Addis Ababa prosperity women’s league- ብልፅግና
Creating democrat, vibrant and front line womens that has accepted and ready to implement programs a
ራዕይ
የከተማችን ሴቶች፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ተሳታፊነትን በማጎልበት እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ የብልጽግና ፓርቲን ተልእኮ በብቃት መወጣትና የመደመር መንገዳችን ቀጣይነት ማረጋገጥ
ተልዕኮ
- ህብረተሰባዊ ለውጥን ማፋጠን፣
- የወቅቱን ፓርቲያዊ ተልዕኮዎች በሚገባ ተገንዝቦ በብቃት መፈጸም፣
- የሴቶችን ሁለንተናዊ ጥቅም ለማስጠበቅ መረባረብ፣
- የሴቶችን የትግል መድረክ ሆኖ ማገልገል፣
- ሁሉንም ሴቶች በጋራ ዓላማዎች እና ጥቅሞች ዙሪያ ማንቀሳቀስ፣
ዓላማ
ከተማችንን ሴቶች በሁለንተናዊ የለውጥ እንቅስቃሴያችን ዙሪያ በንቃት በማሳተፍ ደረጃ በደረጃ ተጠቃሚ በማድረግ የህዳሴ ጉዞአችንን ማቀላጠፍ
የከተማችንን ሴቶች በመሰረታዊ ጥቅሞቻቸው በመነሳት ዙሪያ እንዲሰባሰቡና በመደመር እሳቤ ዙሪያ እነዲሰባሰቡና በቀጣይነት እነዲተጉ ማስቻል፡፡
ፓርቲያችን ብልፅግና ብሔራዊነት ገዢ ትርክት እንዲሆን የፈለገበት የመጀመሪያው ምክንያት ትርክቱ "አማካይ በመሆኑ" የተነሳ ነው!!
ኅብረ ብሔራዊነትን፣አካታችነትን ፍትሀዊነትን እና እኩልነትን ለሁሉም ኢትዮጵያውያን የሚያረጋግጥ አሰባሳቢ ትርክት ሀገራችን ያስፈልጋታል ብሎ ብልፅግና ፓርቲ ያምናል።
አብሮነትን ክዶ ልዩነት ላይ ብቻ የሚያተኩር ትርክት፣ብዝኃነትንም ደፍጥጦ ፍፁማዊ አንድነት ላይ የሚያተኩር ትርክት ለምናስበው ሀገራዊ ብልፅግና አይጠቅመንም።
ኢትዮጵያ ሀገራችን ትናንት ሀገራዊ አንድነትን ለማስጠበቅ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ዋጋ የከፈሉላት፣ህዝቦቿ ብዙ የተድላ እና የፈተና ጊዜያትን በጋራ ወጥተው የወረዱባት፣በአንድነትም በልዩነትም ትርክት የተነሳ ግጭት እና ፈተናዎችን ያሳለፈች ሀገር ናት።
የብልፅግና ብሔራዊነት ትርክት ትናንትን አምርሮ የሚረግም ወይም አግንኖ የሚያወድስ አይደለም። ከትናንት ጠቃሚ የሆኑ ወረቶችን ለማስቀጠል የሚሰራ፣ጥፋቶችን የሚያርም ነው።ዛሬን ግን ለስራ እንጂ ለቁዘማ አይጠቀምበትም።
የአ/አ ብልፅግና ሴቶች ሊግ በአራዳ ክ/ክፍለ ከተማ በመገኘት ከወረዳ አመራሮችና ከመ/ድርጅት እንዲሁም ከህዋስ አመራሮች ጋር ስለተቋሙ የስራ አፈፃፀም ፍሬያማ ውይይት አድርገናል። በውይይቱ የሴቶች ተሳትፍና ተጠቃሚነት ላይ እየተሰራ ያለው ስራና የኑሮ ውድነትን ለማቃለል የተጀመረው ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትና ለተግባሩ ውጤታማነትም የበኩላቸውን እንደሚወጡ ከመግባባት ተደርሷል።
መረዳዳት የቀደመ ባህላችን ነው።
የአዲስ አበባ ብልፅግና ሴቶች ሊግ ዛሬ በጉለሌ ክ/ከተማ ከመዋቅሩ አመራርና አባላት ጋር የስራ ግምገማና የመስክ ጉብኝት አድርገናል።በግምገማው በክ/ከተማው የዝግጅት ምዕራፍ ተግባራት በጥሩ ሁኔታ መከናወናቸውንና የተግባር ምዕራፍ ስራዎችም በተሻለ ፍጥነት እየተሰሩ መሆኑን በተለይ የሴቶች ተጠቃሚነት ላይ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን በመስክ ምልከታችን አረጋግጠናል።
የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ሊግ በክረምት የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብና የበጋ በጎ ፈቃድ ስራን የማስጀመር ተግባር ዛሬ በ15/3/2016 አከናውኗል። በተጨማሪም በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ወረዳ 10 ተጀምሮ የነበረ የአቅመ ደካማ እናትን የመኖሪያ ቤት በማጠናቀቅ የማስረከብ ስራ ተሰርቷል። መርሃ ግብሩ እንዲሳካ የማስተባበር ስራውን ለተወጡ ሁሉ ምስጋናችን ይድረሳችሁ።
በከንቲባ አዳነች አቤቤ ዘመን! ውብ እና ፅዱ ከተማ!
ለሚ ኩራ! የመንገድ አካፋዮች እንዲህ ተውበዋል!
Click here to claim your Sponsored Listing.
Videos (show all)
Category
Contact the organization
Website
Address
Bole Michael
Addis Ababa, G.P.O
ይህ በቦሌ ክ/ከተማ ስር በሚገኘው በወረዳ 1 ብልጽግና ፓርቲ የ?
Addis Ababa
Kaayyoon Kenya haqaa dhokate basne baketi mulisudhaa kanafu nu hordofun haqaa cina dhabachun eru nun
Belay Zeleke Street, Pissa Road
Addis Ababa, 251,56
providing facts of prosperity party