele
0919862112
Addis Ababa

Football News Football News
Addis Ababa

We are the source of football news.

Adisu syefu Adisu syefu
Addis Ababa, 9890

Dan World Taekwondo Club Dan World Taekwondo Club
Addis Ababa, SHIBIRIE

World Taekwondo Kick boxing, Muay thai boxing and Aerobics &Fittness Training Club.

hulu bje hulu bje
Addis Ababa

Izadin Imam Abdu Izadin Imam Abdu
Addis Ababa