የሲቀላ ቀበሌ ታክስ ማዕከል

29/03/2023

👉የቀን ገቢ ግምት መርህ👈
***
👉 “ገቢ” ማለት በክልሉ የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 165/2009 አንቀጽ 2/14 መሠረት መደበኛ ያልሆነ ገቢን ጨምሮ ከማንኛውም ምንጭ በጥሬ ገንዘብ ወይም በዓይነት የተገኘ ወይም በማንኛውም መንገድ ለግብር ከፋዩ የተከፈለው፣በስሙ የተያዘለት ወይም የተቀበለው ማንኛውም የኢኮኖሚ ጥቅም ነው፡፡

👉 “የቀን ገቢ” ማለት አንድ ግብር ከፋይ በቀን ዕቃ ሸጦ ወይም አገልግሎት ሰጥቶ የሚያገኘው አማካይ ዕለታዊ ገቢ ነው፡፡ ይህ በቀን የሚገኘዉ የሽያጭ ገቢ የተሸጠውን ዕቃ የተገዛበት (የተመረተበት)፣ የሥራ ማስኬጃ ወጪዎችን እና ለሥራው ዋስትና ለማሰጠት እንዲሁም ከንግድ ሥራው የሚያገኘውን ትርፍ ያካትታል፡፡

👉 የቀን ገቢ ግምት በሚከናወንበት ጊዜ የሚወሰደው የግብር ከፋዩ አማካይ ዕለታዊ ገቢ እንጂ የተጣራ ትርፍ እንዳልሆነ በገማች ኮሚቴም ሆነ በአጣሪ ቡድኑ ግንዛቤ መወሰድ ይኖርበታል፡፡

👉 በሣምንት በተወሰኑ የገበያ ቀናት ብቻ እየሰሩ በሌሎች ቀናት ድርጅታቸውን ዘግተው የሚቆዩ ግብር ከፋዮች በሚያጋጥሙበት ጊዜ በሰሩበት ቀናት ያገኙትን የሽያጭ ገቢ በመደመርና ለሰባት ቀናት በማካፈል አማካይ የዕለት ሽያጭ ገቢያቸው ይወሰዳል፡፡

👉 ግብር ከፋዩ በታክስ ከፋይነት ያልተመዘገበ ወይም ተመዝግቦ የጸና የንግድ ሥራ ፈቃድ ሳይኖረው በዕቃ ሽያጭ ወይም በአገልግሎት መስጠት ሥራ ላይ የተሰማራ እስከሆነ ድረስ የቀን ገቢ ግምት ሥራው መከናወን ይኖርበታል፡፡

👉 ግብር ከፋዩ ከአንድ በላይ በሆነ የንግድ ወይም የአገልግሎት መስጠት ሥራ ላይ የተሰማራ ከሆነ ባከናወነው የዕቃና የአገልግሎት ሽያጭ ዓይነት የቀን አማካይ ሽያጭ ገቢ ተለይቶ መገመት ያለበት ስለሆነ ግብር ከፋዩ በየሥራ ዘርፉ በአማካይ የሚያገኘው የዕለት ሽያጭ ገቢ ይዘትና ስፋት ለመገመት አመላካች የሆኑ ታሳቢዎችን ሁሉ በጥልቀት በማጤን ተመጣጣኝ የሆነ ግምት ሊገመት ይገባል፡፡

22/03/2023

የጋሞ ልማት ማህበር ''ደሬ ጋሞ ልማትና ቢዝነስ ኮርፖሬሽን" በሚል ስያሜ ዋና ጽ/ቤቱን በአርባምንጭ ከተማ ያደረገ ኮርፖሬሽን ፈቃድ አገኘ።

ኮርፖሬሽኑ በስሩ በርካታ የንግድ ዘርፎችን በመያዝ ቀጣይነት ያለው ገቢ የሚያመነጭ ተቋም መሆኑም ተገልጿል ።

አርባምንጭ ፡ መጋቢት 12/2015 ዓ.ም የተጀመሩ የልማት ስራዎች ለማስቀጠል በአካባቢው የሚገኙትን ሀብት ለልማት የማሰባሰብ እና ገቢ የሚያመነጭ" ደሬ ጋሞ ልማትና ቢዝነስ ኮርፖሬሽን ተመስርቷል ።

ኮርፖሬሽኑ በውስጡ ከያዛቸው ስምንት የንግድ ዘርፎች መካከል "የአርባምንጭ ግብርና ልማት ኃላፊነቱ የተወሰነ ማህበር" ፣ " ጉጌ እንስሳት እርባታ ኃ/የተወሰነ ማህበር" እና " ነጭ ሣር የሆቴል አገልግሎት የተወሰነ ማህበር " የPLC ፈቃድ አግኝተዋል።

የአክስዮን ሽያጭ የጀመረው የሠላም ማይክሮ ፋይናንስ አክስዮን ማህበርን ጨምሮ ፣ የማዕድን ዘርፍ እና የደረጃ አራት የኮንስትራክሽን እና ሌሎች ዘረፎችን ወደ ሥራ ለማስገባት የጥናትና ቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቋል።

"ደሬ ጋሞ ልማትና ቢዝነስ ኮርፖሬሽን" ከቀድሞው አደረጃጀት በተሻለ ለበርካታ ሰዎች የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ ፣ ከአርሶአደር እስከ ምሁር ተጠቃሚ ያደርጋል በንግድ ሕግ መሠረት ትልልቅ ሥራዎችን ይሰራል።

ኮርፖሬሽኑ በመመሪያና ደንብ የሚተዳደር እና በሥራ አመራር ቦርድ የሚመራ መሆኑ በየዓመቱ ከሚያገኘው ትርፍ የመንግስትን ግብር በመክፈል ለልማት ማህበሩ የሀብት ማግኛ ምንጭ መሆኑን ተገልጿል።

የጋሞ ልማት ማህበር ላለፉት ዓመታት ልማቱን ለማስቀጠል በገቢ ማስገኛ ስራዎች ቢሰማራም ልማቱ የሚጠይቀውን የሀብት መጠን ማሟላት ይቻል ዘንድ ተጨማሪ 8 የቢዝነስ ተቋማትን በማደራጀት ለልማት ስራው እንዲደጉም በማቀድ በማህበሩ ቦርድ ተወስኖ አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅቶች ሲከናወኑ ቆይቷል።

በቀጣይም የልማት ማህበሩ የተቋቋመበትን ዓላማና ተግባራት በብቃት የሚወጣው ሲሆን በአንጻሩም ኮርፖሬሽኑ ትርፋማነትን መሠረት አድርጎ ማህበረሰቡን ሆነ ልማት ማህበሩን በበርካታ የሚደግፍ ተቋም መሆኑን ከጋሞ ልማት ማህበር የተገኙ መረጃዎች ያመላክታሉ።

22/01/2023

👉🏻የታክስ/ግብር አስገራሚ እውነታዎች 👈🏻(2)
***
🫳 በአሜሪካ አንድ የታክስ ማጭበርበርን ያጋለጠ/ሪፖርት ያደረገ/ ሰው በመጠቆሙ ከሚሰበሰበው 30 /ሠላሣ/ በመቶ የሚሆነውን ድርሻ ያገኛል ወይም ይሰጠዋል፤

🫳 በአትላስ ሸርጅድ (Atlas shrugged) ላይ የሚገኙ አጠቃላይ የቃላት ብዛት 645ሺህ፣ መጸሐፍ ቅዱስ ደግሞ ወደ 700ሺህ ቃላት ሲኖራቸው የአሜሪካው የፌደራል ታክስ ኮድ 3 ማሊዮን 700ሺህ ቃላትን ይዟል፤

🫳የአሜሪካ ባለኃብቶች ከመካከለኛና ዝቅተኛ ገቢ ካላቸው ዜጎች ይልቅ ከፍተኛውን ታክስ/ግብር ይከፍላሉ፡፡ የባለኃብቶቹ ብዛት ከአጠቃላይ ሕዝብ አንድ በመቶ ብቻ ቢሆንም አጠቃላይ ማህበረሰቡ ከሚያገኘው ገቢ 19 በመቶ የሚያገኙ ናቸው፡፡ ከሚሰበሰበው አጠቃላይ የገቢ ግብር አኳያ ግን 37 በመቶውን የሚሸፍኑት እነርሱ ናቸው፤

🫳ኤክሳይዝ ታክስ/ግብር በአሜሪካ “የኃጢያት ግብር (Sin tax)” የሚል ተቀፅላ መጠሪያ ተሰጥቶታል፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት በአልኮል/ በሲጋራ እና በቁማር ላይ የሚጣል ታክስ/ግብር በመሆኑ ነው፤

🫳እንግሊዝ ከመኖሪያ ቤት ጋር ተያይዞ የሚከፈልን ታክስ/ግብር በ1691 ስታስከፍል የነበረው ቤቶቹ ባላቸው የመስኮት ቁጥር እና መጠን ነበር፡፡ ይህን ተከትሎ ነዋሪዎቿ የሚከፍለውን ግብር መጠን ለመቀነስ ሲሉ አዲስ በሚገነቧቸው ቤቶች ላይ የሚያኖሯቸውን መስኮቶች ብዛት በቁጥር አነስተኛ ያደርጉ ነበር፡፡ በፊት ከገነቧቸውም ቤቶች የመስኮት ቁጥሪቸውን በማሸግና በመድፈን ይቀንሱ ነበር፡፡ በዚህ የተነሳ ግን በንፁህ አየር እጥረት ለተለያዩ የጤና ችግሮች ይጋለጡ ነበር፡፡ ይህን የተረዳው መንግሥት ታዲያ በ1851 ሕጉ እንዲሻሻል አድርጓል፡፡

🫳 በ1705 የሩሲያው ገዥ የነበረው ታላቁ ፒተር በፂም ላይ ታክስ ጥሎ ነበር፡፡ የገዢው ይሄን ያደረገው በምዕራብ አውሮፖ ታዋቂ የነበረው ፂምን ተላጭቶ እና አምሮ የመታየትን ባሕል ለማስረፅ ሲል ነበር፤

Photos from የሲቀላ ቀበሌ ታክስ ማዕከል's post 18/01/2023

ለከተማ እድገት ሀብት፣ ቴክኖሎጂ፣ የማህበረሰብ ጉልበት፣ ጊዜንና የአመራር ቁርጠኝነት የጎላ ድርሻ እንዳለው ተጠቆመ

ጥር 10/2015 ዓ.ም_ ለከተማ እድገት ሀብት፣ ቴክኖሎጂ፣ የማህበረሰብ ጉልበት፣ ጊዜንና የአመራር ቁርጠኝነትን የሚጠይቅ በመሆኑ በዚህ ረገድ ትኩረት ሊደረግ እንደሚገባ የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ።

የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ም/ቤት ቋሚ ኮሚቴ የአዳማ ከተማን የእድገት ግስጋሴ በመጎብኘት የልምድ ልውውጥ አድርጓል።

የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ኃይሉ ጀልዱ በልምድ ልውውጡ ላይ እንደገለጹት፥ ያሉ መልካም አጋጣሚዎችን በመለየት ለከተሞች እድገት ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርና ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ይገባል።

በዚህ ረገድም በአዳማ ከተማ ማህበረሰቡን፣ ባለሀብቱን፣ አመራሩን በማሳተፍና በማቀናጀት ተጨባጭ ለውጥ መምጣቱን ገልጸዋል።

በተለይም የገቢ አቅምን ከማሳደግና የመሬት ልማትን ከማስተዳደር አኳያ ሰፊ ስራ መሠራቱን ጠቁመው፥ አርባምንጮችም ከመልካም ጅማሯችን ጥሩ ልምድ ይቀስማሉ ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉ ጠቁመዋል።

የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ማርቆስ ማቴዎስ በበኩላቸው የአዳማ ከተማ በዲጅታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ ሰፊ ስራ መስራቱ የሚደነቅ ነው።

በተለይም ከተማን ለማሳደግ ሀብት፣ ቴክኖሎጂ፣ ጊዜንና ቁርጠኝነትን የሚጠይቅ በመሆኑ አቅም ያለው ባለሀብት፣ ዕውቀት ያለው ወጣት፣ ጉልበት ያለው ማህበረሰብና ቁርጠኛ የሆነ አመራርን መፍጠር ከተቻለ በአዳማ ከተማ የታየውን ተሞክሮ በአርባምንጭ ከተማ መድገም አያቅትም ብለዋል።

እንደዚሁም በህብረተሰብ ተሳትፎ የሚሰሩ ስራዎችን በማስፋት የተሻለ ዕድገትና ልማት ማምጣት እንደሚቻል ከአዳማ ከተማ ልምድ መቀመራቸውን ተናግረዋል።

የአከባቢን ሰላም በማስጠበቅና የህብረተሰብ ተሳትፎን በማጠናከር በተሰራው ስራ በአዳማ ከተማ አይነተኛ ለውጥ ተመልክተናል ያሉት ደግሞ የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ስንታየሁ አበረ ናቸው፡፡

በከተማዋ ያየነውን ልምድና ተሞክሮ ወደ ከተማችን በማውረድ ለተሻለ ለውጥ ልንተጋ ይገባል ብለዋል።

የከተማዋ ነዋሪና ባለሀብቱ ለአርባምንጭ ከተማ እድገት እና ለውጥ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ሊያበረክቱ እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል።

09/01/2023

ከሽያጭ ታክስ/ Turn over tax/ ክፍያ ነፃ ግብይቶች

• ቢያንስ ሁለት ዓመት ያገለገለ የመኖርያ ቤት ሽያጭ እና የመኖርያ ቤት ኪራይ
• የፋይናንስ አገልግሎቶች
• ለሳንቲሞችና መዳልያዎች ጥናት አገልግሎት ከሚውሉት በስተቀር የአገር ውስጥና የውጭ አገር ገንዘቦች እና የዋስትና ሰነዶች ማሰራጨት
• በሃይማኖት ድርጅቶች የሚሰጡ የእምነት ወይም ከአምልኮ ጋር የሚገናኙ አገልግሎቶች
• የሕክምና አገልግሎቶች እና አግባብ ባለው የመንግስት መሥርያ ቤት በሚወጣ መመርያ መሠረት ነፃ የተደረጉ አገልግሎቶች
• በትምህርት ተቁዋማት የሚሰጡ የማስተማር አገልግሎቶች እንዲሁም ለሕፃናት ጥበቃ በመዋእለ ሕፃናት የሚሰጡ አገልግሎቶች
• ለሰብአዊ ዕርዳታ የሚውሉ ዕቃዎችና አገልግሎቶች፣ የኤሌክትሪክ፤የኬሮሲን እና የውሃ አቅርቦት፣ የትራንስፖርት አገልግሎቶች
• ማንኛውም የስራ እንቅስቃሴ ለማከናወን ለሚስጥ ፈቃድ ለመንግስት የሚሰጥ ክፍያ
• ከ60% በላይ ሠራተኞቹ አካል ጉዳተኞች የሆኑበት አካል ጉዳተኞችን ቀጥሮ የሚያሰራ ድርጅት የሚቀርባቸው ዕቃዎችና አገልግሎቶች
• መፃሕፍት( ወደ ሀገር የሚገቡ፣ በሀገር ውስጥ የሚሸጡ እና መጻህፍትን ወቅታዊ ለማድረግ የሚወጡ እትሞች )
• የምግብ እህል (ጤፍ፤ ስንዴ፣ ገብስ፣ በቆሎ፣ ማሽላ፣ ዘንጋዳ ፣ዳጉሳ ፣ አጃ፣ እንዲሁም የነዚህ ዱቄት ከጥራጥሬ አተር ፣ባቄላ፣ምስር ፣አኩሪ አተር፣ሽንብራ ፣ግብጦ ፣ጓያ )
• የቅባት እህሎችም ሆኑ ፕሮሰስ የተደረጉ ምግቦች፣ ፉርሽካም ጭምር የታክስ መነሳት አይመለከታቸውም ፡፡

07/01/2023

የአርባ ምንጭ ከተማ ከንቲባ አቶ ማርቆስ ማቲዮስ ለኢየሱስ ክርስቶስ ልደት (ገና) በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።

ከንቲባው በመልዕክታቸው ለመላው የአርባ ምንጭ ከተማ ነዋሪዎችና የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን አደረሳችሁ በማለት በዓሉን በጋራ፣ በአንድነትና በመተጋገዝ እንዲያሳልፉ ገልፀዋል።

መልካም በዓል!

Photos from የሲቀላ ቀበሌ ታክስ ማዕከል's post 04/01/2023

የአርባምንጭ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት ከዝህ በታች በዝርዝር የገለፃቸውን የሺያጭ መመዝገቢያ ማሺን ተጠቃሚ ነጋዴዎች የማሺን እድሳት እንድያደረጉ በተገለፀው ጊዜ በመቅርብ የማሽን እድሳት እንድታደረጉ ያሳስባል።
የአርባምንጭ ከተማ ገቢዎች

Photos from የሲቀላ ቀበሌ ታክስ ማዕከል's post 21/12/2022

የማዕከላችን በተግባራቸው ግንባር ቀደም የሆኑ በገቢ አስባስብ ስርዓቱን በማዘመን የሚታወቁት የሲቀላ ታክስ ማዕከል ባለሞያዎች ከሚኖሩበት አከባቢ የምርጫ ጣቢያ በመሄድ አድሱን የደቡብ ኢትዮጲያ ክልል'' መመስረት የምያስችለውን የመራጭነት ካርድ በመውሰድ ድምፅ በመስጠት ዴሞክራሲያዊ መብታችሁን በመጠቀም ግዴታቸውን ለመውጣት ካርድ ወስደዋል።

Photos from የሲቀላ ቀበሌ ታክስ ማዕከል's post 18/12/2022
10/12/2022

አርባምንጭ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት ባወጣው የቅጥር ማስታውቂያ መስርት የፈተና ቀን ስለማሳውቅ ይሆናል
________________
መ/ቤታችን በቀን 16_3_2015 ዓ.ም ባወጣው የቅጥር ማስታወቂያ ላይ የተመዘገባችሁ አመልካቾች ፈተና የሚሰጠው በቀን 4_4_2015 ዓ.ም መሆኑን እየገለጽን ወደ ፈተና ስመጣ ማንነታችሁን የምገልጽ መታወቂያ እንድትዙ እያሳሰብን ነገር ግን ስልክ ይዞ መግባት በፍጹም የተከለከለ መሆኑን በጥብቅ እናሳውቃለን ። የአርባምንጭ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት

Photos from የሲቀላ ቀበሌ ታክስ ማዕከል's post 06/12/2022

በአርባምንጭ ከተማ በገቢ ጸ/ቤት አዘጋጅነት ከ6ቱ ቀቤሌ ለተወጣጡ ለሴቶች እና ወጣቶች አደረጃጀቶች በግብር እና በታክስ ግንዛቤ ማሳደጊያ ስልጠና ተሰጠ ፡፡
**********************************************

መስሪያ ቤቱ ግብር እና ታክስ ሥርዓቱ ላይ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ የተለያዩ ተግባራትን አከናውኗል።

ከዚህ በመነሳት በተለያዩ አደረጃጀቶች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎች የተሰጡ ሲሆን ከሴቶች አደረጃጀቶች እና ከወጣቶች አደረጃጀቶች ጋር የሚደረገው ውይይት ካላቸው ተደራሽነት አንፃር እና ከሚያከናውኑት የገብይይት ሲተያይ ከፍተኛ ስለሆነ ለይት ያደርገዋል ፡፡

በመሆኑም ይህ ስልጠና በከተማ አቀፍ ደረጃ ከ12 ቀጠናዎች ለተወጣጡ የአደረጃት ክፍሎች የተሰጠ ስሆን በቀጣይ በተዋረድ በየቀጠናወ ስልጠናው በወሰዱ ሰልጣኞች አማካይነት የሚሰጥ ይሆናል ፡፡ በስልጠናው ወቅት ከሰልጣኞች ጥያቄዎች ተነስቶ በሚመለከተታቸው የሥራ ኃላፊዎች ምላሽ ተሰጥቷል ፡፡

Photos from የሲቀላ ቀበሌ ታክስ ማዕከል's post 21/11/2022

ሕገወጥ ደረሰኞችን እንዴት በቀላሉ መለየት እንችላለን?
***
ግብይት በምናካሄድበት ጊዜ ደረሰኝ የመቀበል ልምዳችን መዳበር የሚገባው ጉዳይ ነው፡፡ ነገር ግን የምንቀበለው ደረሰኝ ሕጋዊነቱን ማጣራት እና ማወቅ ደግሞ ያስፈልገናል፡፡
አንዳንድ ጊዜ በሕገወጥ ደረሰኞች ግብይት የሚካሄድ ሲሆን ይህም በገዢው ላይ ከፍተኛ ኪሳራ እና ከዛም ባለፈ በሕግ እስከመጠየቅ የሚያደርስ ጉዳይ ነው፡፡
ለመሆኑ ሕገወጥ ደረሰኞች እንዴት ወዲያውኑ መለየት እንችላለን
ምንግዜም ግብይት ሲያደርጉ በመጀመሪያ
1. በእጅ ስልክዎ ጎግል ላይ ገብተው e-trade gov et በማለት ሰርች ያድርጉ፣
2. በመቀጠል የንግድ ድርጅት መረጃ ያጣሩ የሚለውን ይጫኑ
3. ቀጥሎ በመጣው ሰሌዳ ላይ የንግድ ፈቃድ ማጣሪያ ከሚለው ስር የፈቃድ ወይም የግብር ከፋይ ስም በሚለው ቦታ ላይ የግብር ከፋዩን TN No ያስገቡ
4. ቀጥሎ በመጣው ሰሌዳ ላይ የንግድ ድርጅትን ሙሉ መረጃ በሚገባ ማይት ይችላሉ፡፡

የሊንኩ ቅደም ተከተል በፎቶግራፍ ከዚህ በታች እንደቀረበው ነው፡፡

ራስዎንም ሆነ ሌሎችን ከሕገወጥ የደረሰኝ ዝውውር ይከላከሉ፡፡

Photos from የሲቀላ ቀበሌ ታክስ ማዕከል's post 19/11/2022

የአ/ከ/ገቢዎች ባለሥልጣን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለሠራተኞቹ ሥልጠና ሰጠ ፡፡መ/ቤቱ የገቢ አሰባሰቡን ውጤታማ ለማድረግ በአሰራር ወቅት በሚታዩ ክፍተቶች እና በይበልጥ ተሻሽሎ በፀደቀው የማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ አሰባሰብ መመሪያ ላይ ባለፈው በአመራሩ ስልጠና ወቅት የተቀመጠውን አቅጣጫ ተከትሎ ስልጠናው መዘጋጀቱን በመግቢያው ላይ የተገለፀ ሲሆን በዕለቱ የጋሞ ዞን ገቢዎች መመሪያ ኃላፊ አቶ አብረሃም ቱሉ ተገኝተው ስልጠናው የተጣለብንን ከፍተኛ ግብር የመስብሰብ ኃላፊነት በዕውቀት ለመምራት በእጅጉ አስፈላግ መሆኑን ገልፀው ሰልጣኙ በትኩት እንድከታተል ያሳሰቡ መሆኑን እንድሁም የአርባ ምንጭ ከተማ ገቢዎች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደግፌ አማረ በበኩላቸው ስልጠናው የአፈፃፀም ወጥነት ችግርን እንደሚፈታ ካስረዱ ወዲህ ከሥልጠናው ማግስት ግንዛቤ አልተፈጠረልኝ በሚል የሚፈጡ ክፍተቶች ላይ መ/ቤታችን አይታገስም ብለዋል ፡፡ በዕለቱ ስልጠናው ለፈፃሚዎች ከተሰጠ በኃላ በተሳታፊዎች ሥልጠናው በጣም አስፈላጊ ነው ግን ዘግይቷል ፣ ባለሙያው ራሱን ለማብቃት ውስንነቶች አሉ መስተካከል ብችል ፣ ዋናው ባለቤት ማዘጋጃ ቤታዊ ጽ/ቤት ሆኖ ለማዘጋጃ ባለሙያ ሳይሰጥ ለእኛ ብቻ መሰጠቱ ሙሉ አያደርገውም በዚህ የተነሳ ብዙ ገቢዎች እያመለጡ ነው ምን ታስባል ፣ የልዝ ወለድ አሰራር በተመለከተ ግልጽ አይደለም ብራራ እና በሥም ዝውውር ጊዜ ከምኖሩ ክፍያዎች የካፕታል ዕድገት ግብር የንግድትርፍ ግብር አከፋፈል እና በሽያጭ ታክስ አከፋፈል ዙሪያ የተለያዩ ጥያቄዎች ተነስተው በተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች ምላሽ የተሰጠ ሲሆን የማዘጋጃ ቤታዊ ጽ/ቤት ባለሙያ ሥልጠናን በተመለከተ በጣም አስላጊ በመሆኑ ከተቋሙ ኃላፊዎች ጋር በጋራ ተቀናጅተን ስልጠናው የሚሰጥበት አግባብ እንደሚመቻች ተገልፃል ፡፡

Photos from የሲቀላ ቀበሌ ታክስ ማዕከል's post 18/11/2022

ለግብር ከፋዮችና ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ ፡፡
////////////////////////////////////////////////////
በጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪያ የታክስ ትምህርት፣ ኮሙኒኬሽንና ቅሬታ አጣሪ ዳይሬክቶሬት ከአርባምንጭ ዩንቨርስቲ ጋር በመተባበር ከህዳር 8/2015ዓ/ም ጀምሮ ለሁለት ቀናት በካምባ ክላስተር ለሚገኙ የደረጃ "ሀ" እና "ለ" ግብር ከፋዮች እና የገቢ ጽ/ቤት ባለሙያዎች የሂሳብ መዝገብ አያያዝ እና አዲስ በወጡ መመሪያዎች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል ፡፡
የስልጠናው ዓላማ ግብር ከፋዮች የሂሳብ መዝገባቸውን በተገቢውን እንዲይዙ፣ በግብይት ወቅት ደረሰኝ እንዲጠቀሙ እና የወጡ መመሪያዎችን ጠንቅቀው በማወቅ የግብር ግዴታቸውን በታማኝነትና በራስ ተነሳሽነት እንዲወጡ ለማስቻል እንዲሁም የባለሙያዎችን የመፈፀም አቅም ለማሳደግ የሚያስችል ሲሆን የሥልጠናው ተሣታፊዎችም ግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናው ለሥራቸው ከፍተኛ እገዛ እንደሚሰጥና ያገኙትን ግንዛቤ በተግባር ለመተርጎም የበኩላቸውን ግዴታ እንደሚወጡ ገልጸዋል፡፡

በጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪየ/ ህዝብ ግኑኝነት አርባምንጭ

Photos from የሲቀላ ቀበሌ ታክስ ማዕከል's post 09/11/2022

የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በጋሞ ዞን ስር ካሉ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች በ2014 በጀት ዓመት የላቀ አፈፃፀም በማስመዝገቡ የዕውቅናና የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል ።

የከተማ አስተዳደሩ ገቢዎች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የተሻለ አፈፃፀም አምጥቶ እንዲሸለም የከተማው አመራር ፣ የግብር ከፋዩ ህብረተሰብ ክፍል፣ የገቢ ሰክተሩ ማኔጅመንት አባላትና አጠቃላይ ሰራተኞች ድርሻ የጎላ ሚና ተጫውቷል ።

የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደርም በተገኘው ውጤት ገቢን በወቅቱ በመክፈል ግንባር ቀደም ግብር ከፋዮችንና የሚመለከታቸውን ባለድርሻ አካላትን ሁሉ በማመስገን በቀጣይም የተሻለ ውጤት ለማምጣት ገቢን አሟጦ በመሰብሰብ በከተማው የተጀመረውን ልማት ስራ ለማስቀጠል በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባ ገልጿል ።

Photos from የሲቀላ ቀበሌ ታክስ ማዕከል's post 08/11/2022

የጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪያ የ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና የ2015 ዓ/ም ዕቅድ ላይ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

03/11/2022

ለአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ከከተማ አስተዳደሩ የቀረበ የምስጋና መልእክት
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
ክቡር ጠቅላይ ሚንስተር ዶ/ር አብይ አህመድ፣ ሚንስተሮች፣ የየክልል ርዕሰ መስተዳድሮችና ከንቲባዎች ወደ ከተማዋ ከገቡ ጀምሮ የእስከዛሬው የስታድየም የውይይት መድረክ እጅግ ደማቅ በሆነ ጨዋነት የተሞላ እንግዳ አቀባበል ፍቅራችሁን በመግለፃችሁ የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ለመላው የከተማዋ ነዋሪዎች ምስጋናውን ያቀርባል።

በቀን 24/02/2015 ዓ.ም የከተማዋ ነዋሪዎች ደከመኝ ሰለቸኝ ሳትሉ ሌሊት ብርድ ሳይበግራችሁ ላደረጋችሁት እጅግ ጨዋነት በተሞላው እንግዳ አቀባበል በክቡር ጠቅላይ ሚንስትሩ አንደበት ሳይቀር የመልካምነትና የሰላም ተምሳሌትነታችሁ ተመስክሮላችኋል።

የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደርም ከአቀባበል ጀምሮ የዛሬው የስታድዬም መድረክ ላይም እጅግ በርካታ መቶ ሺህ ህዝብ በነቂስ በመውጣት ያለምንም ኮሽታ በሰላም እንዲጠናቀቅ ላደረጋችሁት ክብር ከተማ አስተዳደሩ ትልቅ ምስጋና ያቀርባል ።

በአጠቃላይ በከተማው አንድም የፀጥታ ችግር ሳይፈጠር እንግዶች ከመጡበት ጊዜ ጀምሮ በትጋት ፀጥታውን ስታስከብሩ ለቆያችሁ የፖሊስ ፣ልዩ ሀይል፣ ፈደራል ፖሊስ፣ ሚሊሻና ህዝባዊ ሰራዊትም የሰላሙ ደጀን በመሆን ላደረጋችሁት አስተዋጽኦም ምስጋና አቅርበዋል።

የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ
አቶ ማርቆስ ማቴዎስ

Photos from የሲቀላ ቀበሌ ታክስ ማዕከል's post 02/11/2022

ከአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ለመላው የከተማው ህዝብ የተላለፈ ጥሪ
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
መላው የከተማዋ ነዋሪዎች በነገው ዕለት ሀሙስ ጥቅምት 24/2015 ዓ/ም ክቡር ጠቅላይ ምንስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከአርባ ምንጭ ከተማ ህዝብ ጋር ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በአርባምንጭ ዩንቨርስቲ አባያ ካምፖስ ስታዲየም እንድትገኙ ጥሪውን ያስተላልፋል ።

በመሆኑም የከተማዋ ነዋሪዎች የተለመደውን የሰላም ተምሳሌት እና የእንግዳ ተቀባይነት ውብ ባህላችሁን በዚህም እለት በመድገም ለክብር ጠቅላይ ምንስትሩ ፍቅራችሁን እንድትገልፁ ከተማ አስተዳደሩ ጥሪ አቅርቧል ።

Photos from የሲቀላ ቀበሌ ታክስ ማዕከል's post 02/11/2022

//የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር አብይ አህመድ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት አርባምንጭ ከተማ ገቡ//
💦💦💦💦💦💦💦💦💦💦💦💦💦💦💦💦
አርባምንጭ ፣ ጥቅምት 22/2015 ዓ.ም፦
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር አብይ አህመድ አርባምንጭ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በመንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና የጋሞ አባቶች ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። የሲቀላ ቀበሌ ታክስ ማዕከል ኃላፊ እንዲሁም ሠራተኞች የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር አብይ አህመድ እንኳን ወደ ምድረ ገነት የጋሞ ዞን ከተማ አርባ ምንጭ በደህና መጡ!!

Photos from የሲቀላ ቀበሌ ታክስ ማዕከል's post 25/10/2022

ዜና ሹመት:-
የአርባምንጭ ከተማ ህዝብ ምክር ቤት 2ኛ ዙር መርሃ- ግብር 10ኛ አስቸኳይ ጉባኤ ሹመት አጽዲቋል።

በዚህም መመሠረት

1. ወ/ሮ ስንታየሁ አብሬ:- የአርባምንጭ ከተማ አስ/ር ህዝብ ም/ቤት ዋና አፌ-ጉባኤ
2. አቶ ሻንዳማ ሻንቆ:- አ/ምንጭ ከተማ አስ/ር /ም/ከንቲባና ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ
3. አቶ ደሳለኝ ደመላሽ ካሣዬ :- አ/ምንጭ ከተማ አስ/ፐ/ሰርቨስጽ/ቤት ኃላፊ
4. ታምራት ጌታቸው አሰፋ-:-አርባምንጭ ከተማ አስ/ር ፕላን ጽ/ቤት ኃላፊ
5. አቶ ማትዮስ ማናዬ ማዶ: አርባምንጭ ከተማ አስ/ር ባህልና ቱሪዝም ፅ/ቤት ኃላፊ
6. አቶ ደግፌ አማሬ :- አ/ምንጭ ከተማ አስ/ር ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ
7.ወ/ሮ ሊዲያ ከንቲባ ካራ:- አ/ምንጭ ከተማ አስ/ር ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ
8. አቶ ቦጋል ቦቾ ዳዲኖ:- የአ/ምንጭ ከተማ ከንቲባ ህዝብ ግ/ዋ/አማካሪ
9. አቶ አስጨናቂ ዳዊት ዳጌ:- አም/ከተማ አስ/ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ
10. አቶ ደጋጋ ዳውላ ዳንጋሮ:- ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ
11. አቶ አጅሬ አዳሙ አቶ: -ከንቲባ ሀብት ልማት አማካሪ
12. አቶ ሳሙኤል ግርግሳ :- አርባምንጭ ከተማ አስ/ር ህብረት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ
13. አቶ መሀለት ደፈርሻ:- የአርባምንጭ ከተማ አስ/ር ሴቶችና ህፃናት ጽ/ቤት ኃላፊ
14. ወ/ሮ አዜብ ዘውዱ :- አ/ምንጭ ከተማ አስ/ር መንግስት ኮ/ሽን ጽ/ቤት ኃላፊ
15. ወ/ሮ ወይንሸት ሳሙኤል:- የአ/ምንጭ ከተማ አስ/ር ማዘጋጃ ቤ/ዊ/አገ/ጽ/ቤት ም/መሬት ልማት ዘርፊ ኃላፊ
16. አቶ ባህሩ በዙ :- አ/ከተማ አስ/ር ብ/ፓ/ፖለትካናሪዕዮተ ዓለም ግ/ም/ኃላፊ
17. አቶ አስጨናቅ ቆንጆ:- ሥራ ዕድል ፈ/ኢን/ዝ/ጽ/ቤት ም/ማኑፋክቸርንግ ዘርፊ ኃላፊ
18. አቶ ሸዋንግዛው ኡራጌ:- አ/ም/ከተማ አስ/ር ብ/ፓ/ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፊ ም/ኃላፊ
19. አቶ ሀ/ሚካኤል ሴኮ :- አ/ምንጭ ከተማ አስ/ር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ም/ወጣት ዘርፊ ኃላፊ
የአርባምንጭ ከተማ አስ/ር አሁን ከደረሰበት የልማትና ዕድገት ሂደቱን ቀጣይነት በሚያረጋግጥ መንገድ ብቁና ታማኝ የህዝብ አገልጋይ አመራሮችን ሹመት ፈጽሟል። በአመራርነት የቆዩና ትጋታቸው በውጤት የታጀበ መሆኑን በመመዘን የማትጋት ሥራ በትምህርት አቅማቸውን እንድያሳድጉም በ2015 ዓ/ም ከፊተኛ ትምህርት ዕድል ፈጥሯል።

Photos from የሲቀላ ቀበሌ ታክስ ማዕከል's post 20/10/2022

ለኢትዮጵያ እቆማለሁ በሚል መሪ ቃል ታላቅ ህዝባዊ ሰልፍ በአርባምንጭ ሁለገብ እስታዲየም ቅዳሜ ከጥዋቱ 12:30 ጀምሮ ይካሄዳል። በዝህም ህዝባዊ ስልፍ ላይ የማዕከላችን ሠራተኞች የቀበሌያችን ግብር ከፋዮች የከተማችን ነዋሪዎች እንዲሁም ወጣቶች በነቂስ በመወጣት ድምፃችንን ለማስማት ዝግጅት ተጀምሯል ቅዳሜ በአርባምንጭ ሁለገብ ስቴድየም እንገናኝ።

Photos from የሲቀላ ቀበሌ ታክስ ማዕከል's post 19/10/2022

የገቢ አሰባሰብ ሂደት ውስጥ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ።

ጥቅምት 09/02/2015 ዓ.ም፦ (አርባምንጭ ከተማ መ/ኮሚዩኒኬሽን) የአርባምንጭ ከተማ ገቢዎች ባለስልጣን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በገቢ አሰባሰብ ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሂዷል።

በከተማው የገቢዎች ባለስልጣን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሪት ሊዲያ ከንቲባ በከተማው ገቢ አሰባሰብ ሂደት ውስጥ የባለድርሻ አካላት ሚና ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑን ገልጸው ቅንጅታዊ አሰራሮች ላይ የተጠናከረ ሥራ መሠራት እንዳለበት ተናግረዋል ።

በበጀት አመቱ የከተማውን የመልማት ፍላጎት ለማጣጣም የበጀት ዓመቱ ዕቅድ ከፍተኛ ሲሆን በዚህም ገቢን አሟጦ ለመሰብሰብ የባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ ስራ ውሳኝ ነው ብለዋል።

በምክክር መድረኩ የተገኙት የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ማርቆስ ማቴዎስ የገቢ ምንጮችን በመጠቀም የህብረተሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ደረጃ በደረጃ መፍታት እንደሚቻል ጠቁመዋል።

ባለፈው 2014 በጀት ዓመት በቅንጅት በመሰራቱ የተሻለ ገቢ ለማሰብሰብ መቻሉን የተናገሩት ከንቲባው በዘንድሮ 2015 በጀት ዓመትም ከአምናው የተሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ ሁሉም ባለድርሻ አካላት መረባረብ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

በመድረኩ የማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ አሰባሰብ ሂደት ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት ሥልጠና ተሰጥቶአቸዋል ።

በመጨረሻም ሁሉም ባለድርሻ አካላት የ2015 ዕቅዱን በተሻለ ቅንጅት ለመፈጸም የበኩላቸውን ሚና ለመወጣት የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል።

በአሰፋ ጪሻ

Photos from የሲቀላ ቀበሌ ታክስ ማዕከል's post 17/10/2022

የሰንደቅ ዓላማ ቀን በደማቅ ሁኔታ ተከበረ***************************************************ዛሬ ቀን 7/1/2015 ዓ.ም የሰንደቅ ዓላማ ቀን የሲቀላ ቀበሌ አመራሮች እና የቀበሌው የሴክተር መስሪያ ቤት ሠራተኞች በጋራ የባንድራ ቀንን ምክንያት በማድርግ በደማቅ ሁኔታ አክብረዋል፡፡ በዕለቱም የሲቀላ ቀበሌ አስተዳደር እና የቀበሌው ዋና አፈ ጉባኤ የሰንደቅ ዓላማን በዓል ማክበር ለምን እንዳስፈለገ ፤ በሀገራችን ለ15ተኛ ዙር እየተከበረ መሆኑን እና ሀገራችን የጀመረችውን የለውጥ ጉዙ በይበልጥ ለማስቀጠል ውስጣዊ አንድነታችንን ማጠናከር እና ሀገራችን ከገጠማት ውስጣዊ ችግር ለመላቀቅ እኛ ኢትዮጵያውያን ከጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ጎን በመሆን በአንድነት በሀገራዊ ስሜት መንቀሳቃስ ያሻል ያሉ ሲሆን በዕለቱም ሰንደቅ ዓላማችን የብዝሃነታችን መገለጫ የሉዓላዊነታችን ምሶሶ ነው !! በሚል መሪ ቃል የተከበር ስሆን የኢትዮጵያ ህዝቦች መዝሙር በጋራ ከተዘመረ በኃላ የዕለቱ ፕሮግራም ተጠናቋል ፡፡

Photos from የሲቀላ ቀበሌ ታክስ ማዕከል's post 14/10/2022

አርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር እጀግ በጣም ዘመናዊና ደረጃውን የጠበቀ የእሳት አደጋ መኪና/ማሽን/ግዢ ፈጽሞ ተረከበ።

የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር የከተማዋን የለውጥ ግስጋሴ ባገናዘበ መንገድ ዘመናዊ የእሳት አደጋ መከላከያ ተሽከርካሪ ማሽን አስፈላጊ እና መሠረታዊ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ህበረተሰቡ የእሳት አደጋ በሚፈጠርበት ወቅት ስጋት ውስጥ እንዳይወድቅ እና ለቅድመ ጥንቃቄ አስፈላጊ መሆኑን በማሰብ የአርባምንጭ ከተማ ከንቲባ አቶ ማርቆስ ማቴዎስ ግዥ ፈጽሞ ተረክበዋል። ለከተማችን ማህበረስብ የመሰርተ ልማት እና የተለያዩ ፍላጎቶችን ለማሳካተሰ የገቢ አቅማችንን ማሳደግ ሌብነትን መከላከል እና አመለካከቶችን መታገል ከአንድ የመልማት ፍላጎት ካለው የከተማ ማህበረስብ እንዲሁም ከግብር ከፋዮቻችን ይጠበቃል።

13/10/2022

ለፀረ-ሙስና ትግሉ መጠናከር የሚዲያ ሚና
/የፌደራል ስነ ምግባርና ፀረሙስና ኮሚሽን /
ሙስና በተንሰራፋበት ሀገር ሚዲያው ነጻና ገለልተኛ ሆኖ ለማገልገል አዳጋች ይሆንበታል፤ ለህብረተሰቡ መረጃዎችን ማድረስ ይቅርና የራሱም መረጃ የማግኘት መብቶች ይጣሳሉ፣ ተልዕኮውንም በአግባቡ ሳይወጣ ይቀራል፡፡

ይህ ደግሞ መገናኛ ብዙኃን ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን የመከላከል ሥራ ከዋና ዋና ሥራዎቻቸው ውስጥ አንዱ ሊያደርጉት እንደሚገባ ያመላክታል፡፡ መገናኛ ብዙኃን በፀረ-ሙስና ትግሉ ውስጥ በራሳቸው ከሚያደርጉት አስተዋጽኦ በተጨማሪ ሕብረተሰቡ በፀረ-ሙስና ትግሉ ረገድ ጽኑ አቋም እንዲኖረው በማድረግ በኩል የማይተካ ሚና ይጫወታሉ፡፡

ይህ ሁኔታ በአለማችን ላይ በስፋት የተሰራበትና እየተሰራ ያለበት ጉዳይ ነው፡፡ ለአብነት ያህል በአሜሪካ የፕሬዚዳንት ኒክሰን መባረር (የወተርጌት ቅሌት)፣ የኢንዶኔዥያ ፕሬዚደንት ሱሃርቶ፣ እ.ኤ.አ. በ1990ዎቹ በላቲን አሜሪካ የመገናኛ ብዙኃን የሙስና ዘገባዎች የኢኳዶሩን አብደላ ቡካራምን፣ የቬኔዙዌላውን ካርሎስ አንድሬስ ፔሬዝ፣ የብራዚሉን ፈርናርዶ ኮሎርን፣ የደቡብ አፍሪካ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማን እና ሌሎች ሙስናዎች በማጋለጥ መሪዎቹ ሥልጣን እንዲለቁ ሚዲያ የአንበሳውን ድርሻ መጫወቱን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡

ይሁን እንጅ በአገራችን እስከ አሁን ሚዲያ በፀረ-ሙስና ትግሉ ረገድ የሰራቸው ሥራዎች በቂ ናቸው ማለት አይቻልም፡፡ የአንድ ወቅት ሥራ ብቻም መሆን የለበትም፡፡ የመገናኛ ብዙኃን ትኩረታቸውን መልካም ሥነ-ምግባርን በመገንባት ላይ በማድረግ ስለሙስና የማስተማር፣ በጉዳዩ ዙሪያ ለሕዝቡ መረጃ የመስጠትና ግንዛቤ በማስጨበጥ ንቃተ ህሊናን የማሳደግ፣ የሙስና ተግባራት በምርመራ ጋዜጠኝነት አብጠርጥሮ በማውጣት የማጋለጥና የህግ ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ የማድረግ ሥራዎችን መስራት ይኖርባቸዋል፡፡

በዋናነት በሥነ-ምግባር የታነፀ ማህበረሰብ እንዲጎለብት በማድረግ ሙስናን መከላከል የሚዲያ አጀንዳ ሊሆን ይገባል፡፡ ሚዲያው ሙስና የብልጠት ሳይሆን የሞራል ውድቀት መሆኑን ስራዬ ብሎ ህዝቡን ሊያስተምር ይገባል፡፡ የህብረተሰቡን በተለይም የህጻናትና ወጣቶችን ሥነ-ምግባርና ግብረ-ገብነትን ከማህበራዊ ሕይዎትና ከሀገራዊ ፍቅር ጋር አዛምዶ ማስተማርና መልካም ባህሪ እንዲያብብ ማድረግ በዋናነት ሚዲያ ሊሰራቸው ይችላል ተብሎ የሚጠበቁ ተግባራት ናቸው፡፡

የፀረ-ሙስና ትግሉን እንቅስቃሴ የሚያሳዩ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ በስፋት ተደራሽ በማድረግ በኩልም ከሚዲያ የተሻለ አማራጭ መንገድ የለም፡፡ በዚህም ረገድ ሚዲያ ከወትሮው በተለየ መልኩ ጠንክሮ በመስራት ሀገራዊና ህዝባዊ ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል፡፡ በተለይ በአገራችን እምበዛም ያልተሰራበት የምርመራ ጋዜጠኝነት ሥራ በፀረ-ሙስና ትግሉ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት ሊሰራበት የሚገባው አብይ ጉዳይ ነው፡፡

"የምርመራ ጋዜጠኝነት ሥራ ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን ያጋልጣል፣ ግልፅነትና ተጠያቂነት እንዲሰፍን በር ይከፍታል፣ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ይረዳል፤ እንዲሁም በመረጃ ምንጭነትም ያገለግላል፡፡

Photos from የሲቀላ ቀበሌ ታክስ ማዕከል's post 13/10/2022

የቀድሞ የጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ወንድሙ ኩምሳ በምትካቸው ለተሾሙት አቶ አብረሃም ቱሉ የሥራ ርክብክብ አደረጉ፡፡ //////////////////////////////////////////////////////////////////////////
የጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ የነበሩት አቶ ወንድሙ ኩምሳ በምትካቸው ለተሾሙት አቶ አብረሃም ቱሉ ጥቅምት 02/2015ዓ/ም የሥራ ርክብክብ ፈጸሙ፡፡ አቶ አብረሃምም ከማኔጅመንት ዓባላት ጋር ትውውቅ አድርገው ሥራቸውን በይፋ ጀምረዋል፡፡ /የመ/ቤቱ ህዝብ ግኑኝነት እንደዘገበው/
አቶ ወንድሙ በርክብክቡ ወቅት በ2015ዓ/ም ተለጥጦ የታቀደውን የ2.8 ቢሊዮን ብር የገቢ ዕቅድ ለማሳካት በተሻለና ቁርጠኛ በመሆን የተለያዩ ተግባራትን ለማከናወን ዝግጅት በማድረግ ወደ ተግባር የተገባበት ወቅት ላይ ተቋሙ እንደሚገኝ ገልጸው ለዚሁም የተጀመሩና በቀጣይ ለመተግበር የታቀዱና ትኩረት ሊሰጥባቸው የሚገባቸውን ዋና ዋና ተግባራትን በምትካቸው ለተሾሙት አብራርተዋል፡፡
የማኔጅመንት ዓባላትም አብረዋቸው በሠሩባቸው ወቅት መልካም የሥራ ግኑኝነት እንዳላቸው፣ በቡድን የመሥራት ልምዳቸውን ማገዝና በቅንነት መምራት በመቻላቸው በጋራ የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገብ መቻሉን አውስተው በሄዱበት መልካም የሥራ ጊዜ እንዲሆንላቸው ተመኝተዋል፡፡ በተመሳሳይም ከአቶ አብሃምም ጋር በሙሉ አቅም በጋራ በመሥራት የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት ቁርጠኛ መሆናቸውን በመግለጽ እንኳን ደህና መጡ!! ብለዋል፡፡
አቶ አብረሃም ቱሉ የጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊም ከተሰጣቸው አጭር ገለጻ በኃላ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት የተለያዩ ስልቶችን በመንደፍ ወደ ተግባር እንደሚገቡና በተለይም የገቢ መሠረት የማስፋት፣የሰው ሀይል ምርታማነት የማሳደግ፣የገቢ ፖቴንሽያል ለይቶ ማከናወን፣የህግ ማስከበር ሥራ የማጠናከር፣የውዝፍ እዳ የማስመለስና ሌሎችን ተግባራትን በማከናወን ከዞናችን ኢኮኖሚ ጋር ተመጣጣኝ የሆነ ገቢ በመሰብሰብ የተቀመጠው ግብ እንዲሳካ እንደሚሰሩና በተለይም የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ የማሳደግና ውጤታማ የሆነ የድጋፍና ክትትል ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል በማድረግ ከዞኑ የወጪ ፍላጎት በገቢ የሚሸፈነውን ለማሳካት ተግተው እንደሚሰሩ በውይይት ወቅት አሳውቀዋል፡፡መልካም የሥራ ጊዜ እንመኛለን።

Photos from የሲቀላ ቀበሌ ታክስ ማዕከል's post 08/10/2022

የአርባምንጭ ከተማ ከንቲባ የመውሊድ በዓልን በማስመልከት ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ፤

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1 ሺህ 497 ዓመት የነብዩ ሙሀመድ የልደት (መውሊድ) በዓል በሠላምና ጤና አደረሳችሁ ።

በዓሉ የፍቅር እና የአብሮነት እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ ።

መላው ሕዝበ ሙስሊም 1497ኛ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር የነቢዩ ሙሐመድ አስተምህሮ የሆኑትን የእዝነት፣ የርህራሄ፣ የቸርነት ሰብእናን በመጎናጸፍ እና እርስ በእርስ የመደጋገፍ በጎ አኗኗሩን ይበልጥ የሚያጠናክርበት ሊሆን ይገባል፡፡

በዓሉን እምነቱ በሚያዘው መሰረት አቅመ ደካሞችን በማሰብና ያለው ለሌለው በማካፈል እንዲሆንም አሳስባለሁ ።

በድጋሚ መልካም የመዉሊድ በዓል !
ኢድ ሙባረክ!

አቶ ማርቆስ ማቲዎስ
የአርባ ምንጭ ከተማ ከንቲባ

መስከረም 28/2015 ዓ.ም

06/10/2022

👉ግብርን ዘግይቶ መክፈል የሚያስከትለው ቅጣት👈
***
ግብርዎን በወቅቱ ሲከፍሉ ከብዙ እንግልት ከመዳንዎ በተጨማሪ አላስፈላጊ ቅጣት ከመቀጣት ይድናሉ፡፡ ግብርን በወቅቱ ከከፈሉ ደግሞ ለአገርዎ እና ለእርስዎ የሚጠቅመውን በወቅቱ እና በአስፈላጊው ወቅት ያደረጉ ኃላፊነት የሚሰማዎት ዜጋ መሆንዎን የሚያስመሰክሩበት ነው፡፡
ግብርዎን በተለያየ መክንያት ሳይከፍሉ ካዘገዩ ከሚደርስብዎት ውጣ ውረድ በተጨማሪ ቅጣቶችንም ለማስተናገድ ይገደዳሉ፡፡ ከነኚህ ቅጣቶች ውስጥ ለአብነት ያህል የሚከተሉት ይገኙበታል፡፡

ማንኛውም ግብር ከፋይ በግብር መክፈያ ጊዜው ውስጥ ግብሩን ሳይከፍል ከቀረ ለዘገየበት ጊዜ፡-
1- ለአንድ ወር ወይም የወሩ ከፊል ለሆነው ጊዜ ባልተከፈለው ታክስ ላይ 5% (አምስት በመቶ) ፤ እና
2- ከዚያ በኋላ ለዘገየበት ለእያንዳንዱ ወር ወይም የወሩ ከፊል ለሆነው ጊዜ ባልተከፈለው ግብር ላይ ተጨማሪ 2 % (ሁለት በመቶ) ቅጣት ይከፍላል፤
ግብርዎን በወቅቱ እና በታማኝነት በመክፈል ለአላስፈላጊ እንግልት እና ቅጣት አይዳረጉ፡፡

Photos from የሲቀላ ቀበሌ ታክስ ማዕከል's post 05/10/2022

ቢሮው በ 2014 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና በ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ በ ሀድያ ዞን ሆሳዕና ከተማ ምክክር እያካሄደ ነዉ።
******
የደቡብ ብ/ብ/ህ/ክልላዊ መንግስት ግቢዎች ቢሮ የክልል ዓመራሮችን ጨምሮ ከዞን እና ከልዩ ወርዳ ገቢ መዋቅር እንዲሁም የተለያዩ ባልድርሻ አካላት በተገኙበት ዓመታዊ ጉባኤ እያካሄደ የሚገኝ ሲሆን ጉባኤውን የእንኳን ድህና መጣችሁ የመክፍቻ ንግግር ያደረጉት የሃድያ ዞን ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ እያሱ ሻንቆ እንደገለጹት በሃገሪቷ ያለዉን የኢኮኖሚ ጫና ተቋቁሞ በማለፍ አስተማማኝ የልማት አቅም መፍጠር የሚቻለው የተጀመረውን ሃገር በቀል የኢኮኖሚ ፖሊሲ ትግበራ አጠናክሮ በመቀጠል እና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ሊሰበሰብ የሚገባውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ የልማት ውጪን በራስ አቅም መሽፈን ሲቻል ብቻ ነው ብለዋል። የመንግስት የገቢ አቅም መጠናከር በየደረጃው ለሚነሱ የህዝቦች የልማት ጥያቄዎች አስተማማኝ ምላሽ መስጠት በመሆኑ የሚሰበሰበው ግብር ተመልሶ ለየአካባቢያችን ልማት በመሆኑ ሁላችንም በትኩረት ልንሰራ ይገባል ብለዋል።
የደቡብ ብ/ብ/ህ/ክ/መንግስት ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ዘይቱና ኢብራሂም በበኩላቸው ባለፈው በጀት አመት ህገ ወጥ የንግድ እንቅስቃሴን ለመከላከል ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት በርካታ አዳዲስ ግብር ከፋዮች እንዲመዘገቡ የተደረገ መሆኑን ገልጸው አገልግሎት አሰጣጡን በማዘመን ፍትሃዊነትና ግልጸኝነትን የሚያረጋግጥ ቴክኖሎጂ ተደራሽ እየተደረግ ነዉ ብለዋል።
በባልፈው በጀት ዓመት 14.1 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ገልጸው በተያዘው በጀት አመትም ከመደበኛ እና ማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ ብር 17.9 ብር በመሰብሰብ ከክልሉ አጠቃላይ ምርት ያለውን ድርሻ 10.65 በመቶ እንዲሁም ክልላዊ የወጪ ሽፋን ወደ 38.69 በመቶ ለማድረስ እቅድ መያዙን በመግልጽ ለዚህም ስኬት ሁሉም የድርሻውን እንዲውጣ ጥሪ አቅርብዋል።
በጉባዔዉ የ2014 የዕቅድ አፈፃፀም እና የ2015 ዕቅድ ቀርቧል።

Want your school to be the top-listed School/college in Adama?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Category

Telephone

Address

Df
Adama
Other Schools in Adama (show all)
Kedirabuna Kedirabuna
Adama
Adama, 1000

Driver licence school Adama mm promotion kedirabunafacebook yutube instegetam telegerm imo facebook yuotube telegrok yuotube telegram okbarachuu nidanda'an

Ibn Abbas Training & Development Center Ibn Abbas Training & Development Center
Adama
Adama

Found by Abbas Ibrahim | Includes Quran lessons| Hadith of Prophet (saw)|and more courses

Simon Tesfaye Simon Tesfaye
Fichee
Adama, NO

Promo

Sena Yerosan School of Excellence Sena Yerosan School of Excellence
Ganda Hara & Bole
Adama

Sena Yerosan School provides quality education for all citizens.

Youtu.be/neeh5w1rxbw Youtu.be/neeh5w1rxbw
Saqalo
Adama, 7.46

Sami Sami
Gelan
Adama

School  life School life
Adama

Leyila mohammed

Homacho sabaa Homacho sabaa
Hinjiruu
Adama, ZIIPI

Maddaa walaabuu Yuuniivarsiitii Maddaa walaabuu Yuuniivarsiitii
Diree Dawa
Adama, GAMEE

Kube generation show lammii baraatetu gaffii mirgaa gafaata.

Awash  Academy Awash Academy
Adama

Awash Academy is a private organization.the school generates knowledgeble students that have a skill and it contributes to the country a good students .

Ifa boruu Ifa boruu
Alii Birraa
Adama

Ifa boruu like fi sher godhaa

Moke man Moke man
Arsi
Adama, MOK1212