Sunday Service, Debre Genet Kidist Dingil Mariyam EOTC San Antonio, TX
This page is created and hosted by Dingil Mariyam Ethiopian Orthodox Tewahedo church . Service like: Liturgy, hymns and preaching.
The purpose of this page is to share service provided every Sunday services online.
✝️⛪️◈⛪️ ✝️ ✍እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወርሃዊ በዓል አደረሳችሁ ነገ ጠዋት ማክሰኞ፣ ነሐሴ፣ ፳፩ ፪ሺ፲፮ Tuesday, August 27, 2024
ደብራችን ደብረ ገነት ከ4:30AM ጀምሮ ጸሎተ ኪዳን እና ቅዳሴ ስላለ የበረከቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ
መንፈሳዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። አድራሻ ፡ 5400 Callaghan Rd,
San Antonio, TX 78228 ✞ ✞✞ 🙏🙏 🙏✞ ✞ ✞
ዘሰማየ ገብረ ሰማየ ገብረ ወምድር ሳረረ ( ፪ )
አልቦ ዘይመስሎ ለአምላክነ ( ፪ )
ሰማይን የዘረጋ መሬትን ያፀና { 2 }
ሀያል ጌታ ህያው አምላክ ያለ አንተ ማን አለና { 2 }
ዕርገታ ውስተ ሰማያት/2/
ወበዓታ /2/ ውስተ ገነት/4/
እርገታ ውስተ ሰማያት/2/
ገነዝዋ /2/ ሐዋርያት/4/
ዕርገታ ውስተ ሰማያት/2/
ገነዝዋ/2/ በስብሐት /4/
ትርጉም ፡- እመቤታችን ወደሰማይ ማረጓ ወደ ገነት መግባቷ ተሰማ። ሐዋርያትም በክብር ገነዙአት
የራማው ልዑል ገብርኤል (2)
ተመላለስ ምሃላችን ስምህን ጠርተን ና ስንል (2)
ብርሃን ልብሱ እሳታዊ መልአክ
አንተ አማልደን ከመሃሪው አምላክ (2)
አዝ….
የምስራች ነጋሪ ድንቅ ልደት አብሳሪ
የጽድቅ ፋና የምህረት ጎዳና (2)
አዝ….
ላመኑብህ ለተማጸኑብህ
ፈጥኖ ደራሽ አለኝታቸው ነህ (2)
አዝ….
የአናንያ የአዛርያ የሚሳኤል ከለላቸው
ከእሳት ነበልባል ያዳንካቸው (2)
አዝ….
ምሰሶ አምባችን መጠጊያችን
ቅዱስ ገብርኤል ጠባቂያችን (2)
አዝ….
ዕለት ዕለት የምንማልድህ
ልጀችህን ይምራን መንፈስህ /2
አዕረግዋ መላእክት ውስተ ሰማያት/2/
አዕረግዋ መላእክት ውስተ ሰማያት/2/
አሳረጓት መላእክት ወደ ሰማያት /2/
አሳረጓት መላእክት ወደ ሰማያት /2/
✝️✝️✝️ በደብረ ታቦር(3x)
ተሰብሐ(3x) በደብረ ታቦር ✝️✝️✝️
እንኳን ለደብረ ታቦር በዓል አደረሳችሁ።
"ታቦር እና አርሞንዔም በስምህ ደስ ይላቸዋል።"
ማርያም ፊደል የሁሉም መማሪያ/2/ በንፅና/2/ ተፅፋለችና/ 2/የደብራችን የህጻናት መዘምራን ሶልያና ዝማሬ መላእክትን ያሰማልን።
አማን በአማን (፪)
አማኑኤል ተመስገን ለዚህ ፍቅርህ ምን እንበል (፪)
ድብቁን ኃጢአት አንተ ብትገልጸው
ይቅር ብለኸኝ ባትሸፋፍነው
እንደሰው በቀል ቢኖርህ ጌታ
ለኔስ ኃጢአቴ የለውም ቦታ
አማኑኤል ተመስገን ለዚህ ፍቅርህ ምን እንበልህ(፪)
በየደቂቃው ኃጥያት ስሰራ
ስሰርቅ ስበድል አንተን ሳልፈራ
አንተ ግን ፊትህ ምንም ቢቀየር
በቁጣ በትር አልገረፍከኝም
ምሕረትን ልከህ አድነኝ ዛሬ
ታክቶኛልና በኃጥያት መኖሬ
አለም በኃጢአት እየሳበችኝ
በጽድቅ ደስታ መኖር አቃተኝ
የኃጢአት ጉዞ ጣፋጭ ቢመስልም
ውጤቱ መሮ ፍጹም አይጥምም
እንደበደሌ ስላልከፈልከኝ
ተመስገን እንጂ ሌላ ምን አለኝ
የብርሃን ጎርፍ ናት ድንግል እናታችን
ከሰማይ እያበራች ደስ አለው ልባችን
ፍቅርሽን ሰላምሽን ድህነት ይሁነን ኸ ኸ
ፍጥረት በሙሉ(2)ፊትሽ ይወድቃሉ
ፀጋሽ ይድረሰን(2)ይሰጠን እያሉ
የእኔ ልብ ምን ፅድቅ አለው አንቺ ለማስተናገድ
የሀጥያት ጎተራ ነው የተሞላው በስሥት
ኧረ እንዴት(2) ድንግል ትኑርበት ኸ ኸ
አትፀየፍም የእኔ ልብ ታሳናዳዋለች
ስለሀጥያቴ የእኔ እናት ምልጃ ታቀርባለች
ልባቸውን የዘጉ ድንግልን ለማስገባት
ህሊናቸው ይመለስ እንፀልይ ለዚህ ጥፋት
አምላክን ይዛ ነው ድንግል የምትመጣው ኸ ኸ
እሷን ስንመልስ ጌታ ነውን የምናስቀይመው
ብፁዕ ውእቱ ሰላማ አቡነ/2/
ዘከሰተ ለነ ብርሃነ /2//2/
ትርጉም:-
በጨለማ ሳለን ብርሀንን የገለጠልን አባ ሰላማ ንዑድ ክቡር ነው
መርቆሬዎስ ሀያል ሀያል መስተጋድል/2/
ገባሬ ተአምር ኮከበ ክብር/2/
===========
ሐመልማለ ወርቅ (2x)
ዑራኤል(3x) ሐመልማለ ወርቅ ===========
እሁድ፣ ሐምሌ፣ ፳፩ ፪ሺ፲፮ Sunday, July 28, 2024
††† በዓለ እግዝእትነ ማርያም ወዑራኤል መልአከ ወልደተ ኤዎስጣቴዎስ ወሱስን ዮስ ሕፅዉ ወአባ በጸሎተ ሚካኤል ወአወ ክርስቶስ ወላእከ ማርያም ኢትዮጲያዊ †††
============
ሰላም እለኪ(3)
ሰላማዊት ኪዳነ ምህረት ኧኸ
========
አረጋዊ ጻድቅ ዘደብረ ዳሞ/2/
ዘውገ ሙሴ ወገብረ ክርስቶስ/2/
ትርጉም:-
የደብረዳሞው ጻድቅ አረጋዊ ሙሴ እና ገብረ ክርስቶስ በሥራቸው በምግባራቸው አንድ የሆኑ ጓደኛሞች ናቸው።
ወለደት ነቢየ/3/
ኤልሳቤጥ /3/ወለደት ነቢየ/2/
ትርጉም:-
ቅድስት ኤልሣቤጥ ነቢይ ወለደች (ዮሐንስን)
አንፈርዓፀ/3/
በውስተ ከርስየ /3/ አንፈርዓፀ
ትርጉም:-
ኤልሣቤጥ ጽንስ በሆዴ ዘለለ አለች (የማርያምን መምጣትና ድምጽ በሰማች ጊዜ
ያርኍ ክረምተ/2/በበአመት /2/
ይሰምዑ /3/ ቃሎ ደመናት /2/
ትርጉም:-
በየአመቱ ክረምትን ያፈራርቃል /ያስገባል / ደመናትም ድምጹን ይሰማሉ
ምን ሰማህ ዮሐንስ በማጸን ሳለህ /2/
ህፃን ሆነህ ነቢይ ለክብር የተጠራህ /2/
እንደ እንቦሳ ጥጃ ያዘለለህ ደስታ /2/
ምን አይነት ድምፅ ነው ምን አይነት ሰላምታ /2/
አ.ዝ-------------\\
ከተፈጥሮ በላይ ያሰገደህ ክብር
እንዴት ቢገባህ ነው የእናታችን ፍቅር /2/
ሌላ ድምፅ አልሰማም ከእንግዲህ በኋላ
ለውጦኛልና የሰላምታ ቃሏ /2/
አ.ዝ-------------\\
በረሀ ያስገባህ ለብዙ ዘመናት
ምዓነት ያለ ራዕይ እንዴት ያለ ብሥራት/ /2/
አንደ አዲስ ምስጋና ስልቱ የተዋበ
ተደምጦ የማያውቅ ጭራሽ ያልታሰበ /2/
አ.ዝ-------------\\
ከሴት ከተገኙ ከደቂቀ አዳም
ድንግል ስለሆነ በህይወቱ ፍፁም /2/
ከማህፀን ሳለ ተመርጦ በጌታ
ለማዳመጥ በቃ የኪዳን ሰላምታ /2/
ከህጻናት አንደበት ምስጋናን አዘጋጀህ ማቴ 21:16 ህጻን ሶልያና ዝማሬ መላእክትን ያሰማልን።
የእለቱ ትምህርት በመጋቤ ጥበብ ቀሲስ ሺበሺ
+++ለኔስ ልዩ ነሽ+++
===============
ለኔስ ልዩ ነሽ ድንግል ማርያም
ለኔስ ልዩ ነሽ እመብርሃን
ፈልጌ /4/ ላንቺ ምሥጋና አላገኘሁም /2/
ልቤ ሲያበቅል የኃጢአት አረም
ውስጤ ሲሸፍት አልተወችኝም
ከቤተ መቅደስ እጇን ዘርግታ
ትጠራኛለች የኔ መከታ
አዝ …
የሆዴን ሐዘን የልቤን ምሥጢር
እነግርሻለሁ አንድም ሳይቀር
የምትሸሽጊ የሕዝብን ኃጢአት
ለእኔስ ልዩ ነሽ ድንግል አዛኚት
አዝ …
ጣዕሙ ልዩ ነው ካንቺ ጋር መኖር
ድንግልን ይዤ መቼም አላፍር
ወደ ጽድቅ ሕይወት ትወስደኛለች
ድንግል ማርያም እናቴ እኮ ነች
አዝ …
በሐዘን ስሰበር ማንን እጠራለሁ
ውስጤ ሲደማ ለማን እነግራለሁ
ከኃጢአት እድፍ ንጹሕ መሆኛዬ
አንቺ ነሽ ለኔ የኔስ መጽናኛዬ
አዝ …
የኃጢአት ቁስል ያላንቺ አይጠግም
ልቤ ሳይፈቅድ በሕይወት አልኖር
ከልጅሽ ሌላ መድኅን የለኝም
ከጸሎት በቀር ፍጹም አልድንም
አዝ …
✍ እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከ33ቱ በዓላት አንዱ ለሆነው ሕንጸተ ቤታ (ሕንጸታ) ቤተክርስቲያን በሰላም አደረሳችሁ፣ .../አደረሰን። ይህቺ እለት የመጀመሪያዋ ቤተክርስቲያን በአምላካችን በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሰኔ 20 ታንጻለች። 👉 ዳግመኛም በማግሥቱ ሰኔ 21 ቀን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ድንግል እናቱን እመቤታችንንና ቅዱሳን መልአክትን አስከትሎ ወረደ፡፡ እመቤታችንን መንበር ፣ ቅዱስ ጴጥሮስን ተራዳኢ ካህን ፣ እስጢፋኖስን ሠራዒ ዲያቆን አድርጎ ቀድሶ ለሐዋርያቱ አቁርቧቸዋልና ፍጹም ደስታም ሆነ፡፡ ዳግመኛም ቅዱስ ጴጥሮስን እጁን ጭኖ ፓትርያርክ አድርጎ ሾሞታል፡፡ በዚህም ጊዜ ሰማያውያን መላእክት ምድራውያን ሐዋርያት አንድ ሆነው አመስግነዋል፡፡
👉 ከዚህ በኋላ ሐዋርያት ከጌታችን እንዳዩት በዓለም ዞረው ቤተክርስቲያን አንጸዋል፡፡ ✝️ ⛪️◈⛪️ ✝️ ይህንን ታላቅ በዓል ምክንያት በማድረግ ደብራችን ደብረ ገነት እለቱን ሰኔ 21/2016(Jun 28/2024)ከ11AM ጀምሮ ጸሎተ ኪዳን እና ቅዳሴ ስላለ የበረከቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ
መንፈሳዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። አድራሻ ፡ 5400 Callaghan Rd,
San Antonio, TX 78228 ✞ ✞✞ 🙏🙏 🙏✞ ✞ ✞
Click here to claim your Sponsored Listing.
Videos (show all)
Category
Contact the place of worship
Telephone
Address
5400 Callaghan Road
San Antonio, TX
78228
Opening Hours
4am - 12pm |
2255 Horal Street
San Antonio, 78227
Glorifying God through Transformed Lives Know God. Love Others. Live the Gospel.
10907 W 1604 N
San Antonio, 78254
Middle & High School Ministry of Gateway Fellowship Church. • Helping Friends Become Devoted Followers of Jesus. • Wednesday Service at 7PM
20377 FM-2252
San Antonio, 78266
A Church where we Love All, Grow Disciples, Serve Community. We also love our Bracken Preschool!
10050 W Commerce Street
San Antonio, 78227
Helping people find God, grow their faith, discover their purpose and to build God’s Kingdom
11503 Big Mesa Drive
San Antonio, 78245
We lead people far from God into a life-changing encounter with Jesus.
2718 Frontier Drive
San Antonio, 78227
Taking the gospel light to all nations
San Antonio, 78223
We are spiritual community that celebrates the gift of God that empower us to engage in the struggles of life,to care for each other, and to serve Christ where we work and live.Joi...
Latinoamérica
San Antonio
Se hacen trabajos esotéricos con brujos y chamanes de toda Latinoamérica
2623 SE Military Drive
San Antonio, 78223
The Church at Brooks is a Christian community which serves the Brooks City Base area in San Antonio, TX. We meet Sunday mornings at 10am at City Base Cinema. Theatre 9. Families...
4114 Lockhill Selma
San Antonio, 78249
At The Rim, we desire to create space for people to discover the beauty of Jesus.
San Antonio
Founded on biblical principles and empowered by God; knowing Jesus and making Jesus known, by reaching up, reaching out and reaching in to help others be saved, equipped, and empow...