Egha leegha እኛ ለእኘኛ

ለሰው ደራሹ ሰው ነው

15/06/2023
Photos from Egha leegha እኛ ለእኘኛ's post 27/01/2023

የዚህ ፔጅ ዋነኛ አላማ ለተቸገሩ ሰዎች መድረስ ነው ማገዝ የምትፈልጉ የተቸገሩ ሰዎችን አድራሻ በውስጥ መስመር ማግኘት ትችላላችሁ ለተቸገረ ሰው መርዳት ለአላህ እንደማበደር ነው ጀዘክ አላህ ኸይረን

26/01/2023

አሰላም ዋሌኩም ራህመቱላሂ ወበረካቱም ያ ጀማ አንድ ሁለት አህለል ኸይሮችን እንፈልጋለን ኢንቦክስ ገባ ገባ በሉማ

Photos from አል-ነጃሺ ልማታዊ መረዳጃ ዕድር's post 23/10/2022
15/10/2022

ከረሳናቸው ሱንናዎች ውስጥ አንዱና ዋናው የለይል ሶላት ነው።

▪️እስኪ ከፊል የሰለፎች ንግግር ስለ ለይል ሶላት ያሉትን እንመልከት…።

⇨«ከዒባዳዎች ሁሉ በዉድቅት ሌሊት መስገድን የሚያህል አላየሁም፡፡»
🏷(ሐሰን አል-በስሪ)

⇛«ለመቃብር ጨለማ ይጠቅማችሁ ዘንድ በሌሊት ጨለማዎች ተነስታችሁ ስገዱ፡፡»
🏷(አቡ ደርዳእ)

⇛«ከዱንያ ጥፍጥናዎች የቀሩት ሦስት ነገሮች ብቻ ናቸው - የሌሊት ሶላት፣ ከወንድሞች ጋር መገናኘት፣ የጀማዓ ሶላት፡፡»
🏷 (ኢብኑል ሙንከዲር)

⇛«አንድ ሰው በሌሊት ይሰግዳል፤ ሰዎችም ፊቱን አይተው ብቻ ይወዱታል፡፡
🏷(ሰዒድ ኢብኑል ሙሰየብ)

⇛«በሌሊት የአላህን ምህረት ከመለመን በላይ አንድን የአላህ ባርያ መቃብሩ ዉስጥ የሚጠቅመው ነገር የለም፡፡ »
🏷(አቡል ሚንሃል)

☞ለሌሊት ሶላት ለመነሳት ከሚያግዙ ነገሮች
⇒ ወንጀልን መተው፣
⇒ ብዙ አለማምሸት፣
⇒ ጠግቦ አለመብላት፣
⇒ ዱዓ ማድረግ፣
⇒ ሐላል መመገብ፣
⇒ ቀን ላይ ጥቂት መተኛት፣
⇒ አላህን ማውሳት ማብዛት…፣
♻️አላህ ሁላችንንም ያግራልን።

12/09/2022

ማሰብያን የሚቆጣጠሩ የሲህር ምልክቶች ፡፡
በኡስታዝ ዶክተር አቡ ፈርሃን፡፡
ክፍል 1
አልሃምዱሊላህ እነሆ አሏህም ብሎ እዚህ ደርሰናል፡፡ አላህ ምንግዜም አሸናፊ ነው፡፡ ከአላህም ጋር የተዋደደ የርሱንም ጥበቃ የሚሻ ሰው በሙሉ በርሱ መንገድ ላይ ቀጥ ለጥ እስካለ ድረስ አሸናፊ ነው፡፡ እነሆ እናንተም የሚታይባችሁን ምልክቶች ቁብ በመስጠት እራሳችሁን በቁርአን አሸናፊ አድርጉ፡፡
1. የሙድ መለወጥ ወይም እጅግ በጣም ድብርትና ሞተራል የመሟት ስሜት፡፡ ይህ ስሜት ብቻ በአንድ ክፍል ውስጥ አስሮ ሊያውላቸው ይችላል፡፡
2. በአንድ ነገር ላይ ትኩረት ማድረግ አይችሉም፡፡ አንድ ነገር ላይ ሲባል ለምሳሉ በሂሳብ ላይ ወይም ወሬ ላይ እንኳ በአትኩሮት ማድመጥ አይችሉም፡፡ ወዲያው ወድያው ትኩረታቸው ከነገሮች ላይ ይነሳል፡፡
3.ቶሎ ቶሎ ይተነፍሳሉ፡፡ በአቬሬጅ የአንድ ሰው የመተንፈሻ እንቅስቃሴ ደቂቃ ውስጥ ከ 12-20 ሲሆን እነርሱ እስከ 30 ድረስ ሊተነፍሱ ይችላሉ፡፡ ይህ ህፃናትን አይጨምርም፡፡
4.አንድን ነገር ከመጠን በላይ መፍራት፡፡ ወይም እጅግ በጣም ፀፀተ መሰማት፡፡
በቃ ሰውን የማያስቀይም ነገር የሚያስቀይም ይመስላቸዋል፡፡ በሌላ ሁኔታው ደግሞ የዛሬ አምስት አመት የተናገሩህን አሁን ላይ ደውለውም ይሁን በአካል አንተ ጋር መጥተው አውፍ በለኝ ይሉሃል፡፡ ይህም ከልባቸው ልክ አሁን እንደተፈጠረ አይነት ስሜት ይሰማቸዋል፡፡ ሳምንት ወይም ጥዋት የተካሄደን ነገር አልቅሰው አፉታን ይጠይቃሉ፡፡ በሌላ በኩሉ ደግሞ ቢላ ወይ ዱላ ወይ ደግሞ አንድን ሰው አብዝተው ይፈራሉ፡፡ መድረስም መንካትም አይሹም፡፡
5. ከቤተሰብ ከጓደኛ ብሎም ከማህበረሰባዊ ኑሮ ይገለላሉ፡፡
ይህ አይነቱ ፍጹም ከሰውነት የወጣና ወደ እብደት ይወስዳል ተብሎ በማህበረሰባችን የሚወሰድ ሲሆን አብዝቶ ሲታይባቸውም ወደ ስነ አእምሮ ህክምና መውሰዱ የተሻለ ነው፡፡ ይሁን እኛ መድሃኒት ሳይጀምሩ ወደ ሩቅያህ ቢመጡ እንወዳለን፡፡ ይህም ብዙ ኮምፕሊኬሽን እንዳይኖር ያደርጋል፡፡ መድሃኒት የስነ አእምሮ የሚወስዱ ከሆነ ግን ማቋረጡ ተገቢ አይደለም፡፡
6.ድንገት ሱሰኛ ይሆናሉ፡፡
ይህም ሲጃራ የጫት የአልኮል ሱስነ ውስጥ ልታገኛቸው ትችላለህ፡፡ መች እንደገቡ ላይታወቅ ይችላል፡፡ ግን ደግሞ በሱስ ውስጥ ተዘፋቂዎች ነቻው ወይም ተዘፍቀዋል፡፡
7 የፊት መጥቆር፡፡
ፊታቸው እጅግ በጣም ከሰል ይሆናል፡፡ ይህም ለተመልካች የሆነ ችግር መኖሩን ያውቃል ይረዳል፡፡ በዚህም ወቅት እጅግ በጣም ሰው አስተያየት ለቤተሰብ ይበዛል፡፡
8 ሰው በአንዳች ነገር ሲስቅ ‹‹በኔ ነው የምትስቁት››
ብሎ ማሰብ፡፡ ሰው ሲያወራ በኔ ላይ ነው ሚመክሩት ብሎ ማሰብ ሰው ሲያዩ እኔን እየተከለታተለኝ ነው ብሎ ማሰብ፡፡ ይህ ለእብደት ሩብ ጉዳይ የቀረው ሁኔታ አስቸኳይ ወደ ሩቅያህ መጠጋት ያለበት ጉዳይ ነው፡፡
9 .ከተቀመጡበት አይነሱም፡፡
ይህ ሚን አጃኢበቲሂ ታካሚ ቤታችሁ ኑሮ ብታዩ በተርግጠኝት ታውቃላችሁ፡፡ ከጸባያቸው መለዋወጥ በተጨማሪ አንድ ቦታ ላይ ተቀምጠው ሶስት ሳምንት ሊሞላቸው ይችላል፡፡ ከዚያ ቦታ ሰው ጎትቶ ካላነሳቸው አይነሱም፡፡ ሰውነታቸው ቆስሎ እስኪተላ ድረስ ከቦታቸው ላይ አይነሱም፡፡
10 የአመጋገብ ስርአታቸው መበላሸት፡፡
ይህም ምግብ እየተመገቡ በፊት የሚወዱት ምግብ ተሰርቶ አንድ ጉርሻ እንኳን አይበሉም፡፡ በተቃራኒው አፈር መብላት ቆሻሸ መብላት ካልሲ የተለበሰ መመገብን ይወዳሉ፡፡ አንዳንዴም መጥፎ ነገርን ተመግበው ልታገኟቸው ይችላሉ፡
11 የወሲብ ፍላጎት እጅግ በጣም መቀነስ፡፡
ይህ በብዙውን ግዜ በሴቶች ላይ ያይላል፡፡ ውስጣቸው ጭራሽ የወሲብ ፍላጎት ይሞታል፡፡ ባል በየግዜው ስሞታ የሞያሰማውም በዚሁ ላይ ነው፡፡
12 . እላያቸው ላይ መጠቃቀም መጀመር፡፡
ይህ በመሃል በቀልድ ዝም እየተባለ ይመጣና እዚህ እስቴጅ ላይ ሲደርሱ ደህና ነበረችኮ ወደሚለው ቀልድ ይመጣል፡፡ በፈስ መልክ እላያቸው ላይ ይጸዳዳሉ፡፡ እነርሱ መበላሸታቸውን ቢያዩ እንኳ ከመለቃለቅ ይልቅ ሰው እንዳይነካቸው ያደርጋሉ፡፡ ሰው ወደነርሱ ሲቀርብ ነብር ይሆናሉ፡፡ ይህን የማያደርጉና ዝም የሚሉ ከሆነ ደግሞ የበሽታውን እጅግ ስር መስደድ አመላካች ነው፡፡

በጅንም ይሁን በሲህ ልክፍት ለደረሰባችሁ በሙሉ፡፡ በቀልብ ዶክተር የቴሌግራም አድራሻ ቻናል ውስጥ በመግባት የኡስታዞችን ወይም የዶክተሮችን አድራሻ በመውሰድና ምልክቶቻችሁን በማስረዳት ህክምናችሁን መከታተል ትችላላችሁ፡፡

ቻናላችንን ለኡማው ያስተዋውቁ 👇
https://t.me/Qallbdoc

የዩቲዩብ 👉 https://www.youtube.com/c/የቀልብዶክተር

ህክምና ለማግኘት👇
https://t.me/freeeeeeeeeeeere

👆

ህክምና ለማግኘት👇
https://t.me/UstazulQallb

👆

24/07/2022

√በቁርጥማት
√በነርቭ
√በወገብ ህመም ተቸግረዋል?
እንግዲያውስ ፍቱን መፍትሔ ይዘንሎት መጥተናል ዘመናዊ ማሳጅ ቴራፒን ከባህላዊ ወጌሻ ጥበብ ጋር በማጣመር ህክምና ልንሰጥዎ ተዘጋጅተናል ያማክሩን
0973383604

29/06/2022

💠 ከዙል-ሒጃ አስሩ ቀናቶች ውስጥ በቀኑ
ክፍለ ጊዜ ከሚባሉት ዚክሮች መካከል ፦

لا اله الا لله عدد الدهور............... ١٠ مرات
لا إله إلا لله عدد امواج البحور ....١٠ مرات
لاإله إلا لله عدد نبات والشجر.......١٠ مرات
لاإله إلا لله عدد القطر والمطر........١٠ مرات
لا إله إلا لله عدد لمح العيون.........١٠ مرات
لا إله إلا لله خير مما يجمعون.......١٠ مرات
لاإله إلا لله من يومنا هذا إلا
يوم ينفخ في الصور....................١٠ مرات

ላኢላሃ ኢለሏህ አደደ ዱሁር...............10 ጊዜ
ላኢላሃ ኢለሏህ አደደ አምዋጀ ቡሁር...10 ጊዜ
ላኢላሃ ኢለሏህ አደደ ነባቲ ወሸጀር.........10ጊዜ
ላኢላሃ ኢለሏህ አደደ ቀጥሪ ወል መጠር...10ጊዜ
ላኢላሃ ኢለሏህ አደደ ለምሂ አል ዑዩን........10ጊዜ
ላኢላሃ ኢለሏህ ኸይሩ ሚማ የጅመዑን......10ጊዜ
ላኢላሀ ኢለሏህ ሚን የውሚን ሀዛ ኢላ የውሚ ዩንፈኹ ፊሱር...........10 ጊዜ

💚በሸይኽ ዐዲል አህመድ
[ ሐፊዘሁሏህ ]

አሏህ ይወፍቀን 😊

#ሼር
#ሼር

16/06/2022

ትጥበታችሁን ሁሉ ወዱዕ አድርጉት። ምክንያቱም መታጠባችሁ ካልቀረ በዚያውም ሶስት የማይተኩ ጥቅሞችን ታገኛላችሁ።

♦️ አንደኛ፡- ወዱዕ ወንጀልን ያጥባል።

ነቢዩ (ዐሰወ) ስለዚሁ ሲናገሩ «አንድ ሰው ወዱዕ ሲያደርግ ከመጨረሻው ጠብታ ጋር አብሮ ወንጀሉ ይወርድለታል።» ብለዋል።
(ሙስናድ አህመድ 21680)

♦️ ሁለተኛ፡- ወዱዕ ከሸይጧን ይጠብቃል።

ነቢዩ (ዐሰወ) «አንድ ሰው ሲተኛ ሸይጧን ሶስት ቁጥራቶችን ያስራል። ተነስቶ ወዱዕ ባደረገ ጊዜ አንዱ ቁጥራት ይፈታል።» ብለዋል።
(ቡኻሪ 3269)

♦️ ሶስተኛ፡- ኢማንህን ትጠብቅበታለህ።

ነቢዩ (ዐሰወ) ስለዚህ ሲናገሩ «ወዱውን የሚጠብቅ የለም ሙዕሚን ቢሆን እንጅ።» ብለዋል።
(አቢ ሸይባህ 1/14)

14/06/2022

ወንድሜ ፈርኦኖቹ የዚህን ሰውዬ ንግግር ቢሰሙና ማድረግ ቢችሉ የአዝሀርን ሙፍቲ ልከው ያስደመስሷቸው ነበር።

እኒህ አልጀሪያዊ ፕሮፌሰር ናቸው። አለም አቀፍ የቁርአን ውድድር ዳኛ ናቸው። በአልጀሪያ በሚካሄደውና የዳውድ ቅኝቶች (مزامير داوود) የቁርአን ውድድር ኮሚቴ ሰብሳቢ ፣ የገይስ የቁርአን ጽሁፍ አርታኢ ፣ በ10 የቁርአን አቀራር ስልቶች ፈቃድ ሰጭ ፣ የአልዋዲ ዩኒቨርስቲ የቂራአትና ተፍሲር መምህር ናቸው። በተለያዩ የአለማችን ክፍሎች በጀርመን በርሊን ፣ አሜሪካ ፣ ሳዉዲ ዓረብያ ፣ በኳታር አለማቀፍ ውድድሮችን የዳኙ ጉምቱ ሰው ናቸው።

በአጤረራው እንዲህ ብለዋል....
ኢትዬጵያ የሰላም ሀገር ናት። የሰላም ሀገር ሰላም ካልሆነ አይገባትም ፣ ጠላት ጥፋት ለመዝራት ቢለፋ ፣ ሙስሊሞችና ሙስሊሞች እርስበርሳቸውእንዲጠፋፉ ቢለፋ ፣ ሙስሊሞችና ክርስትያኖች እንዲጠፋፉ ጠላት የለፋውን ቢለፋ ፣ የፈለገ ቢጥርና ቢግር አይሳካም። ምክንያቱም ኢትዬጵያ ሰላም ናት ። ሰላም እንጅ አይገባትማ።

የተከበርክ ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ አሊ ፣
አንተ የአያትህ የነጃሺ ልጅ ሆይ ሰላምታዬ ይድረስህ ፣
ሚሊዬን ሰላምታዬ ይድረስህ !....
ለዘላለም ሰላም ትሆናለችም !...
ነጃሺ የናንተ
ኡሙ አይመን የናንተ
ቢላል የናንተ ....
የሀበሻ ሰዎች ሆይ ! ለመሆኑ በናንተና በፈጣሪ መካከል ምን ሚስጥር ቢኖር ነው ?

በመጨረሻም አንድ ልጨምር

አንዲት ጥቁር ሀበሻዊት ነበረች። መስጅድ ታጸዳ ነበር። መልእክተኛው ሶዐወ አንድ ቀን አጧትና ጠየቁ። ያች ሴት የት ሄደች? አሉ። አይ ሞታ ቀበርናት እኮ ብለው ነገሯቸው። ለማንም አድርገውት የማያውቁትን መቃብሯ ላይ ሄደው ሰገዱባት። ይሄ ለአንዴም ለመጨረሻም የተደረገው ለሀበሻዊቷ ነው።

አህመድ ሙሀመድኑር

01/06/2022

____ አደራ አደራ ሳታነቡት እንዳታልፉ ____
*** አሰላም ወአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ ***
= ከእለታት አንድ ቀን ነብዩ ሙሃመድ (ሰ.አ.ወ) ዘንድ አንድ አገጠር የመጣ ኑሮዉ
ያልሰመረለት ድሃ ግለሰብ #ሰሃን ሙሉ ወይን ስጦታ ያመጣላቸዋል
_ ነብዩም (ሰ.አ.ወ) ስጦታዉን ተቀብለዉ ወይኑን መብላት ጀመሩ __
_ የመጀመሪያ ጎርሰዉ ፈገግ አሉ .....
_ ሁለተኛዉም ጎርሰዉ ፈገግ አሉ ግለሰቡም እጅጉን ተደሰተ ...
_ የነብዩ ጋደኞች #ሶሃቦች ሁሌም ለነብዩ (ሰ.አ.ወ) ስጦታ
ሲመጣላቸዉ ስለ ሚያካፍሏቸዉ ይህንን #ጣፋጭ ወይን እንዲያካፍሏቸዉ
በጉጉት ይጠብቃሉ
_ የአላህ መልእክተኛ ግን ሳያካፍሏቸዉ እያንዳንዱ የወይን ፍሬ እየበሉና ፈገግ
እያሉ ሁሉንም በልተዉ ጨረሱ _
_ ስጦታ አቅራቢው እጅግ ተደስቶ ስጦታውንም ስለ ወደዱለት አመስግኖ ሄደ ...
አንድ የነብዩ (ሰ.አ.ወ) ጓድ #ሶሃባ ጠጋ ብሎ ነብዩን ጠየቃቸው
* የአላህ መልእክተኛ ሆይ ምነዉ ሳያካፍሉን ??
_እርሳቸውም ነብዩ (ሰ.አ.ወ) ፈገግ ብለዉ መለሱለት ''
_ ሰዉየዉም መደሰቱን አይታችኋል አይደለም ? !
_ ወይኑን ስቀምሰዉ በጣም ይመር ነበር ....?!!!
_ ባካፍላችሁ አንዳችሁ ግለሰቡን የሚያስከፋ እና ደስታዉን የሚያደፈርስበት
ነገር እንዳታሳዩት ሰጋሁ !!

ፊዳከ አቢ ዋ ኡሚ ያረሱለላህ !!!

*** S.A.W ***
*** S.A.W ***
*** S.A.W ***
#አደራ አደራ አንብባችሁ ስትጨርሱት ሼር አድርጉት 🙏🙏🙏🙏

01/06/2022

ጂብሪል ዐሰ የሰማይ መልዕክቱን ወደ ረሱል ሰዐወ ካደረሰ በኋላ በተወሰነ መልኩ እዝያው እየቆየ የማውጋት ልምድ አለው።

አንድ ቀን በመጣበት ያወጋቸው ጀመር። ጫወታን ጫወታ ያነሳዋል'ና፦‹‹ምን ያህል እድሜ ኑረኃል?›› ብለው ነቢ ሰዐወ ጠየቁት።

‹‹አንቱ የአላህ ነብይ! በወል አላውቀውም። ግን ከ 4ኛው ሒጃብ ምትወጣ አንዲት ኮከብ አለች፤ እና ያች ኮከብ በየ 70,000 አመት አንዴ ብቻ ብቅ እያለች ትጠልቃለች። እና ያችን ኮከብ 72,000 ግዜ ደርሼ ተመልክቻለሁ እንጂ እድሜዬን እንደው አላውቀውም ›› አላቸው።

‹‹በጌታዬ ክብር እምልልኃለሁ! ያች ኮከብ እኔ ነበርኩ›› ብለው አስደመሙት።

አንድ በል!
--------------------------------------------------------------------

አደም በድሎት አለም ከአላህ ተጎራብቶ ፍፁም ፀጋን እያጣጣመ በነበረበት ግዜ ጉርብትናን ሳይፈራ የአላህን ትዕዛዝ ጥሶ ተገኘ።

አላህም ተቆጣ፤ እርምጃ ለመውሰድ ምልክቶችንም አከታተለበት። ኣደም ዋለለ፣ ወዲህ ወድያ ተሯሯጠ። የለበሳቸው ልብሶቹ አይኑ እያየ ከገላው ተላቅቀው መብረር ጀመሩ።

ለጉርብትና ክብር እና ውዴታ ከአናቱ ተደፍቶለት የነበረው መለኮታዊ ዘውድም ከራስ ቅሉ ከፍ ብሎ በጫካው መኃል እርቃኑን አስቀረው።

መሔጃ ጠፋ፣ የአላህ ዛቻዎች ወቀሳዎች በአድማሱ በተደጋጋሚ ይስተጋቡ ጀመር። አደም በማያውቀው አለም ተደናበረ ከእርቃን ሽሽት ከጫካው ቅጠል እየቀጠፈ ከገላው መለጣጠፍ ጀመረ።

መሻሻ አለመኖሩን በተረዳ ግዜ እንዲህ ሲል ተጣራ፦‹‹ጌታዬ! በነቢ ሙሀመድ ይሁንብህ ይቅር በለኝ››

‹‹ሙሀመድን ግና ያልፈጠርኩት ስሆን እንዴት አወቅኸው? ›› ሲልም አላህ ጠየቀ።

‹‹ጌቴዬ! ፍጥረቴን ባጠናቀቅክ ግዜ ገና ቀና ከማለቴ ከዙፋንህ መሶሶዎች ላይ "ላ ኢላሃ ኢለ ላህ ሙሀመዱን ረሱሉሏህ" እሚል ፅሁፍ ተመለከትኩ።

ያን ግዜ ከስምህ ጎን ያሰፈርከው አካል ያንተ ውድ ፍጡር መሆኑን ተረዳሁና በሱ ለመንኩህ›› አለው አደም።

አላህም፦‹‹ኣደም ሆይ! እውነት ተናግረኃል። በሱ ከለመንከኝማ ይቅር ብዬኃለሁ። እሱ ባይኖር እኮ አንተንስ መች እፈጥርህ ነበር!›› ብሎ ታረቀው።

ሁለት በል!
------------------------------------------------------------------------

ኑሕ ዐሰ የነቢያት አባት በመባል የሚታወቅ ሲሆን እጅግ ረጅም አመታት ዳዕዋ በማድረጉ የላቀ እና የታፈረ ነብይ ነው።

ኢብራሂምም ዐሰ የነቢያት ዘር አባት ተብሎ ከመታወቁም ባሻገር የአላህ ከሊል ተብሎ የመወዳጃ ቅፅል ስም የተቸረው እጅግ ክቡር ነቢይ ነው።

ሙሳም ዐሰ ጋ ብትመጣ የአላህ አውጊ፣ ፍፁም የለፋ ነቢይ ከመሆኑ ባሻገር ተከታዮቹ የቂያም ቀን አድማስ በመሸፈን በብዛታቸው ከልቁን ዐጀብ ያሰኛሉ። አላህም አንቀባርሮ ካሳደጋቸው ነቢያት አንዱ ከመሆኑ የተነሳ የመልዐክ አይን አጥፍቶ እንኳ "ወግድ!" ያልተባለ ክቡር ነቢይ ነው።

ዒሳ'ን ዐሰ ብትመለከተው ፍጥርጥሩ ጉድ ያሰኛል። ለክብር ክብር ከተባለ የአላህ መንፈስ መሆኑ ብቻ በቂው ነው።

ነቢያትን ሁሉ ብትመለከት አላህ ሲያልቃቸው እና ሲያከብራቸው የደረጃቸው ከፍታ አንገት ያስደፋል። ከፊታቸው መቆም ቀርቶ ከኋላቸው መሄድ ያስፈራል።

ወደ ነብይህ ሰዐወ ስትመጣ ግን ዘርዝረህ ስለማትዘልቀው፤ ዝምታ መንገድህ ይሆናል። ያ ሁሉ ክቡር ያ ሁሉ ከሊም ያ ሁሉ ከሊል ያ ሁሉ ነቢይ ከኋላቸው ይሰግዳል። ከኋላቸው መስገድ ለዝያ ሁሉ ነቢይ ትልቁ ክብራቸውም ይሆናል።

ያን ሁሉ ነቢይ ምን ትመኛለህ ብለህ ብትጠይቀው ትልቁ ምኞታቸው ለነቢይህ ኡመት መሆን ነበር የሚሆነው ምላሻቸው።

Sefwan Ahmedin
--------------------------------------------------------------
رواه الحاكم وصحح
ورواه البيهقي في كتابه المسمى ((دلائل النبوة))

29/05/2022

«መዋረስ»
የደጋሚና የጅን ውል!

ደጋሚዎች ከጅኖች ጋር የሚያደርጉት ስምምነት በአገራችን ቋንቋ «መዋረስ» ይባላል። ይህንን ጉዳይ የሚያስፈፅሙት ጠንቋዮች ደግሞ «አዋራሾች» ይባላሉ። አንድ ደጋሚ ከጅን ጋር መዋዋል ከፈለገ መጀመሪያ አዋራሽ ወደሚባሉት የታወቁ ጠንቋዮች ይሄዳል። ከዚያም አዋራሾች ከጅኖቹ አለቃ ጋር በማገናኘት የሚጠበቅበትን ፈፅሞ በስሩ ጅኖች የሚታዘዙለት ደጋሚ እንዲሆን ያስችሉታል።

እነዚህ ተወካይ ጂኖች ደግሞ የተከሰተን ነገር በማሳወቅ፣ ባልና ሚስትን በማፋታት እና አጠቃላይ የድግምት ስራዎች ላይ ለጠንቋዩ አገልጋይ ባሪያ ይሆናሉ። ይህን የማያደርጉ ከሆነ ደግሞ ከመሪያቸው እስከ መገደል የሚደርስ ቅጣት ይጠብቃቸዋል።

ደጋሚው ጂኑ አልታዘዝ ካለው ወደ መሪው በተለያዩ የሺርክ ተግባራት ሂርዛሂርዞችን በመተብተብና በማጉተምተም ይማፀናል። አለቃውም ጂኑን በመቅጣት እንዲታዘዝ ያደርገዋል። በዚህም ምክንያት ብዙ ጊዜ አገልጋይ ጂኖች ከደጋሚው ጋር የሚኖራቸው ግንኙነት በጥላቻ ላይ የተመሰረተ ነው። ጅኖቹም በበቀል በደጋሚውና በቤተሰቡ እንደዲሁም በንብረቱ ላይ አደጋ በመጣል የሌሊት ድንጋጤ፣ ተደጋጋሚ ራስን መሳት፣ ልጅ እንዳይወልዱ ማህፀንን ላይ ፅንስን ማበላሸት ወዘተ ይበቀሏቸዋል። ልጅ ለማግኘት ሲሉ ደጋሚነታቸውን የሚተውም ጠንቋዮች አሉ።

አንድ ደጋሚ ከጅን ሸይጣኖች ጋር ውል የሚፈፅማባቸው የሽርክና የኩፍር መንገዶች ብዙ ቢሆንም ዋናዎቹ ስምንት ናቸው።

♦️1፡- የመሃላ ስልት

ደጋሚው ያለጠሀራ፣ በጀናባ ወይም ነጃሳ ልብስ በመልበስ ወደ ጨለማ ክፍል ይገባል። ከዚያም እሳት ያቀጣጥልና ለሚፈለግበት ጉዳይ የሚያስጠላ ወይም ጥሩ ሽታ ያላቸው ዕጣን ያጨስበታል። ከዚያም የሽርክ መተቶችን ያነበንባል።

እነዚህ መተት ንግግሮች በውስጣቸው የጂን መሪዎችን እርዱኝ በማለት መለማመንንና በስማቸው መማልን እንዲሁም አገልጋይ ጅኖቹን «በአለቃችሁ ይሁንባችሁ» እያሉ መማፀንን የያዙ ሲሆን ይህም ለጂን መሪዎች ኩራት የተገባ የሆነ ከባድ ሺርክን ነው።

ደጋሚው እነዚህን የኩፍር መተቶቹን አነብንቦ ከጨረሰ በኋላ ጅኑ በውሻ ፣ እባብ ወይም ሌላ ምስለ ጥላ ይከሰትለታል። አንዳንድ ጊዜ የሚከሰት ነገር ሳይኖር ድምፅ ብቻ ሊሰማ ይችላል። አንዳንዴም ድምፅም ላይሰማ ይችላል። ከዚያም ደጋሚው ድግምት ሊሰራበት የሚፈለገውን ግለሰብ ላብ፣ ፀጉር እና እና ሌሎች ነገሮች ቆጣጥሮ ጂኑን የሚፈልገውን ነገር እንዲፈፅምለት ያዘዋል።

♦️ 2ኛ፡- የእርድ ስልት

ድጋሚው በጂኑ ፍላጎት መሰረት ወፍ፣ ዶሮ፣ ጉጉት ወይም ሌላ እንስሳ በልዩ መገለጫዎች ያቀርባል። አብዛኛውን ጊዜ ጂኖች ጥቁር ቀለምን ስለሚመርጡ ጥቁር ቀለም ያለውን እንስሳ ይጠቀማል። ከዚያም የአላህን ስም ሳያወሳ ያርደዋል። አንዳንዴም ታማሚውን በደሟ ይቀባዋል። ከዚያም የታረደችውን እንስሳ በቆሻሻ ቦታ ወይም ሸለቆ ወይም ሰው የማይኖርበት ራቅ ያለ ስፍራ ይወረውራታል። እነዚህ ቦታዎች ባብዛኛው የጂን መኖሪያ ስፍራዎች ናቸው። ከዚያም ወደ ቤቱ ይመለስና የሺርክ ቲባቲቦዎቹን በማነብነብ ጂኑን በሚፈልገው ነገር ያዝዘዋል።

♦️ 3ኛ፡- የተዋርዶ ስልት

ይህ ውል ከደጋሚዎች ሁሉ የከፋውን ኩፍር የሚፈፀምበት ሲሆን በደጋሚዎች ዘንድ «የተዋርዶ ስልት» በመባል ይታወቃል። ደጋሚውም ለዚህም ተግባሩ ብዙ አገልጋይ ጅኖች ይሰጡታል።

በቅድሚያ ደጋሚው ቁርኣንን በእግሩ እንደጫማ ይጫመታል። ከዚያም ወደ መፀዳጃ ቤት በመግባት የሺርክ ቲባቲቦዎችንና ጠላሲሞችን ያነበንባል። ከዚያም ተመልሶ ወደ ግርዶው በመግባት ይቀመጥና ጂኑን የፈለገውን ያዝዘዋል። ጂኖችም ለትእዛዙ ይሽቀዳደማሉ።

ይህ ተዋራጅ ደጋሚ ከዚህ ተጨማሪ ሌሎች ከባባድ ወንጀሎችን እንዲፈፅም መስፈርት የሚቀመጡለት ሲሆን በሸሪዓው ማግባት ከማይበቃለት ሴቶች ጋር ዝሙት እንዲፈፅም፣ ግብረሰዶማዊ እንዲሆን፣ ዲኑን እንዲያቋሽሽ ወዘተ ይታዘዛል።

♦️ 4ኛ፡- የነጃሳ ስልት

በዚህ ስልት ደግሞ ደጋሚው ከቁርኣን የተወሰኑ ምዕራፎችን በወር አበባ ደም ወይም በሌሎች ነጃሳ ነገሮች ይጽፋል። ከዚያም የሺርክ ቲባቲቦዎችንና ጠላሲሞችን በማነብነብ ጂኑን የሚፈልገውን ያዝዘዋል።

♦️ 5ኛ፡- የመገልበጥ ስልት

በዚህንኛው ስልት ደጋሚው ከተከበረው የአላህ ቃል አንድን ምዕራፍ በነጠላ ፊደላት የተገለበጡ አድርጎ በመፃፍ የሺርክ ቲባቲቦዎችንና ጠላሲሞችን ያነበንባል። ከዚያም ጂኑን ያስከስትና የሚፈልገውን ያዝዘዋል።

♦️ 6ኛ፡- ኮከብ ቆጠራ

በዚህ ስልት ደጋሚው ልዩ የሆነ ኮከብ የሚወጣበትን ጊዜ ይከታተላል። ከዚያም የኮከብን ሩሃኒያ እያወረድኩ ነው በማለት የሺርክ ቲባቲቦዎችንና ጠላሲሞችን ያነበንባል። በዚህ ጊዜ ሸይጣኖች የርሱን ትእዛዝ ለመተግበር ይመጣሉ። እንደ ደጋሚዎች እምነት ከሆነ በዚህ ወቅት ያደረጉት ድግምት ኮከቡ በሌላ ጊዜ ተመልሶ እስኪወጣ ድረስ አይፈታም ብለው ይሞግታሉ።

ደጋዎቹ በሌላ ደጋሚ ሲህር ለተደረገባቸው ሰዎችም እነዚህን በአመት አንድ ጊዜ ብቻ የሚታዩ ኮከቦችን በመጠባበቅ ሲህሩን እንዲፈታላቸው በሺርክ ዝማሬ ያነበንባሉ።

ነገር ግን ይህ የደጋሚዎች እምነት እንጂ ሙወሒድ ሩቃ አድራጊዎችም ሆኑ በአላህ ያመኑ ሙእሚኖች ድግምቱ በአላህ ፍቃድ በቁርአንና ነብያዊ ሩቃ በቅፅበት እንደሚፈታ በተግባር ያረጋገጡት ነው።

♦️ 7ኛ፡- የመዳፍ ስልት

በዚህ ስልት ደግሞ ደጋሚው ለአቅመ ኣደም ያልደረሰ ህፃን ልጅን ያቀርባል። ህፃኑ ውዱዕ የሌለው መሆን ይኖርበታል። ከዚያም የግራ እጅ መዳፉን ይይዝና አራት ማዕዘን ቅርፅ በመሳል ዙሪያውን የሺርክ ጠላሲሞችን ይከትባል። ከዚያም በህፃኑ መዳፍ ላይ ቅባትና ሰማያዊ አበባ በማስቀመጥ ልጁን በወፍራም ልብስ ሙሉ ለሙሉ ይሸፍነዋል።

ከዚያም ይህ በድጋሚ የሺርክና የከባድ ኩፍር ጠላሲሞችን ማነብነብ ይጀምራል። ህፃኑ አየሩ ወደ ብርሃናማነት እንደተቀየረና በመዳፉም ላይ የሚንቀሳቀስ ምስል ይታየዋል። በዚህ ጊዜ ደጋሚው ለህፃኑ «ምን ይታይሃል?» ይለዋል። «የሆነ ሰው ከፊት ለፊቴ ይታየኛል» ይለዋል። ደጋሚውም ጠላሲም የሚያነበው ሰውዬ እንዲህ እንዲህ ይልሃል በለው ይለዋል። ለልጁ የሚታየው ምስል በትዝዛዙ መሰረት ይንቀሳቀሳል። በዚህም ስልት ከጅኑ ጋር ንግግር ያደርጋሉ።

♦️ 8ኛ፡- የፋና ስልት

በዚህ ስልት ደግሞ ደጋሚው ከታማሚው ፋናዎቹን ይፈልጋል። ፎጣ፣ ጥምጣም፣ ቀሚስ፣ ሸሚዝ ወይም ማንኛውም የታማሚውን የላብ ሽታ የያዘ ነገር በማስመጣት ጫፍና ጫፉ ላይ ያስርና አራት ጣት በጥንቃቄ ለክቶ ይቋጥራል። ከዚያም በቁርኣን እንደሚያድን ለማስመሰል ድምፁን ከፍ አድርጎ ሱረቱ ተካሱርን ወይም ሌላ አጭር ምዕራፍ ያነባል። ቀጥሎም ድምፁን ዝቅ አድርጎ የሺርክ ጠላሲሞችን ማነብነብ ስከትላል።

ከዚያም ጂኖቹን ይጣራና «ይህ ታማሚ ያለበት ጂን ከሆነ አሳጥሩት። ያመመው የሰው ዐይን ከሆነ አርዝሙት። ያመመው የህክምና በሽታ ከሆነ ተውት።» ይላቸዋል።

ከዚያም ልብሱን ይለከዋል። ከአራት ጣት በላይ ከረዘመ አንተ አይን አለብህ ይለዋል። ካጠረ ጂን ይዞህ ነው ይለዋል። ምንም ካልሆነ ደግሞ ምንም የለብህም ሀኪም ቤት ሂድ በማለት ያዘዋል።

🔷 እነዚህ ከላይ ለመጥቀስ የሞከርናቸው ስልቶች ደጋሚው ከጅኖች ጋር በመግባባት ከሚሰራባቸው ውሎች ጥቂቶቹ ሲሆኑ ሁሉም የሽርክና ኩፍር ተግባራት ናቸው። ይህንን ማወቁው ሙስሊሞች «ድግምታዊ ፈውስ» እና «ቁርኣናዊ ፈውስን» ለይተው እንዲረዱ ያስችላቸዋል።

ድግምት በኢስላም የኩፍር ተግባር ሲሆን አላህ በቁርኣኑ፡-

«ሰይጣናትም በሱለይማን ዘመነ መንግስት የሚያነቡትን ድግምት ተከተሉ። ሱለይማንም አልካደም፤ ድግምተኛ አልነበረም፤ ግን ሰይጣናት ሰዎችን ድግምትን የሚያስተምሩ ሲሆኑ ካዱ።»
(በቀራህ 102)

ባለው መሰረት ድግምትን መስራቱ ይቅርና መማርና ማስተማሩም ጭምር ከኢስላም እንደሚያስወጣ ነግሮናል።

በ Ismaiil Nuru

25/05/2022

#ፍቅር ማለት፦ቁረይሾች ነብዩን ﷺ በተኙበት ሊገድሏቸው ሲመጡ አልይ እብን አቢ ጧሊብ 'እርሰዎን ከሚገድሉ እኔን ይግደሉኝ 'ብለው በቦታቸው ላይ ተኝተው መገኘታቸው ነው።
---------
#ፍቅር ማለት ፦ነብዩ ﷺ ሚስታቸው ዓኢሻ በጠጡበት እቃ በጠጡበት ቦታ ላይ መርጠው መጠጣታቸው ነው።
--------
#ፍቅር ማለት፦ነብዩ ﷺ ለባልደረባቸው ሰውባን ረ.ዐ ምንድነው ፊትህን የቀየረው? ብለው ሲጠይቁት «በሽታም ሆነ ህመም የለብኝም፤ ግን አንቱን ሳላገኝ ስቀር ከባድ የሆነ ብቸኝነት ይሰማኛል፤ አንቱን እስከማገኞዎ ድረስ» ማለቱ ነው።
---------
#ፍቅር ማለት፦አቡበከር አስ-ሲዲቅ ረ.ዐ ከነብዩ ﷺ ጋር በሂጅራ ጉዟቸው ወደ ዋሻ ከመግባታቸው በፊት
«ወሏሂ ካንቱ በፊት ካልገባው በስተቀር አትገቡም፣ የሆነ ነገር ቢኖር እንኳ ካንቱ በፊት እኔን ይጉዳኝ» ማለታቸው ነው።
--------
#ፍቅር ማለት፦ቢላል አል-ሐበሺይ ረ.ዐ ነብዩ ﷺ ሲሞቱ የነብዩ ﷺ ፍቅር መዲና አላስቀምጥ ብሎት አዛን ማድረጉን መተዉና መዲናን ጥሎ መሄዱ ነው፤ ይህ ብቻም ሳይሆን ነብዩ ﷺ በህልሙ መጥተውበት ለምን አትዘይረንም? ሲሉት ገና ሌሊቱ እንደነጋ የነብዩን ﷺ ቀብር ዚያራ ለማድረግ መጓዛቸው ነው፤ ከዛም አዛን እንዲያደርግ ለምነውት ያን አዛን ሲያደርጉ የመዲና ህዝብ በሙሉ በእንባ መራጨቱ ነው። ነብዩ ﷺ ከሞቱ በኃላ እንጂ እንደዛ አይነት እልቅሻ አልታየም ተብሎ በታሪክ ኢስኪፃፍ ድረስ።
---------
#ፍቅር ማለት፦ ከበኒ ዲናር የሆነች ሴት ባሏ፣ አባቷና ወንድሟ ወደ «ኡሑድ» ዘመቻ ወጥተው ሳለ ሙስሊሞች ከውግያው ሲመለሱ ሁሉም እንደሞቱ ሲነገራት «ነብዩ ﷺ እንዴት ሆኑ? ብላ መጠየቋ ነው፤ ከዛም እሳቸው አልሞቱም ሲሏት እሳቸውን ካላየው ብላ ነብዩን ﷺ ስታያቸው «ካንቱ በኃላ ያለ ሙሲባ ሁሉ ለኔ ገር ነው» ማለቷ ነው።
--------
#ፍቅር ማለት፦ ዙበይር ረ.ዐ የ15 አመት ወጣት ሆኖ የነብዩን ﷺ መገደል የውሸት ወሬ ሲሰማ የመካ መንገዶች ላይ ሰይፉን እየጎተተ መውጣቱ ነው።
---------
#ፍቅር ማለት፦ረቢዐተ ኢብን ከዕብን ረ.ዐ ነብዩ ﷺ ምንድነው ሓጃህ (ጉዳይህ) ሲሉት ካንቱ ጋር በጀነት ጓደኛ መሆን ነው ማለቱ ነው።
ፍቅርን ፍቅር ከሆነ ሰው ተማር!!!
/እኛም ነብዩን ﷺ ትክክለኛ ፍቅር የምናፈቀርና ከርሳቸው ጋር የምንቀሰቀስ አላህ ያድርገን --ሰው ከሚወደው ጋር ነውና የሚቀሰቀሰው
ሼር ሼር ስለ ኢስላም ❤

25/05/2022
Want your organization to be the top-listed Non Profit Organization in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Videos (show all)

Telephone

Website

Address

Addis Ababa
Other Charity Organizations in Addis Ababa (show all)
imagine1day imagine1day
2Q3W+XV2 Imagine1day, Gabon Street
Addis Ababa, 1000

Educating people to transform themselves, their communities, and the world.

ናድቢስ ትዉልድ ናድቢስ ትዉልድ
Adiss Abeba
Addis Ababa

Organization for Welfare & Development in Action - OWDA Organization for Welfare & Development in Action - OWDA
Meskel Square , Lion Building , 9th Floor
Addis Ababa, 1502A.A

OWDA is a charity organization that Promotes conditions of sustainable human development through implementing programs on basic service delivery, economic opportunities, livelihood...

Women and Children Empowerment Organization-WCEO Women and Children Empowerment Organization-WCEO
Addis Ababa. Ethiopia
Addis Ababa

WCEO is Charity Society Organization (CSOs) founded to engage in empowering the community particularly women and children through designing different interventions that create econ...

Jaldu Page Jaldu Page
Addis Ababa, ###X

This page is where Jaldu Woreda people will share their ideas, views and discuss on what ever agendas raised

Relief Organization for South Sudan Addis Ababa, Ethiopia Relief Organization for South Sudan Addis Ababa, Ethiopia
Addis Ababa

To coordinate humanitarian assistance to save lives, restore dignity through psycho-socio rehabilita

waldah qurana waldah qurana
Addis Ababa, 1000

الجمعية الخيرية لخدمة القرآن في إثيوبيا �

ኑስራ የበጎ አድራጎት ድርጅት/ Nusra Charitable organization ኑስራ የበጎ አድራጎት ድርጅት/ Nusra Charitable organization
Mesalemia
Addis Ababa

በበጎነት ማህበረሰቡን እናብቃ!!

Spiritan Community Outreach Ethiopia - SCORE Spiritan Community Outreach Ethiopia - SCORE
SCORE A. A Office
Addis Ababa

We are part of 3000 Spiritans working in over 57 countries. We have been Serving in Ethiopia since 1972. We minister in areas for which the Church has difficulty in finding workers...

Abdellah Ibnu Umi Mekhtum-አብደላህ ኢብኑ ኡሚ መኽቱም Abdellah Ibnu Umi Mekhtum-አብደላህ ኢብኑ ኡሚ መኽቱም
Around 6kilo
Addis Ababa

Abdellah Ibnu Umi Mektum Qur’an Association is a certified religious non-governmental organization