Addis Ababa Prosperity Party Youth's - ብልፅግና
Creating democrat, vibrant and front line youth that has accepted and ready to implement programs an
#ስፖርት ለወንድማማችነት መንፈስ_መጎልበት መሰረት ነው በሚል መሪ ቃል በጀሞ ወረዳ በብልጽግና ፓርቲ አባላት መካከል የወዳጅነት የእግር ኳስ ጨዋታ ተከናወነ።
ታህሳስ 13/2016 ዓ.ም
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለከተማ ወረዳ ጀሞ ብልፅግና ፓርቲ የወጣቶች ሊግ አባላት እና የቢሮ አባላት መካከል "ስፖርት ለወንድማማችነት መንፈስ መጎልበት መሰረት ነው"በሚል መሪ ቃል የወንድማማችነት የእግር ኳስ ጨዋታ ተካሄደ።
በወንድማማችነት ጨዋታ ላይ የተገኙት የን/ስ/ላ/ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለልኝ ወንዴ እንደተናገሩት ወጣቶች ሁሌም አዳዲስ ነገሮችን የሚፈልጉ በመሆናቸው በተለያዩ ማህበራዊ መሰረት ያሉ አባላትን የሚያቀራርቡ ፕሮግራሞችን መፍጠር በፓርቲው ውስጥ አባላት ወንድማማችነትን እንዲያጠናክሩ እንደሚያደርግ የገለፁ ሲሆን በቀጣይነትም በሁሉም ማህበራዊ መሰረት የሚገኙ የፓርቲያችን አባላት በሚያቀራርቡን እና ኢትዮጵያዊነትን በሚያጎሉ ተግባራት ላይ ቀዳሚ በመሆን አርዓያነታቸውን መግለጥ እና ምሳሌ መሆን እንደሚገባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።
የን/ስ/ላ/ክ/ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ም/ፓርቲ ኃላፊ እና የፕለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ፍራኖል ሞሲሳ እና የን/ስ/ላ/ክ/ከተማ የብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ መርክነህ ያዕቆብ በውድድሩ ላይ የተገኙ ሲሆን አሸናፊ ለሆኑት የወጣት ሊግ ቡድን አባላት የዋንጫ እና የሰርተፍኬት ሽልማት በማበርከት ወንድማማችነትን ማጠናከር የፓርቲን ተልዕኮ በሚፈለገው ልክ ለማሳካት ሚናው የጎላ መሆኑን ገልፀዋል።
የእግር ኳስ ጨዋታ ግጥሚያው በወረዳ ጀሞ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት የተዘጋጀ ሲሆን በተደረገው የእግር ኳስ የወንድማማችነት ግጥሚያ የወጣት ሊግ 5 ቢሮ 3 ግብ በማስቆጠር የዋንጫ አሸናፊ ሆነዋል።
ታህሳስ 11/2016 ዓ.ም
በንፍስ ስልክ ላፍቶ ክፍለከተማ ወረዳ 11 ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ አስተባባሪነት የአቅመ ደካማ ዜጎች ቤት እድሳት ተከናወነ።
የበጋ በጎ ፍቃድ ተግባር የሆነው የአቅመ ደካሞች ቤት እድሳት በ ን/ስ/ላ ክ/ከተማ ወረዳ 11 አስተዳደር በብልፅግና ፖርቲ ወጣቶች ሊግ አስተባባሪነት ከወረዳው በጎ ፍቃጓደኞች በጋራ በመሆን የአቅመ ደካማዎች የቤት እድሳት መርሀ ግብር አከናውኗል ።
በበጋ በጎ ፍቃድ የተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎችን በማስተባበር ለአቅመ ደካማ ዜጎች ቤት ለማደስ የታቀደ ሲሆን በዛሬው እለትም የአንድ የአቅመ ደካማ ቤት እድሳት የወረዳዉ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አሳሱ እንዳለ እና የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሀለፊ ወ/ሮ የአብስራ ልባይ ና የወጣት ሊግ አስተባባሪ ዳዊት አባተ እንዲሁም ሌሎች አመራሮች እና ወጣቶች በተገኙበት የእድሳት ፕሮግራም መርሃ ግብሩን አስጀምረዋል ።
ኪነ-ጥበብ ለሀገራዊ መግባባት በሚል መሪ ቃል
በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶቾ ሊግ አስተባባሪነት የኪነጥበብ ምሽት ተካሄደ።
በፕሮግራሙ ላይ የተለያዩ ስለሀገር አንድነት፣ ስለ ኢትዮጵያዊነት በተለያዩ ተውኔታዊ ዝግጅቶች ቀርበዋል።
የፕሮግራሙን መክፈቻ ያደረጉት የክፍለ ከተማው ወጣት ሊግ ሰብሳቢ ወጣት ግዛው አለሙ እንደገለጸው የፕሮግራሙ ዋና ዓላማው የኪነጥበብ ተሰጥኦ ያለቸውን ወጣቶችን ተሰጥኦዋችውን ማውጣትና ማሳደግ እንዲችሉ እና ለሀገራዊ መግባባት መጎልበት ሚናውን የሚወጣ ዝግጅት እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
የወረዳ 7 ወጣት ሊግ ሰብሳቢ ወጣት ግርማ እንዳለ በበኩሉ በቀጣይ እንደዚህ አይነት ፕሮግራሞችን በማዘጋጀት የወጣቱን የሀገር ወዳድነትና፣ የሀገር አንድነት ለማጠናከር እንሰራለን ብለዋል።
"የአንድነታችን ዓርማና የመጪው ትውልዳችን ልዩ ስጦታ የሆነውን ታላቁ የህዳሴ ግድባችን በማይናወጥ መርህ ፀንተን በተባበረ ክንዳችን ለፍፃሜ እናደርሳለን!!"ወጣት ግዘው አለሙ የልደታ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ አስተባባሪ
በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ብልፅግና ፓርቲ ወጠቶች ሊግ አስተባባሪነት "ታላቁ የህዳሴ ግድባችን የብርሃን ፍላጎታችን፣ የልማት ትልማችንና የቱሪዝም እድገታችን እውን የምናደርግበት ሲሳያችን ነው!"በሚል መሪ ቃል የቦንድ ግዢ ንቅናቄ እየተካሄደ ይገኛል።
በቦንድ ግዢ ንቅናቄ የተገኙ የልደታ ክፍለ ከተማ ወጣት ሊግ አስተባባሪ ወጣት ግዘው አለሙ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በመላው ኢትዮጵያዊያን ተሣትፎ እየተገነባ የሚገኝ ጨለማን ወደ ብርሃን እና ለሙን አፈራችን ወደ ልማት በመቀየር ድህነተን ታሪክ የማድረግ ትልማችን ሊያፋጥን የሚችል ፕሮጀክት እንደሆነ ገልፀዋል።
ወጣት ግዘው አለሙ አክለውም የአንድነታችን ዓርማና የመጪው ትውልዳችን ልዩ ስጦታ የሆነውን የህዳሴ ግድባችን በማይናወጥ መርህ ፀንተን በተባበረ ክንዳችን ለፍፃሜ እናደርሳለን ብለዋል።
ታላቁ የዳሴ ግድባችን እንደ ዓይናችን ብሌን የምናየው የመደመር ትውልድ ታሪካዊ አሻራ ነው ያሉት የወረዳው ወጣት ሊግ ሰብሳቢ ወጣት ሠላማዊት መኮንን ጀምረን ለብርሃን እንዳበቃን ጨርሰን ራዕያችን እውን ለማድረግ ሁለንተናዊ ተሳትፎአችን አጠናክረን እንቀጥላለን በማለት ተናግረዋል።
በቦንድ ሽያጭ ንቅናቄው የወረዳው የወጣት ሊግ አባላት፣ የአከባቢው ነዋሪዎች፣ የንግድ ማህበረሰብ እና ወጣቶች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ከ2500 በላይ ወጣቶች የተሳተፉበት የደም ልገሳ ፕሮግራም በመስቀል አደባባይ ተካሄደ።
"ደም በመለገስ ህይወት እንታደግ" በሚል መሪ ቃል በብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አስተባባሪነት የደም ልገሳ ፕሮግራም ተካሂዷል።
የበጋ በጎ ፍቃድ ተግባር በሆነው በዚህ የወጣቶች የደም ልገሳ ፕሮግራም ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የብልፅግና ፓርቲ አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የዲሞክራሲ ግንባታ ዘርፍ ሃላፊ አቶ የኃላሸት በቀለ እንደተናገሩት የከተማዋ ወጣቶች በበጎ ፍቃድ ተግባር እያከናወኑት ያሉት ተግባር እጅግ ውጤታማ የሆነና ብዙ አቅመ ደካማ ነዋሪችን መደገፍ የቻለ በመሆኑ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ወጣቶች ሊግ ጽ/ቤት ኃላፊ ወጣት መለሰ አባተ በበኩላቸው ሊጉ በክረምት እና በበጋ በጎ ፍቃድ በሚፈጽማቸው ተግባራት ላይ በርካታ ወጣቶች የሚሳተፉበትና በከተማው ወጣቶች መሀል መደጋገፍና በጎ ትብብር ባህል እየሆነ መምጣቱን የገለፁ ሲሆን ወጣቶች ለሀገራዊ አንድነት መጎልበት እየተጫወቱ የሚገኘውን ገንቢ ሚና አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ጠቁመዋል።
ደም ለመለገስ ተራቸው እስኪደርስ በሰልፍ ከሚጠባበቁት ውስጥ ያነጋገርናቸው ወጣቶችም ወጣትነታችውን ሃገራቸውን በሚገነቡ፣ አቅመ ደካማ ነዋሪዎችን በሚደግፉ ተግባራት ላይ በማዋላቸው ደስተኛ መሆናቸውንና መሰል በጎ ተግባራትን አጠናክረው እንደሚቀጥሉበት ገልፀውልናል።
በፕሮግራሙ ላይ የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ጥበቡ በቀለን ጨምሮ የሊጉ አመራሮች እና አባላት ተገኝተዋል።
በቦሌ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ በ11 ዱ ወረዳዎች የ2 ቀናት በወጣቶች ተጠቃሚነት እና በሚድያ አጠቃቀም ዙሪያ ስልጠና ሰጠ
ታህሳስ 2016
ለሁለት ቀን በቆየው ስልጠና ላይ የማህበራዊ ሚድያ አጠቃቀም ለሀገር ግንባታ ለብሄራዊ መግባባት የሚያበረክተው ጉልህ ሚና በወጣቱ በመንግስት መካከል ቀጣይነት ያለው ጥብቅ የኢንፎርሜሽን ትስስር በመፍጠር በሀገር ደረጃ የሚሰሩ ስራዎች ከመደበኛ ልማዳዊ መገናኛ ብዙሃን በተጨማሪ ማህበራዊ ሚድያን በመጠቀም የነቃ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚገባ ተገልጿል።
በተጨማሪም ከወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ ጋር በተያያዘ ስራን ሳናማርጥ መስራት ራሳችንን መለወጥ ለዚህም በስራው ውስጥ ገንዘብ ብቻ ሳይሆን ዕውቀት ሞያ ልምድ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ማየት መልመድ መረዳት እንደሚቻል የተብራራ ሲሆን
ወጣቶችም ለመለወጥ ስናስብ የውስጥ ዕምነት ለምንሰራው ስራ ከፍተኛ ፍላጎት እና ተነሳሽነት ማሳየት በድፍረት በራስ መተማመን ሰርቶ ነገሮችን መቀየር እንደሚገባ አንስተዋል።
መድረኩን የወጣት ሊግ አስተባባሪዎች እና የስራ ዕድል ፅፈት ቤት አመራሮች በጋራ መርተውታል
ቦሌ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ
በውሸትና በሀሰተኛ መረጃ ህብረተሰቡ እንዳይደናገር ሚዲያን በአግባቡ በመጠቀም ስኬታማ የሆነ የመረጃ ልውውጥ እንዲኖር ማደረግ እንደሚገባ ተገለጸ።
ኮልፌ ኮሙኒኬሽን ታህሳስ 8/2016 ዓ ም
የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽ ጽ/ቤት ከወጣቶች ሊግ ጋር በመተባበር "ስኬታማ የህዝብ ግንኙነት እና የነቃ የሚዲያ ተሳትፎ" በሚል መሪ ቃል ለማህበረሰብ አንቂዎች እና ባለደርሻ አካላት ስልጠና ሰጠ።
በስልጠናው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ምርምር ሀይሌ እንደተናገሩት ስልጠናው የማህበረሰብ አንቂዎች በሀገር ገጽታ ግንባታ ላይ ሚናቸውን ለማሳየት እንዲሁም በእያንዳንዱ የህዝብ ግንኙንት ስራዎች ላይ የነቃ ተሳትፎ ለማድረግ እና ህብረተሰቡ የሚፈልገውን ትክክለኛ መረጃ በአግባቡ እንዲደርሰው በማድረግ የውሸትና የሀሰተኛ መረጃ ሰለባ እንዳይሆኑ ያግዛል ብለዋል።
የክፍለ ከተማው ወጣት ሊግ ሰብሳቢ ወጣት ቤተልሄም ትዳሩ በበኩላቸው ስልጠናውን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት ከዕለት ወደ ዕለት የሚዲያ አጠቃቀማችንን በማስተካከል በሀገራችን ገጽታ ግንባታ ዙሪያ ማህበረሰቡ የተሻለ ግንዛቤ ኖሮት ትክክለኛ መረጃዎች ተደራሽነታቸው እንዲጨምር እገዛ የሚያደርግ በመሆኑ እጅግ በጣም አስፈላጊ በመሆኑ ወጣት የማህበረሰብ አንቂዎች በአግባቡ ስልጠናውን መከታተል አለባችሁ ብለዋል።
በአጠቃላይ በማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም እና ትክክለኛ መረጃዎች አጻጻፍ፣በአሉታዊ እና ተጻራሪ አመለካከቶች ማስተካከያ ዙሪያ የስልጠና ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል።
የስልጠናው ተሳታፊዎች ስልጠናው እጀግ በጣም ጠቃሚ እና ለስራዎቻችን አጋዥ በመሆናቸው ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል ሲሉ አስተያይት ሰጥተዋል።
"ለስፖርት እድገት እተጋለሁ ለወጣቱ እቆማለሁ"! በሚል መሪ ቃል የወጣቶች ስፖርታዊ ውድድር በቂርቆስ ወረዳ 09 እና 10 ተካሄደ
**************************
ታህሳስ 07/2016
በሁለቱም ወረዳዎች የሊግ አባላትና የወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት አማካኝነት የተዘጋጀው የእግር ኳስ ውድድር ዋና ዓላማው ወጣቱን በአካል ብቃት ማዳበርና በኢትዮጵያዊ አንድነት ላይ የጋራ አስተሳሰብ እንዲኖረው ማድረግ መሆኑን ከሊጉ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
በአመራርና በሊጉ አባላት እንዲሁም በቀጠናዎች መካከል በተካሄደው በዚህ ውድድር ላይ የክፍለ ከተማው ወጣቶች ሊግ ሰብሳቢ ወይዘሮ ፍፁም ግረፌ ተገኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል። ለአሸናፊዎቹም የዋንጫ ሽልማት አበርክተዋል።
" ሰው ተኮር ተግባር ለሰጪው የህሊና እርካታን ያጎናጽፋል "
ቦሌ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ታህሳስ 2016
🏡🏡🏡🏡🏡🏡🏡🏡🏡
የበጋ በጎ ፍቃድ ተግባር የሆነው የአቅመ ደካሞች ቤት እድሳት በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 11 አስተዳደር በብልፅግና ፖርቲ ወጣቶች ሊግ አስተባባሪነት ከወረዳው በጎ ፍቃድ ጋር በመሆን የአቅመ ደካማዎች የቤት እድሳት መርሀ ግብር አከናውኗል ። በበጋ በጎ ፍቃድ የተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎችን በማስተባበር ለአቅመ ደካማ ዜጎች ቤት ለማደስ የታቀደ ሲሆን በዛሬው እለትም አንድ ቤት የወረዳ የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሀለፊ አቶ አዲሱ ደበላ ና የወጣት ሊግ አስተባባሪ ሚልኪያስ አሰፋ እንዲሁም ሌሎች አመራሮች እና ወጣቶች በተገኙበት የእድሳት ፕሮግራም መርሃ ግብሩን አስጀምረዋል ።
ታህሳስ 2016 ዓ.ም ቦሌ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የችግኝ እንክብካቤ ተደረገ።
ታህሳስ 8/ 2016:- በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ በክፍለ ከተማው ወጣቶች ሊግ አስተባባሪነት የችግኝ እንክብካቤ መርሃ ግብር ተካሂዷል::
በመርሀ ግብሩ የብልፅግና ፓርቲ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለልኝ ወንዴን ጨምሮ የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች እንዲሁም የተለያዩ የወጣት አደረጃጀቶች ተገኝተዋል።
የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለልኝ ወንዴ እንደገለፁት በክረምት ወራት በችግኝ ተከላ ያሳየነው ንቅናቄ በችግኝ መንከባከብ ላይ በመድገም ለአረንጓዴ አሻራ ስራችን መሰረት መጣል ይኖርብናል ብለዋል።
ኃላፊው አክለው እንደገለፁት የደን ሽፋናችንን በማሳደግ ለነዋሪዎቿ የምትመች ውብና አረንጓዴ ከተማ በማድረግ እየተሰራ ባለው ስራ የወጣቶች ተሳትፎ የጎላ መሆኑን በመግለፅ ችግኞችን ውሀ ማጠጣት፣መቆፈርና መንከባከብ የሁሉም ባለ ድርሻ አካላት ሀላፊነት ሊሆን ይገባል ብለዋል።
የክፍለ ከተማው የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባተ አበበ የችግኝ እንክብካቤውን አስመልክቶ የተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎችን እያስተባበርን በአንድ ጀንበር በርካታ ችግኞች በተከልነው አግባብ በበጋ በጎ ፍቃድ ተግባራችን ደግሞ ተንከባክቦ እንዲያድጉ ማድረግ ይጠበቅብናል ብለዋል።
የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ አስተባባሪ ወጣት አብዱልሀኪም ቡልጉ በበኩላቸው ወጣቶች በተለያዩ የልማትና መልካም አስተዳደር ስራዎች ላይ እያደረጉ ያሉት እንቅስቃሴ የሚበረታታ መሆኑን ገልፀው በአረንጓዴ አሻራና ችግኝ ተከላ የታየውን ግለት አሁን ደግሞ በእንክብካቤ ላይ ማስቀጠል ያስፈልጋል ብለዋል።
አረንጓዴ አሻራ የመጭው ትውልድ ቅርስና ውርስ ነው!!
የጉለሌ ክ/ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ አባላት ፣በጎፍቃደኛ የትራፊክ አስተባባሪዎች እንዲሁም የኢትዮ ፊትነስ ማህበር ወጣቶች በክረምት በጎፍቃድ የተተከሉ ችግኞችን በእንጦጦ ፓርክ በመገኘት የችግኝ እንክብካቤ ፕሮግራም አከናወኑ፡፡
ባሳለፍነው 2015/16 ክረምት ዛሬን ነገ እንትከል በሚል መሪ ቃል እንደ ክ/ከተማ በሁሉም ወረዳዎች እንዲሁም በእንጦጦ ፓርክ የችግኝ መትከያ ቦታ በመረከብ ከቁፋሮ እስከ ተከላ በጠቅላላው ሊጉ የክፍለከተማውን ወጣቶች በማስተባበር ከ300 ሺ በላይ ችግኞችን መትከል የቻለ ሲሆን እነዚህ የተተከሉ ችግኞች እንዲጸድቁ የችግኝ እንክብካቤ ንቅናቄ በዛሬው እለት በአእንጦጦ ፓርክ በመገኘገኘት አከናውኗል፡፡
የክፍለከተማው ከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ አበባዬ ደምሴ በፕሮግራሙ ተገኝተው ባስተላፉት መልዕክት ባሳለፍነው ክረምት እንደ ክፍለከተማ ማህበረሰቡን በማስተባበር ከ1.5 ሚሊየን በላይ ችግኞች መትከል የተቻለ ሲሆን የክ/ከተማው ወጣት ሊግ የቁፋሮ ፕሮግራም በቀዳሚነት ከማስጀመር ጀምሮ እስከ ተከላው በነበረን የንቅናቄ ስራ ከፊት ሆኖ ወጣቶችን በማስተባበርና በምምራት ትልቅ አስተዋጾ የነበረው መሆኑን የገለጹ ሲሆን በሀላፊነት የተረከበውን ቦታ ከቁፋሮ እስከ እንክብካቤ ስራ ላይ አባላቱ ስለነበነበራቸው አስተዋጾ አመስግነው በቀጣይ አባላቱ ተግባሩን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል፡፡
የልደታ ክፍለ አስተዳደር በሰላምና በሀገር ግንባታ ዙሪያ ከክፍለ ከተማው ወጣቶች ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ።
መድረኩ "ለሰላምና ለሀገር ግንባታ የወጣቶች ሚና" በሚል መሪ ቃል ተካሂዷል።
የሌደታ ክፍለ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ክብረዓለም ደምሴ እንደገለጹት ሰላምንና ሀገርን ለመገንባት የዜጎች ኃላፊነት በተለይም የወጣቶች ሚና ትልቅ በመሆኑ ወጣቶች ሀገርን በመገንባት በኩል ኃላፊነታቸውን መወጣት ይገባቸል ብለዋል።
ዘላቂ በሆነ መልኩ ሰላምን ለመጠበቅና ብሄራዊ አንድነት እንዲጠናከር ብሄራዊ እሴቶችን ማስገንዘብ ፋይዳው ትልቅ መሆኑን የገለጹት አቶ ክብረዓለም ወጣቶች ብሄራዊ እሴቶችን ተግባራዊ በማድረግ ጠንካራ መንግስትና ዘላቂ ሰላም እንዲኖር ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።
የልደታ ክፍለ ከተማ ወጣቶች ሊግ ሰብሳቢ ወጣት ግዛው አለሙ በበኩላቸው ወጣቶች ኢኮኖሚያዊ ፣ማህበራዊና ፖለቲካዊ ስኬቶች እንዲመዘገቡ በማድረግ በኩል ድርሻቸው ትልቅ ሲሆን ወጣቶች ለሀገር ግንባታ ያላቸውን ኃላፊነት ተረድተው ሰላምን በመጠበቅና ጠንካራ ሀገርን ለመገንባት የበኩላቸውን ኃላፊነት ሊወጡ ይገባል ብለዋል።
"እኔ ለሀገሬ" በሚል መሪ ቃል የወጣቶች የህዳሴ ግድብ ቦንድ ግዢ ንቅናቄ በደማቅ ሁኔታ ተጀምሯል!!"
---------------------------------------------------------
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የወጣቶች ሊግ የወጣቶች የእግር ኳስ ውድድር እና "እኔ ለሀገሬ" በሚል መሪ ቃል የህዳሴ ግድብ ቦንድ ግዢ ንቅናቄ በደማቅ ሁኔታ አስጀምሯል።
በመርሀ ግብሩ መጀመሪያ የወረዳ 5 እና በወረዳ 14 ወጣቶች መካከል በወረዳ 9 ሁለገብ ሜዳ የእግር ኳስ ግጥሚያ የተደረገ ሲሆን የጨዋታውን ማብቃት ተከትሎ 5ሚሊዮን ብር ቦንድ ግዢ የሀገራችንን ወጣቶች ብቻ በማስተባበር ያለመው የህዳሴ ግድብ ቦንድ ግዢ ንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሀ ግብር በወረዳ 9 መሳለሚያ አደባባይ በይፋ ተጀምሯል።
ይህ በወጣቶች ዘንድ ከፍተኛ መነቃቃት እንደሚፈጥር የታመነበትና በአዲስ ከተማ ክፍለ እየተደረገ ባለው የንቅናቄው ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ላይ የክፍለ ከተማው ወጣቶች ሊግ ሰብሳቢ አቶ ያሬድ ተፈራ፣የዘርፉ የወረዳ አመራሮችና ከተለያዩ ወረዳዎችና ወጣቶች በተገኙበት ማስጀመር የተቻለ ሲሆን ወጣቶች ስለ ህዳሴው ግድብ ያላቸውን ተቆርቋሪነት የእኔነት መንፈስ ያሳዩበት መርሀ ግብር ነው።
በቀጣይ በዚህ ንቅናቄ በመሳተፍ ቦንድ በመግዛት ግድቡ እስከፍፃሜው እንዲደርስ እና የትውልድ ባለአደራነት ሀላፊነታቸውን በሚገባ ሁኔታ ለመወጣት በሀላፊነት ስሜት እንደሚንቀሳቀሱ በማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ የተገኙ ወጣቶች ቃል ገብተዋል።
የአርሶ አደር የእርሻ ሠብል መሠብሠብ የበጎ ፍቃድ ተግባር በወረዳ 13 አስተዳደር
የለሚ ኩራ ከፍለ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ወጣት ሊግ ከወረዳ 13አስተዳደር ጋር በጋራ በመሆን "በጎነት ለህብረት" በሚል መሪ ቃል የአርሶ አደር የሠብል ምርት መሠብሠቡን አሳወቀ።
በዚህ የበጎ ፍቃድ ተግባር ላይ በመገኘት ተግባሩን ያስጀመሩት የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 አስተዳደር ዋና ስራ አሰፈፃሚ አቶ ያየህይራድ ዳምጠው እንዳሉት በወረዳችን በርካታ አርሶ አደሮች መኖሪያ እንደመሆኑ መጠን በርካታ የአርሶ አደሩን ጥያቄ መመለስ የቻሉ ስራዎች ተሠርተዋል አሁንም በበጋ የበጎ ፍቃድ ተግባር የአርሶአሩን ጉልበትን ወጪ በመቀነስ ሠብሉን የመሰብሠብ ስራ እየሠራን እንገኛለን ብለዋል።
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የወጣቶች ሊግ አስተባባሪ የሆኑት ኢንጂነር ጫላ አሠፋ በበኩላቸው እንዳሉት የሊጉ አባላት እንዲሁም አመራሮች በህብረት የበጎነት ስራን በመሠራት ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን እየተወጡ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
የጥቁር አንበሳ የአየር ትርዒት እየተካሄደ ነው
***********************
88ኛው የኢትዮጵያ አየር ኃይል የምሥረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት “የጥቁር አንበሳ የአየር ትርዒት” እየተካሄደ ይገኛል።
የኢትዮጵያ አየር ኃይል የተመሠረተበትን ኅዳር 20 ቀን 1928 ዓ.ም መነሻ በማድረግ 88ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን ለተከታታይ ቀናት በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ሲያከብር የቆየ ሲሆን ዛሬ ታኅሣሥ 6 ቀን 2016 ዓ.ም የበዓሉ የማጠቃለያ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው።
የተከልናቸው ችግኞች ፍሬ እንዲያፈሩ የወጣቱ ድርሻ ከፍተኛ ነው
🌳🪴🌴🌱🌿☘️🍀🌲🌲🌲🌵🌿🍁🌱
የቦሌ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ
የቦሌ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ በክረምት የተተከሉትን ችግኞች ውሃ የማጠጣት የመንከባከብ መርሃ ግብር በ5ት ሰፋፊ የችግኝ ተከላ በተካሄደባቸው ወረዳዎች ማለትም ወረዳ 1,5,11,12,13 የወጣትሊጉ አመራሮች አባላት እንዲሁም የወረዳው ፓርቲ አመራሮች በተገኙበት ተካሂዷል ይህ መርሃ ግብር እንደ ቦሌ ክ/ከተማ ብልፅግና ወጣቶች ሊግ በየሳምንቱ በየወረዳው እየተከናወነ መሆኑን በማስታወስ
የአረንጓዴ አሻራ መነሻ አላማው መትከል ብቻ ሳይሆን የተተከሉትን በመንከባከብ ማፅደቅ በደን የተሸፈነ ውብ ማራኪ ለኑሮ ምቹ ዘላቂ አየር ፀባይ ያለው አካባቢን መፍጠር መሆኑን በመገንዘብ ወጣቶች ለአላማችን ታማኝ እና ፅኑ በመሆን በየአካባቢያችን የተከልናቸውን ችግኞች የመንከባከብ ሃላፊነት እና ድርሻም ከፍተኛ መሆን እንደሚገባው የክ/ከተማችን የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ አስተባባሪ ወጣት ሄለን ለገሰ ገልፃለች።
ቦሌ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ታህሳስ 2016
"የኪነጥበብ ስራዎች ከማዝናናት ባሻገር ለሰላምና ለአብሮነት እንዲሁም የወል ትርክትን ለመፍጠር ትልቅ ድርሻ እንዳላቸው ተገለፀ!!
******************************
ታህሳስ 05/2016
የወጣቱን የኪነ ጥበብ ብቃት ከፍ ማድረግን ታሳቢ ያደረገ የኪነጥበብና የስነ ፅሁፍ ምሽት በቂርቆስ ወረዳ 07 ተካሂዷል
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ እና በወረዳ 07 ባህል ኪነ ጥበብና ቱሪዝም ጽ/ቤት እንዲሁም በወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት አማካኝነት የተካሄደው ይህ የወጣቶች የሻማ ምሽት ዋና አላማው በየወረዳውና በየመንደሩ የሚገኙትን ጀማሪ የኪነጥበብ ባለሙያዎችን በማበራታታት እና በማስተዋወቅ ወደ መድረክ እንዲወጡ ከማድረግ ባሻገር ኪነ ጥበብ ለሰላም ለአብሮነት እና ለወል ትርክቶች ያላትን አስተዋጽኦ ለማጠናከር ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።
የኪነ ጥበብ ምሽቱ በተለያየ ርዕስ በሁሉም ወረዳዎች በየሳምንቱ ሲካሄድ መቆየቱን ያስታወሱት በክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት የወጣቶች ሊግ ሰብሳቢ ወይዘሮ ፍፁም ግረፌ በዛሬው እለት በተለያዩ የኪነ ጥበብ ስራዎች መጠናቀቁን ገልፀዋል።
በእለቱም ከቀረበው የግጥም፣ድራማ፤ የወግ እና የመነባነብ ውድድሮች በተጨማሪ የሻሎም ለኢትዮጵያ የባህል ቡድን ባለቤት ወጣት ወንዴ ሻሎም የህይወት ተሞክሮውን ለወጣቶቹ አካፍሏል።
በኪነ ጥበብ ምሽቱ ላይ የተለያዩ የባህል ቡድን አባላት የተለያዩ ጣዕመ ዜማዎችን እና የባህል ውዝዋዜዎችን በማቅረብ ታዳሚዎችን ማዝናናት ችለዋል።
በእለቱም የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዲላላ ሁላላ፣ የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ የወጣት ሊግ ሰብሳቢ ወይዘሮ ፍፁም ግረፌ ተገኝተው ለወጣቶቹ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ለፕሮግራሙ መሳካት አስተዋጽኦ ለነበራቸውም የእውቅና ሰርተፊኬት ተሰጥቷቸዋል።
በክፍለ ከተማው ወረዳ 05 ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ና ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት "ኪነጥበብ ለኢትዮጵያ ብልፅግና" በሚል ርዕስ ምሽት ተዘጋጀ።
ኮልፌ ኮሚኒኬሽን ታህሳስ 05/2016ዓ.ም
የኪነ ጥበብ ምሽቱ ላይ አቶ አለማየሁ ፍቃዱ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ምክትል ና የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ ፣የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፖርቲ ወጣቶች ሊግ ኃላፊ ፣ የወረዳው ከፍተኛ አመራሮች ፣ታዋቂ ሰዎችና የኪነ ጥበብ አፍቃሪያን ታድመዋል።
በምሽቱም የስነ ግጥም፣ወግ፣መነባንብ፣የሰርከስ ትርኢት፣ባህላዊ ና ዘመናዊ ውዝዋዜዎች ቀርበዋል።
" የሌማት ትሩፋት እና የጓሮ አትክልት ስራዎቻችን ለወጣቶች አንዱ የስራ አማራጭ በመሆን ላይ ይገኛሉ" ወጣት አብዱልሃኪም ቡልጉ
የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ በልፅግና ወጣቶች ሊግ አመራሮች በ 3 ወረዳ እየተሰሩ ያሉ የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ስራዎችን ጎበኙ።ጉብኝቱ የተደረገው በ ወረዳ 10፣11 እና 12 ሲሆን በስራው ውጤታማነት እና በዘርፉ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮችን ተዘዋውረው መመልከት ችሏል።
ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ የሌማትና የጓሮ አትክልት ስራዎቻችን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣የኑሮ ውድነትን ከመቀነስ አልፎ አማራጭ የወጣቶች የስራ ዕድል እና የላቀ ተሳትፎ የሚጠይቅ የአካባቢ ፀጋ ሆኖ መገኘቱን የክ/ከተማው ብልፅግና ወጣቶች ሊግ አስተባባሪ ወጣት አብዱልሃኪም ቡልጉ ገልፀዋል።
በተያያዘ ዜናም በርካታ ወጣቶች በተቀናጀ የግብርና ልማት ስራዎች እየተሳተፉ እንደሆነ ገልፀው የተመጣጠነ አልሚና ገንቢ ምግቦችን በቀላሉ በማግኘት እንደሚቻል እና እንደ ከተማም ሆነ እንደ ሀገር ራስን በምግብ የመቻል እንቅስቃሴ ውስጥ ሁሉም እንዲረባረብ መልዕክት በማስተላለፍ ሁሉም የክ/ከተማው ወጣቶች በተለይ በስራ ገበታ ላይ የልሆኑት ባላቸው የአካባቢ ፀጋ ይህንን ተግባር እንዲሞክሩ ጥሪ አስተላልፏል።
ሠላምን ቅድመ ተግባሩ ያደረገው የብልፅግና ወጣት ሊግ አባላትና አመራሮች
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ወጣት ሊግ "እኛ ወጣቶች ለሀገራችን ሠላም ዘብ እንቆማለን" በሚል መሪ ቃል የሊጉ አባላትና አመራሮች የአካባቢያቸውን ሠላም በንቃት እየጠበቁ ይገኛሉ።
በክፍለ ከተማው ያሉ ወጣቶች የመኖሪያ አካባቢያቸውን በንቃት በመጠበቅ የሀገርን ሠላም ለማረጋገጥ መንግስት እያደረገ ያለውን ሂደት በመደገፍ ላይም ይገኛሉ።
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ወጣት ሊግ አስተባባሪ የሆኑት ኢንጂነር ጫላ አሠፋ ወጣቱ በማንኛውም ተግባር ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድን አቅጣጫ በመቀበል በርካታ ተግባር ተኮር ስራዎች ሲሠራ ቆይቷል አሁንም ሠላምን ተቀዳሚ ስራው በማድረግ የሊጉ አባላትና አመራር ትኩረት ሠጥቶ እየሠራ ይገኛል ብለዋል።
የወጣቶችን ተሰጥኦ ማጎልበት ላይ ያተኮረው የኪነ ጥበብ ምሽት ዛሬም በቂርቆስ ወረዳ 09 ተካሄደ ።
**************************
ታህሳስ 04/2016 ዓ.ም
የኪነጥበብ ስራዎች ከማዝናናት ባሻገር ለሰላምና ለአብሮነት እንዲሁም የወል ትርክትን ለመፍጠር ትልቅ ድርሻ እንዳላቸውም በኪነጥበብ መድረኩ ተገልጿል።
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 ባህል ኪነጥበብና ቱሪዝም ጽ/ቤት አዘጋጅነትና በክፍለ ከተማው ወጣቶች ሊግ አስተባባሪነት እየተካሄደ ያለው የኪነ ጥበብ ምሽት ወጣቶች ልዩ ችሎታቸውን የሚያጎለብቱበት፣ የህይወት ተሞክሯቸውን የሚጋሩበትና ልምድ የሚለዋወጡበት መድረክ ሆኖ ቀጥሏል።
ኪነ-ጥበብ ለሀገር ሰላምና እድገት፤ የህዝቦች አንድነትና ወንድማማችነት መልካም እሴቶች ይበልጥ እንዲጠናከሩ በማድረግ ረገድ የማይተካ ሚና አለው ብለዋል ፕሮግራሙን ያስጀመሩት የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሮ ጥሩ ወርቅ አንዳርጌ ገልፀዋል ።
የቂርቆስ ክ/ከተማ ወጣቶች ሊግ ሰብሳቢ ወይዘሮ ፍፁም ግረፌ በበኩላቸው ኪነ-ጥበብ የተለያየ አመለካከት ያለውን የህብረተሰብ ክፍል በማቀራረብና ልዩነቶችን በማቻቻል ፤ህብረ ብሔራዊ ወንድማማችነት እና እህትማማችነት በማጎልበት በሀገሪቱ ሰላም እንዲሰፍንና ልማት እንዲፋጠን እንዲሁም ጠንካራ ሀገረ መንግስት እንዲገነባ በማድረግ ረገድ የሚያበረክተው አስተዋጽአ የላቀ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።
የወረዳው የብልጽግና ፓርቲ ሀለፊ አቶ ጫላ ቸሩ በበኩላቸው ኪነ-ጥበብ ከመዝናኛነት ባለፈ ሌሎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች እንዳሉት በመጥቀስ ወጣቶች ጊዚያቸውን በማይረባ ቦታ ከማጥፋት ወጥተው ያላቸውን ተሰጥኦ በእንዲህ አይነት መድረኮች ላይ ማውጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል ።
በኪነ- ጥበብ ምሽቱ በርካታ ህብረ ብሄራዊ ዝማሬዎች፣ የሀገራችን ብሄር ብሄረሰቦች ዘፈኖችና ውዝዎዜች ፣አስተማሪና አነቃቂ የስነ ፅሑፍ ስራዎችን በታዳጊዎችና በኪነ -ጥበብ ባለሙያዎች መቅረቡን የወረዳው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ዘግቦታል።
ለሀገር ሰላም ዋጋ የሚከፍሉ ለሀገር አንድነት ራሳቸውን የሚሰጡ በርካታ ጀግኖች አሉ። ራሳቸውን አሳልፈው ለህዝብ ለሀገር የሚሰጡ ጀግኖችን ደግሞ ሊመሰገኑ ይገባል።
በዛሬው 4/04/2016 እለት የኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ቅ/ጽ/ቤት ወጣቶች ሊግ ከህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበርያ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በጦር ሀይሎች ኮምፕሬሄሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በመገኘት ማዕድ የማጋራት ፕሮግራም አከናወነ፡፡
አቶ አለማየሁ ፍቃዱ የኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ቅ/ጽ/ቤት ምክትልና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ እንዳሉት የሀገር መከላከያ ሰራዊት ራሱን ሰቶ በከፈለው መስዋእትነት ሀገራችን ተከብራ እንድትቆይ ከፍተኛ ዋጋ ይከፍላል። ለዚህም ምስጋናችንን ልናቀርብላቸው ይገባል። በቀጣይም ከሰራዊቱ ጎን በመሆን ጀግኖቹን የማጀገን የመንከባከብ ተግባር አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል፡፡
ወጣት ቤተልሄም ትዳሩ የኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ቅ/ጽ/ቤት ወጣቶች ሊግ ሰብሳቢ እንዳሉት የሀገር መከላከያ ሰራዊቱ የከፈለው መስዋእትነት በማክበርና በመከተል ወጣቶች ሁሌም ቢሆን ድጋፋቸውና አብሮነታቸውን ሊያሳዩ ይገባል ብለዋል፡፡
በፕሮግራሙ ላይ የህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበርያ ጽ/ቤት ተወካይ አቶ ዳንኤል ደምለው እንዲሁም የ11ዱም ወረዳ ወጣቶች ሊግ ሰብሳቢዎች ተገኝተዋል፡፡
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ከክ/ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ወጣት ሊግ ጋር በመሆን በወጣት ሊግ ውስጥ ለሚገኙ የሚዲያ ሰራዊት አባላት በማህበራዊ ሚድያ ምንነትና አጠቃቀም ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ይከበር ስማቸው በስልጠናው ላይ ተገኝተው ለሚዲያ ሰራዊቱ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን በክፍለ ከተማችን እየተሰሩ ያሉ የልማትና መልካም አስተዳደርን ስራዎችን ለህዝቡ እንዲደርስ ሚዲያ የማይተካ ሚና አለው ብለዋ።በመሆኑም የሚድያ ሰራዊቱ ተሳትፎ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለውጥ የመጣ በመሆኑ የለውጡ ቱርፋቶችን ለህዝባችን ተደራሽ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል ይገባል ብለዋል።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዮሐንስ ነጋሽ የስልጠና ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን ማህበራዊ ሚድያ ሰዎች በኢንተርኔት ኮፒውተር(ተንቀሳቃሽ ስልክ)በመጠቀም እርስ በርስ የሚገናኙበት፣መረጃን የሚያጋሩበት እና የሚለዋወጡበት የማህበራወዊ ትስስር ገፅ ነው።በክፍለ ከተማችን ማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊና ፓለቲካ ክንዋኔዎች በስፋት እየተከናወኑ ነው ያሉ ሲሆን የሚዲያ ሰራዊቱ በሁሉም ፕላት ፎርሞች የነቃ ተሳትፎ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል።
የሊጉ ሰብሳቢ ወጣት ደሱ ሳህሌ እንደገለፁት የሉጉ አባላት የማህበራዊ ሚድያን ተሳትፎን በማሳደግ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ለአባላችንና ለህብረተሰቡ ተደራሽ ልታደርጉ ይገባል ብለዋል።
"በዲሞክራሲ ውስጥ ሀገራዊ አንድነትና የወጣቶች ሚና" አራዳ ክፍለ ከተማ ወጣቶች ሊግ
********
የአራዳ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ወጣቶች ሊግ"በዲሞክራሲ ውስጥ ሀገራዊ አንድነትና የወጣቶች ሚና"በሚል ለስራ አስፈፃሚዎችና ለመ/ድርጅት አመራሮች ስልጠና የሰጠ ሲሆን በስልጠናውም ሀገረ-መንግስትና ብሔረ-መንግስት፤እንደ ሀገር እያጋጠሙን ያሉ ተግዳሮቶችና መፍትሔዎቻቸው፤ሀገር ግንባታ ጋር ተያይዞ የወጣቱ ሚና ምን መሆን እንዳለበት በስልጠና ለወጣቶች የተሰጠ ሲሆን በዚህ ላይም ወጣቶች ሰፊ ውይይት አድርገዋል።
የተከልናቸው ችግኞች ህይወታቸው እንዲቀጥል ቀጣይነት ያለው እንክብካቤ ከወጣቱ ይሻሉ"
የየካ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ በሁሉም ወረዳዎች የወጣት ሊግ አመራሮችን እና አባላት ችግኞችን ውሃ የማጠጣትና የመንከባከብ መርሃ ግብር አካሄዱ።
የአረንጓዴ አሻራ ዋና ግባችን መትከል ብቻ ሳይሆን የተከልነውን ማፅደቅ ነው። የተከልናቸው ችግኞች ህይወታቸው እንዲቀጥል ደግም ቀጣይነት ያለው እንክብካቤ ከእኛ ስለሚሹ ልንከባከባቸው ይገባል ብለዋል በችግኝ እንክብካቤው ላይ የተገኙት ወጣቶች ናቸው
በቀጣይም በክ/ከተማ ደረጃ በአንድ ማዕከል እንደሚካሄድ ከክ/ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ሰብሳቢ ወጣት መስፍን ያገኝነው መረጃ ያመላክታል።
‹‹በጋራ ማጽዳትን ባህል ያደረገ ማህበረሰብ በመፍጠር አካባቢን ውብና ፅዱ እናድርግ››
የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ወጣት ሊግ
ታህሳስ 04/2016 ዓ/ም
የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ “ጽዳት የስልጣኔ መገለጫ ነው ” በሚል ሃሳብ በወረዳ 8,1 እና 3 የጽዳት ንቅናቄው አካሄዱ::
በጽዳት ንቅናቄ መርሀ-ግብሩ የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ስራ አስኪያጅ አቶ ደረሰ ጨምሮ የወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
የክ/ከተማው ስራ አስኪያጅ አቶ ደረሰ ንቅናቄውን ሲያስጀምሩ እንደተናሩት የጤና ችግር ከሚያስትሉ ችግሮች መካከል አካባቢን አለማፅዳት አንዱ መሆኑን ገልፀው አካባቢን በማፅዳት ውብ ጽዱ፣ ጤናማ አካባቢን በመፍጠር የራስንና የአካባቢን ጤና ማስጠበቅ ያስችላል ብለዋል፡፡
የክ/ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ወጣት ያሬድ ተፈራ የጽዳት በንቅናቄው ባስተላለፉት መልዕክት ፅዳት ከቤትና ከግል የሚጀምር በመሆኑ ማንኛውም ሰው ኃላፊነት እንዳበት በመገንዘብ ያለአግባብና ያለቦታ ቆሻሻን መጣል እንዴለለበት ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም ወጣቶች መልካም ተግባሮችን አጠናክረው ሊሰሩ ይገባል ።
የብልፅግና ፓርቲ ወጣት ሊግ የችግኝ እንክብካቤ መርሀግብር አካሄደ
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ወጣት ሊግ አባላትና አመራሮች "በጎነት ለህብረት" በሚል መሪ ቃል በክረምት ወራት የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ሊጉ በተረከበበት ቦታ ላይ የ2016 የበጋ የቦጎ ፍቃድ የችግኝ ተከላ እንክብካቤ በወረዳ 06 አስተዳደር አኪሄዷል።
በዚህ የችግኝ እንክብካቤ መርሀ ግብር ላይ የተገኙት የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት ሲስተር ግሩም ንጉሴ ሲናገሩ የብልፅግና ወጣት ሊግ አባላትና አመራሮች ከዚህ ቀደም በክረምት መርሀ ግብር በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተቀመጠውን የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም ስኬታማ እንዲሆን በርካታ ችግኞችን ተክሏል አሁን ደግሞ የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ የማፅደግ ተግባሩን በዚህ መልኩ መጀመሩ ለስራው ወጣቱ ትኩረት መስጠቱን ማሳያ ነው ብለዋል።
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ወጣት ሊግ አስተባባሪ ኢንጂነር ጫላ አሠፋ በበኩላቸው ወጣቱ በሠላም ፀጥታው፣በልማቱ ፣በበጎ ፍቃድ ስራው እንዲሁም በሌሎች ተግባራት የክፍለ ከተማውን ገፅታ ከመቀየር አንፃርም ከፍተኛ ስራዎችን ሠርትዋል አሁንም በአረንጓዴ አሻራ በክረምት መርሀ ግብር የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ ዘመንና ትውልድ ተሻጋሪ ስራዎችን በመስራት ላይ ይገኛል ሲሉ ተናግረዋል።
የኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ
በክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ተግባር ላበረከተው ከፍተኛ አስተዋፅኦ የዋንጫ እና የምስክር ወረቀት ተበረከተለት
ታህሳስ /2016
የኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ህብረተሰብ ተሳትፎ እና የበጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በ2015 የክረምት በጎ ፍቃድ መዝጊያ እና 2016 የበጋ በጎ ፍቃድ መክፈቻ ፕሮግራም ላይ በ2015 የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ተግባር የክ/ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ጽ/ቤት በሰው ተኮር ተግባር በቤት ዕድሳት ፣ በደም ልገሳ፣ በጎነት በሆስፒታል፣ለተማሪዎች የት/ት ቁሳቁስ አሰባሰብ፣በትራፊክ አገልግሎት፣ በአረንጓዴ አሻራ ጉድጓድ ቁፋሮና ችግኝ ተከላ እንዲሁም እንክብካቤ በመሳሰሉት ተግባራት ክ/ ከተማው ላይ ካሉ የወጣት አደረጃጀቶች እና ጽ/ቤቶች የተሻለ አፈፃፀም በመያዝ ከክ/ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊ ከአቶ ሙልጌታ ጉልማ የዋንጫ እና የምስክር ወረቀት የተበረከተለት ሲሆን ከ መደበኛ ፓርቲ ስራዎች ጎን ለጎን በበጋ ወራትም የተተከሉ ችግኞች የመንከባከብ በተጨማሪ ሌሎች ሰው ተኮር ተግባራት ላይ ሊጉ የሚያደርገውን ተሳትፎ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገልጿል።
"ለሰላምና ለሀገር ግንባታ የወጣቶች ሚና"
የየካ ክፍለ ከተማ ወጣቶች እና ስፓርት ፅ/ቤት "ለሰላምና ለሀገር ግንባታ የወጣቶች ሚና" በሚል መሪ ሀሳብ በክፍለ ከተማው ከሚገኙ ወጣቶች ጋር ውይይት አካሂዷል።
የውይይት መድረኩን የመሩት የየካ ክፍለ ከተማ ወጣቶች እና ስፖርት ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ደረጄ ተሬቦ አገራዊ ለውጡ ዕውን እንዲሆን ወጣቶች በግንባር ቀደምትነት ተሳታፊ በመሆንና መስዋዕትነት በመክፈል ተጠቃሽ ሚና መጫወታቸውን አንስተው ለሁለንተናዊ ብልጽግና ሰላም ወሳኝ በመሆኑ የክፍለ ከተማው ወጣቶች በሰላም ሠራዊት ተደራጅታችሁ እያደረጋችሁት ያለው ተሳትፎ አጠናክራችሁ በማስቀጠል የከተማችን ሰላም እንዲረጋገጥና በመዲናዋ የተጀመረው ልማት እንዲቀጥል ከእስካሁኑ በበለጠ ንቁ ተሳታፊ ልትሆኑ ይገባል ብለዋል።
የክፍለ ከተማው ሰላምና ፀጥታ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ጎሳዬ ሀሰን በበኩላቸው በሀገር ግንባታ ላይ ትልቅ ሚና ያላችሁ ወጣቶች "የሰላም ዋጋ በቀላሉ የማይተመን መሆኑን በመገንዘብ ሰላምን በማረጋገጥ ሂደት ውስጥ በንቃት በመሳተፍና የጸረ ሰላም ኃይሎችን አጀንዳ ባለመቀበል የበኩላችሁን ኃላፊነት መወጣት ይጠበቅባችኋል" ብለዋል።
በውይይቱ በሰላም እና በሀገረ መንግሥት ግንባታ የወጣቶች ሚናን በተመለከተ በየካ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ወጣቶች ሊግ ሰብሳቢ አቶ መስፍን ዘውዱ መነሻ ሰነድ አቅርበው ባለፉት ዓመታት የለውጡን ቀጣይነት ለማስጠበቅና ብልጽግናን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ወጣቶች በንቃት መሳተፋቸውን አውስተው፣ የተገኙ ድሎችን ለማሰናከል ብሎም የአዲስ አበባና የኢትዮጵያን ሰላም ለማደፍረስ ጸረ ሰላም ኃይሎች ወጣቶችን መሣሪያ ለማድረግ የሚያደርጉትን መፍጨርጨር ለማክሸፍ ወጣቶች የሰላም ኃይል በመሆን የድርሻችንን እንወጣ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
በልደታ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ አባላት የተሰሩ የከተማ ግብርና እና የሌማት ትሩፋት ተግባራት የመስክ ጉብኝት ተካሄደ
********
በልደታ ክ/ከ ወረዳ 2 ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ የ9 ስራ አሥፈጸሚ አባላት ተሳትፎ የተከናውኑ የሌማት ትሩፋት እና የከተማ ግብርና ስራዎች የመስክ ጉብኝት ተከናወነ።
በመስክ ጉብኝቱ ላይ የተገኘው የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ አስተባባሪ ወጣት ግዛው አለሙ እንድገለፀው የሊጉ አባላት በሌማት ትሩፋት ስራ እያደረጉ ያለው ተሳትፎ እጅግ የሚበረታታ መሆኑን በመግለፅ የምግብ ዋስትናን ችግር እና የሥነ ምግብ ሚዛን መዛባትን ማስተካከል የሚቻለዉ የየአካባቢውን እምቅ አቅሞች በማልማት ነዉ። ለዚህ ወጣቶች ንቁ ተሳትፎአቸውን አጠናክረው መቀጠል አለባቸው ብለዋል።
"ብሩህ ወጣት ለብልፅግና" የአቃቂ ቃሊቲ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ
የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ከክፍለ ከተማው ህብረተሰብ ተሳትፎ እና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ፅ/ቤት በጋራ በመሆን በዛሬ እለት የወሰን ተሻጋሪ በጎ ፍቃድ አገልግሎት አከናወኑ:: የሊጉ አባላት የወሰን ተሻጋሪ አገልግሎትን ያከናወኑት በሸገር ከተማ ቀርሳ ወረዳ ዉስጥ ሲሆን የአቅመ ደካማ አርሶ አደር ሰብልን የማጨድና የመከመር ተግባር ፈፅመዋል::
በንቅናቀዉ ላይ የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ መዝገቡ ይስማዉ: የክፍለ ከተማው አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ፋኪያ ሸሪፍ:የክፍለ ከተማው ብልፅግና ወጣቶች ኃላፊ ወጣት ማቴዎስ ጌታቸው: የክፍለ ከተማው ህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ተወካይ አቶ ብሩክ ዘርጋ እንዲሁም ከተለያዩ ወረዳዎች የተወጣጡ የሊጉ አባላት ተሳትፈዋል::
ወጣት ማቴዎስ እንደገለፀው የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ አባላትን በማሳተፍ በተቋም ደረጃ የተለያዩ የበጋ በጎ ፍቃድ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ጠቅሶ የዛሬው ተግባር የወሰን ተሻጋሪ መርሀ ግብር አካል እንደሆነ ተናግረዋል::
የዕለቱ ክብር እንግዳ ሆኖ የተጋበዙት አቶ መዝገቡ በበኩላቸው በጎ ፈቃደኝነት ለወንድማማችነት ድልድይ መሆኑን ገልፆ ወጣቶች ተመሳሳይ ተግባራትን አጠናክሮ እንዲቀጥሉ መልእክት በማስተላለፍ በተግባሩ የተሳተፉ አካላትን አመስግነዋል::
በወጣቶች ዘንድ የመሀል አመለካከትና ሚዛናዊነትን መፍጠርን ዓላማው ያደረገ የኪነ ጥበብ ምሽት በቂርቆስ ወረዳ 01 ተካሄደ
**************************
ታህሳስ 01/2016
በኪነ ጥበብ ምሽቱ ላይ የተለያየ talent ያላቸው ወጣቶች ዘመናዊ ዳንስ ፣ድምፅ፣ግጥምና ሌሎች የኪነ ጥበብ ውጤቶችን አቅርበዋል።
በዕለቱም ገጣሚ፣ የአሃዱ እና የአዋሽ ሬዲዮ ጋዜጠኛና የጀግኒት ፕሮግራም አዘጋጅ ወጣት ሃብታሙ ሃ/ሚካኤል በግጥሙ ለወጣቶቹ መልዕክት ያስተላለፈ ሲሆን ገጣሚ ኪሩቤል ግርማም ከግጥም መድብሎቹ በማቅረብ ምሽቱን ማድመቁን ከክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ሰብሳቢ ከወይዘሮ ፍፁም ግረፌ ያገኘነው መረጃ ያስረዳል።
#የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ የችግኝ የመንከባከብ መረሃ-ግብር አደረገ
******
በመረሃ-ግብሩም የክፍለ ከተማ አመራሮች የወረዳ አመራሮች እና የሊጉ አባላት በተገኙበት በወረዳ 13 አስኮ ት/ቤት ጀርባ በመገኘት የችግኝ የመንከባከብ መረሃ-ግብር አደረገ።
የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ሰብሳቢ ወጣት ያሬድ ተፈራ እንዳሉት ከበጋ በጎ ተግባራት መረሀ ግብር አንዱ የሆነው የችግኝ እንክብካቤ ስራ በሁሉም ወረዳዎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አበክረው ገልጿል።
የሀገራችን መለያ የሆነው የአረንጓዴ ሊጋሲ ተግባራችን አበክረን ማስቀጠል መቻል እንዳለበት የገለፁት የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ኃላፊ ወ/ሪት ሀብታሟ ቡልቻ ይህ የችግኝ መንከባከብ ስራ በሌሎቹም በጎ አድራጎት ተግባራቶች ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስቧል።
የችግኝ መንከባከብ ስራው የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ወጣቶች ሊግ በፈር ቀዳጀነት የጀመሩት ስራ የአየር ንብረት ለውጥ ትልቅ ሚና እንዳለው በመገንዘብ ሌላውም አደረጃጀት ተሞክሮውን በመውሰድ ሊሠራበት ይገባል ብሏል።
የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ የችግኝ የመንከባከብ መረሃ-ግብር አደረገ።
የወጣቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ በማረጋገጥ ብልፅግናን በፅኑ መሰረት ላይ እናፀናለን በሚል የመተዳደሪያ ደንብና አሰራር ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ ።
የቦሌ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ የወጣቶች ሊግ የሊጉን መተዳደሪያ ደንብ እና ፕሮግራም በ11ዱም ወረዳ በ2016 ለተመለመሉ አዳዲስ አባላት ማወያየት እና ማስገንዘብ ችሏል። የቦሌ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ የወጣቱን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እስካሁን በርካታ ስራዎችን መስራት መቻሉን በዚህም ተጨባጭ የሆነ ውጤት እንደተገኘ በተደረገው ውይይት ተገልጿል አሁንም ያለንን ትስስር በተጠናከረ መንገድ በማስቀጠል ውጤቶችን ማስቀጠል ይገባናል ያሉት ተወያዮች ።
ከዝግጅት ምዕራፍ ጊዜ ጀምሮ የተሰሩት ስራዎችን ከህገደንቡ እና ከፕሮግራሙ ጋር በዝርዝር ያቀረቡት የ11 ዱም ወረዳው ወጣቶች ሊግ ኃላፊውች ሲሆኑ በወረዳው ከእቅድ ጀምሮ እስከ ስኬታማ አፈፃፀም ድረስ ለተገኙ ድሎች የመተዳደሪያ ደንቡ ላይ ተመስርተን በመስራት ለተገኙ ስኬቶች የወጣቶች ሚና ከፍተኛ ነበር ብለዋል ።
የፓለቲካ ዘርፍ ኃላፊዎችም ያለንን ጅምር ስኬቶች አጠናክረን በማስቀጠል በልማት ፣ በሰላም ፣ በመልካም አስተዳደር ላይ ያሉትን የወጣቶች ተሳትፎ አፅንተን መሄድ ይገባናል በማለት ገልጸዋል ።
በመጨረሻ ከቀጣይ ስራዎች እና ከመመሪያው አንፃር እና ተግባራት ዙሪያ ለጠየቁት ጥያቄ አባላቶች ምላሽ ማብራሪያ ተሰተዋል
የከተማችንን ሰላም በተደራጀ የወጣቶች ተሳትፎ እናረጋግጣለን !!!!!
*************************
ከተማችን ፍፁም ሠላማዊና ደህንነቱ የተረጋገጠ እንዲሁም ከፀረ ሠላም ሀይሎች ለመጠበቅ የከተማችን ወጣቶች የተደራጀ ተሳትፎ በሁሉም ክፍለከተማና ወረዳ ተጠናክሮ ቀጥሎአል። በየደረጃውም ያሉ ወጣቶች ከፀጥታ አካላት ጋራ በቅንጅት በመስራት ከተማችን ሰላሟ የተረጋገጠ እንድትሆን የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እየተወጡ ይገኛሉ።
የተተከሉ ችግኞች ማፅደቅን ታሳቢ ያደረገ የችግኝ እንክብካቤ በቂርቆስ ክፍለከተማ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ አስተባባሪነት ተካሄደ!!!
**************************
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ አባላት አማካኝነት የተካሄደው የችግኝ እንክብካቤ መርሐ ግብር ዋና ዓላማው ችግኞችን ከመትከል ባለፈ ተንከባክቦ ማፅደቅን ታሳቢ ያደረገ ነው።
መርሐ ግብሩ በሁሉም ወረዳዎች እየተካሄደ ሲሆን ቀጣይነት እንደሚኖረውም የክፍለ ከተማው ወጣቶች ሊግ ሰብሳቢ ወይዘሮ ፍፁም ግረፌ ገልፀዋል።
በሀገራችን የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት ላይ የወጣቶች ሚና ከፍተኛ በመሆኑ በሁለንተናዊ ዘርፍ ተሳትፏቸውን መጨመር አለባቸው ሲል የክፍለ ከተማው ወጣቶች ሊግ አስታወቀ።
ህዳር 29/2016 ዓ ም
የክፍለ ከተማው ወጣቶች ሊግ ከሁሉም ወረዳዎች ከተውጣጡ ወጣቶች ጋር በሀገራዊ እንዲሁም በክፍለ ከተማው ወቅታዊ እና የጸጥታ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አካሄደ።
በሀገራችን ብሎም በአከባቢያችን ልማትንና መልካም አስተዳደር እንዲኖር በጸጥታ ጉዳዮች እንዲሳለጡ ፣በሰው ተኮር ተግባራቶች የወጣቶች ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ተሳትፏቸውን መጨመር እንደሚገባ ከመድረኩ ተገልጿል።
ቦሌክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት የተቋማት ሱፐር ቪዥን ተካሄደ
ህዳር 2016
የቦሌ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ በክ/ከተማ ደረጃ ባሉ 11 ወረዳዎች የተቋማት የሱፐርቪዥን ስራዎች ተከናውነዋል በዚህ የሱፐርቪዥን ስራ በዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች በተቋሙ የተከናወኑ እና የተተገበሩ እንዲሁም በከተማ እና በክ/ከተማ ደረጃ በመጀመሪያ ዙር በተደረጉ ሱፐርቪዥኖች የተሰጡ ግብረ መልሶችን ማዕከል ባደረገ ደረጃ የተስተካከሉ እና ምላሽ የተሰጠባቸውን ተግባራት መነሻ በማድረግ የሱፐርቪዥን ስራዎች የተደረጉ ሲሆን ከዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ እስከ ትግበራ ምዕራፍ በተለይም ወጣቶችን አመለካከት ከመቅረፅ ከማብቃት የአመለካከት እና የተግባር አንድነት ይዞ ከመንቀሳቀስ አኳያ እንዲሁም ልዩ ልዩ ስልጠናዎችን ከመስጠት ተቋማዊ አሰራሩን በጠበቀ ሁኔታ ተቋማትን መገንባት በተቋም የተሰሩ ስራዎች ምን ደረጃ ላይ ናቸው የሚለውን የሱፐርቪዥን ቡድኖች በማመልከት አጭር ውይይት በማድረግ የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ መግባባት ላይ በመድረስ ማጠናቀቅ ተችሏል
ቦሌ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ
የተሳሳተ ትርክትን በህብረ ብሔራዊነት መተካትን ታሳቢ ያደረገ የወጣቶች የእግር ኳስ ውድድር በቂርቆስ ወረዳ 07 ተካሄደ
**************************
ህዳር 28/2016
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ አስተባባሪነትና በወረዳ 07 አዘጋጅነት የተካሄደው ይህ የእግር ኳስ ውድድር ዋና ዓላማው የተሳሳተ ትርክትን በህብረ ብሔራዊነት መተካትን ታሳቢ ያደረገ እንደሆነ የሊጉ ሰብሳቢ ወይዘሮ ፍፁም ግረፌ ገልፀዋል።
ውድድሩ በወጣቶች ሊግ አባላትና በቢሮ ባለሙያዎች መካከል የተካሄደ መሆኑን የገለፁት ወይዘሮ ፍፁም ጨዋታው በቢሮ ባለሙያዎች አሸናፊነት መጠናቀቁንም ገልፀዋል።
እንዲህ ዓይነት ስፖርታዊ ውድድሮች የወጣቱን ስብዕና ከማጎልበት ባሻገር ለሀገራዊ መግባባት ሚናቸው የጎላ ነውና በሁሉም ወረዳዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ወይዘሮ ፍፁም አክለው ገልፀዋል።
የወጣቶችን ተሰጥኦ ማጎልበት ላይ ያተኮረው የኪነ ጥበብ ምሽት ዛሬም በቂርቆስ ወረዳ 03 በደመቀ ሁኔታ ተካሂዷል
****************************
ህዳር 26/2016
በባህል ኪነጥበብና ቱሪዝም ጽ/ቤት አዘጋጅነትና በክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ አስተባባሪነት እየተካሄደ ያለው የኪነ ጥበብ ምሽት ወጣቶች ልዩ ችሎታቸውን የሚያጎለብቱበት፣ የህይወት ተሞክሯቸውን የሚጋሩበትና ልምድ የሚለዋወጡበት መድረክ ሆኖ ቀጥሏል።
በዛሬው እለትም በወረዳ 03 ተወልዶ ያደገውና የስራ ፈጣሪ የሆነው ወጣት ሳምሶን ፀጋዬ በስራ ዕድል ፈጠራ እና ክህሎት ዙሪያ ለወጣቶቹ የህይወት ተሞክሮውን ማካፈሉን የሊጉ ሰብሳቢ ወይዘሮ ፍፁም ግረፌ ገልፀዋል።
የወረዳ አስተዳደሩ ወጣቶች የተለያዩ ተሰጧቸውን የሚያቀርቡበትና እውቀታቸውን የሚያጎለብቱበት የመዝናኛ ስፍራ ማዘጋጀቱን የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ድሪባ ዶጃ ለወጣቶቹ ገልፀዋል።
የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ሊግ ሰብሳቢ ወይዘሮ ሀዊ ጌታቸውም ወጣቶቹ ውስጣቸው ያለውን እምቅ አቅም ኪነጥበብን ተጠቅመው እንዲያወጡት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
በመድረኩም ውዝዋዜዎች፣ መነባነቦች፣ ግጥሞችና የተለያዩ የኪነጥበብ ውጤቶች ቀርበው ታዳሚውን አዝናንተዋል።
በመጨረሻም ለኪነ-ጥበብ ምሽቱ መሳካት ከፍ ያለ አስተዋጽኦ ለነበራቸው አካላት የእውቅናና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።
Click here to claim your Sponsored Listing.
Videos (show all)
Category
Contact the organization
Telephone
Website
Address
Addis Ababa
Bole Michael
Addis Ababa, G.P.O
ይህ በቦሌ ክ/ከተማ ስር በሚገኘው በወረዳ 1 ብልጽግና ፓርቲ የ?
Yeshi Building 7th Floor
Addis Ababa
Addis Ababa
Kaayyoon Kenya haqaa dhokate basne baketi mulisudhaa kanafu nu hordofun haqaa cina dhabachun eru nun
Belay Zeleke Street, Pissa Road
Addis Ababa, 251,56
providing facts of prosperity party