Garo Gere Soccer Agency

A soccer agency work on football. our services
- player and club representation
- legal support a

22/11/2022
ስፖርት ዞን sport zone 16/09/2022

Let's Vote Our Young Boy Alazar Markos as he perform very well on 2014 Betking Ethiopia Premier League!!

ስፖርት ዞን sport zone የአመቱ ምርጥ ግብ ጠባቂን ማን ያሸንፋል ? public poll ሚኬል ሳማኪ – 245 👍👍👍👍👍👍👍 66% ቻርለስ ሉክዋጎ – 81 👍👍 22% አላዛር ማርቆስ – 44 👍 12% 👥 370 people voted so far.

Photos from Garo Gere Soccer Agency's post 29/08/2022
Photos from Garo Gere Soccer Agency's post 28/08/2022

መልካም ተግባር ነው ደግፈናልም!!!

ዛሬ ነሃሴ 22/2014 የሃዋሳ ስፖርት ክለብ ደጋፊዎች ማህበር ከሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሜሪጆይ የአረጋውያንና መርጃ ማህበር ግቢ ውስጥ ለ150 አረጋውያን መአድ የማጋራት መርሃ ግብር በማድረግ ለአረጋውያን ይኣለውን ድጋፍ አሳይታል። የክለቡ ደጋፊዎች ማህበር ፕሬዝዳንት እንዳሉት ከሆነ በሚቀጥለው ሳምንት በሃዋሳ ከተማ "ለክለቤ አሮጣለው" በሚል መሪ ቃል የክለቡ ደጋፊዎች ለክለባቸው ድጋፍን እንዲያደርጉ የጎዳና ላይ እሩጫን ከከተማው ባህልና ስፖርት ጋር በመተባብር ያዘጋጀ ሲሆን ማህበረሰቡ በነቂስ ወጥቶ ድጋፍን ሊያሳየን ሚችለው እኛ ማህበረዊ ሃላፊነታችንን ስንወጣና ስንተጋገዝ ሲያይ በመሆኑ ቀድመን እንደዜጋ የሚጠበቅብንን ድጋፍ አረጋውያንን ወላጆቻችን አድርገናል ብለዋል። ድርጊቱ በየግዜው የሚቀጥልና በሌላውም ስፖርት ክለቦች ሊለመድ የሚገባ ነው ያሉ ሲሆን በሚቀጥለው እሁድ የሃዋሳ ክለብ ደጋፊዎችና የከተማው ባህልና ስፖርት "ለክለቤ እሮጣለው" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው የጎዳና እርጫ ላይ በመሳተፍ ለሃዋሳ ከነማ ስፖርት ክለብ ድጋፉን እንዲያሳይ ጠይቀዋል።

ይህ አይነት መልካም ድርጊት በስፖርቱ አለም ያልተለመደ ግን ሁሉም ክለቦች ማህበራዊ ሃላፊነት እንዳለባቸው በመረዳት ሊከተሉት የሚገባ ሲሆን እኛም በዚህ አይነት ድርጊት የተሳተፍን የመጀመሪያ ክለብ በመሆናችን እንደደጋፊ ኩራት ተሰምቶናል። በሚቀጥለው ከኔ ለማህበረሰቤ በሚል መሪ ቃል ከዚ ሰፋ ያለ የበጎ አድራጎት እቅድ እንዳለ የደጋፊዎች ማህበር ፕሬዘዳንት ያሳወቁ ሲሆን በመርሃ ግብሩ ላይ የክለቡ አመራሮችና ካስ ተጫዋቾች ተሳታፊ ይሆናሉ ብለዋል።እኛም የስፖርቱ ባለድርሻ እካላት እናም የክለቡ ደጋፊዎች ለንደዚ አይነት ቀና ስራ ክለቡንና የክለቡን አመራር በሞራል በማንኛውም አስፈላጊ ነገሮች ድጋፋችንን ልንገልጽና የበኩላችንን አስተዋጾ ልናበረክት ይገባል።

17/07/2022

የደስታ ቀናችን ነው !!!
#ኢትዮጵያ 2ኛውን ወርቅ አገኘች

ኢትዮጵያዊው አትሌት ታምራት ቶላ በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮን የወንዶች ማራቶን 1ኛ ሆኖ በመጨረስ፣ ለሀገሩ 2ኛውን የወርቅ ሜዳሊያ አስገኝቷል። ሌላው ኢትዮጵያዊው አትሌት ሞስነት ገረመው ውድድሩን በ2ኝነት አጠናቆ ለሀገሩ የብር ሜዳለያ አስገኝቷል።

እንኳን ደስ አለን!!

Garo Gere Soccer Agency

13/07/2022

The Big Central Defense Solomon Wodessa is Loading

13/07/2022

Done Deal!! Birhanu Ashamo to Hawassa City FC

Photos from Garo Gere Soccer Agency's post 12/07/2022

Done deal!! Mujib Kasim and Adisu Atula
to Hawassa City FC

05/07/2022

ሐምሌ ፩ የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዝውውር መስኮት መከፈቱን ተከትሎ በጋሮ ገሬ የእግር ኳስ ተጫዋቾች ወኪል በኩል ሚከናወኑ ዝውውሮችን ይህን ፔጅ ፎሎው በማድረግ ይከታተሉ።

30/06/2022

ዋንጫውን ቅዱስ ጊዮርጊስ ወይስ ፋሲል ያነሳው ይሆን እንዲሁም ሶስተኝነትን ሲዳማ ቡና ያስጠብቅ ይሆን ወይስ ሀዋሳ ከተማ ይረከበው ይሆን እንዲሁም ሶስተኛው ወራጅ ማን ሊሆን ይችላል ተብሎ የሚጠበቀውን የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የመጨረሻ ሳምንት መርሐግብር ለመመልከ ወደ ውቢቷ ባህር ዳር በማቅናት ላይ ነኝ!!

I am heading to the beautiful city Bahir Dar to watch the last and expected Betting Ethiopian Premier League 2014 Weekend schedule to see if the trophy will be won by St. George's or Fasil and Will Sidama Coffee retain the third place or will Hawassa take over? and who will be the third runner-up: Dire Dawa City, Adama city or Adiss Ababa city??

Garo Gere Soccer Agency

Photos from Garo Gere Soccer Agency's post 04/06/2022

Good Luck Ethiopia!!

መልካም ዕድል ለሀገሬ!!

For the games ahead

Ethiopia Vs Malawi June 5 @ 10:00
Ethiopia Vs Egypt June 9 @ 4:00

Photos from Garo Gere Soccer Agency's post 28/04/2022

Ayidde Cambalaalla!!
=================
አይዴ ጫምባላላ!!

Hawalle Sidaamu Fichee-Cambalaallate Ayyaanira Keere Iillishinke!

እንኳን የሲዳማ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል ፍቼ ጫምባላላ በሰላም አደረሳችሁ።

Fichee jeejji jeejji!!
ሚያዝያ 2014 ዓ.ም ሀዋሳ!
Garo Gere Soocer Agent!!

12/04/2022

ተጠባቂው የቤትኪንግ ኢትዮጲያ ፕሪሜርሊግ ጨዋታ ነገ አመሻሽ 12:00 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ስታዲየም የሲዳማ ክልል ክለቦች ሲዳማ ቡና እና ሀዋሳ ከነማ(ሮዱዋ ደርቢ) መካከል ይደረጋል።
Guess and get your reward
ይገምቱ ይሸለሙ !!
Good Luck to both of you!!!

Photos from Garo Gere Soccer Agency's post 09/01/2022

Guess and get your reward
ይገምቱ ይሸለሙ !!
Good Luck Ethiopia!!
መልካም ዕድል ለሀገሬ!!

08/10/2021

The coaches!!!
Have a great year!!
This is the picture that I like!!!

መልካም የውድድር አመት ይሁንላቹ!!!

Photos from Garo Gere Soccer Agency's post 02/10/2021

እንኳን 2014 ኢሬቻ በዓል በሠላም አደረሰን አደረሳችሁ!! ኢሬቻ "የሰላምና የአንድነት ምልክት"

Irreechu "Keerunna Mittimmate Malaateeti" Hawalle iillishi'ne!

Mallattoo nageenyaa fi tokkummaa kan ta'e Irreecha bara 2014 baga geessan!

Irreecha: A symbol of peace & unity. Happy Irreecha festival!

29/09/2021

በሲዳማ ጎፈሬ ካፕ በሁለተኛዉ ዙር ጨዋታዎች በሮዱዋ ደርቢ የሲዳማ ክልል ክለቦች ሲዳማ ቡና እና ሀዋሳ ከነማ የሚገናኙ ሲሆን በዛሬው እለት በሀዋሳ አርተፊሻል ሜዳ ከቀኑ በ8:00 ሰአት ላይ የሚጫወቱ ይሆናል።

Photos from Garo Gere Soccer Agency's post 24/09/2021

🏆

በሲዳማ ክልል አዘጋጅነት ለመጀመሪያ ግዜ በ5 የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች መሀከል ከነገ ጀምሮ የሚደረገዉ የጎፈሬ የሲዳማ ካፕ ዉድድር የእጣ ማዉጣት ስነስርዓት በትላንትናው እለት በሀዋሳ ሌዊ ሪዞርት ተካሂዷል።

በዚህም መሰረት ከባለ ሜዳዉ ቡድን ሲዳማ ቡና ጋር ለመጫወት በቅድሚያ እጣ የወጣ ሲሆን ድሬዳዋ ከነማ ደርሶታል።

የመክፈቻዉ ጨዋታ ነገ ከቀኑ 8:00 ሰአት ላይ በሀዋሳ አርተፊሻል ሜዳ በሲዳማ ቡና እና በድሬዳዋ ከነማ መሀከል ይደረጋል።

ጎፈሬ ካንፓኒ ለተወዳዳሪዎች ለአምስቱም ክለቦች በነፃ ሙሉ ትጥቅ ያቀረበ ሲሆን ለክለቦቹ በትላንትናው እለት አስረክቧል።

ጋሮ_ገሬ_ስፖርት_ማናድመንት ደግሞ የዚህ ዉድድር አጋር በመሆን የሚሰራ ይሆናል።

ቀሪ ጨዋታዎች ደግሞ :-

እሁድ መስከረም 16

ሰበታ ከተማ 8 : 00 ሀዲያ ሆሳዕና

አራፊ – ሀዋሳ ከተማ

ረቡዕ መስከረም 19

ሀዋሳ ከተማ 8 : 00 ሲዳማ ቡና
ድሬዳዋ ከተማ 10 : 00 ሀዲያ ሆሳዕና

አራፊ – ሰበታ ከተማ

ቅዳሜ መስከረም 22

ሲዳማ ቡና 8 : 00 ሰበታ ከተማ
ሀዋሳ ከተማ 10 : 00 ድሬዳዋ ከተማ

አራፊ – ሀዲያ ሆሳዕና

ማክሰኞ መስከረም 25

ሰበታ ከተማ 8 : 00 ድሬዳዋ ከተማ
ሀዋሳ ከተማ 10 : 00 ሀዲያ ሆሳዕና

አራፊ – ሲዳማ ቡና

አርብ መስከረም 28

ሲዳማ ቡና 8 : 00 ሀዲያ ሆሳዕና
ሰበታ ከተማ 10 : 00 ሀዋሳ ከተማ

አራፊ – ድሬዳዋ ከተማ

በዚህ ዉድድር ላይ ደጋፊዎች እንዲገቡ የተፈቀደ ሲሆን እኛም ሙሉ ዉድድሩን በቀጥታ በገፃችን ላይ የምናቀርብላችሁ ይሆናል።

Photos from Garo Gere Soccer Agency's post 11/09/2021

Hawalle toophiyu haaru dirira keerunni iillishi'ne, iillishinke.

2014 MD keerunnihanna ikkonke.

Baga Waggaa Haaraa Bara 2014 Nagaa fi Fayyaadhaan nuu gahe

❤❤ Happy New Year ❤❤❤

እንኳን ለ2014 ዓ.ም አዲስ ዓመት በሰላምና በጤና አደረሰን አዲሱ ዓመት የተሻለች: የበለፀገች እና ሰላሟ የተረጋገጠባት ህዝቦቿ የሚኮሩባት ኢትዮጵያ ሀገሬን ሁላችንም የምናይበት የበረከት ዓመታችን ነው እንኳን አደረሰን።

Photos from Garo Gere Soccer Agency's post 07/09/2021

እንኳን ደስ አለሽ ሀገሬ ኢትዮጵያ!!

Congratulations 🎉 Ethiopia 🇪🇹!!

ሽልማቱን የሚወስዱ ግምቱ የተሳካላቸው ሥስቱ ተከታታዮቻችን ከታች በፎቶ ባስቀመጥነው መለያ ተለይተው ታውቅዋል እነርሱም : -
1. Firew Ye Buniye
2. Bura H HT
3. Wendi Make

ተሸላሚዮቻችን እንኳን ደስ አላቹ እያልኩ ሽልማታቹን ስልክ ቁጥራቹን በውስጥ በማስቅመጥ ደውለን የምንሰጣቹ ይሆናል።

06/09/2021

ይገምቱ ይሸለሙ!

ባለፍው ጫወታ ግምቱ ተሳክቶለት የሸለምነው Ras Wudnhe Teshome ሲሆን ነገ 10:00 ላይ በባህር ዳር ዓለምአቀፍ ስታዲየም የሚደረገው የኢትዮጵያ እና ዚምባብዌ ጨዋታን ውጤት በመገመት አሁንም ይሸለሙ።
ውጤቱን በትክክል ለሚያገኙ ሦስት (3) ቀዳሚ መላሾች የሲዳማ ቡና ደጋፊዎች ለሆናቹ አዲሱን የቡድናቹን የደጋፊዎች ቲሸርት እንዲሁም ላልሆናቹ ደግሞ የጎፈሬ ምርት የሆነ አሪፍ የዐመት ባዐል ቲሸርት የምንሸልም ይሆናል።
መልካም ዕድል ለሀገሬ!!

Guess and get your reward!!

Ras Wudnhe Teshome, who won the last match guess reward now we are requesting you to guess and get your reward the tomorrow match between Ethiopian and Zimbabwe at the Bahir Dar International Stadium.
We will reward the three (3) first responders 👕 who get the result correctly.
Good Luck Ethiopia!!

03/09/2021

Guess and get your reward
ይገምቱ ይሸለሙ !!
Good Luck Ethiopia!!
መልካም ዕድል ለሀገሬ!!

Photos from Garo Gere Soccer Agency's post 01/09/2021

በዕውቀት እንዲሁም ድንቅ በሆነ አሰልጣኝነቱ በግል የማውቀው ወጣቱ ዳዊት ታደለ ገላን ከተማን ለማሰልጠን ተስማምቷል።
መልካሙ ሁሉ ይግጠምህ !!

Photos from Garo Gere Soccer Agency's post 26/08/2021

የተሳካ ስምምነት

በተጠናቀቀው የቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ ተስፈኛ ወጣት ተጫዋች ወንድምአገኝ ሀይሉ (ፎቼ) በሀገራችን የመጀመሪያውን የስፖንሰርሺፕ ስምምነት ከኢትዮጵያው የስፖርት ትጥቅ አምራች ድርጅት ከሆነው ጎፈሬ(Gofere Sports Wears) ጋር ለሁለት አመት የሚያቆየውን ውል ፈፅመናል።

ይህ ለሀገራችን ተጫዋቾች ትልቅ ጅማሮ ነው ደግሞም የሚያድግ ነው!

Done Deal!!

The hopeful young player in the completed Ethiopian Betking Premier League Wondimagegn Hailu (Foche) have signed a two-year Sponsorship contract with an Ethiopian Sports Wears Manufacturer, Gofere Sports Wears.

Photos from Ethiopian Football Intermediary Association የኢትዮጵያ ፉትቦል ኢንተርሚዲሪ ማህበር's post 06/07/2021
Photos from Garo Gere Soccer Agency's post 26/06/2021

በዕውቀት እንዲሁም ድንቅ በሆነ አሰልጣኝነቱ የማውቀው ወጣቱን ዳዊት ታደለን እናስተዋውቆት።

ትውልድ እና ዕድገቱ አዳማ ከተማ ውስጥ ነው፡፡ እግር ኳስን በግብ ጠባቂነት በመጫወት የተጫዋችነት ህይወቱን የጀመረው የያኔው ተጫዋች የአሁኑ አሰልጣኝ ዳዊት በሙገር ሲሚንቶ ፡ አዳማ ከተማ ፡ ፊንጫ ስኳር ፡ ኦሮሚያ ፓሊስ እና ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በወጥነት ተጫውቶ አሳልፏል፡፡ ቀጥተኛ ተናጋሪ ነገር ግን አዳማጭነቱ ላቅ የሚለው ይሄ ወጣት አሰልጣኝ ወደ አሰልጣኝነቱ ከገባ በኃላ ቦሌ ባፕቲስት እና ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ የሱ መነሻዎቹ ናቸው፡፡ በብዙሀኑ የአዳማ ህዝብ ወደ አሰልጣኝነቱ ጎራ እንደገባ በትልቅ ደረጃ በተሻለው መገኘት እንደሚችል ይናገሩለት የነበረው አሰልጣኝ ዳዊት ታደለ ወደ አዳማ ከተማ ተስፋ ቡድን አሰልጣኝነት በ2008 ከተቀላቀለ በኃላ በርካታ ወጣት ተጫዋቾችን ከየሰፈሩ መልምሎ ለአዳማ ከተማ ግብአት በማድረግ እጅጉን የገዘፈ ታሪክን የሁለት አመት የቡድኑ ቆይታው ማሳየት ችሏል፡፡

የአሁኖቹ የሰበታ ተጫዋች ቡልቻ ሹራ እና ፉአድ ፈረጃ ፡ ኤፍሬም ቀሬ ፡ ሙሉቀን ታሪኩ የአሁኑ የፋሲል ከነማ ተጫዋች በረከት ደስታ የባህርዳር ከተማው መናፍ አወል በኢትዮጵያ ቡና የተጫወተው የኃላሸት ፍቃዱ እና በርከት ያሉ ተጫዋቾችን በማፍራት ምጡቅነቱን አስመስክሯል፡፡

በመቀጠል በገላን ከተማ እና አቃቂ ቃሊቲ የአሰልጣኝነት ህይወቱን የመራው አሰልጣኙ በባህሪው ቁጡ እና በስራው ጠንካራ እንደሆነ ብዙዎች የሚመስክሩለት ሲሆን ለብዙሀኑ ወጣት አሰልጣኞች ተምሳሌት ይሆናል በማለት በአጭሩ አቅርበንላችኋል፡፡

Photos from Garo Gere Soccer Agency's post 24/06/2021

ሁለቱ የኔ ድንቆች ሀገራቸውን በማገልገል ላይ ናቸው።
ሁሌም ነው ምኮራባቹ
ይገዙ ቦጋለ እና ሰለሞን ወዴሳ !!!
My two best boys are serving their country!!
Am always proud of you!!
The Goal Machine Yigezu Bogale and best defender Solomon Wodesa!!

22/06/2021

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የተጫዋቹን ምዝገባ ጊዜ ቀን አሳወቀ!!

1. የመጀመሪያ ዙር የዝውውር ጊዜ (84 ቀን)
ከሐምሌ 1/2013 ዓ.ም. --- መስከረም 19/2014 ዓ.ም.
JULY 8/2021 --- SEP. 29/2021
2. የሁለተኛ ዙር የዝውውር ጊዜ (30 ቀን)
ከየካቲት 28/2014 ዓ.ም. -- መጋቢት 28/2014 ዓ.ም.
MARCH 7/2022 --- APRIL 6/2022

©Zewdinesh Yirdaw Guadu
Ethiopian Football Federation
IT, FIFA CONNECT and FIFA TMS Manager

20/06/2021

Our outstanding is leading!!!

Africa Soccer Zone - 30 OUTSTANDING AFRICAN PLAYERS in 2021(In no particular order)!

1. 🇪🇹 Abubeker Nassir - Ethopian Coffee
2. 🇿🇦 Peter Shalulile - Sundowns
3. 🇲🇿 Luis Jose Miquissone - Simba SC
4. 🇿🇦 Themba Zwane - Sundowns
5. 🇪🇬 Mohamed Magdy Afsha - Al Ahly
6. 🇿🇲 Clatous Chama - Simba SC
7. 🇨🇲 Lambert Gueme Araina - Coton Sport
8. 🇲🇦 Soufiane Rahimi - Raja
9. 🇹🇳 Mohamed Ali Ben Romdhane - Espérance
10. 🇩🇿 Mouad Haddad - MC Alger
11. 🇨🇩 Ben Malango - Raja
12. 🇩🇿 Ahmed Kendouci - ES Sétif
13. 🇰🇪 Joash Onyango
14. 🇨🇲 Sibiri Sanou - Coton Sport
15. 🇳🇬 Anayo Iwuala - Enyimba
16. 🇬🇭 Ismail Abdul-Ganiyu (Kotoko)
17. 🇺🇬 Eric Kambale - ExpressFC
18. 🇩🇿 Mohamed Amoura - ES Sétif
19. 🇬🇭 Augustine Boakye - WAFA
20. 🇬🇭 Salifu Ibrahim - Hearts of Oak
21. 🇲🇼 Maxwell Gasten Phodo
22. 🇺🇬 Shafik Kagimu - URA FC
23. 🇬🇭 Samuel Abbey Quaye - Accra Great Olympics
24. 🇿🇦 Njabulo Ngcobo - Swallows FC
25. 🇳🇬 Rasheed Ahmed - Katsina United
26. 🇿🇦 Evidence Makgopa - Baroka FC
27. 🇬🇳 Kalil Toure - Wakriya AC
28. 🇿🇦 Nkosingiphile Ngcobo - Kaizer Chiefs
29. 🇧🇮 Asman Ndikumana - Aigle Noire
30. 🇧🇮 Frank Nduwimana - Royal FC

Anyone that should have been here?

Photos from Garo Gere Soccer Agency's post 19/06/2021

The best right back player of our soccer family!!

Photos from Garo Gere Soccer Agency's post 18/06/2021

የ2013 አ/ም የሲዳማ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዉድድር በ40 ቡድኖች በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ የቆየ ሲሆን ዉድድሩ ጥሎ ማለፍ እየተደረገ አሁን ላይ 4 ቡድኖች ብቻ እነሱም ሀሁ አዲስ ከተማ ፣ ምስራቅ ክ/ከተማ ፣ አለታ ጩኮ እና አለታ ወንዶ ከተማ የቀሩ ሲሆን ለዋንጫዉም የሚፎካከሩ ይሆናል።

ዛሬ ከሰአት ላይ ለፍፃሜ ለማለፍ 7 ሰአት እና 9 ሰአት ላይ ጨዋታዎች የሚደረጉ ይሆናል።

እኛም እየተከታተልን የምናቀርብላችሁ ይሆናል።

እንዲህ አይነት ዉድድሮች የሚደገፉ እና የሚበረታታ ነዉ። በዚህ ዉድድር ላይ በርካታ ችሎታዉ ያላቸው ልጆችን እየተመለከትን እንገኛለን።



ካሰቡበት የስኬት ማማ ለመድረስ ምርጫዎ ያድርጉን።

Photos from Garo Gere Soccer Agency's post 10/06/2021

መረጃ
!

በሄንግሎ -ኔዘርላንድ ትላንት ምሽቱን መላውን ኢትዮጵያዊያንን ያስደሰተ ድንቅ የ10ሺ ሜትር ክብረወሰን ላስመዘገበችው ጀግናዋ አትሌት ለተሰንበት ግደይ ሪከርዱን በ48 ሰአታት የተነጠቀችው በትውልድ ኢትዮጵያዊ በዜግነት ሆላንዳዊት አትሌት ሲፋን ሀሰን የእንኳን ደስ ያለሽ መልዕክት አስተላለፋች። አትሌት ሲፋን ሀሰን የዓለም ክብረወሰኗን በመነጠቋ እንኳን ደስተኛ መሆኗን የሚከተለውን ለኔዘርላንድ ኒውስላይፍ ድረ ገፅ ተናገረች

” በእንደዚህ በጣም በተቀራረበ የቀናት ልዩነት ሁለት የዓለም ሪከርድ መሠበር ማለት የ10 ሺ ሜትር ውድድር ምንያህል ተወዳጅ ርቀት መሆኑን የሚያመላከተ ነው። እንደዚህ አስደሳች ውድድሮችን ሰዎች እንዲዩ ከመነገር ውጭ ሌላ የምለው አይኖርም ” ካለች በኃላ አትሌቷ ቀጥላ

” ለዚህ ግሩም ስኬት ለተሰንበት ግደይ በመብቃቷ እንኳን ደስ ያለሽ እላለሁ። ትልቅ ስኬት ነው። ይህንን ስኬት እንደምታደርግ አውቅ ነበር። ስለሆነም በዚህ አጋጣሚ እንኳን ደስ ያለሽ ማለት እፈልጋለሁ ፡፡ በመጣችው ውጤት በጣም ደስተኛ ነኝ። ለተሰንበት ጥሩ አትሌት ናት። እሷ ችሎታ እንዳላት ይህንን እንደምታሳካው አውቃለሁ ። በቀጣይ በቶኪዮ አስደሳች ውድድር እናደርጋን ብዬ አስባለሁ ” በማለት በ48 ሰአታት ልዪነት ክብረወሰኑን የተነጠቀችው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ሲፋን ሀሰን ተናግራለች።

እንደሚታወሰው የ10,000 ሜትር ክብረወሰን በኢትዮጵያዊቷ አትሌት አልማዝ አያና ለ5 ዓመታት ተይዞ እንደነበር ይታወሳል።



ካሰቡበት የስኬት ማማ ለመድረስ ምርጫዎ ያድርጉን።

Photos from Garo Gere Soccer Agency's post 08/06/2021

በ2013ቱ የዉድድር አመት አጀማመሩን በተከታታይ ሽንፈት ከጀመረዉና ወዲያውም አንጋፋውን ኢትዮጵያ ቡናን በማሸነፍ ድንቅ የሆነ አቋም በማሳየት በጥሩ ውጤት ያጠናቀቀው ሐዋሳ ከተማ በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው ከ23 ዓመት በታች የሴካፋ ውድድር 3 ተጫዋቾች ማስመረጥ ችሏል።
እነርሱም
የ2013ቱ ወጣት ኮኮብ ተስፈኛው ወንድማገኝ ሀይሉ (ፎቼ ) - (አማካይ)
መስፍን ታፈሰ - (አጥቂ)
ብሩክ በየነ - (አጥቂ) ናቸው::

ለወደፊቱም ታዳጊ ልጆች ላይ በደንብ ከተሰራ በርካታ ልጆችን ማፍራት ይቻላል።
በዚው አያይዤ የሐዋሳ ከተማ ስፖርት ክለብ አመራሮች ወጣት ልጆችን በማፍራት ላይ እየሰራችሁ ያላችሁትን መልካም ስራ ሳላደንቅ እናም ሳላመሰግን ማለፍ ይከብደኛል:: ለወደፊት በተሻለ ሃሳብ የተሻለ ነገር እንደምትሰሩ ተስፋ አለኝ::



ካሰቡበት የስኬት ማማ ለመድረስ ምርጫዎ ያድርጉን።

Photos from Garo Gere Soccer Agency's post 07/06/2021

በ2013ቱ የዉድድር አመት አጀማመሩ ላይ በደካማ ከጀመረዉና ወደበኋላ ግን ድንቅ የሆነ አቋም በማሳየት ከመዉረድ ከተረፈዉ ሲዳማ ቡና በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው ከ23 ዓመት በታች የሴካፋ ውድድር 4 ተጫዋቾች ተመርጠዋል።

እነሱም :-

ፍቅሩ ዉዴሳ (በረኛ)
አማኑኤል እንዳለ (ተከላካይ)
ብርሀኑ አሻሞ (አማካይ)
ይገዙ ቦጋለ (አጥቂ)

ለወደፊቱም ታዳጊ ልጆች ላይ በደንብ ከተሰራ በርካታ ልጆችን ማፍራት ይቻላል።



ካሰቡበት የስኬት ማማ ለመድረስ ምርጫዎ ያድርጉን።
በቀጣይ ከሐዋሳ የተምረጡትን የምንገልፅ ይሆናል

Photos from Garo Gere Soccer Agency's post 01/06/2021

ከሐዋሳ የተገኘውን የመሀል ሜዳው ተስፈኛ ወንድማገኝ ሀይሉ

በባህርዳር ስታዲየም መካሄደ የጀመረው 12ኛ ሳምንት የቤትክንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ዛሬ ሐዋሳ ከተማን ከፋሲል ከተማ አገናኝቶ ፋሲል ከተማ ሁለት ለአንድ ባሸነፈበት ጨዋታ በአሰልጣኝ ሙልጌታ ምህረት እምነት የመሰለፍ እድል ያገኘው ወጣቱ አማካይ ወንድማገኝ ሀይሉ በሊጉ ታሪክ የመጀመሪያው ጎሉን ነው ከመረብ ያሳረፈው ይህ ወጣት ከአምስት ወራት በፊት ከሀዋሳ ወጣት ቡድን ካደገ በኃላ በፕሪምየር ሊጉ አስደናቂ ብቃትን ባለፉት ጨዋታዎች ላይ እያሳየን ይገኛል:: መልካሙን ሁሉ እመኝልሃለሁ !! በርታ!!

There is Big potential inside of you my player !!!
Good Luck !! And i except big from you!!

ለማስታወስ ያህል ነው!!

The 2021 promising and best youth player of the year!!
Congratulations My Boy!!!

Photos from Garo Gere Soccer Agency's post 25/05/2021

በሀዋሳ የሚገኘው ስታር ኮፊ ካፌ በሀዋሳ ቆይታን ላደረጉ የኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ ክለቦች ሀዋሳ ስለነበራቸው ቆይታ በማመስገን በዛሬው ዕለት የኬክ መቁረስ እና የምስጋና ፕሮግራምን አዘጋጅቷል፡፡

በፕሮግራሙ ላይ አሰልጣኝ አብረሀም መብራቱ ፡ ገብረመድህን ሀይሌ እና ሙሉጌታ ምህረት የኬክ ቆረሳውን አከናውነዋል፡፡
እኔም በቦታው በመግኘት ደስ የሚል ጊዜ አሳልፊያለሁ!!

Photos from Garo Gere Soccer Agency's post 17/05/2021

#ከቀላል ጉዳት_ተመልሶ_የደመቀው_ኮከብ

ሲዳማ ቡና በቤቱ ካፈራቸው ተስፈኛ ልጆች መካከል የፊት መስመሩ ጎል አምራች ይገዙ ቦጋለ ይገኝበታል። ከሲዳማ ክልል ጩኮ ከተማ ሲዳማ ቡናን የተቀላቀለው ይገዙ ቦጋለ በቀድሞ የክለቡ አሰልጣኝ ዘርዓይ ሙሉ እድሉ ተሰጥቶት ዋናውን ቡድን ከተቀላቀለ በኃላ ለክለቡ የቁርጥ ቀን ደራሽ መሆኑን በተሰለፈባቸው ጨዋታዎች ማስመስከር ችሏል። በዘንድሮው የኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪሚየር ሊግ ገና ከጅምሩ ድንቅ ብቃቱን እያሳየ ባለቤት የጉዳት ሰለባ ሆኖ የቁጭት እና የእልህ እንባ እየረጨ ከወጣበት ሜዳ በቅርቡ አገግሞ ተመልሷ።

የአሸናፊነት መንፈስ ተጎናፅፎ ሜዳ የከተመው ይገዙ ቦጋለ በ22ኛው እና በ23ኛው የቤትኪንግ ውድድር ላይ ያሳያቸውን እንቅስቃሴ በምናይበት ጊዜ ልጁ ኳስን በደንብ አውቋት እንደሚጫወታት እና ነገም ትልቅ ቦታ መድረስ የሚችል ተጫዋች መሆኑ ለመገመት ሌላ እውቀት አያስፈልግም። ከወራጅ ቀጠና እራሱን ለማራቅ ከፍተኛ ትንቅንቅ ውስጥ የሚገኘውን ክለቡን ከቅዱስ ጊዮርጊስ እና ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረጉት ጨዋታ ላይ ወሳኝ ግብ በማስቆጠር ብቃቱን ማስመስከር ችሏል። ከጉዳት መልስም የክለቡ ድምቀት ሆኗል። በመልካም ባህሪ እና በድንቅ ችሎታህ ቀጥልበት እንላለን።

Photos from Garo Gere Soccer Agency's post 13/05/2021

!
እንኳን ለ1442ኛው የኢድ አል ፊጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!
عيد مبارك تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال

Want your business to be the top-listed Gym/sports Facility in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Telephone

Website

Address


Bole
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 05:00 - 21:00
Tuesday 05:00 - 21:00
Wednesday 05:00 - 21:00
Thursday 05:00 - 21:00
Friday 05:00 - 21:00
Saturday 05:00 - 21:00
Sunday 05:00 - 21:00
Other Sport & Recreation in Addis Ababa (show all)
Addis Ababa Hash House Harriers a.k.a AAHHH a.k.a A2H3 Addis Ababa Hash House Harriers a.k.a AAHHH a.k.a A2H3
Hilton Hotel
Addis Ababa, ADWAAVENUE

The Addis Hash, the highest Hash in Africa (2500 m.), runs every Saturday afternoon, rain or shine, outside the city of Addis Ababa. We meet at 2:00pm at the Hilton Hotel parking l...

Spoortii90 Spoortii90
Addis Ababa, SPORTS

Tsis sport page is only fo the purpose of sport information only

Abex fitness Abex fitness
Addis Ababa

Tik tok account:- https://vm.tiktok.com/ZMLPjLSj6/

Great Hikers Ethiopia Great Hikers Ethiopia
Behind Bras Maternity Hospital TOTAL Gas Station Building
Addis Ababa

Hiking, camping, exploring, adventure, challenge, sport, recreation, family, friends, and fun,Join us

Kidan satellite dish technical Kidan satellite dish technical
Addis Abeba
Addis Ababa

ቻናላችንን ጆይን በማድረግ ትኩስ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ያ�

Xilo jano Xilo jano
Addis Ababa

Ethio Ethio
Addis Ababa

Information About Wushu Martial Art In Ethiopia.

Today sport Amharic Today sport Amharic
Addis Ababa

Ebrahim Ebrahim
A A
Addis Ababa

a

Bijiga Negera Gibe Bijiga Negera Gibe
Addis Ababa

Nuyi garuu kiristoos isa fannifame ni lallabna. 1Qor 1:23

Babi Fitness Babi Fitness
Bole Medhanialem
Addis Ababa, 1000

Stay fit and healthy🔱

Akim Stephen Akim Stephen
Addis Ababa

Footballer