Addis Ketema Special Woreda

Addis Ketema Prosperity Party is a party of its generation that is committed to leading the Sub-Cit

Our office is found a little further from Medinalem Square, near Ras Hailu Park

Photos from Addis Ketema Special Woreda's post 12/06/2023

"ሚዲያ ለበጎ ዓላማ፣ ለሠላምና ለአገር ግንባታ’’
**************************

በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ማስተባበሪያ ዘርፍ ለልዩ ወረዳ መሠረታዊ ፓርቲ አመራችና ህዋስ አመራሮች ‘’ጠንካራ፣ የተቀናጀና ወቅታዊነቱ የተጠበቀ ሚዲያ ለጠንካራ ሀገር-ግንባታ’’ በሚል ርዕስ ዙሪያ የተዘጋጀ ስልጠና ሰጠ፡፡

ስልጠናዉ ያተኮረዉ የሚዲያ ጠቀሜታ፣ የመንግስት የለዉጥ ምዕራፍ ስራዎችን ማስተዋወቅና ወቅታዊ መረጃ ተደራሽነትን ማስፋት፣ በጎ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆኑ በጎ አክቲቪስቶችን ማብዛት፣ የህዝብ ግንኙነት ሚናን ማሳደግ፣ ለሀገር ገንቢ የሆኑ መልዕቶችን ለይቶ መጠቀም ዙሪያ……ወዘተ. ናቸዉ፡፡

ስልጠናዉን የሰጡት የአዲሰ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ የሚዲያና ኮሚኒኬሽን ኃላፊ አቶ ፤ሌሊሳ ሲሆኑ በመድረኩም ላይ የዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ፑል አስተባባሪ ወ/ሮ ተዘራሽ እና ሌሎች ደጋፊ አመራች ተገኝተዋል፡፡
አቶ ሌሊሳ ዱሬሳ ምክራቸውን ሲሰጡ፣ በድሮ/ባህላዊ ሚዲያ( Old/Traditional Medea) ጥቂቶች ይናገራሉ፣ ብዙዎችም ያዳምጣሉ፣ በዘመናዊው ሶሻል ሚዲያ(New Social Media) ብዙዎች ይናገራሉ፣ ብዙዎችም ያዳምጣሉ። በመሆኑም ከዘመኑ ጋር በሚሄድ እውቀት የፓርቲያችንን ገፅታ ለማሳደግ አዲስ ሚዲያን በአግባቡ መጠቀም እንድንችል ጠንከር ያለ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በማህበራዊ ሚዲያ የሀገራችንን ሰላምና ልማት በአዎንታዊ መልኩ በማጉላት የለውጥ ሐዋርያ መሆናችንን እናረጋግጣለን!

17/10/2022

የኢትዮጵያን ብርሃን ማንም ሊያቆመው አይችልም!
የኢትዮጵያ ብርሃን የኢትዮጵያ ልጆች ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ብርሃን መልካም ሃሳብን የሰነቁ የኢትዮጵያ ልጆች ናቸው፡፡
የኢትዮጵያ ብርሃን ክፉዋን አስወግደው በበጎ በመልካም የብልፅግና ጎዳና ሊያረማምዷት የተነሱ የቁርጥ ቀን ልጆች ናቸው፡፡
የኢትዮጵያ ብርሃን ልጆቿን እናሰባስባለን ብለው የተነሱ ልባሞች ናቸው፡፡
የኢትዮጵያ ብርሃን ጨለማውን ገለጠው ፀዳሏ እንዲታይ ግርዶሹን የገፈፉ ናቸው፡፡
የኢትዮጵያ ብርሃን አሁን ተገልጧል፡፡ ጨለማ አያሸንፈውም፡፡
የኢትዮጵያ ብርሃን ገና ሳይገለጥ አሸናፊ ነው፡፡

21/12/2020

Ethiopian Federal Police Commission - ህዝብ ግንኙነት

የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ 68 ለሚሆኑ በሰንደፋ በኬ ከተማ በአነስተኛ የገቢ ደረጃ የሚኖሩ ተማሪዎችን በዘላቂነት በዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ ታቅፈው ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ የትምህርት ቁሳቁስ እና የምገባ ፕሮግራም አስጀመረ፡፡
**********************************************************
አዲስ አበባ፣ታህሳስ፣ 08-2013 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ታህሳስ 08/2013 ዓ.ም በፊንፊኔ ዙሪያ ኦሮሚያ ልዩ ዞን ሰንደፋ በኬ ከተማ በአነስተኛ የገቢ ደረጃ ለሚኖሩ 68 ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል፡፡
ድጋፍ የተደረገላቸው በገቢ ችግር ምክንያት ትምህርታቸውን በአግባቡ ለመከታተል የአቅም ውስንነት ላለባቸው ከሰንዳፋ በኬ ከተማ አስተዳደር ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ ተማሪዎችና ልጆቻቸውን በአግባቡ ለማስተማር የማይችሉ የተማሪ ወላጆች መሆናቸው ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የተገኘ መረጃ ያመለክታል፡፡
ዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ ከትምህርት ቁሳቁሱ ድጋፍ በተጨማሪ ለተማሪዎቹ የምገባ ፕሮገራሙን ታህሳስ 08/2013 ዓ.ም በእራት ምገባ መርሐ ግብር በይፋ አስጀምሯል፡፡ በዚሁም መሰረት 68 ተማሪዎችን በቋሚነት የምግብና ፕሮግራሙ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ እና በቀጣይም ለተማሪዎች ተጨማሪ ለትምህርታቸው አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶች እንደሚሟላላቸው የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የማህበረሰብ አገልግሎት ዲፓርትመንት ተወካይ ኃላፊ የሆኑት ኢንስፔክተር አስናቀ ወልዴ ባቀረቡት ሪፖርት ገልፀዋል፡፡
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ፕሬዝዳንትና የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር ጀኔራል መስፍን አበበ ̋ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጃችን እንደ ማንኛውም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከትምህርት፣ ስልጠናና ምርምር ባሻገር ሙያችንን መሰረት ያደረገ የማህበረሰብ አገልገሎት ስራ በመስራት የአካባቢውን ማህበረሰብ ችግር መፍታት እና ለሀገር መስራት ይጠበቅብናል ̋ ብለዋል፡፡
ወ/ሮ መሰረት ንጋቱ የሰንዳፋ በኬ ከተማ አስተዳደር ሴቶችና ህፃናት ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ኃላፊ ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በተለያዩ ጊዚያት ለከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የሆነ ድጋፍ ማድረጉን በማስታወስ በእለቱ ለተማሪዎች ለተደረገው ድጋፍ እና የምግብና መርሐ ግብር ምስጋና አቅርበዋል ፡፡
በሰንዳፋ በኬ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ፅህፈት ቤት የእቅድና በጀት ቡድን መሪ የሆኑት አቶ አማን ደደፎ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ ይህን ድጋፍ እና የምገባ ፕሮግራም በመጀመሩ ለዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በሌላ በኩል ድጋፉ የተደረገላቸው ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች የተሰማቸውን ደስታ በመግለፅ ለተሻለ ውጤት እንደሚሰሩ እና ለፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ ያላቸውን ክብር ገልፀዋል፡፡

19/12/2020

የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ከታህሳስ 8 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የቆየዉን መደበኛ ስብሰባ አጠናቋል፡፡

ኮሚቴዉ በሰላም፣ በልማት፣ በዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታና መጪዉን አገራዊ ምርጫ በተመለከቱ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት ተወያይቶ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል፡፡

በዋናነት ባለፉት ሁለት አመታት ተኩል በአገራችን የታየዉ ለዉጥ በርካታ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፈተናዎችን ተጋፍጦ የአገራችንን ብልጽግና እዉን ለማደረግ ሰፊ እድል የፈጠረና አገራችንን ከብተና አደጋ ያዳነ መሆኑ በዉይይቱ ከስምምነት ተደርሷል፡፡

በተለይም ብልጽግና ዉሁድ ህብረ ብሄራዊ አገራዊ ፓርቲ ሆኖ መደራጀቱ አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ለመገንባት ከፍተኛ እድል ከመፍጠሩም በላይ ከአገሪቱ ፖለቲካዊ ተሳትፎ ተገለዉ የዳር ተመልካች የነበሩ በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለማቀፍና ለማሳተፍ የቻለ የመጪዉ ትዉልድ ፓርቲ መሆኑ ተረጋግጧል፡፡

በአገራዊ ለዉጡ የተገኙ ድሎችን ጠብቆ በማስቀጠል ወደ ሁለንተናዊ ብልጽግና ማሳደግ እንደሚያስፈልግ የተገለጸ ሲሆን ለዚህም የፓርቲዉን መርሆዎች፣ እሴቶችና አሰራሮችን በጥብቅ ዲሲፕሊን ተግባራዊ ማድረግና ጠንካራ ተቋማዊ ባህል መገንባት አስፈላጊ መሆኑ ከስምምነት ተደርሷል፡፡

ኮሚቴዉ በሁለቱ ቀናት መደበኛ ስብሰባዉ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ የሚከተሉትን አቅጣጫዎች አስቀምጧል፡፡

1. አገራችንን ለመበታተን በከፍተኛ ሁኔታ ሲዘጋጅ ቆይቶ ፍጹም አረመኔያዊ በሆነ መልኩ በአገር መከላከያ ሰራዊታችን ላይ ጥቃት መሰንዘሩ ይታወቃል፡፡ ይህ ስግብግብ ጁንታ በአጭር ጊዜ እንዲፈርስና አገራችን ከዚህ ከሃዲ ሃይል ነጻ እንድትወጣ ጀግናዉ መከላከያ ሰራዊታችን፣ የአማራና አፋር ክልሎች ልዩ ሃይልና ሚሊሻ እንዲሁም በተለያየ ደረጃ ድጋፍ ላደረጉ መላዉ የሀገራችን ህዝቦች ታላቅ ምስጋና እናቀርባለን፡፡ ጀግንነት ልምዳችን ስለሆነ በዚህ ድል ሳንኩራራ ይህንን አገራዊ የአንድነት ስሜትና ቁርጠኝነት በሌሎች የልማት ዘርፎችም በመድገም የአገራችንን ብልጽግና ለማረጋገጥ ርብርብ እንዲደረግ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡

2. የወንጀለኛዉን ከሃዲ ጁንታ አባላት ከተደበቁበት አድኖ ለፍርድ ለማቅረብ ከሚደረገዉ ርብርብ ጎን ለጎን በህግ ማስከበር እርምጃው ሂደት ውስጥ የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቀዬያቸዉ ተመልሰዉ እንዲቋቋሙና እብሪተኛው ጁንታ ያፈራረሳቸዉ የህዝብ መሰረተ ልማቶች በፍጥነት ተጠግነዉ ለአገልግሎት እንዲውሉ ለማድረግ የተጀመረዉ ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡ በትግራይ ክልል የህዝብ አገልግሎቶችን ለማስጀመር፣ የእለት ደራሽ ሰብዓዊ አገልግሎቶችን በፍጥነት ለማድረስና ህብረተሰቡ ወደ መደበኛ የእለት ተእለት ህይወቱ እንዲመለስ በሚደረገዉ ርብርብ ዉስጥ የፓርቲዉ አመራሮች፣ አባላት፣ ደጋፊዎችና መላዉ የአገራችን ህዝቦች የቻሉትን አስተዋጽዖ ሁሉ እንዲያደርጉ ኮሚቴዉ ጥሪ ያቀርባል፡፡

3. በኢትዮጵያ የሀገረ መንግስትና ብሄረ መንግስት ግንባታ ሂደት የተለያዩ የፖለቲካ ሃይል አሰላለፎች የሚታዩበት ነዉ፡፡ በአገራችን የሚታየዉን ዉስብስብ ብዝሃነት የሚያስተናግድ አገራዊ አንድነት ከመገንባት አንጻር በወንድማማችነት እሴት ላይ የተመሰረተ ህብረብሄራዊ አንድነትን የሚያረጋግጥ የፌዴራል ስርዓት ግንባታ እዉን እንዲሆን የፓርቲያችን አመራሮችና አባላት በቁርጠኝነት እንዲታገሉ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡

4. በተለያዩ አካባቢዎች ህዝቦች የሚያነሷቸዉ የማንነት ጥያቄዎች ተገቢነት ያላቸዉ ፍትሃዊ የህዝብ ጥያቄዎች መሆናቸዉን ኮሚቴዉ ያምናል፡፡ እነዚህ ጥያቄዎች ነባራዊ ሁኔታዉን መሰረት በማድረግ የህዝቦችን ወንድማማችነትና አብሮነት እንዲሁም የህዝቡን ነጻ ፍላጎት ከግምት ባስገባ መልኩ ህጋዊ አሰራርን ተከትሎ ምላሸ እንዲሰጣቸዉ ኮሚቴዉ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡

5. በተለያዩ የአገራችን አካባቢዎች በንጹሃን ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ማንነትን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች በአፋጣኝ እንዲቆሙ ተገቢዉ እርምጃ ሁሉ እንዲወሰድ ኮሚቴዉ ከስምምነት ደርሷል፡፡ እነዚህን እኩይ ተግባራት የሚፈጽሙ የጥፋት ሀይሎች በቁጥጥር ሥር ለማዋልና እርምጃ ለመዉሰድ በሚደረገዉ ርብርብ በየደረጃዉ የሚገኙ የብልጽግና አመራሮች በከፍተኛ ጽናትና ቁርጠኝነት እንዲሰሩ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡

6. የአገራችንን ፖለቲካዊ፣ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮች ለመፍታት በሚደረጉ ጥረቶች በየትኛዉም ቦታ የሚገኙ የብልጽግና አመራሮችና አባላት ከሚለያዩ ጥቃቅን ጉዳዮች ወጥተዉ ከፍ ያለ አገራዊ እይታ በመያዝ ኢትዮጵያንና የሁሉንም ዜጎቿን ሁለንተናዊ ብልጽግና እዉን በሚያደርግ መልኩ እንዲደጋገፉ፣እንዲረዳዱ፣በአብሮነትና በትብብር መንፈስ መስራት እንደሚገባቸዉ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡

7. በ2013 ዓ.ም የሚካሄደዉ ምርጫ አገራችን ወደ እዉነተኛ የዲሞክራሲ ስርዓት ለምታደርገዉ ሽግግር ያለዉ ትርጉም እጅግ ከፍተኛ መሆኑ ይታመናል፡፡ የሚካሄደዉ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ነጻና በሂደቱም ሆነ በዉጤቱ በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነት ያለዉ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የብልጽግና አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች በከፍተኛ ቁርጠኝነት እንዲሰሩ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡

8. ብልጽግና ፓርቲ በመጪዉ ምርጫ ጠንካራ ተወዳዳሪ ሆኖ በዉጤታማነት እንዲያጠናቅቅ በፓርቲዉ ማኒፌስቶ ላይ በጥልቀት ተወያይቶ አጽድቆታል፡፡ መላዉ የፓርቲዉ አመራሮችና አባላት የጸደቀዉን ማኒፌስቶ መሰረት በማድረግ አስፈላጊዉን ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡

9. በአገራችን በህጋዊ መንገድ ተመዝግበዉ በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ወደ እዉነተኛ የዲሞክራሲ ስርዓት ለመሸጋገር የተወሰዱ የአገራዊ ለዉጥ እርምጃዎችን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም መጪዉ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ነጻና በሂደቱም ሆነ በዉጤቱ በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነት ያለዉ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸዉን አስተዋጽዖ እንዲያደርጉ ጥሪ እናቀርባለን፡፡

10. መላዉ የአገሪቱ ህዝቦች ባለፉት ሁለት ተኩል አመታት በኢትዮጵያ የታዩ ለዉጦችና የተገኙ ድሎች ተጠናክረዉ እንዲቀጥሉ፣መጪዉ አገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ነጻና ተቀባይነት ያለዉ ሆኖ እንዲጠናቀቅና የዜጎች ፖለቲካዊ፣ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ብልጽግና የተረጋገጠባት ጠንካራ አገር ለመገንባት በሚደረገዉ ርብርብ ዉስጥ የሚጠበቅባቸዉን አስተዋጽዖ ሁሉ እንዲያደርጉ ጥሪ እናቀርባለን፡፡

©ብልጽግና ፓርቲ

18/12/2020
18/12/2020

Addis Ketema Communication

ቀን፡- 08-04-2013
ህበረተሰቡን ማገልገል ከክብርም በላይ ድርብ ክብር ስለሆነ ህዝቡን በቅንነት ማገልገል እንደሚገባ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ሰራተኞች ባደረጉት ውይይት ተገለፀ፡፡

የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ይታያል ደጀኔን ጨምሮ ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ውይይት የሩብ አመት የሱፐርቪዥን ሪፖርትና የሰው ሃብት ኦዲት ግኝት በሰነድ መልክ ቀርቦ ምክክር ተደርጎበታል፡፡

በመድረኩ ተገኝተው ማነቃቂያ ንግግር ያደረጉት መጋቤ ሃዲስ እሸቱ አለማየሁ በትህትና የማገልገልን ጥቅም ለሰራተኞች አዝናኝና ቁም ነገር አዘል በሆነ መንገድ አቅርበዋል፡፡

የተጀመረውን የለውጥ ጉዞ ለማስቀጠል በብቃት የተደራጀ ውጤታማ ሲቪል ሰርቫንት መገንባት እንደሚያስፈልግ ተገልጧል፡፡
ሪፖርተር አብዮት ይናገር

18/12/2020

አዲስ ቴቪ Addis TV

የአዲስ ከተማ ክፍል ከተማ የስራ ዕድል መፍጠር በሚስችሉና ህዝብ ቅሬታ በሚነሳባቸው የአገልግሎት መስጫ ዘርፎች ላይ ለውጥ ለማምጣት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገለጸ፡፡
የክፍለ ከተማው ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ የህዝብ ቅሬታ በሚነሳባቸው ቁልፍ አግልግሎት መስጫ ተቋማትና ሌሎች የመንግስት የስራ ተቋማት የስራ አፈጻፀም ዙሪያ ሪፖርት አቅርቧል፡፡
ዜጎችን ለማገለግል ያለው የሰራተኞች ተነሳሽነት በመልካም ደረጃ ላይ የሚገኝ ቢሆንም በተለይም ከፍተኛ ቁጥር በሚስተናግዱ ተቋማት ላይ አሁንም ሊሻሻል የሚገባው የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደት መኖሩን ይጠቁማል ሪፖርቱ፡፡
በህዝብ ቅሬታ ረገድ የተለዩ የክፍለ ከተማው አገልግሎት መስጫ ተቋማት ቅናሽ ቢታይባቸውም አሁንም ተደጋጋሚ የመልካም አስተዳዳር ችግር የሚታባቸው ተቋማት አንዳሉም ተመላክቷል፡፡
የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ይታያል ደጀኔ የሶስት ዓመት ሪፖርት ግኝቱ ክፍተቱ ያለባቸው ተቋማትን የለየ በሆኑ ክፍለ ከተማው የተለየ ትኩረት ይሰጥባቸዋል ብለዋል፡፡

የቴሌግራም ትዊተር እና ዩቱብ ቻናላችንን ይቀላቀሉ፤ ፈጣን መረጃ ያግኙ።
https://t.me/addisnewshub
https://twitter.com/AddisAmn
https://www.youtube.com/channel/UC7DAgQRB-eefBmMZ19LyTkA

አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ታህሳስ 8/2013 ዓ.ም

16/12/2020

የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ የሱፐርቪዥን፣ ጥናትና ምርምር ዘርፍ ኮሚቴ በዛሬው ዕለት በ07/04/2013 ዓ.ም ወረዳችንን የመጀመሪያው የ 5 ወር ሱፐርቪዥን አደረገ

የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የሱፐርቪዥን ጥናትና ምርምር ዘርፍ የለውጥ ጉዞውን ውጤታማ ለማድረግ መንግስትና ፓርቲ በየደረጃው ጠንካራ የክትትልና ድጋፍ ስርዓት በመጀመር የተገኘውን ውጤት መሠረት በማድረግ የማስተካከያ እርምጃዎች እየተወሰደ ነው ፡፡

የፓርቲ አባላትን ለማጠናከር በፓርቲያችን ሥራ ውስጥ በአንፃራዊነት የብልጽግና እና የመደመር ሀሳቦቻችንእስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ ያሉ መሪዎቻችን በተገኙ ጥንካሬዎችና ድክመቶች ላይ ተመስርተው የተሻሉ አሰራሮችን ለመቅረፅ እንዲችሉ እንዲሁም ጉድለቶችን ለማረም እና ጥንካሬን ለመገንባት ይቻል ዘንድ የድጋፍ ሱፐርቪዥን ተደርጓል፡፡ የፓርቲያችን አመራርና አበል የፖለቲካ ጤንነት መጠናከር እንደሚገባም ተገለፀ፡፡ የፓርቲው አባላት የተቀሩት ህዝቦች የብልፅግና እና የወገንተኝነት ሁኔታ ያሉበትን ሁኔታ በሚረዱበት ሁኔታ ሊሰሩ እንደሚገባ ተገልጻል ፡፡

በመጨረሻም የፀረ-ሰላም ኃይሎች አጀንዳ ፣ የሚጠቀሙበት ስልት; የሚሰሩትን እንቅስቃሴና ያሉበትን ሁኔታ በማወቅ ከአገር ወዳዱ ማኅበረሰብ ጋር በመሆን እጅ ለእጅ ተያይዘው የክፋት ተግባራቸውን እንዲያፈርሱ ለሁሉም መልእክት አስተላልፈዋል፡፡

15/12/2020

ቀን፡- 06-04-2013
የታህሳስ ወርን ለስራ እድል ፈጠራ በሚል የተጀመረው የንቅናቄ ስራ ተስፋ ሰጭ ጅምር ላይ መሆኑ ተገለፀ፡፡

የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የታህሳስ ወርን የስራ እድል ፈጠራ ወር በማለት ሰይሞ በንቅናቄ 10ሺ 690 ስራ አጥ ነዋሪዎችን ወደስራ ለማስገባት አቅዶ እየሰራ ያለበትን ሂደት ዛሬ የወረዳና የክፍለ ከተማ አመራሮች በተገኙበት እየተገመገመ ይገኛል፡፡

የተቀናጀ የአረንጓዴ ተፋሰስን በማልማት ከ1ሺህ በላይ ዜጎች ስራ እንዲፈጠርላቸው ፀጋ መለየቱን የገለፁት የክፍለ ከተማው ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ጥሩዕድል አስቻለ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት፣ ተፋሰስና የአረንጓዴ ልማት ጽ/ቤት፣ አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት እና አርሶ አደርና ከተማ ግብርና ጽ/ቤት ተቀናጅተው የሚፈፅሙት ተግባር መሆኑን አሳውቀዋል፡፡
በስራ እድል ፈጠራው ዙሪያ ባለፉት ስድስት ቀናት ተስፋ ሰጭ ጅምሮች መታየታቸውን የገለፁት የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ይታያል ደጀኔ ለእቅዱ መሳካት ሁሉም አመራርና ባለድርሻ አካል በቁርጠኝነት መረባረብ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አሰፋ ቶላ በበኩላቸው ያሉትን ፀጋዎች በሙሉ በመለየት አንገብጋቢውን የስራ አጥነት ጥያቄ ለመቀነስ ሁሉን አቀፍ ርብርብ ከተደረገ የማይሳካ ነገር አይኖርምና በትኩረት መስራት አለብን ሲሉ ገልፀዋል፡፡
ሪፖርተር አብዮት ይናገር

15/12/2020

በ1935 ዓ.ም የተመሠረተው እና አንጋፋ የሚድያ ተቋም የሆነው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ያስገነባውን አዲስ የሚዲያ ኮምፕሌክስ ጎብኘቻለው።

አዲሱ ኮምፕሌክስ ውስጡ የያዛቸው ዘመናዊ የሬዲዮ፣ የቴሌቪዥን ስቱዲዮዎች እና የተለያዩ የአገልግሎት መስጫ ክፍሎች አሰራር ደረጃውን የጠበቀና ተወዳዳሪ ሊያደርገው የሚችል በመሆኑ ለአገራችን የሚዲያ እድገት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው። ለሌሎች የሚዲያ ተቋማትም በአርዓያነት ሊወሰድ ይችላል።

ኢ.ዜ.አ ከከተማ አስተዳደሩ የወሰደውን መሬት አጥሮ ከመቀመጥ ይልቅ በማልማት እንደዚህ አይነት ደረጃውን የጠበቀ ስራ በመስራቱ ሊመሰገን ይገባዋል።

15/12/2020

"...ወደ ብልፅግና የሚወስደዉ መንገድ አማራጭ የሌለዉ የለዉጥ መንገድ ነዉ!..."
========

ሀገር በብዙ ዉጣ ዉረድ ፈተናዎችን አልፋ ለአዲሱ ትዉልድ መሆን የምትችለዉ ይህ ትዉልድ የአሸናፊነትና በጋራ የመበልፀግ ራዕይ ሲኖረዉ ነዉ። እኛ ኢትዮጵያዉያን ችግሮችን በጋራ ተጋፍጠን ህብረ-ቢሔራዊነታችንን አስጠብቀን በኩራት የቆምን ህዝቦች ነን። ፈተናዎቻችን ከሩቅ የሚመጡ ሳይሆኑ በራሳችን ባንዳዎችና ጥቅምን በብሄርተኝነት በሚያቃጡ ተኩላዎች የሚጠነሰሱ ናቸዉ።

ከዚህ ቀደም የነበረዉን ወጣቱን ለራስ ጥቅም የማዋልና በወጣቱ ደምና በእናቶቻችን እምባ የመነገድ ዘይቤ ችግሮችን ሲጋፈጥ የቆየዉ ይህ ትዉልድ ባንዳዎችንና የእናት ጡት ነካሾችን ነቆሎ በመጣል አብዮታዊ ፖለቲካዉን በማክሰም ወደ ምጣኔ ሀብት አብዮት/Economic Revolution በመቀላቀል ለዉጥ እያመጣ ለሃገር ዕድገትም የጀርባ አጥንት እየሆነ ይገኛል።
ጁንታዉና ተላላኪዉ ቡድን ላለፉት አመታት ወጣቱን እየቻሉ እንዳይችሉ፤ ሰርተዉ እንዳይለወጡ፤ ከሀገርና ከራሳቸዉ ለዉጥ ይልቅ ለጥቂቶች ፍላጎትና እድገት ግብረ-አበር ሆነዉ እንዲያልፉ ሲያረግ ቆይቷል። በወጣቱ የብልፅግና ጉዞ ከታየዉ ለዉጥ መማር ያልቻለዉ ይህ ቡድን በፈፀመው ክህደት የማያዳግም ቅጣት በመቀጣት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ጉድጓድ ገብቷል። እራሱን ከወቅቱና ሀገርና ህዝቡ ከሚፈልገዉ ሁኔታ ጋር መለወጥ አለመቻል ዋጋ ያስከፍላል።

እኛ ኢትዮጵያዉያን የጁንታዉን ሃገር የማጥፋት ድግስ ለደጋሹና ተላላኪዎች አድርገን ዛሬም ከከሃዲዎቹ ቀብር ማግስት ሀገራችን ለስኬት የሚተጋና ለሀገር ክብር ዘብ የቆመን ትዉልድ ይዛ በብልፅግና ጎዳና በከፍተኛ ፍጥነት ቀጥላለች። በብልፅግና ጎዳና የሚምዘገዘገዉን ባቡር ሊያስቆመዉ የሚቻለዉ ሃይል የለም። የፈተና መንገዶችን በለዉጥና ስኬት ጎዳና እየቀየርን ከህዝቦች ጋር ወደ ልዕልና የምናደርገዉን ጉዞ እንቀጥላለን!"

(አቶ አሰፋ ቶላ የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊ)

For more and reliable update information, Follow us on:-
👉page:- https://www.facebook.com/pg/addisketema.pp/about/
👉Instagram Link:- https://Instagram/
👉Twitter Link:- https://Twitter.com/Addis Party/
👉Telegram፡-https://t.me/c/1307614050/3
Prosperity is in our community!

14/12/2020

ታህሳስ 5 ቀን 2013

የልዩ ዘመቻዎች ኃይል ማሰልጠኛ ማዕከል ትናንት ያስመረቃቸው ኮማንዶዎች ፣ በግዳጅ አፈፃፀም ወቅት ፣ ሰው ሰራሽ መሰናክሎችን የማዘጋጀት ፣ ፈንጂዎችን የማጥመድና የማስወገድ ጥበብ እንዲኖራቸው ተደርጏል ።ታህሳስ 5 ቀን 2013

የልዩ ዘመቻዎች ኃይል ማሰልጠኛ ማዕከል ትናንት ያስመረቃቸው ኮማንዶዎች ፣ በግዳጅ አፈፃፀም ወቅት ፣ ሰው ሰራሽ መሰናክሎችን የማዘጋጀት ፣ ፈንጂዎችን የማጥመድና የማስወገድ ጥበብ እንዲኖራቸው ተደርጏል ።ታህሳስ 5 ቀን 2013

የልዩ ዘመቻዎች ኃይል ማሰልጠኛ ማዕከል ትናንት ያስመረቃቸው ኮማንዶዎች ፣ በግዳጅ አፈፃፀም ወቅት ፣ ሰው ሰራሽ መሰናክሎችን የማዘጋጀት ፣ ፈንጂዎችን የማጥመድና የማስወገድ ጥበብ እንዲኖራቸው ተደርጏል ።

14/12/2020

በትግራይ ክልል የቴሌኮም አገልግሎት ሲቋረጥ የሚያሳየው የሲሲቲቪ ካሜራ ምስል ተለቀቀ
****************
በትግራይ ክልል የቴሌኮም አገልግሎት ሲቋረጥ የሚያሳየውን የሲሲቲቪ ካሜራ ምስል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ ይፋ አድርጎታል።
በትግራይ ክልል ከጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ የኮሙዩኒኬሽን መቋረጥ ተከስቶ እንደነበር ይታወሳል።
ብቸኛው የቴሌኮም አቅራቢ የሆነው ኢትዮ-ቴሌኮም ማንነታቸው ያልታወቀ ሰዎች ሆነ ብለው ኔትወርክ እንዲቋረጥ ሲያደርጉ የሚያሳይ የሲሲቲቪ (CCTV) ካሜራ ቅጂ ከሰሜን ሪጅን ጽ/ቤት ያገኘ መሆኑንም ከዚህ ቀደም አስታውቆ ነበር።
ጋቢ የለበሱ የኢትዮ-ቴሌኮም የሰሜን ሪጅን የጥበቃ ሠራተኞች በእነዚህ ባልታወቁ ሰዎች ተገፍትረው ከግቢ ሲወጡ በካሜራው ላይ ይታያል።
የጥበቃ ሠራተኞቹ ከግቢው ወጥተው ሌሎች ሰዎች ግቢውን ሲቆጣጠሩ እና ሌሎች ሰዎች ደግሞ ወደ ግቢው ሲገቡ ይታያል።
እነዚህ ሰዎች በቀጥታ የሳይቱ ዋና ሲስተም ወዳለበት ክፍል በማምራት ያቋርጡታል። ዋና ጽ/ቤት ያሉ የኢትዮ-ቴሌኮም ሠራተኞች እየሆነ ስላለው ነገር የሚያውቁት ነገር አልነበረም።
ሠራተኞቹ ያሰቡት የባትሪ ችግር የተፈጠረ ወይም ጄኔሬተሩ በትክክል መሥራት ያቆመ መስሏቸው ነበር።
ከሲሲቲቪ ካሜራ የተገኘው ምስል እንደሚያሳየው ግን ሲስተሙ የተቋረጠው በቀጥታ ወደ ቦታው በማምራት ሆነ ብለው በዘጉት ሰዎች ነው።
እንደ አጋጣሚ ሆኖ ሁሉም ሲስተም ሲዘጋ የሲሲቲቪ ያለበት ክፍል ኃይል አልተቋረጠም ነበር። በሲሲቲቪ ካሜራ የተያዘው ምስልም ሳይሰረዝ ተገኝቷል።
ካሜራው እስከ ጥቅምት 25 ከቀኑ 10 ሰዓት ከ20 ድረስ ሲቀርፅ የነበረ ሲሆን የመጨረሻ ምስሉም አንድ ግለሰብ ወደ ክፍሉ ገብቶ ካሜራውን እስኪያጠፋው ድረስ የነበረውን ሂደት ያሳያል።
EBC

14/12/2020

የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ ዛሬ ያስተላለፉት መልዕክት
👉ይህ ጦርነት እኛ የፈለግነውና የጀመርነው ጦርነት አይደለም እናንተም እንደምታውቁት መንግስትም ከፍተኛ የማባበልና ችግሮቹን በሰላማዊ መንገድ የመፍታት ስራን ለሁለት አመት ሲሰራ ነበር፤
👉 አንዳንድ የመከላከያን እንቅስቃሴ የሚያደናቅፉ ስራዎች ጁንታው እየሰራ መከላከያም ከፍተኛ ትዕግስት አድርጎ እንቅስቃሴው ተገቶ እያለ በመነጋገርና በመደራደር ስራውን ለመስራት ነው ሲሞክር የነበረው፤
👉 ይህ ሁሉ ሲደረግ የነበረው ወደ ጦርነት ወደ ውጊያ ላለመግባት ነው፤ ይህ ሀገር ተደጋጋሚ ጦርነት የተካሄደበት ሀገር ስልሆነ ከአሁን በኋላ ጦርነት ለዚህ ሀገር አይመጥንም ይህ ሀገር ወደ ኋላ ይመልሳል የእስከዛሬው ታሪካችን ይበቃል በይቅርታ መንፈስ ሀገራችንን እንገንባ የሚልው የመንግስት አቅጣጫ በሰራዊቱም ተግባራዊ ሲደረግ ስለነበር ነው፤
👉 ያም ሆኖ ግን ሰዎቹ ከመጠን በላይ አብጠው የገዢ መደብ መንፈስ ተላብሰው ስለነበርና ገዢ መደብ ደግሞ ነገር አይገባውም፤
👉 ገዢው መደብ ህዝብ አያዳምጥም ተጓዳኝ ነገር አያዳምጥም፣ ትምክህተኛ ነው፤ ይህ የገዥው መደብ ባህሪ በጣም ስለተፀናወታቸው ነገ ከነገወዲያ ይቀዘቅዛሉ ይሻሻላሉ ችግሩን በሰላማዊ መንገድ ይፈታሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነበር፤
👉እነሱ ግን ህገ መንግስቱ በሰጣቸው መብት የፀጥታ ሀይል አሰልጥነውና አደራጅተው ወደ መከላከያ ነው ያዘመቱት፤
👉 መከላከያው ቀደም ሲል እነሱ 27 ዓመት ሙሉ በስልጣን ላይ በነበሩነት ወቅት የገነቡት ነው፤ የእነሱ ልጅ ነው፤
👉 እነሱ ቀስቅሰው ሀገር ተከላከል ብለው ቃለመሀላ አስገብተው እኛም አብረን ያደራጀነውን ሰራዊት ነው መልሰው ያጠቁት፤ ሰው ልጁን አይበላም፤
👉 እነሱንና የትግራይ ህዝብን የሚጠብቅና የሚከላከልን ሰራዊት፣ እነሱን የሚያገለግል የሚያከብር በኢኮኖሚው ላይ ተሳትፎ ያለውን ሰራዊት፣ በጣም ታዛዥና ህዝባዊ ሰራዊት የነበረውን ሀይል በጣም ክህደት በተሞላው ምንም ጭላጭ ሰብአዊነት የሌለው ሀይል ስለሆነ እራሱ ያሳደገውን የራሱን ልጅ የበላ ሀይል ነው፤
👉 ይህ ሀይል የኢትዮጵያም የትግራይ ህዝብም ጠንቅ ነው፤ አሁን ደግሞ ለመከላከያም ጠንቅ ሆኖዋል፡፡ መከላከያ እራሱን የመከላከል ግዴታ አለበት መጀመሪያ ሀገር ለመጠበቅ የራሱ ደህንነት መጠበቅ አለበት አሁን ግን የመከላከያ ደህንነት ነው የተደፈረው፤
👉 ችግሩን በሰላማዊ መንገድ ይፈታሉ ተብሎ እየተጠበቀ እያለ እነሱ ሕገመንግስቱ በሰጣቸው መብት የጸጥታ ሀይል አደራጅተው የጸጥታ ሀይሉን ወደ መከላከያ ነው ያዘመቱት፤
👉 መከላከያ ቀደም ሲል እነሱ 27 ዓመታትን በስልጣን ላይ በነበሩበት ጊዜ እነሱ የገነቡት ነው፡፡ የእነሱ ልጅ ነው፡፡ እነሱ ቀስቅሰው ፣አገር ተከላከል ብለው ቃለመሐላ አስገብተው አብረን ነው ያደራጀነው ሰው መልሶ ልጁን አይበላም፤
👉 ነካክተው ወደማንፈልገው ውጊያ አስገብተውናል፤ ወደ ውጊያ ከገባን በኋላ ደግሞ በጀግንነት፣ በእልህ እና በቆራጥነት በተጠቂነት መንፈስ ሰራዊታችን ከጫፍ እስከጫፍ ተነቃንቆ አንድ ወታደር ራሱን አባዝቶ ደምስሷቸዋል፤ ለሁለት አመት ያደረጉት ዝግጅት በሙሉ ዜሮ ገብቷል፤
👉 በግለሰብም ይሁን፣ አራት አምስትም ሆነው ሸሽተው የገቡበት ገብተን ለቅመን ታሪክ ካላደረግናቸው ትግራይም ኢትዮጵያም ሰላም አይሆኑም፤ ይሄ ጸረ ሰላም ሀይል ነው፤ በጣም አደገኛ ጁንታ ነው፤
👉 ህዝቡ ጁንታዎቹ የታሉ ይላል፤ አይጥ መፈለግ በጣም ከባድ ነው፤ ወደጎሬ የገባ አይጥ መፈለግ ከባድ ነው፡፡ ቢሆንም መያዛቸው መደምሰሳቸው አይቀርም፤ ግን ጊዜ ይጠይቃል፤
👉 ሰራዊታችን አሁንም አንዳንዶቹን ተቆጣጥሯል፤ አንዳንዶቹ ማልያ ቀይረው ወደከተማ ገብተው ተደብቀዋል፤ ሰራዊታችን እየያዛቸው ነው፤ በጣም ጥሩ ደረጃ ላይ ነው ያለነው፡፡ Ethiopian press Agency

14/12/2020

የኢትዮጵያ ገለልተኛ የብሄራዊ የኢኮኖሚ ምክር ቤት መመስረቱን የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት አስታውቋል።

የመንግሥትን የማሻሻያ ፕሮግራም በስኬት ለማስፈጸምና በአጠቃላይ የኢኮኖሚውን እድገት ቀጣይነት ለማረጋገጥ የምሁራንና ባለሙያዎችን ምክር እንዲሁም ግብረ መልስ መቀበል ጠቃሚ ነው ፅህፈት ቤቱ የገለፀው።

ገለልተኛ ከሆኑ ምሁራንና ባለሙያዎች ሃሳብ መቀበል የፖሊሲን አካታችነት ከመጨመር ባለፈ፤ ያልታዩ ጉዳዮችን ለማየት፣ ሃገሪቱ ያለችበትን ውስብስብ የሆነ የድህነትንና ሌሎች ማኅበራዊ ችግሮችን ለመረዳትና ዉጤታማ የፖሊሲ አማራጮችን ለመመርመር ያስችላል ነው የተባለው።
ከዚህም በመነሳት በታህሳስ 21 ቀን 2012 ዓ.ም. በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት በወጣው ማስታወቂያ መሰረት የገለልተኛ ብሔራዊ የኢኮኖሚ ምክር ቤት እጩ አባላትን በጥቆማና በስራ ማመልከቻ መቀበል መጀመሩን ይፋ አድርጎ እንደነበር ነው ፅህፈት ቤቱ የገለፀው።

ይህንንም ጥሪ ተከትሎ በጥቅሉ ወደ 290 እጩዎች የቀረቡ ሲሆን፣ በሶስት ደረጃ የተከፈለ የማጣራት ሂደት ከተከናወነ በኋላ 16 ምሁራን ፍቃደኝነትታቸው ተረጋግጦ የመጀመሪያው የገለልተኛ ብሔራዊ የኢኮኖሚ ምክር ቤት አባላት ሆነው መመረጣቸው ተጠቁሟል።
በዚህም መሰረት÷

1. ፕሮፌሰር አለማየሁ ገዳ
2.ፕሮፌሰር ብርሃኑ አበጋዝ
3. ፕሮፌሰር ጋቢሳ እጀታ
4. ፕሮፌሰር መላኩ ደስታ
5. ፕሮፌሰር ሰይድ ሀሰን
6. ዶክተር ታደለ ፈረደ
7. ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደ ሃና
8. ዶክተር አለማየሁ ስዩም
9. ዶክተር አሉላ ፓንክረስት
10. ዶክተር ዲማ ነገዎ
11. ዶክተር እሌኒ ገ/መድህን
12. ፕሮፌሰር ለማ ወልደ ሰንበት
13. ዶክተር ራሄል ካሳሁን
14. ዶክተር ሰገነት ቀለሙ
15. ዶክተር ዮናስ ብሩ
16. አቶ ህላዊ ታደሰ የገለልተኛ የብሔራዊ የኢኮኖሚ ምክር ቤት አባላት ሆነው ተመርጠዋል።

14/12/2020

የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በመቀሌ ቆይታቸው

👉ከሀገር መከለከያ ሰራዊት አመራሮች ጋርም በድሉ ዙሪያ ውይይት አድርገዋል፤ በዚሁ ወቅት የተናገሯቸው ዋና ዋና ነጥቦች
👉 ጠላት በርከት ያሉ የእኛን መኮንኖች ይዞ ስለቆየ እነሱን ይዞ ነበር የሚንቀሳቀሰው፤ ስለሆነም ማታ ማታ በምናደርገው ኦፕሬሸን በርከት ያለ ሰው በሚኖርበት ሰአት ይህ ሀይል የእኛ ሃይል ሊሆን ይችላል በሚል ያቆየናቸው ሚሳየሎችና ቦንቦች ዛሬ ያኮሩኛል። ያንን ተጠቅመን ቢሆን ኖሮ ዛሬ በመካከላችን ያሉትን መኮንኖች አናያቸውም ነበር፤
👉 ይህ ኢትዮጵያን የመታደግ ኢትዮጵያን የማኩራት ብቃት፤ ተልዕኮን በአጭር ጊዜ የመፈጸም ብቃት የተቋማችን የሁልጊዜ አርማ መሆን አለበት፤
👉 በተደጋጋሚ እንዳልኩት የመከላከያ ሰራዊት የብልጽግና ሰራዊት አይደለም፤ የአብይ ሰራዊት አይደለም፤ የኢትዮጵያ ህዝብ መከታና ኩራት የሆነ ወታደር ነው፤
👉 እኛ የምንፈልገው ፕሮፌሽናል ጠንካራ አርሚ እንድትሆኑ እንጂ ለአንድ ፓርቲ የሚገዛ እንድትሆኑ አንፈልግም፤
👉 ኢትዮጵያ ከብልጽግናም ከፓርቲም በላይ ናት፤ ትልቋን አገር የመታደግ ሃላፊነት ተጥሎባችኋል፤
👉 ፖለቲካው የተበላሸ ነው፤ የማያውቀውን የደም ስር እና ሀረግ እየፈለገ የሚቧደን ነው፤ እናንተ ግን ጀግኖች ብቻ ሳትሆኑ ንጹህ ኢትዮጵያዊ ናችሁ፤
👉 ጦርነቱን ስንጀምር በጣም ብዙ ሰዎች በአጠረ ጊዜም ብቻ ሳይሆን ማሸነፍም ይከብዳል የሚል ግምግማና ግምት ይናገሩ ነበር፤ ይሄ አልሆነም፤
👉 እኛን የሚዋጉን ሰዎች ዘመናዊ ጦርነት አያውቁም፤ የጦርነት ሳይንስ አያውቁም፤ የሚያውቁት የሽምቅ ውጊያ ነው፤ እሱ የሽፍቶች ውጊያ ነው፤ እሱ በሰው ሃይልና በተተኳሽ ቁጥር ማሸነፍ የምናረጋግጠብት ውጊያ ነው፤
👉 የኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ስንት ሺህ ወጣት እንዳስከፈለን ስንት ጊዜ እንደወሰደ እናውቀዋልን፤ ይሄ የአሁኑ ኦፕሬሽን ደግሞ በምን ያህል ባነሰ የሰው ሃይልና መስዋዕትነት ለድል እንደበቃን ታውቃላችሁ፤
👉 ከሁመራ መቀሌ በእግር መጓዝ ማለት ብዙዎች አዲስ አባበ ሆነው ዝም ብሎ ጀግና እንደሚሉት አይደለም፤ በዚህ መልክዐ ምድር በዚህ ሙቀት ስንቅና ትጥቅ ተሸክሞ ይሄንን ያህል ጉዞ መጓዝ የማንም አገር ወታደር አይደግመውም፤
👉 ይሄንን ጀግንነት ወንጀለኞችን በመያዝ መድገም ያስፈልጋል፤ ወታደሩ የተሰጠውን ተልዕኮ መቶ በመቶ አሳክቷል፤ የሚቀረው ወንጀለኞችን ለህግ ማቅረብ ነው እሱንም በፍጥነት ማከናወን ያስፈልጋል፤
👉 ወንጀለኞችን ለህግ ለማቅረብ የትግራይ ህዝብ ሃላፊነት አለበት፤ የተደበቁትን ሰዎች፣ ከመኪና ወርደው እግረኛ የሆኑትን ሰዎች በመያዝ ለሀገር መከላከያ ሰራዊትና ለትግራይ አስተዳደር ማስረከብ አለበት፤ ያ ካልሆነ ወታደሩ አገር የመጠገን ጊዜውን ወንጀለኛ በማደን ስለሚያሳልፍ የሚጎዳው ራሱ ህዝቡ ነው፤
👉 ከኢትዮጵያ መንግስት ልማት ድጋፍ መጠየቅ ተገቢ ነው፤ ነገር ግን ወንጀለኞችን አሳልፈው መስጠት ደግሞ ግዴታ ነው፤ ይህ ስምምነት ካለ ነው ስራችንን በአጭር ጊዜ በማከናወን ወደልማት የምንገባው፤
በርካታ ወንጀለኞችን እንደተያዙ፤ የተቀሩትም የት እንዳሉ መረጃው አለኝ፤
👉 የሀገር መከላከያ ሰራዊት የኢትዮጵያ ህዝቦች ኩራት መሆኑን፤ በዚህ ቀጣና የሚነሳ ማንኛውንም አደጋ በሚፈለገው ልክ ለመመከት የሚያስችል ብቃት ያለው ጦር መሆኑን በድጋሜ አረጋግጧል፤
👉 የጁንታው ሃይል በቁጥር ከ80 ሺህ በላይ ይገመታል፤ አዳዲስ መሳሪያዎችን ታጥቋል፤ ከፍተኛ የተተኳሽ ዲፖዎች ነበሩት፤ ኮማንዶ ሜካናይዝድ ሮኬት መተኮስ የሚችሉም ሰዎችነበሩት፤ እኛ ግን መቀሌ እስከገባንበት ቀን ድረስ ሮኬት አልተኮስንም በእኛና በጁንታው መካከል ያለው ልዩነት ይሄ ነው፤ እኛ ያልተኮስነው ህዝባችን እዚህ እንዳለ ስለምናውቅ ነው፤
👉 እኛ ሮኬት የተጠቀምነው ጁንታው መቀሌን ለቆ በረሀ ለበረሃ ለማምለጥ ሲሞክር ነው፤ ይሄ የእውነት ይሄ የፍትሃዊነት ልዩነታችን አሸናፊ አድርጎናል
#ኢፕድ

14/12/2020

"የኢትዮጵያ ህዝብ ከእነዚህ መሰሪና በጣም አስቸጋሪ ሰዎች ተገላግሏል” - ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ
የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ መቀሌ ላይ ሆነው መግለጫ ሰጥተዋል

ከጁንታው መደምሰስ በኋላ በመላ ኢትዮጵያ ሰላም መስፈኑን የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ አስታወቁ።

ላለፉት ሁለትና ሶስት አመታት ራሱን እያደራጃ በመላ አገሪቷ ግጭት እየለኮሰ የቆየው የህወሓት ጁንታ ከተደመሰሰ በኋላ በመላ ኢትዮጵያ ሰላም መስፈኑን የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ዛሬ መቀሌ ላይ ሆነው በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።
እንደ ጄኔራል ብርሃኑ ገለጻ፤ ጁንታው በመደምሰሱ የኢትዮጰያ ህዝብ እፎይታ አግኝቷል፤ በመላ አገሪቱ አሁን ሰላም ነው።

ቀደም ባሉት ሁለትና ሶስት አመታት በየቦታው እነሱ ግጭት ይለኩሱ እንደነበረ ያስታወሱት ጄኔራል ብርሃኑ፤ በአሁኑ ወቅት እነሱ በመመታታቸው ምክንያት ሁሉም አካባቢ እፎይታ ሰፍኗል ሲሉም ነው ያስታወቁት።

“የኢትዮጵያ ህዝብ ከእነዚህ መሰሪና በጣም አስቸጋሪ ሰዎች ተገላግሏል” ያሉት ጄኔራል ብርሃኑ፤ የትግራይ ህዝብም ነጻ ወጥቷል፤ ከዚህ በሁዋላ እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ማግኘት የሚገባውና በጁንታው ተቋርጠው የነበሩ የመሰረተ ልማት ስራዎች በፍጥነት ይከናወናሉ ብለዋል።

ጁንታው ላለፉት ሶስት አመታት ህግ መንግስቱ የሚፈቅድለትን መብት በመጠቀም ራሱን በልዩ ሃይል ስም ሲያደራጅ መቆየቱን፤ በቅርብ ቀናትም አዲስ አበባ እንደሚገቡ ለህዝቡ መንገራቸውን፤ ለጎረቤት አገራትም 250 ሺ ሰራዊት አደራጅተናል፤ ሰሜን ዕዝን ደምስሰናል ትጥቅ ወስደናል ስለዚህ ፌዴራል መንግስት አቅም የለውም ከአሁን በሁዋላ ኢትዮጵያ በእኛ እጅ ናት በሚል ውስጥ ለውስጥ ፕሮፖጋንዳ ሰርተዋል” ያሉት ጄኔራሉ መከላከያ ሰራዊት ይህንን የትምክህት፣ የገዥ መደብና የድንቁርና አስተሳሰብ አምክኖታል ብለዋል።
#ኢፕድ

14/12/2020

ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ሲዲሲ አፍሪካ ዋና መስሪያቤት የግንባታ መሠረተ ድንጋይ አስቀመጡ።

በቻይና መንግስት ሙሉ ወጪ ግንባታ የሚካሄደው የሲዲሲ አፍሪካ ዋና መስሪያቤት ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤን ጨምሮ በአፍሪካ ህብረት የማህበራዊ ጉዳዮች ኮሚሽን ኮሚሽነር አሚራ ኢልፋዲል ሞሃመድ ፣ በአፍሪካ ህብረት የቻይና አምባሳደር ሊኡ ዩጂ፣ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ እና ሌሎች የአፍሪካ ህብረት ተወካዮች በተገኙበት የመሠረተ ድንጋይ አስቀምጠዋል ።

የሲዲሲ አፍሪካ ዋና መስሪያቤት በአዲስ አበባ መገንባት አፍሪካውያን የኮቪድ -19 ፣የኢቦላ እና ሌሎች ወረርሽኞችን አስቀድሞ ለመከላከል እና የምርምር ማዕከል ሆኖ እንደሚያገለግል በአፍሪካ ህብረት የማህበራዊ ጉዳዮች ኮሚሽን ኮሚሽነር አሚራ ኢልፋዲል ሞሃመድ ገልጸዋል።

የሲዲሲ አፍሪካ ዋና መስሪያቤት ግንባታን ሙሉ ወጪ ለመሸፈን ድጋፍ ላደረጉ የቻይና መንግስት እና ለማዕከሉ ግንባታ የመሬት አቅርቦት የኢትዮጵያ መንግስትን አመስግነዋል ።
በአዲስ አበባ ንፋስ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ሀይሌ ጋርመን አካባቢ የሚገነባው የሲዲሲ አፍሪካ ዋና መስሪያቤት 90 ሺህ ስኩዌር ሜትር የሚሸፍን የጤና ምርምር ማዕከላት የሚኖሩት ሲሆን በቀጣይ 25 ወራት ውስጥ ግንባታው እንደሚጠናቀቅ ተገልጿል ።

14/12/2020

"ኢትዮጵያ ከብልፅግናም ከፓርቲም በላይ ናት ፤ ትልቋን ሀገር የመታደግ ሀላፊነት ተጥሎባችኋል ።"
የኢፌድሪ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ

14/12/2020

በህገ ወጥ መንገድ የተያዙ ቤቶችን በሚቀጥለው የስልክ ቁጥር ጥቆማ ይሰጡ ዘንድ ጥሪ ተላልፏል።
1ኛ፡-0118277736
2ኛ፡- 0118699174

12/12/2020

ታህሳሰ 3 ቀን 2013
“ ጠላት እና ወገንን የለየ ኦፕሬሽን ተካሂዶ ነጻ ወጥተናል”፦ የሰሜን እዝ ለኦፕሬሽን ምክትል አዛዥ ብርጋዴል ጄኔራል አዳምነህ መንግሥቴ ።

የሕወሓት ጁንታ ወንጀለኞችን በማደንና በመልሶ ግንባታ ምዕራፍ ጠላትን ከወገን በለየ ልዩ ዘመቻ የታገቱ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ነጻ መውጣታቸውን የሰሜን እዝ ለኦፕሬሽን ምክትል አዛዥ ብርጋዴል ጄኔራል አዳምነህ መንግሥቴ ገለጹ።

በጁንታው አባላት ክህደት ተፈጽሞባቸው ከእገታ በአገር መከላከያ ሠራዊት እና የፌዴራል ፖሊስ አባላት ነጻ የወጡት የሰሜን እዝ ለኦፕሬሽን ምክትል አዛዥ ብርጋዴል ጄኔራል አዳምነህ መንግሥቴ “ቤታችን ነን ባልንበት ሰዓት ክህደት ተፈጽሞብናል” ብለዋል።

“ክህደት በተፈጸመብን ወቅት ረጅም የእግር ጉዞ እና አስቸጋሪ ሁኔታዎችን አሳልፈናልም፤ ሆኖም በጁንታው ኃይል ላይ የመከላከያ ሠራዊታችን ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ ጠላትን ከወገን የለየ አስደናቂ ኦፕሬሽን በመፈጸም ነጻ ወጥተናል” ብለዋል ብርጋዴል ጄኔራል አዳምነህ።
ከፊት እና ከኋላ በመሆን የተለያዩ ቴክኒኮችን በመፈጸም እና ጠላትን በማስጨነቅ አስደናቂ ተግባር መፈጸሙንም ነው የገለጹት።

“እንዲህ ዓይነት የክህደት ሁኔታዎችን ተቋቁመን ነፃ በመውጣት አገራችን ያለችበት ሁኔታ በማየቴ ደስተኛ ነኝ” ያሉት ደግሞ የ20ኛ ክፍለ ጦር አዛዥ ብርጋዴል ጄኔራል ኑሩ ሙዘይን ናቸው።
በመከላከያ ሠራዊትንና በፌደራል ፖሊስ የጋራ አሰሳ ነጻ ከወጡ በኋላ በሰጡት አስተያየት “የጁንታው ኃይል የክህደት ተግባር ከፈጸመብን በኋላ በርካታ አስቸጋሪ ጊዜያቶችን አሳልፈናል፤ እኛ ተስፋ በመቁጥ ለአገራችን ልንሰዋ ነበር፤ መከላከያ ሠራዊታችን በአስደናቂ ሁኔታ ነጻ አውጥቶናል እንኳን ደስ አለን ልል እፈልጋለሁ” ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

አገር ላይ ክህደት በፈጸመው ጁንታ ቡድን ላይ ያሳየነውን አንድነት በልማት እና በዕድገት ስራዎቻችን ላይ በማሳየት አኩሪ ተግባር መፈጸም ይኖርብናልም ሲሉ ገልጸዋል።

በጁንታው ቁጥጥር ስር የቆዩት የመከላከያ ሠራዊት አባላት ጁንታው የጥፋት ቡድን ከ40 ቀናት በላይ በስቃይ እንዳቆያቸው እና ለረጅም ኪሎ ሜትር የእግር ጉዞ እንደዳረጋቸው ገልጸዋል።
የመከላከያ ሠራዊት አባላቱ መንግሥት እና የኢትጵዮያ ሕዝብ ላደረገላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።

Ethiopian Broadcasting Corporation

12/12/2020

በህወሀት ጁንታ ቡድን አማካይነት በቀን እስከ 25ሺህ የሀሰት መረጃዎች በቲውተር ሲሰራጭ እንደነበር የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ገለጸ

አዲስ አበባ ታህሳስ 2/2013፡- በህወሀት ጁንታ ቡድን የማህበራዊ ትስስር ገጾችን በመጠቀም ከፍተኛ የሆነ የስነ-ልቦና ጦርነቶችን ሲያከናዉን እንደነበር የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ከፍያለዉ ተፈራ ገለጹ፡፡

ሃገሪቷን ወደ ለየለት ትርምስ ለማስገባት ጁንታዉ የሳይበር ምህዳሩን በመጠቀም ከፍተኛ የማወናበድ ስራ ሲሰራ እንደነበርም ሃላፊዉ ተናግረዋል፡፡
ጁንታው የዲጂታል ወያኔ የተባለ የሃሰት መረጃዎችን የሚያሰራጭ ቡድን በማቋቋም በበላይነት ሲመራ እንደነበር ያነሱት ሃላፊዉ የሳይበር ተፋላሚዎችን በመቅጠር የኦሮሞ ብሄር ተወላጅ መስለው አማራን ߹ የአማራ ብሄር ተወላጅ መስለው ደግሞ የኦሮሞን ስም ሲያጠለሹ መቆየታቸዉን አንስተዋል፡፡

ጥቀምት 24 በመከላከያ ሰራዊታችን ላይ ጥቃት ከማድረሳቸው በፊት ከመሃል ሃገር የሚደረጉ ግንኙነቶች እንዳይኖሩ የመገናኛ ስርዓቱን ከጥቅም ዉጪ ማድረጋቸውን የገለጹት አቶ ከፍያለው ከዛም ባለፈ ቲዊተርን በመጠቀም የሃሰት መረጃ በማሰራጨት ከፍተኛ የሆነ የስም ማጥፋት ዘመቻዎችን ሲያከናዉኑ መቆየታቸውን ገልጸዋል፡፡

በዚህ የሃሰት ፕሮፖጋንዳ ከተለያዩ ብሄር ጽንፈኛ የሆኑ ደጋፊዎቻቸዉን እና የዉጭ ዜጋ ሆነዉ ከዚህ ቀደም የጥቅም ትስስር የነበራቸዉን አካላትን በማደራጀት የዘመቻዉ አካል እንዳደረጓቸዉ ያስታወሱት ም/ዋና ዳይሬክተሩ በዚህ ዘመቻም በቀን እስከ 25 ሺ ሃሰተኛ ቲዊቶችን ߹ የሃሽታግ አካዉንቶችን በመክፈት ደግሞ በቀን ከ13ሺ እስከ 18ሺ ሃሰተኛ መረጃዎችን ሲያሰራጩ እንደነበር ተናግረዋል፡፡

በዚህ የሃሰት ፕሮፖጋንዳም የህግ ማስከበር ሳይሆን ግዛት ማስፋፋት ተግባር አድርጎ የማቅረብ፣ በጦርነቱ ንጹሃን በከፍተኛ ሁኔታ እየተጨፈጨፉ እንደሆኑ የማስተጋባት፣ በትግራይ ተወላጆች ላይ የዘር ማጥፋት ዘመቻ እየተፈጸመ እንደሆነና በመላዉ ሃገሪቱ የትግርኛ ተናጋሪዎች ተነጥለዉ የጥቃት ኢላማ እንደሆኑ በማስመሰል መዘገብን ይገኙበታል፡፡

መንግስት በጁንታው ቡድን ላይ የህግ ማስከበር ተግባር መጀመሩን ተከትሎ የተለየ የሳይበር ጥቃት እንዳልተከሰተ ያነሱት አቶ ከፍያለዉ ሆኖም በዓለም አቀፍ ደረጃ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ መከሰቱን ተከትሎ ብዙዎቹ በቤታቸው ሆነው በኦንላይን እየሰሩ ባለበት ሁኔታ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከተጠበቀዉ በላይ በ3 እጥፍ የሳይበር ጥቃት መጨመሩን ጠቅሰዋል፡፡

በህግ ማስከበር ዘመቻዉ ወቅት የህወሃት ጁንታው ቡድን የዲ ደብሊዩን እና የትግራይ ቲቪ ፍላይ አዌይ ስርዓትን በመጠቀም ግዙፍ የሃገሪቱን የሚዲያ ተቋማት አገልግሎት ለማቋረጥ ሙከራ እንዳደረገ ሃላፊዉ ጠቁመዋል፡፡

የዚህ ጥቃት ኢላማ ከነበሩ ሚዲያዎች መካከልም ኢቢሲ߹ ዋልታ እና ኦ ቢ ኤን ዋናዎቹ እንደነበሩ ያነሱት ሃላፊዉ ፋና እና ሌሎች መሰል ሚዲያዎችን ስርጭት የማቋረጥ ተግባር የመፈጸም አዝማሚያ እንደነበር ሃላፊዉ አስታውሰዋል፡፡ ሆኖም ኤጀንሲዉ በወሰደዉ ቅድመ መከላከል በሚዲያዎቹ ላይ ሊደርስ የታሰበውን የጠለፋ ተግባር ለማክሸፍ መቻሉን ጠቁመዋል፡፡

ከዲጂታል ወያኔ በተጨማሪ ሌሎች የጥቅም ተጋሪዎች በጥፋት ዘመቻዉ ተሳታፊ እንደነበሩ የገለጹት ም/ዋና ዳይሬክተሩ በግለሰቦች ደረጃ ከ50 እስከ 500 የሚደርሱ ሰዎችን በስራቸዉ በማሰማራት እና ክፍያ በመፈጸም ጥቃት ለማድረስ መሞከሩን ነዉ ያነሱት፡፡

በአዲስ አበባ ዉስጥም አንድ ለአምስት እና አንድ ለሃያ አደራጅተዉ አጀንዳ እየሰጡ ብሄርን ከብሄር ህዝብን ከህዝብ ሲያጋጩ የሚዉሉ ሃይሎች መኖራቸው እንደተደረሰበት አቶ ከፍያለዉ ጠቁመዋል፡፡

ከዚህም ባለፈ በዉጭ ሃገራት ከሚገኙ ጽንፈኛ ቡድኖች እና ሚዲያዎች ጋር በመናበብ የተለያዩ የጥፋት እንቅስቃሴዎችን ሲያከናዉኑ ነበር ያሉት ሃላፊዉ ለአብነትም ኦ.ኤም.ኤን ቲቪን ጨምሮ ኢትዮ-360 ከሚባል የማህበራዊ ትስስር ገጽ ጋር ሲሰሩ መቆየታቸዉን ገልጸዋል፡፡

በመሆኑም ህብረተሰቡ የሳይበር ምህዳሩን በመጠቀም ከሚሰራጩ የሀሰተኛ መረጃዎች እራሱን በመጠበቅ ትክክለኛዉን መረጃ ከሚመለከተዉ አካል ብቻ ለማግኘት መሞከር አለበት ብለዋል፡፡

12/12/2020

በአዲስ አበባ ከተማ ታሪካዊ ቅርሶችን የመጠበቅ እና የህዝብ መዝናኛ ስፍራዎች የማስፋፋት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለፀ ።

ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤን ጨምሮ በምክትል ከንቲባ ማእረግ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተባባሪ አቶ ጃንጥራር አባይ ፣በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የማዘጋጃ ቤታዊ ዘርፍ ስራ አስኪያጅ አቶ ጥራቱ በየነ ና የከተማው ካቢኔ አባላት የተለያዩ የመዝናኛ ፓርኮችን እና የሼህ ኦጀሌ ቤተመንግሥትን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱም በከተማዋ የሚገኙ ታሪካዊ ቅርሶችን በመጠበቅ ፤ የህዝብ መዝናኛ ስፍራዎችን በማስፋፋትና ከተማችንን ለመዝናኛነት ምቹ በማድረግ ለሀገር ውስጥም ሆነ ለውጪ ቱሪስቶች ክፍት ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ተገልጿል ።

በዛሬው እለት ጉብኝት ከተካሄደባቸው የመዝናኛ ስፍራዎች መካከል በግንባታ ላይ ያለው ፒኮክ ፓርክ ፣ ሆላንድ ፓርክ ፣ ህዳሴ ፓርክ እና የሼህ ኦጀሌ ቤተመንግሥት ይገኙበታል ።
እነዚህ ታሪካዊ ቅርሶች እና የህዝብ መዝናኛ ስፍራዎች ውስጥ ለማከናወን የታቀዱ የመሠረተ ልማት ግንባታና የእድሳት ስራዎች ፍጥነት ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግ በልዩ ትኩረት እንደሚሠራ ተጠቁሟል ።

12/12/2020

KOLFE keranio communication/ኮልፌ ኮሙኒኬሽን

ትክክለኛ ሰው ለትክክለኛው ቦታ እስከተቀመጠ ድረስ መስራት አለበት ሲሉ የወረዳ የስራ ዕድል ፈጠራ አመራሮች ተናገሩ፡፡
******************************************ኮልፌ ቀራኒዮ 04-04-2013 ዓ.ም
በቀጠለው ውይይት የወጣቶችና በጎ ፍቃድ በስራ ዕድል ፈጠራ ዙሪያ ሚናው ምንድነው፤ተግባሮች ወደ ወረዳ ብቻ እየወረደ ነው፤በወረዳ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ወደ ተግባር አለመግባት የሚሉና መሰል ሀሳቦችን አመራሮቹ አንስተዋል፡፡
በመጀመሪያ የተነሱ ነገሮችን ወደ ራስ ወስዶ በማየት የአመለካከት ለውጥ ማምጣት እንዲሁም ኮር አመራሩ ግፊት ማድረግ እንዳለበት አስተግባሪ ኮሚቴዎቹ ገልፀዋል፡፡
ትክክለኛ ሰው ለትክክለኛው ቦታ እስከተቀመጠ ድረስ መስራት አለበት ሲሉ የወረዳ የስራ ዕድል ፈጠራ አመራሮች በውይይቱ ላይ ተናግረዋል፡፡
አቶ አስጨንቅ ብርሀኑ የክፍለ ከተማው የስራ ዕድል ፈጠራና የኢንተፕራይዞች ልማት ፅ/ቤት ኃላፊ የተነሱትን ሀሳቦች በመውሰድ የስራ ዕድል ፈጠራ ስራን ማሳካት ይኖርብናል ብለዋል፡፡
አስተግባሪ ኮሚቴዎቹ በሚያቀሩብት ሀሳብ መሰረት ተገቢ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ አቶ ሲኢድ አሊ የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ፅ/ቤት ምክትል ኃላፊ ገልፀዋል፡፡
አቶ ብርሀኑ አበራ የፓርቲው ጽ/ቤት ኃላፊ የተነሱትን ማነቆዎች በአንድ አቋም ለመፍታት መረባረብ ይኖርብናል ብለዋል፡፡

12/12/2020

ቀን 03/04/2013 ዓ.ም የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ አስተዳደር የምግብ ዋስትናና ልማት ሴፍትኔት ፕሮግራም የምክር ቤት ጉባኤ ዛሬ በአዳማ አዳማ ራስ ሆቴል አካሄደ።
በአለም ባንክ ድጋፍ በዝቅተኛ ኑሮ የሚገኙ ማህበረሰቦች የተለያዩ ስልጠናዎችን በመስጠትና የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ራሳቸውን ችለው የሚኖሩበትን ድጋፍ የሚደረግ መሆኑን ለምክርቤቱ አባላት ግንዛቤ ተፈጥሯል። የምክር ቤት አባላት በበኩላቸዉ ይህንን ፕሮግራም ውጤታማ ለማድረግ በቀጣይ የካውንስል ምክር ቤት አባላት በየጊዜው እስከ ወረዳና ማህበረሰቡ ዘንድ በመውረድ ስራዎችን በመከታተል ውጤታማነቱን ማረጋገጥ ቢቻል፣በዚህ ፕሮግራም የሚሳተፉ ሰዎች ልየታ ላይ ትኩረት ተደርጎ ቢሰራ ፣ስልጠናውን የወሰዱና ተመርቀው ብር የወሰዱ ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ መግባታቸው የሚደረገው ድጋፍና ክትትል ትኩረት ቢደረግ የሚሉ ሀሳቦች ከካውንስል ም/ቤት አባላት ተነስተዋል።

የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶይታያል ደጀኔ የተነሱ ሀሳቦች አስተማሪና ትኩረት ሊደረጉባቸው የሚችሉ ሀሳቦች መሆኑን በመግለፅ በቀጣይ ሁሉም የምክር ቤት አባላትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በንቃት በመሳተፍ የምናገለግለውን ህዝብ በኑሯቸው ተለውጠው ራሳቸውን ብቻ ሳይሆን ለሌሎች የስራ ዕድል የሚፈጥሩበትን አቅም መፍጠር አለብን ብለዋል።አቶ ይታያል አክለውም በቀጣይ የተለያዩ የትኩረት አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ በተቀመጠለት ጊዜ በመገናኘት ዓላማውን ከግብ ማድረስ አለብን በማለት ግንዛቤ ፈጥረዋል።

12/12/2020

የብልጽግና ፓርቲ ሳምንታዊ መልዕክት!

ብልጽግናን ማረጋገጥ የሚቻለው ወንድማማችነትን በማጎልበት ብቻ ነው!
የብልጽግና ፓርቲ አንድ እሴት ወንድማማችነት ነው፡፡ በወንድማማችነት ውስጥ መቻቻል፣ መተጋገዝ፣ የሌላውን ጉዳት የራስ ጉዳት አድርጎ የመውሰድና ለጋራ ዓላማ በአንድ ላይ በጽናት መቆምን የያዘ ነው፡፡ ብልጽግና የተፈጠረው ይህ መሰረታዊ እሴት በመጥፋቱና አገራችን የቁልቁለት ጉዞ ውስጥ በመግባቷ ነው፡፡

ባሳለፍናቸው ሁለት አስርት ዓመታት ውስጥ በአገራችን ዜጎች በአንድ ከማሰብ ይልቅ እርስ በእርስ ቅሬታ ውስጥ እንዲገቡ፣ ችግሮች ሲፈጠሩም ወደውስጥ አይቶ የጋር ህመሞችን በጋር ከማከም ይልቅ እዚህና እዚያ በመወራወርና በመሳሳብ ለዓመታት የኖረው ማህበረሰባዊ እሴት እንዲሸረሸር ሆኗል፡፡

ብልጽግና የሁሉም ኢትዮጵያዊ እይታ በወንድማማችነት ስሜት ውስጥ መሆን ይገባዋል የሚል እምነት አለው፡፡ ወንድማማችነት ህብረትን የሚያጠናክር በመሆኑ ለአገር እድገትም መሰረት ነው፡፡ በአገራችን በኢኮኖሚው፣ ፖለቲካዊም ሆና ማህበራዊ ሁነቶች ውስጥ እርምጃችን ሁሉ ስኬታማ የሚሆነው እርስ በእርስ ያለንን ትስስር በማጎልበት ብቻ ነው፡፡

የአገር መከላከያ ሰራዊት ላይ በደረሰው ጥቃት ሰራዊቱ እርስ በእርስ ያሳየው ፍቅርና መተሳሰብ የወንድማማችነት ውጤት ነው፡፡ አኔ ልቀደም አንተ ትረፍ እያለ ከወንድሙ በፊት መስዋዕት ለመሆን ራሱን አሳልፎ የሰጠው በወንድማማችነት ውስጥ ያለው መተሳሰብ ትልቅ በመሆኑ ነው፡፡ የአገራችን ህዝብ በየትግል ምዕራፉ ሞሰቡን ዘርግቶ ሰራዊቱን አንጀቱን የደገፈው ራሱን በሰራዊቱ እግር አድርጎ በማሰቡ ነው፡፡ እናቶች ስለሰራዊቱ ሲሉ እምባቸውን እያዘሩ ያሳዩት ፍቅር ውስጣቸው ያለውን የመተሳሰብ ልክ የሚያሳይ ነው፡፡ ወንድማማችነት ይህ ነው፡፡

በአገራችን መገንባት የሚያስፈልገውም እርሰ በእርስ ከመጠላለፍ መተሳሰር፤ ከመሳሳብ መቀራረብ፤ ከመጠራጠር በእምነት ለጋር ግብ መትጋት ነው፡፡ በየትኛውም የአገራችን ጫፍ ያለ ህዝባችን ህልሙ አገራችን ለምታ፣ ሰላሟ ተጠብቆ፣ ፍትሃዊ የሆነ ተጠቃሚነት የተረጋገጠባትና ለሁለም የተመቸች አገር ሆና ማየት ነው፡፡ ይህ ደግሞ ያለመተሳሰብ፣ ያለመደጋገፍ እውን አይሆንም፡፡ የመዳረሻችን መሰረት ደግሞ ወንድማማችነትን ማጎልበት ነው፡፡ ብልጽግና በወንድማማችነት ውስጥ የሚገኝ ድል ነው!

12/12/2020

"ሁላችንም ያለንን አቅም ሳንሰስት በመጠቀም ለሀገራችን ብልፅግና መሳካት ልናውልና ልንጠቀም ይገባል! " - አቶ መለሰ ዓለሙ

በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ለታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚሆን ከ159ሚሊዮን ብር በላይ ተሰበሰበ ።

ከህዳር 6 እስከ ታህሳስ 2/2013 ዓ.ም በየካ ክፍለ ከተማ ቆይታውን ያደረገው የታላቁ የህዳሴ ግድብ ዋንጫ ከ159 ሚሊዮን ብር በላይ በቦንድ ግዢ እና በስጦታ ማሰባሰብ ተችሏል ። በዛሬው ዕለት የአዲስ አበባ ብልፅግና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መለስ ዓለሙ በተገኙበት ዋንጫን ለተረኛው ለቂርቆስ ክፍለ ከተማ አስረክበዋል ።

በዋንጫ ርክክቡ መርሃ ግብር ላይ አቶ መለሰ ዓለሙ እንደገለፁት የሀገራችን የከፍታ ዘመን ብስራት የሆነው የታላቁ የህዳሴ ግድብ ከዳር እንዲደርስ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ያላቸውን ዕውቀት ፣ ጉልበት እና ገንዘባቸውን በመስጠት የሀገራችንን የከፍታ ዘመን ብስራት መቃረቡን እና ከሁሉ በላይ ድህነትን ለማሸነፍ የአሸናፊነት መንፈስ ያለን ህዝቦች መሆናችን የሚያረጋግጥ መሆኑን ያሳየንበት ተግባር በመሆኑ እንኳን ደስ አላቹ በማለት ገልጸዋል ።

ይህ ዛሬ ያስመዘገብነው ስኬት የመተሳሰባችን ፣ የአንድነታችንና የብዝሃነታችን መገለጫ ድምር ውጤት ነው ያሉት አቶ መለሰ ሁላችንም ያለንን አቅም ሳንሳስት በመጠቀም ለሀገራችን ብልፅግና መሳካት ልናውልና ልንጠቀም ይገባል ብለዋል ።

በአዲስ አበባ ከተማ የታላቁ የህዳሴ ግድብ ዋንጫ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች በነበረው ቆይታ ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ መሰባሰብ የተቻለ እንደሆነ የገለጹት አቶ መለሰ ዓለሙ በየካ ክፍለ ከተማም ዋንጫ በነበረው ቆይታ ከ159 ሚሊዮን ብር በላይ መሰባሰብ መቻሉ የውጤታማነቱ መገለጫ የህዝቦች አንድነትና መተባበር መሆኑን አንስተዋል ። በዚህም የድጋፍ ተግባር ላይ ለተሳተፉ እና ላስተባበሩ አካላት በሙሉ በከተማ አስተዳደሩ ስም እና በብልፅግና ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።

በዕለቱም ለታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ በቦንድ ግዢ እና በስጦታ ከፍተኛ አስተዋጾ ላበረከቱ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችና ወረዳዎች የእውቅና ሽልማት ተበርክቷል ።

12/12/2020

በሕወሓት ጁንታ ቡድን በቀን እስከ 25 ሺህ የሀሰት መረጃዎች በቲውተር ሲሰራጭ ነበር - የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ገለጸ

በሕወሓት ጁንታ ቡድን በቀን እስከ 25 ሺህ የሀሰት መረጃዎች በቲውተር ሲሰራጭ እንደነበር የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ አስታውቋል።

በሕወሓት ጁንታ ቡድን የማህበራዊ ትስስር ገጾችን በመጠቀም ከፍተኛ የሆነ የስነ-ልቦና ጦርነቶችን ሲያከናውን እንደነበር የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ከፍያለው ተፈራ ገለጹ።

ሃገሪቷን ወደ ለየለት ትርምስ ለማስገባት ጁንታው የሳይበር ምህዳሩን በመጠቀም ከፍተኛ የማወናበድ ስራ ሲሰራ እንደነበርም ሃላፊው ተናግረዋል።

ጁንታው የዲጂታል ወያኔ የተባለ የሃሰት መረጃዎችን የሚያሰራጭ ቡድን በማቋቋም በበላይነት ሲመራ እንደነበር ያነሱት ሃላፊው የሳይበር ተፋላሚዎችን በመቅጠር የኦሮሞ ብሄር ተወላጅ መስለው አማራን፣ የአማራ ብሄር ተወላጅ መስለው ደግሞ የኦሮሞን ስም ሲያጠለሹ መቆየታቸውን አንስተዋል።

ጥቀምት 24 በመከላከያ ሠራዊታችን ላይ ጥቃት ከማድረሳቸው በፊት ከመሃል ሃገር የሚደረጉ ግንኙነቶች እንዳይኖሩ የመገናኛ ስርዓቱን ከጥቅም ውጪ ማድረጋቸውን የገለጹት አቶ ከፍያለው ከዛም ባለፈ ቲዊተርን በመጠቀም የሃሰት መረጃ በማሰራጨት ከፍተኛ የሆነ የስም ማጥፋት ዘመቻዎችን ሲያከናውኑ መቆየታቸውን ገልጸዋል።

በዚህ የሃሰት ፕሮፖጋንዳ ከተለያዩ ብሄር ጽንፈኛ የሆኑ ደጋፊዎቻቸውን እና የውጭ ዜጋ ሆነው ከዚህ ቀደም የጥቅም ትስስር የነበራቸውን አካላትን በማደራጀት የዘመቻው አካል እንዳደረጓቸው ያስታወሱት ም/ዋና ዳይሬክተሩ በዚህ ዘመቻም በቀን እስከ 25 ሺህ ሃሰተኛ ቲዊቶችን፣ የሃሽታግ አካውንቶችን በመክፈት ደግሞ በቀን ከ13 ሺህ እስከ 18 ሺህ ሃሰተኛ መረጃዎችን ሲያሰራጩ እንደነበር ተናግረዋል።

በዚህ የሃሰት ፕሮፖጋንዳም የህግ ማስከበር ሳይሆን ግዛት ማስፋፋት ተግባር አድርጎ የማቅረብ፣ በጦርነቱ ንጹሃን በከፍተኛ ሁኔታ እየተጨፈጨፉ እንደሆኑ የማስተጋባት፣ በትግራይ ተወላጆች ላይ የዘር ማጥፋት ዘመቻ እየተፈጸመ እንደሆነና በመላው ሃገሪቱ የትግርኛ ተናጋሪዎች ተነጥለው የጥቃት ኢላማ እንደሆኑ በማስመሰል መዘገብን ይገኙበታል።

መንግስት በጁንታው ቡድን ላይ የህግ ማስከበር ተግባር መጀመሩን ተከትሎ የተለየ የሳይበር ጥቃት እንዳልተከሰተ ያነሱት አቶ ከፍያለው ሆኖም በዓለም አቀፍ ደረጃ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ መከሰቱን ተከትሎ ብዙዎቹ በቤታቸው ሆነው በኦንላይን እየሰሩ ባለበት ሁኔታ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከተጠበቀው በላይ በ3 እጥፍ የሳይበር ጥቃት መጨመሩን ጠቅሰዋል።

በህግ ማስከበር ዘመቻው ወቅት የሕወሓት ጁንታው ቡድን የዲ ደብሊዩን እና የትግራይ ቲቪ ፍላይ አዌይ ስርዓትን በመጠቀም ግዙፍ የሃገሪቱን የሚዲያ ተቋማት አገልግሎት ለማቋረጥ ሙከራ እንዳደረገ ሃላፊው ጠቁመዋል።

የዚህ ጥቃት ኢላማ ከነበሩ ሚዲያዎች መካከልም ኢቢሲ፣ ዋልታ እና ኦቢኤን ዋናዎቹ እንደነበሩ ያነሱት ሃላፊው ፋና እና ሌሎች መሰል ሚዲያዎችን ስርጭት የማቋረጥ ተግባር የመፈጸም አዝማሚያ እንደነበር ሃላፊው አስታውሰዋል።

ሆኖም ኤጀንሲው በወሰደው ቅድመ መከላከል በሚዲያዎቹ ላይ ሊደርስ የታሰበውን የጠለፋ ተግባር ለማክሸፍ መቻሉን ጠቁመዋል።

ከዲጂታል ወያኔ በተጨማሪ ሌሎች የጥቅም ተጋሪዎች በጥፋት ዘመቻው ተሳታፊ እንደነበሩ የገለጹት ም/ዋና ዳይሬክተሩ በግለሰቦች ደረጃ ከ50 እስከ 500 የሚደርሱ ሰዎችን በስራቸው በማሰማራት እና ክፍያ በመፈጸም ጥቃት ለማድረስ መሞከሩን ነው ያነሱት።

በአዲስ አበባ ውስጥም አንድ ለአምስት እና አንድ ለሃያ አደራጅተው አጀንዳ እየሰጡ ብሄርን ከብሄር ህዝብን ከህዝብ ሲያጋጩ የሚውሉ ሃይሎች መኖራቸው እንደተደረሰበት አቶ ከፍያለው ጠቁመዋል።

ከዚህም ባለፈ በውጭ ሃገራት ከሚገኙ ጽንፈኛ ቡድኖች እና ሚዲያዎች ጋር በመናበብ የተለያዩ የጥፋት እንቅስቃሴዎችን ሲያከናውኑ ነበር ያሉት ሃላፊው ለአብነትም ኦ.ኤም.ኤን ቲቪን ጨምሮ ኢትዮ-360 ከሚባል የማህበራዊ ትስስር ገጽ ጋር ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልጸዋል።
በመሆኑም ህብረተሰቡ የሳይበር ምህዳሩን በመጠቀም ከሚሰራጩ የሀሰተኛ መረጃዎች እራሱን በመጠበቅ ትክክለኛውን መረጃ ከሚመለከተው አካል ብቻ ለማግኘት መሞከር እንዳለበት ኢመደኤ አስገንዝቧል።

Want your organization to be the top-listed Government Service in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Address

Tikur Anbessa Teaching Hospital
Addis Ababa
251
Other Political Organizations in Addis Ababa (show all)
African Union African Union
Addis Abeba
Addis Ababa, 1111

A UNITED & STRONG AFRICA

Qabsoo Bilisummaa Qabsoo Bilisummaa
Finfinne
Addis Ababa, 2560

Injifannoon Kan Abbaa dhugaati

GMN Grand Media Network GMN Grand Media Network
Addis Ababa

Manegment

Bole Wereda 1 Prosperity Party ብልጽግና Bole Wereda 1 Prosperity Party ብልጽግና
Bole Michael
Addis Ababa, G.P.O

ይህ በቦሌ ክ/ከተማ ስር በሚገኘው በወረዳ 1 ብልጽግና ፓርቲ የ?

Anwar Tuti Anwar Tuti
Somaliya
Addis Ababa, HADLIYAAAA

Addis Ketema Woreda 6 Prosperity Party-ብልፅግና Addis Ketema Woreda 6 Prosperity Party-ብልፅግና
Addis Ketema
Addis Ababa

ለሁሉም ዜጋ ብልፅግናን ለማረጋጋጥ እንሰራለን

Free state movement for Addis ababa Free state movement for Addis ababa
Addis Ababa

Political

Imala Haqaa Imala Haqaa
Addis Ababa

Kaayyoon Kenya haqaa dhokate basne baketi mulisudhaa kanafu nu hordofun haqaa cina dhabachun eru nun

Paartii Badhaadhinaa Kutaa Magaalaa Araadaa Paartii Badhaadhinaa Kutaa Magaalaa Araadaa
Belay Zeleke Street, Pissa Road
Addis Ababa, 251,56

providing facts of prosperity party

Abdallaa  Zeenu Abafogi .Follow Abdallaa Zeenu Abafogi .Follow
Jiimmaa
Addis Ababa