በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ስም የተቋቋመ የአባኮራን ወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበር

This Association is an indigenous non-governmental, not-profit and independent organization, founded

12/03/2022

#ምኩራብ
-> የዐቢይ ጾም ሦስተኛ ሣምንት ምኩራብ ይባላል።

-> ምኵራብ ፦ የአይሁድ መቅደስ ቤተ ጸሎት ታላቅ አዳራሽ ነበር።

-> በዚህ ሣምንት ጌታ በመዋዕለ ስብከቱ፡ በምኩራብ ገብቶ ማስተማሩ ይነገራል (ማቴ 4፥23 ማር 1÷21 ሉቃ 4÷15)

-> ክርስቶስ ለማስተማር በገባ ጊዜ አይሁድ ቤተ ጸሎቱን እንደ ስያሜው ሳይሆን መሸጫና መለዋወጫ መገበያያ አድርገውት ስለአገኛቸው ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ መሸጫ መለዋወጫ አደረጋችሁት ብሎ ሰዎችንና እንስሳትን በጅራፍ እየገረፈ ገበታቸውን እየገለበጠ አባሮአቸዋል ስለዚህ ይህ ሳምንት ለታሪኩ መታሰቢያ ምኩራብ ተብሉአል (ማቴ 21፥12-13
ማር 11፥15-18:: ሉቃ 19÷45-47 ዮሐ 2÷14-16)

-> ቅዱሳን ሐዋርያትም እንደ ጌታችን ለጸሎትና
ለትምህርተ ወንጌል ወደ ምኩራብ ይወጡ ነበር፡፡ የሐዋ 3፥1። የሐዋ.13፥5:: የሐዋ.14፥1:: የሐዋ.17-1:: የሐዋ.10-17:: የሐዋ.18-4:: የሐዋ.19፥8)

-> ምኩራብ ፦ ለአምልኮና ለትምህርት ለሕብረተሰቡም ጠቅሞአል

-> ምኩራብ በአለቆች ይመራ ነበር (ማር 5፥ 22፡፡ የሐዋ 3÷14-15:: የሐዋ18፥8)

-> በየሳምንቱ ሕዝቡ ሁሉ በምኩራብ ይሰበሰቡ ነበር፡፡ (ሉቃ 4÷16፡፡ የሐዋ.15 21)፡፡

-> ወንዶችና ሴቶች ለየብቻቸው ይቀመጡ ነበር።

->የእግዚአብሔር ቃል ሲነበብ አንባቢው እንዲሰማ በተዘጋጀው ከፍተኛ ቦታ ይቆም ነበር::
የክብር ወንበሮች ከዚህ ቦታ ፊት ለፊት ነበሩ (ማቴ 23÷6:: ሉቃ 4፥20)

➕ መዝሙር ዘምኩራብ :-
ቦአ ኢየሱስ ምኩራቦሙ ለአይሁድ

➕ ምንባባት ምኩራብ ዘቅዳሴ :-
- ቆላ 2÷16-ፍም፡፡
- ያዕቆብ 2፥14-ፍም::
- ግ.ሐዋ 10፥1-9

➕ ምስባክ ፦
" እስመ ቅናተ ቤትከ በልዐኒ ትዕይርቶሙ ለእለ ይትዔየሩከ ወድቀ ላዕሌየ ወቀጻዕክዋ በጾም ለነፍስየ " (መዝ 68፥9)

➕ ወንጌል ዮሐ 2፥12-ፍም

➕ ቅዳሴ ዘእግዚእነ (ነአኩተከ)

ፍካሬ ሃይማኖት / fikare haimanot (@fikarehaimanot) | Twitter 06/03/2022

#ቅድስት

➕የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሣምንት ቅድስት ይባላል።
- የተቀደሰች ፤ የተባረከች ፤ ንጽሕት ማለት ነው::

➕ ለምን ቅድስት ተባለ?

-> «ጾምን ቀድሰ ጉባኤውን አውጁ ሽማግሌዎችንና በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤተ ሰብስቡ፡፡»
(ት.ኢዩኤል 1፥14) ብሎ በነቢዩ ኢዮኤል አፍ የተናገረ ቅዱስ እግዚአብሔር የጾማት ጾም ስለሆነች (የጌታችን ጾም ከቅድስት ጀምሮ በመሆኑ) ቅድስት ትባላለች።

-> እንዲሁም የዲያብሎስን ፈተና ድል ለመንሳት በቅድስት ከተማ በሰሎሞን ቤተ መቅደስ ጫፍ የቆመባት ዕለት በመሆኗ (ማቴ 4፥5/ ዮሐ 10፥22-23 ) ሰው ሁሉ ጾምን ጾሞ እንደ ፈጣሪው ፈተናን ድል ነሥቶ ቅድስና እና ክብርን ያገኛልና ቅድስት ተብላለች።

--> ቅድስት ዕለተ ሰንበት
«እግዚአብሔር ሰባተኛይቱን ቀን ባረካት ቀደሳት» (ዘፍ 2÷3፣ ዘጸ 20፥8) ሰዎች ፍጥረት ያልተፈጠረባት ዕለት ብለው እንዳይንቋት እንዳያቃልሏት እረፍተ ሥጋ እረፈተ ነፍስ የተገኘባት ዕለት ስለሆነች ቀደሳት አለ፡፡ ቅዱስ ያሬድም " ሰንበትየ ቅድስትየ ዕንተ አዕረፍኩ እምኩሉ ግብርየ ይቤ እግዚኣብሔር " ብሉአል:: በዚህ እሁድ (ሳምንት ) ቀደሳት፣ አከበራት፣ ከፍ ከፍ አደረጋት :- የተባለች ሰንበትን የምትታሰብበት የሰንበትንም ቅድስና የሚመለከቱ መዝሙሮች የሚቀርብበት ሳምንት በመሆኑ ቅድስት ተብሏል።

-> መዝሙር ዘቅድስት ፦
ግነዩ ለእግዚአብሔር

-> ምንባባተ ቅድስት ዘቅዳሌ ፦
- 1ኛተሰሎ.4፥1-13
- 1ኛ.ጴጥ.1÷13-ፍም
- የሐዋ.10፥17-30
- ማቴ 6፥16-25 (4፥1-11)

-> ምስባክ ዘቅድስት፦
" እግዚአብሔርሰ ሰማያተ ገብረ አሚን ወሰናይት ቅድሜሁ ቅድሳት ወዕበየ ስብሐት ውስተ መቅደሱ "
ትርጉም፦ " እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ሠራ፥ ምስጋና ውበት በፊቱ ፥ ቅድስትነትና ግርማ በመቅደሱ ውስጥ ናቸው ። " (መዝ 95፥5)

-> ቅዳሴ ዘቅደስት፦
- ኤጲፋንዮስ

✍️ አምኃ ሥላሴ / መኩሪያ ተስፋዬ

ፍካሬ ሃይማኖት / fikare haimanot (@fikarehaimanot) | Twitter The latest Tweets from ፍካሬ ሃይማኖት / fikare haimanot (). ፍቅር የበጎ ነገሮች ሁሉ ምንጭ ናት

27/02/2022

ዐቢይ ጾም

ዐቢይ ለምን ተባለ ቢሉ ‹‹ዐበየ›› ማለት ከፍ አለ ማለት ሲሆን ከዚህም ግስ አቢይ የሚለው ቅጽል ይገኛል፡፡ ዐቢይ ማለት ከፍ ያለ ትልቅ ማለት ነው፡፡

ዐቢይ ጾም የተባለበት ምክንያት፡-

ሀ. ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው ጾም ስለሆነ

ለ. በቀኑ ቁጥር ከሌሎች አጽዋማት የሚበልጥ ስለሆነ

ሐ. ሦስቱ ታላላቅ የሰይጣን ፈተናዎች ማለትም 'ትዕቢት' 'ስስት' 'ፍቅረ ነዋይ' ድል የተመቱበት ስለሆነ ነው፡፡

በቤተክርስቲያን ስያሜ መሰረት በዐቢይ ጾም ውስጥ የሚውሉ ሰንበታት እያንዳንዳቸው መጠሪያ ስም ሲኖራቸው እነርሱም፡-

1. ዘወረደ
የዐቢይ ጾም የመጀመሪያው ሰንበት ሲሆን ይህም ቅድመ ዓለም የነበረ ዓለምን ፈጥሮ የሚኖር አልፋና ኦሜጋ ከሰማየ ሰማያት መውረዱንና ከእመቤታችን ከቅድስተ ቅዱሳን ከንጽሕተ ንጹሐን ከድንግል ማርያም መወለዱን የሚያመለክት ሥያሜ ነው፡፡

2. ቅድስት
ይህ የሁለተኛው ሰንበት ስያሜ ሲሆን የተባለበትም ምክንያት ስለ ዕለተ ሰንበት ቅድስና ስለሚያወሳ ነው፡፡ እንዲሁም ይህ ዕለት ዕለተ እግዚአብሔር የተባለች የሰንበት ክርስቲያን ቅድስናን ያመለክታል ምክንያቱም የዚች ዕለት ጌታ እርሱ ቅዱስ እግዚአብሔር ነውና ስለዚህም ዕለተ ሰንበት ቅድስት ተብላለች፡፡

3. ምኩራብ
ይህ የሦስተኛው ሰንበት ስያሜ ሲሆን በዚህ ሰንበት ጌታ በመዋዕለ ትምህርቱ በምኩራብ ገብቶ ማስተማሩ ይነገራል፡፡ እንዲሁም ይህች ዕለት መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኩራብ ገብቶ እንዳስተማረ የሚታሰብበት ዕለት ነው፡፡ ምኩራብ ማለት የቤተ አይሁዳውያን የጸሎት ቤት ነው፡፡

4. መጻጉዕ
ይህ የአራተኛው ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ድውያንን መፈወሱ እውራንን ማብራቱ ለምጻምን ማንጻቱ ሽባዎችን መተርተሩ የሚያነሳ መዝሙር የሚዘመርበት እንዲሁም እነዚህ ሁሉ ድንቅ ገቢራተ ታምራቶች የሚዘከሩበት ዕለት ነው፡፡

5. ደብረ ዘይት
ይህ የአምስተኛው ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ሆኖ ነገረ ምጽአቱን እንዳስተማረ የሚወሳበት ሰንበት ነው፡፡ ደብረ ዘይት ማለት ወይራ የበዛበት ተራራ ማለት ነው፡፡

6. ገብርኄር
ይህ የስድስተኛው ሳምንት ሰንበት ስያሜ ሲሆን ይህም ዕለት ለጌታው ታማኝና በጎ የሆነው ባርያ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ ተብሎ እንደተመሰገነ የሚነገርበት ዕለት ነው፡፡

7. ኒቆዲሞስ
ይህ የሰባተኛው ሰንበት ስያሜ ነው፡፡ ይህም ዕለት ኒቆዲሞስ የተባለው የአይሁድ መምህር በሌሊት ወደ ጌታው ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ እየመጣ ይማር እንደነበረ ይታሰብበታል በዚም ዕለት የኒቆዲሞስን ታሪክ የሚያስታውስ መዝሙር ይዘመርበታል፡፡

8. ሆሳዕና
ይህ የስምንተኛው ሳምንት ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት በነቢዩ በዘካርያስ ላይ የተጻፈው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ጌታችም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያይቷ እና በውርንጭላይቷ ላይ ተቀምጦ ሆሳዕና በአርያም ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ ተብ እየተመሰገነ ወደ ቤተ መቅደስ መግባቱ የሚተሰብበት ዕለት ነው፡፡ ሆሳዕና ማለት ‹‹እባክህ አሁን አድን አሁን ባርከን›› ማለት ነው፡፡ በሰሙነ ሕማማት ጸሎተ ፍትሃት ጸሎተ አስተስርዮ ስለማይፈጸም ጸሎተ ፍትሃትና አስተስርዮ የሚደረገው በዚሁ ዕለት ነው::

ጾሙን የበረከት ጾም ያድርግልን፡፡

💚 💛 ❤️

23/02/2022

የካቲት 16
ኪዳነ ምህረት

‹ ኪዳን › የሚለው ቃል ‹‹ ተካየደ – ተዋዋለ ፤ ቃል ኪዳን ተጋባ ፤ ተማማለ ›› ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ሲኾን ፣ ትርጕሙም ኪዳን፣ ውል ፣ መሐላ ፣ ቃል ኪዳን ፣ የውል ቃል ማለት ነው /ዘዳ.፳፱፥፩፤ ኤር.፴፩፥፴፩-፴፫፤ መዝ.፹ ፰፥፫/፡፡ በሌላ በኩል ኪዳን የጸሎት ስም ሲኾን፣ ጌታችን ሞትን ድል አድርጎ ከተነሣ በኋላ፣ ከማረጉ በፊት ለሐዋርያት ያስተማራቸው ጸሎት ኪዳን ይባላል፡፡

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇ ከወዳጇ ከጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የምሕረት ቃል ኪዳን (ውል ፣ ስምምነት) የተቀበለችበት ዕለት (የክብረ በዓል ስም) ደግሞ ኪዳነ ምሕረት ይባላል፡፡

በየዓመቱ የካቲት ፲፮ ቀን የምናከብረው ይህ በዓል እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በጎልጎታ በልጇ በመቃብር ላይ ኾና ‹‹ ኦ ወልድየ ወፍቁርየ እስእለከ በእንተ ዘተሰባእከ እምኔየ ወበማኅፀንየ ዘጾረተከ፤ ልጄ ወዳጃ ሆይ ከሥጋዬ ሥጋ ፣ ከነፍሴ ነፍስ ነሥተህ ሰው ስለመኾንህ ፤ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን ስለቻለችህ ማኅፀኔ ፤ ከአንተ ጋር ከአገር ወደ አገር ስለመሰደዴ መጥተህ ልመናዬን ትሰማኝ ዘንድ እለምንሃለሁ ›› እያለች ስትጸልይ ጌታ እልፍ አእላፍ መላእክቱን አስከትሎ ወደእርሷ መጥቶ ‹‹ ሰላም ለኪ ማርያም እምየ ፤ እናቴ ማርያም ሰላም ላንቺ ይኹን! እንዳደርግልሽ የምትለምኚኝ ምንድን ነው? ›› አላት፡፡

እመቤታችንም በስሟ የሚማጸኑትንና መታሰቢያዋን የሚያደርጉትን፣ ለችግረኛ የሚራሩትን፣ ቤተ ክርስቲያን የሚያንጹትን ፤ ዕጣን ዘይትና መብአ ለቤተ ክርስቲያን የሚሰጡትን ፤ ለእመቤታችንና ለሃይማኖታቸው ካላቸው ፍቅር የተነሣ ልጆቻቸውን በስሟ የሰየሙትን ዅሉ እንዲምርላትና ከሞተ ነፍስ እንዲያድንላት ጠየቀችው፡፡

ጌታችንም ‹‹ ይህን ዅሉ እንዳደርግልሽ መሐልኩ ለኪ በርእስየ ወበአቡየ ወበመንፈስ ቅዱስ ሕያው፤ በራሴ፣ በአባቴ እና በመንፈስ ቅዱስ ማልኩልሽ›› ብሎ ቃል ኪዳን ገብቶላት ወደ ሰማይ ዐርጓል፡፡ ለዚህም ነው ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ በቅዳሴው ‹‹ … ዳግመኛም በእናትህ በማርያም ተማፅነናል፤ ይህችውም አንተን በመውለድ እመቤታችንና የባሕርያችን መመኪያ ናት፡፡ አንተ ‹ መታሰቢያሽን ያደረገ ፣ ስምሽንም የጠራ ፣ የዘለዓለም ድኅነትን ይድናል› ብለሃታልና …፤›› በማለት የሚማጸነው፡፡

በተአምረ ማርያም መጽሐፍ እንደተመዘገበው በዚህ ዕለት የሚታሰቡ ሁለት ተአምራት አሉ፤ ከእነዚህም አንደኛው የስምዖን ታሪክ ነው፡፡ ስምዖን የሚባል እንግዳ ተቀባይ ደግ ሰው ነበር፡፡ ሰይጣን ለምቀኝነት አያፍርምና ከዕለታት አንድ ቀን በእንግድነት ከቤቱ ገብቶ ‹‹ልጅህን አርደህ ካላበላኸኝ ሌላ ምግብ አልበላም›› አለው፡፡ በዚህ ጊዜ ስምዖን ሲያወጣና ሲያወርድ ቆየና ‹‹አብርሃም ልጁን ሰውቶ ነው የእግዚአብሔር ሰው የተባለው ›› በማለት፣ ‹‹ የእግዚአብሔርን እንግዳ›› ላለማሳዘን ሲል ልጁን አርዶ አቀረበለት፡፡

እንግዳ መሰሉ ሰይጣንም ሥጋውን ቅመስልኝ ብሎ ግድ አለው፡፡ ስምዖንም (በላዔ ሰብእ) አርዶ ያዘጋጀውን የልጁን ሥጋ በቀምሰ ጊዜ ሰይጣን ስላደረበት (ስለተዋሐደው) ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ቤተሰቦቹን፣ ጎረቤቶቹንና መንገደኛውን ዅሉ ይበላ ጀመር፡፡ በአጠቃላይ ፸፰ ሰዎችን ከበላ በኋላ አንድ በቍስል የተመታ ሰው አገኘና ሊበላው ሲል ‹‹ውኃ አጠጣኝ›› ብሎ በሥላሴ፣ በቅዱስ ሚካኤል፣ በቅዱስ ገብርኤል ስም ለመነው፤ እርሱም ዝም አለው፡፡

በመጨረሻም ‹‹ በድንግል ማርያም ስም ›› አለው፡፡ ስምዖን የእመቤታችንን ስም በሰማ ጊዜም ወደ ልቡናው ተመልሶ ‹‹እስኪ ቃሉን ድገመው ›› አለው ፤ በሽተኛውም መልሶ ‹‹ ስለ ድንግል ማርያም ውኃ አጠጣኝ›› ብሎ ለመነው፡፡ ያን ጊዜ ‹‹ይህችስ እንደምታስምር በልጅነቴ ሰምቻለሁ ›› ብሎ ጥቂት ውኃ ሰጠው ፤ ውኃው ጕሮሮውን እንኳን ሳያርስለት ‹‹ ጨረስህብኝ ›› ብሎ ነጥቆት ሔደ፡፡

በሌላ ቦታም አንድ ገበሬ አግኝቶ ሊበላ ሲል ገበሬው ‹‹በላዔ ሰብ የምትባል አንተ ነህ? ›› ባለው ጊዜ ‹‹ ለካስ አመሌን ሰው ዅሉ አውቆብኛል ›› ብሎ ዋሻ ገብቶ በመጸጸት በዚያው ሞተ፡፡ ነፍሱንም መላእክተ ጽልመት መጥተው ሲወስዷት እመቤታችን ‹‹ልጄ በማይታበል ቃልህ ይህችን ነፍስ ማርልኝ? ›› አለችው፡፡

ጌታችንም ‹‹ ሰባ ስምንት ነፍስ ያጠፋ፣ ፈጣሪውን የካደ ሰው ይማራልን? ›› አላት፡፡ እመቤታችንም ‹‹በስሜ የተጠማውን ውኃ አጥጥቶ የለምን?›› ብላ ስምዖንን (በላዔ ሰብእን) አስምራዋለች፡፡ ነፍሱንም መላእክተ ብርሃን መጥተው ወደ ገነት አስገብተዋታል፡፡

ሁለተኛው ተአምር ደግሞ ከብሮ ከኖረ በኋላ ለድህነት በተጋለጠ አንድ ምእመን ላይ የተደረገ ነው ፤ ከክርስቲያን ወገን የኾነ ሀብት አግኝቶ ያጣ አንድ ሰው ነበር፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን ‹‹ ከብሬ በኖርኹበት አገር ተዋርጄ አልኖርም ›› ብሎ ጓዙን ጠቅልሎ ከአገሩ ወጥቶ ሲሔድ ሰይጣን ያዘነ ሰው መስሎ ደንጊያውን በምትሐት ወርቅ አስመስሎ ‹‹ ሥላሴን ፣ ጻድቃንን ፣ ሰማዕታትንን ፣ መላእክትን ካድልኝና ይህን ወርቅ እሰጥሃለሁ ›› አለው፡፡ ዅሉንም ካደለትና ወርቁን ተቀብሎ ዞር ሲል ‹‹ ምእመናን የሚመኩባት ድንግል ማርያም ‹ የአምላክ እናት አይደለችም› ብለህ ካድልኝ ›› አለው፡፡

ሰወየውም ‹‹ እርሷንስ አልክድም ›› ስላው በደንጊያ ቀጥቅጦ ገደለው፡፡ መላእክተ ጽልመት የሟቹን ነፍስ ሊወስዱ ሲሉ መላእክተ ብርሃንም አብረው ቀረቡ፡፡ እመቤታችንም ጌታችንን ‹‹ ልጄ ይህችን ነፍስ ማርልኝ?›› አለችው፡፡ እርሱም ‹‹ከልብኑ ይትመሐር እምየ፤ እናቴ፣ ውሻ ይማራልን?›› አላት፡፡ እመቤታችንም፡- ‹‹‹ ስምሽን የጠራውን፣ መታሰቢያሽን ያደረገውን እምርልሻለሁ › ያልኸው ቃል ይታበላልን? ›› አለችው፡፡ በዚህ ጊዜ ‹‹ምሬልሻለሁ›› አላት፡፡

እግዚአብሔር አምላካችን ‹‹ ከመረጥኳቸው ጋር ቃል ኪዳን አደረግሁ ›› ባለው መሠረት ከቅዱሳን ጋር ያደረጋቸው ቃል ኪዳኖች ብዙዎች ናቸው፡፡ ከእነዚህም መካከል ከላይ በተአምራቱ እንደተመለከትነው አንዱ ለእመቤታችን የሰጠው የአማላጅነት ኪዳን ነው፡፡ ማማለድ ማለት ስለሌላው መጸለይ፣ መለመን ፣ የደረሰውን ችግር እንዲወገድ ማድረግ ፣ ማስማር ( ይቅርታ ማሰጠት ) ማለት ነው፡፡

በዚሁ መሠረት ከእግዚአብሔር በታች ከቅዱሳን ዅሉ በላይ ከፍ ከፍ ያለችና የከበረች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከእግዚአብሔር በተሰጣት የማማለድ ሥልጣን ‹‹ ሰአሊ ለነ ቅድስት ፤ ቅድስት ሆይ ለምኚልን ›› እያሉ ለሚለምኗት ዅሉ ከእግዚአብሔር እያማለደችና እየለመነች ምሕረትን እንደምታሰጥ ቀናውንና የተመሰገነውን ሃይማኖት የምንከተል ምእመናን ዅሉ እናምናለን፡፡ ምክንያቱም ቅድስት ድንግል ማርያም የእግዚአብሔር እናትና አገልጋይ እንደመኾኗ ከዅሉም ቅዱሳን በበለጠ ለእግዚአብሔር ቅርብ ናትና፡፡ በእግዚአብሔር ዘንድም ኾነ በሰው ዘንድ ባለሟልነትን ማግኘት ወይም ቅርብ መኾን ደግሞ አንድን ጉዳይ በቀላሉ ለማስፈጸም ይጠቅማል፡፡ ለምሳሌ፡-

👉 መልአኩ ቅዱስ ገብርአል በእግዚአብሔር ፊት የሚቆም ባለሟል በመኾኑ የድኅነትን ምሥጢር አብሣሪ ኾኗል /ሉቃ. ፩፥፲፱-፳፮/፡፡
👉 አስቴር የንጉሡ አርጤክስስ ሚስት በመኾኗ በወገኖቿ አይሁድ የታወጀውን የሞት አዋጅ አስለውጣለች /መጽሐፈ አስቴር ፫፥፲/፡፡
👉 ነቢዩ ሙሴ በእግዚአብሔር ፊት ባለሟል በመኾኑ ‹‹ይህንን ኀጢአታቸውን ይቅር በላቸው፤ ያለዚያ ግን እኔን ከጻፍከው መጽሐፍህ እባክህ ደምስሰኝ?›› በማለት ለእስራኤላውያን ምሕረትን አሰጥቷል /ዘፀ.፴፪፥፲፬/፡፡

16/02/2022

"ወዳጄ ሆይ! እግዚአብሔር ነዳያንን የሚልክልህ መስጠትን እንድትለማመድ ነው፡፡ ዛሬ በነዳያኑ አድሮ የሚለምንህ ለኋለኛይቱ ቀን ስንቅ እንዲያስቀምጥልህ ወድዶ ነው፡፡"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

14/02/2022

ነነዌ ከእነግሳንግሷ ዛሬ በእያንዳንዳችን ሰውነት ተገንብታለች። ስለኾነም ብርቱ ጾምና ጸሎት ያስፈልገናል።

ቫለንታይን የሚባለው ምስቅልቅል አንዱ ነነዌያዊ ገጽታችን ኾኗል። ያሳዝናል። የእኛ አይጥመን የሌላ ስንቀላውጥ ወዛችን እየጠፋ ሔደ።

ጾማችንን የንስሐ ያድርግልን!

Photos from በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ስም የተቋቋመ የአባኮራን ወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበር's post 13/02/2022

እንኳን ለጾመ ነነዌ አደረሰን

ስለ ጾሙ አጭር ማስገንዘቢያ እንሆ፡- ይህ ጾም በነቢዩ ዮናስ ተመክረው የነነዌ ሰዎች እና በእነርሱ ዘንድ ያሉ እንስሳትም.... ሳይቀሩ ከምግብ የተከለከሉበት ( የጾሙት) ጾም ነው፡፡ (ት.ዮና ምዕ.3)

- እንደ ዓቢይ ጾም ሰኞ ዕለትን አይለቅም ለ3 ዕለታት የሚጾም ነው።

- ይህ ጾም የሚጀመርበት መደበኛ ዕለት የለውም፡፡ ነገር ግን በጣም ወረደ ከተባለ ከጥር 17 በታች አይወርድም በጣም ወጣ ከተባለም ከየካቲት 21 አያልፍም በእነዚህ 35 ዕለታት ውስጥ እየተመለላሰ ይደርሳል፡፡

- የዘንድሮ 2014 ዓ/ም ጾመ ነነዌ ነገ የካታቲ 7 ይጀምራል። ጾሙን ጾመን መንፈሳዊ ፍሬያችንን ለማበርከት ያብቃን፡፡

✍️ አምኃ ሥላሴ / መኩሪያ ተስፋዬ

09/02/2022

እንኳን ለታላቁ ገዳማዊ አባ ጳውሊ እና ለጻድቁ አባ ለንጊኖስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

ታላቁ ቅዱስ ጳውሊ

††† በቤተ ክርስቲያን አስተምሕሮ "ታላቁ /ዐቢይ/ THE GREAT" የሚል ስም የሚሰጣቸው አባቶች የተለዩ ናቸው። አንድም እጅግ ብዙ ትሩፋቶችን የሠሩ ናቸው። በሌላ በኩል ደግሞ በተመሳሳይ ስም ከሚጠሩ ሌሎች ቅዱሳን እንለይበታለን።

ገዳማዊ ሕይወት ጥንቱ ብሉይ ኪዳን ነው። በቀዳሚነትም በደብር ቅዱስ አካባቢ ይኖሩ የነበሩ ደቂቀ ሴት እንደ ጀመሩት ይታመናል። ሕይወቱ በጐላ በተረዳ መንገድ የታየው ግን በታላቁ ጻድቅ ሄኖክ ከዚያም በቅዱሱ ካህን መልከ ጼዴቅ አማካኝነት ነው።

ቀጥሎም እነ ቅዱስ ኤልያስ ነቢይ እነ ኤልሳዕ ደቀ መዝሙሩ ኑረውበታል። በሐዲስ ኪዳን ደግሞ ሙሉ ሕይወቱን በገዳም (በበርሃ) ያሳለፈው መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ቅድሚያውን ይይዛል።

ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና መድኃኒታችን ክርስቶስ በገዳመ ቆረንቶስ ለአርባ ቀናት በትሕርምት ኑሮ ገዳማዊ ሕይወትን ቀድሷል፤ አስተምሯል። በዘመነ ስብከቱም ያድርባት የነበረችው የደብረ ዘይቷ በዓቱ (ኤሌዎን ዋሻ) በራሷ ለዚህ ሕይወት ትልቅ ማሳያ ናት።

ከጌታ ዕርገት በኋላም ክርስቲያኖቹ የዓለም ሁካታ ሲሰለቻቸው አንድም በንጹሕና በተሸከፈ ልቡና ለፈጣሪያቸው መገዛትን ሲሹ ከከተማ ወጣ እያሉ ይኖሩ እንደ ነበር የታሪክ መዛግብት ያሳያሉ። አኗኗራቸውም በቡድንም በነጠላም ሊሆን ይችላል። ዋናው ነገር ግን በጾምና በጸሎት መትጋታቸው ነው። ይህም ሲያያዝ እስከ ሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ደረሰ። በዚህ ዘመን ግን አባ ጳውሊ የሚባል ንጹሕ ክርስቲያን ይህንን ሕይወት ወደ ሌላ ደረጃ ከፍ አደረገው። ለሰማንያ ዓመታት ሰው ሳያይ ተጋድሎ "የባሕታውያን አባት" ተባለ። ደንብ ያለው ተባሕትዎም ጀመረ።

ይህ ከሆነ ከሃያ ዓመታት በኋላ ደግሞ አባ እንጦንስ የሚባሉ ደግ ክርስቲያን ይህንን ገዳማዊ ሕይወት በሌላ መንገድ አጣፈጡት። በቅዱስ ሚካኤል አመንኳሽነት ገዳማዊ ሕይወት በምንኩስና ተቃኘ። ስለዚህም አባ እንጦንስ የመነኮሳት አባት ተባሉ።

እርሳቸውም ሕይወቱን ለማስፋፋት ከተለያዩ አሕጉር ደቀ መዛሙርትን እየተቀበሉ አመንኩሰዋል። ቅዱሳን የአባ እንጦንስ ልጆችም ወደየ ሃገራቸው ተመልሰው ሕይወቱን በተግባር አሳይተው ገዳማዊነትን አስፋፍተዋል።

አንድ ቀን ቅዱስ እንጦንስ (የመነኮሳት ሁሉ አባት) እንዲህ ሲል አሰበ። "በውኑ በበርሃ ለበርካታ ዘመናት በመኖር ከእኔ የሚቀድም (የሚበልጥ) ሰው ይኖር ይሆን?" ይህንን ሃሳቡን ገና ሳይጨርሰው ቅዱስ ሚካኤል ወደ እርሱ ዘንድ ደረሰ።

"እንጦንስ ሆይ! ከእኔ የሚቀድም የበርሃ ሰው ይኖር ይሆን ብለህ አስበሃል። በእርግጥም ከአንተ ሃያ ዓመታትን ቀድሞ ወደ በርሃ የገባ፣ በቅድስናው ፈጣሪውን ያስደሰተ፣ ዓለም ከነ ክብሯ የእግሩን መረገጫ ያህል እንኳ የማትመጥነው በጸሎቱና በምልጇው ዓለም የምትጠበቅለት ሞገስን የተሞላ አንድ ሰው በበርሃ ስላለ ሒድና ተመልከተው።" ብሎት ተሠወረው።

ቅዱስ እንጦንስም ከሰማው ነገር የተነሳ እየተደነቀ ተነሳ። እርሱ ካለበት በርሃ በራቀ መንገድም ለቀናት ተጉዞ አንድ በዓት (ዋሻ) በር ላይ ደረሰ። በበሩ አካባቢ የሰውና የአራዊት ኮቴ ተመልክቶ በሩን ጸፋ (ቆፈቆፈ)። በውስጥ ያለው አረጋዊ ሰው ግን ትልቅ ድንጋይ ገልብጦ በሩን አጠበቀው። ለሰማንያ ዓመታት ሰውን አይቶ አያውቅምና ሰይጣን ሊያታልለኝ መጥቷል ብሎ አስቧል። ቅዱስ እንጦንስ ግን "ኃሠሥኩ እርከብ ጐድጐድኩ ይትረኃው ሊተ - ሽቻለሁና ላግኝ፤ ደጅ መትቻለሁና ይከፈትልኝ።" ሲል አሰምቶ ተናገረ።

ቅዱሱ ገዳማዊም ሰው መሆኑን ሲያውቅ በሩን ከፈተለትና ወደ ዋሻው አስገባው። መንፈሳዊ ሰላምታንም ተለዋወጡ። ሲመሽም ቅዱስ እንጦንስ ሽማግሌውን ገዳማዊ "ስምህ ማን ነው?" ቢለው "ስሜን ካላወክ ለምን መጣህ?" ሲል መለሰለት።

ያን ጊዜ ቅዱስ እንጦንስ ቀና ብሎ ሰማይን ሲመለከት ምሥጢር ተገለጠለትና "ቅዱስ ጳውሊ ሆይ! ከአንተ ጋር ያገናኘኝ ፈጣሪ ይክበር፤ ይመስገን።" ሲል ፈጣሪውን ባረከ። ቅዱስ ጳውሊም መልሶ (በጸጋ አውቆት) "አባ እንጦንስ ሆይ! እንኳን ደህና መጣህ።" አለው። ሁለቱም ደስ ብሏቸው ፈጣሪያቸውን እያመሰገኑ ተጨዋወቱ።

ቤተ ክርስቲያን ለሁሉም ዓይነት የቅድስና ሕይወት የመጀመሪያ የምትላቸው አላት። ለምሳሌ፦
የመጀመሪያው ሐዋርያ ቅዱስ እንድርያስ፣ የመጀመሪያው ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ፣ የመጀመሪያው ባሕታዊ (ገዳማዊ) ቅዱስ ጳውሊ እና የመጀመሪያው መነኮስ ቅዱስ እንጦንስን ማንሳት እንችላለን።

ቅዱስ ጳውሊ የተወለደው በሰሜናዊ ግብጽ በእስክንድርያ ከተማ ሲሆን ዘመኑም ሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ነው። ወላጆቹ ባለጸጐች ነበሩ። ቅዱሱንና ታላቅ ወንድሙን አባ ጴጥሮስን ወልደዋል። ሁለቱ ክርስቲያን ወንድማማቾች ገና ወጣት ሳሉ ወላጆቻቸው ሞቱባቸው። ሃዘናቸውን ፈጽመው ሃብት ሲካፈሉ ግን መስማማት አልቻሉም።

ምክንያቱ ደግሞ ትልቁ ጴጥሮስ ደህና ደህናውን እቃ ወስዶ መናኛ መናኛውን ለትንሹ ለጳውሎስ (ጳውሊ) መስጠቱ ነበር። ስለዚህ ነገር ተካሰው ወደ ፍርድ ቤት ሲሔዱ ግን መንገድ ላይ አንድ ባለጸጋ ሙቶ ደረሱ።

ቆመው ሳሉም ቅዱስ መልአክ ሰው መስሎ ጳውሊን "ይህ ሰው ባለጸጋ ነው። በገንዘቡ የሰጠውን ፈጣሪ ሲበድልበት ኑሮ እነሆ ተሸኘ። በሰማይም አስጨናቂ ፍርድ ይጠብቀዋል።" ሲል ነገረው።

በዚያች ቅጽበት የወጣቱ ጳውሊ ሐሳብ ተለወጠ። ወደ ወንድሙ ተመልሶ "ወንድሜ ሆይ! ሁሉ ንብረት ያንተ ይሁን።" ብሎት ከአካባቢው ጠፋ። በመቃብር ሥፍራ ለሦስት ቀናት ያለ ምግብ ጸልዮ የእግዚአብሔር መልአክ ሰው ወደ ማይደርስበት በርሃ ወሰደው።

በዚያም ምንጭ ፈለቀችለት። እየጾመ ይጸልይ ይሰግድ ገባ። ሁሌ ማታ ግማሽ ሕብስት ከሰማይ እየወረደለት ቅዳሜና እሑድ መላእክት እያቆረቡት ለሰማንያ ዓመታት ኖረ። (አንዳንድ ምንጮች ግን ለዘጠና ዓመታት ይላሉ።) ከቅዱስ እንጦንስ ጋር የተገናኙትም ከዚህ በኋላ ነው።

ከቅዱስ እንጦንስ ጋር በነበራቸው የሁለት ቀናት ቆይታም ቅዱስ ጳውሊ ብዙ ትንቢቶችን ተናግሯል። በዚህች ቀን ሲያርፍም መቃብሩን አናብስቱ ቆፍረዋል። ቅዱስ እንጦንስም በክብር ቀብሮታል። ለሰማንያ ዓመታት የለበሳት የዘንባባ ልብሱም ሙት አስነስታለች።

ጻድቅ፣ ቡሩክ፣ ቀዳሚው ገዳማዊ፣ መላእክትን የመሰለና የባሕታውያን ሁሉ አባት ለተባለ ለቅዱስ ጳውሊ ክብር ይገባል!

ዝክረ ቅዱሳን
💚 💚
💛 💛
❤️ ❤️

08/02/2022

የማያቋርጥ ጸሎት ማለት ሁለንተናችሁን ለእርሱ በመስጠት ራሳችሁን ከእግዚአብሔር ጋር አንድ ማድረግ ማለት ነው፥በዚህ ጊዜ ሕይወታችሁ ሁሉ የማያቋርጥ ጸሎት ይሆናል።
ታላቁ_ቅዱስ_ባስልዮስ

04/02/2022

✥✥✥ ንጉሥ የተንከባከበው ባሪያ ✥✥✥
እንደ ሥርዓቱ ንጉሥ ይመጣል በተባለ ጊዜ የሚያርፍበትን ቦታ በማጽዳት ምንጣፎችን በማንጠፍ በማስጌጥ እንስሶችን ለማረድና መብል መጠጥ በማዘጋጀት ኣበባዎችን ፍራፍሬዎችን በማቅረብ ሁሉንም እንደሚፈልገው በማድረግ መልካም ኣቀባበል በማድረግ ተደላ ደስታ እንዲያገኝ ይሆናል።
እግዚኣብሔር ግን ንጉሥ ሆኖ ሳለ ባሪያውን ኣዳምን ሳይፈጥረው በፊት ስድስት ቀን ሙሉ ምግቡን፣ ቦታውን ፣ የሚገዛውን ሁሉ ካዘጋጀለት በኋላ በኣርኣያውና በምሳሌው ሰውን መፍጠሩ ይደንቃል ለሰው የተደረገውን ኣስተዋላችሁን !!!?
ይህን ያደረገለት ለምን ይመስላችኋል ኣዳም በዚህ ምድር የእግዚኣብሔር መንግሥት ምሳሌ ስለሆነ ነው ሁሉን ቢገዛ እንጂ ገዢ የለበትም።
እጅጉን ዕፁብ ዕፀብ ብለን የተደነቅነው ግን ይህን ያህል በጌታው ክብር የተሰጠው ባሪያ ጌታውን በበደለ ጊዜ የሆነለት ነው ! እንደልማዱ ባሪያዎች የጌታቸውን መንግሥት ለማስጠበቅ ብለው ሕይወታቸውን ለንጉሣቸው ኣሳልፈው ይሰጣሉ ጌታችን ግን ለበደለው ባሪያ ለመስቀል ሞት ደርሶ ሕይወቱን በመስጠቱ ይህንን ፍቅር እና እንክብካቤ ከጌታው ያገኘ ባሪያ ሆነ!!!
የእርሱ ባሪያዎች የሆንን እኛ ኣዳማውያን ስላደረገልን ሁሉ ለቸሩ ጌታችን ምን እንከፍለው ይሆን!!!? ዛሬም ዕለት ዕለት እርሱን የምንበድለው ሆኖ ሳለ ምህረቱን ከባሪያዎቹ ያልከለከለ ጌታ የተመሰገነ ይሁን!!!

✍️ አምኃ ሥላሴ / መኩሪያ

03/02/2022

💒 💒
"የኖኅ መርከብ የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ናት፡፡ ሆኖም ቤተ ክርስቲያን ከኖኅ መርከብ እጅግ ትለያለች፡፡ ወደ መርከቡ የገባ ዶሮ ሲወጣም ዶሮ ነው፡፡ ተኩላውም ከመርከቡ ሲወጣ ተኩላ ነው፡፡ ከቤተ ክርስቲያን ግን ዶሮ ገብቶ ርግብ ሆኖ ይወጣል፡፡ ተኩላውም በግ ሆኖ ይወጣል፡፡ ቤተ ክርስቲያን ኃጢአተኞችን ተቀብላ ጻድቃን አድርጋ የምታወጣ መርከብ ናት።’’
/ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ/

✍️ አምኃ ሥላሴ / መኩሪያ ተሰፋዬ

01/02/2022

🕛🕛24🕛🕛
🔔🔔ዜና ቅዱሳን🔔🔔
🍒አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን ዘኢትዮጵያ🍒
🙏🙏እንኳን ለአባታችን ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት ወርሀዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ🙏🙏
🌕ልደት🌕
=>መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ: ጸጋ ዘአብ ካህኑና እግዚእ ኃረያ ናቸው:: እርሱ በክህነቱ: እርሷ በደግነቷ: በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ ፍሬን ሰጥቷቸዋል::
+በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ ቢደርስባቸው ቅዱስ ሚካኤል: ጸጋ ዘአብን ከሞት: እግዚእ ኃረያን ከትድምርተ አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል:: በሁዋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል::
+ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የጸነሱት መጋቢት 24 ቀን በ1206 ዓ/ም ሲሆን የተወለዱት ደግሞ ታሕሳስ24 ቀን በ1207 ዓ/ም ነው:: በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል:: ቤታቸውም በበረከት ሞልቷል::
🌕ዕድገት🌕
=>የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው "ፍሥሃ ጽዮን" ይሰኛል:: ይሕንን ስም ይዘው: አባታቸው ጸጋ ዘአብን ተከትለው አድገዋል:: በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን (ብሉያት: ሐዲሳትን) ተምረዋል:: በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል:: ዲቁናም ከወቅቱ ዻዻስ አባ ጌርሎስ ተቀብለዋል::
🌕መጠራት🌕
=>አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮስ ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ ተሰማ:: የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክት እያመሰገኑ በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ::
+የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ:: "ከዛሬ ጀምሮ ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን:: ከዚህ በሁዋላ አራዊትን ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ:: ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ በግርማ ዐረገ:: ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በሁዋላ ሰዓትን አላጠፉም:: ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ::
🌕አገልግሎት🌕
=>ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል አገልግሎትን ጀመሩ:: በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ (ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው አጠመቁ:: ያን ጊዜ ኢትዮዽያ 2 መልክ ነበራት::
+1ኛ ዮዲት (ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል: ወይም በባዕድ አምልኮ ተጠምዷል::
+2ኛው ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር::
+ግማሹ ሃገር በጨለመበት ወቅት የደረሱት ሐዲስ ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ:: ሕዝቡን: መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን (ጠንቁዋዮችን) አጥፍተዋል::
🌕ገዳማዊ ሕይወት🌕
=>ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል:: እርሳቸው ከሁሉ የተሻሉ ሳሉም በ3 ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል::
+እነዚህም በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ለ12 ዓመታት: በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ ገዳም ለ7 ዓመታት: በደብረ ዳሞ ከአቡነ ዮሐኒ ጋር ለ7 ዓመታት: በአጠቃላይ ለ26 ዓመታት አገልግለዋል::
+በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ በሁዋላም ወደ ምድረ ሽዋ (ዞረሬ) ተመልሰው በአንዲት በዓት ውስጥ ለ22 ዓመታት ቆመው ጸልየዋል:: በተሰበረ እግራቸውም 6 ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል::
🌕ስድስት ክንፍ🌕
=>ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት መካናት ተባርከዋል:: ጻድቁ ምድረ እሥራኤል የገቡት በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ ነበር::
+የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሚካኤል ጋርም ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል:: ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ በሁዋላ ነው:: ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ እንባቸው ይፈስ ነበር::
+ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም:: በገሃድ:-
-በቤተ መቅደስ ብስራቱን
-በቤተ ልሔም ልደቱን
-በቤተ ዮሴፍ ግዝረቱን
-በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን
-በቤተ አልዓዛር ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር::
+የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል ወደ ሆነው ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ::
በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ እመቤታችን ድንግል ማርያም ፈጥና ደርሳ ተክልየን ወደ ሰማይ አሳረገቻቸው::
+በዚያም:-
-የብርሃን ዐይን ተቀብለው
-6 ክንፍ አብቅለው
-የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው
-ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው
-ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም ተደምረው
-ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው
-"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል::
🌕ተአምራት🌕
=>የተክልየ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው::
*ሙት አንስተዋል
*ድውያንን ፈውሰዋል
*አጋንንትን አሳደዋል
*እሳትን ጨብጠዋል
*በክንፍ በረዋል
*ደመናን ዙፋን አድርገዋል::
+ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን መሥርተዋል:: በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት አብረው ኑረዋል:: በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና::
🌕ዕረፍት🌕
=>ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው: እልፍ አእላፍ ፍሬን አፍርተው: በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው ነሐሴ 24 ቀን በ1306 ዓ/ም ዐርፈዋል:: ጌታ: ድንግል ማርያምና ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል:: 10 ትውልድ የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል::
:-ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ
🙏የአቡነ ተክለ ሃይማኖት በረከታቸው ይደርብን፤ጸሎታቸው ይጠብቀን፤ለመንግሥተ ሰማይ መሪ በትር ይሁነን፤ድካማቸው ከጠላት እጅ ያድነን፣የትዕግሥታቸው ሀይል ከእሳት ባሕር ያድነን🙏

Photos from በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ስም የተቋቋመ የአባኮራን ወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበር's post 30/01/2022

በዓለ ሲመቱ ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል
ጥር 22 ቀን 2014 ዓ.ም
ፎቶ © Abraham Tesfamariam
እንዲህ በደጁ እንደሰበሰበን : በሰማያዊ መንግስቱ ለመሰብሰብ የሊቀመልአኩ የቅዱስ ዑራኤል ረድኤትና በረከት ፣ ምልጃና ተራዳኢነቱ ለዘወትር አይለየን። አሜን

Photos from በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ስም የተቋቋመ የአባኮራን ወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበር's post 29/01/2022

ሞትማ ለሚሞት ሰው ይገባዋል የማርያም ሞት ግን በጣም ያስገርማል።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

ጥር 21 ቀን የሚከበረው የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የእረፍት በዓል በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስና መካነ ጎልጎታ ቅድስት ማርያም ቤ/ክ የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ገነት መዝገቡ ላቀው ፣ መልአከ ብርሃን አይነኩሉ ታደሰ (የቦሌ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ) ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ብዙ ምእመናን በተገኙበት የቃል ኪዳኑ ታቦታት ወደ ጸበል ስፍራ በመሄድ የአስተርእዮ በዓል በድምቀት ተከብሯል ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በረከት ረድኤት አምላከ ቅዱሳን ያሳትፈን

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

Photos from በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ስም የተቋቋመ የአባኮራን ወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበር's post 29/01/2022

እልልልልልልልልል…………ዛሬ ልዩ ነበር ዳግማዊ ጥምቀት !
የወልደ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ እና የመካነ ጎልጎታ ቅድስት ማርያም ታቦታት የጸበል ቦታዉን ወርደዉ ባርከዋል ዳግማዊ ጥምቀት (21/5/2014)

Photos from በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ስም የተቋቋመ የአባኮራን ወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበር's post 28/01/2022

✥✥✥ ማርያም ሞተኪ ይመስል ከብካበ ✥✥✥

" ድንግሊቱ የባህርይ ሞት እንጂ የኣዳምን ሞት ኣልተቀበለችም "
የፍጥረታት ሁሉ ባለቤት የሆነው ኣምላካችን የቅርብ ኣገልጋዮቹ ከሆኑ ከሰማያውያን ከኪሩቤልና ከሱራፌል ይልቅ የመወደድና የመከበር ጸጋን ኣድሏታል ምክንያቱም የነሳው የእርሷን እንጂ የእነርሱን ሥጋ ኣይደለምና። (ዕብ 2፥12 )
ወላድያነ ሰብእ ከሆኑ ከምድራውያን ፍጥረታትም ወላዲተ ኣምላክ በመሆን የተለየች " ከፍጡራን በላይ ከፈጣሪ በታች " ናትና የልዕልናዋ መሠረትም ይህ ነው ::
ይሁን እንጂ ሰው በመሆን የሰውነትን ሥራ ሁሉ መፈጸም ስላለ ወደ ላይኛው ሕይወት መሸጋገሪያ በሞት በኩል በትንሳኤ ስለሆነ " ሞትን ተቀብላለች " ። በዚህም ‹‹ለመለኮት ማደርያ ለመኾን የበቃችው ' ኃይል ኣርያማዊት ' ብትኾን ነው እንጂ ምድራዊት ሴትማ እንደምን ሰማይና ምድር የማይችለውን ልትሸከመው ይቻላታል?›› በማለት ሰው መሆንዋን
ለሚጠራጠሩ '' ሰው መሆንዋን " ተገልጧል።

👉 ፈጣሪ ኣዳምን ‹‹ዕፀ በለስን በበላህ ጊዜ የሞት ሞትን ትሞታለህ›› ያለውን ዘንግቶ ዕፀ በለስንም በልቶ የመጣበትን ሞት ድንግሊቱ የሞተች ኣይደለችም እርስዋስ የኣዳምን (የበደልን) ሞት ሳይሆን የተፈጥሮ ሞትን ተቀብላለች፡፡ የባህርይ ሞት የምንለው የሰው ልጅ ሲፈጠር ሞት እንዲሰለጥንበት ሆኖ ባይፈጠርም ሞት ግን ለባህርይው የሚስማማው ሆኖት ነው የተፈጠረው ::

- ለምሳሌ መላእክት ለባህርያቸው ሞት አይሰማማቸውም ሰው ግን ምንም እንኳን እንዲሞት ባይፈጠርም (ሞት ባይሠለጥንበትም) ሞት ግን ለባህርያው ይስማማው ነበር ስንል ለዚህ ማረጋገጫ የሚሆነው ሳጥናኤል እና አዳም የበደሉት በደል አንድ ሆኖ ሳለ ነገር ግን ሰይጣን አዳም ያገኘውን ዓይነት የሥጋ ሞት አላገኘውም ለምን በሉ ሳጥናኤል (በአጠቃላይ መላእክት ሁሉ) ለባህሪያቸው ሞት የማይስማማቸው በመሆኑ ነው።

ስለዚህ ከበደል በፊት ለባህርይው ይስማማው የነበረው ሞት ግን ኣልሰለጠነበትም ነበር ሕግን ተላልፎ ዕፀ በለስን በበላ ጊዜ ሞት የሚሰለጥንበት ሆነ ድንግሊቱ ግን ሕግን በመተላላፍ በኣዳም በኩል የመጣውን ‹‹የሞት ሞትን ትሞታለህ›› የተባለው መርገም ስላልደረሰባት የበደል ሞትን ሳይሆን የባህርይን ሞትን ተቀብላለች «ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የዓጽብ ለኲሉ -ሞት ለሚሞት /ለሟች/ ይገባል የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል» (ቅዱስ ያሬድ)

- ለዚህም ነው የድንግል ማርያም ዕረፍት በመላአክት ምሥጋና በዳዊት ዝማሬ የታጀበ ስለነበር ሊቁ ይህንን ለመግለጽ "ማርያም ሞተኪ ይመስል ከብካበ" ማርያም ሆይ ዕለተ ዕረፍትሽ ደስታ የበዛበት ሠርግን ይመስላል አለ።

- ይህ ቢሆንም እስከ ዕለተ-ምጽአት ድረስ ግን በመቃብር እንድትጠብቀው ኣላደረጋትም እነአልዓዛር በተነሱበት ትንሳኤ ሳይሆን እንደልጅዋም ባለ ትንሣኤ በክብር እንድነትነሳና እንድታርግ ኣደረጋት ይህም የእግዚኣብሔር ድንቅ ሥራ ነውና በዚህም የእናቱን ክብር ገለጠ ፡፡ ( መዝ 131፡8 )
የእመቤታችን በረከቷ ፣ልመናዋና ጸሎቷ ከሁላችንም ጋር ይሁን ኣሜን !

✍️ አምኃ ሥላሴ / መኩሪያ ተሰፋዬ

22/01/2022

🕛🕛ጥር 14🕛🕛
🔔🔔ዜና ቅዱሳን🔔🔔
🍒ቅዱስ ባስሊቆስ ሰማዕት🍒
"" አባቶቼና ወንድሞቼ ሆይ በክርስቶስ ሃይማኖት ጽኑ አትስነፉ.."
🌿ቅዱስ ባስሊቆስ ለጣዖት አልሰግድም በማለቱ እስር ቤት ስለመታሰሩ
🌿ቅዱስ ባስሊቆስ ሰማዕትነትን ከመቀበሉ በፊት ቤተሰቦቹን አግኝቶ ስለመሰናበቱ
🌿መኮንኖቹ ቅዱስ ባስሊቆስን "ለጦኖስ" ከሚባል ደረቅ ግንድ ጋር አስረውት፣ያ የታሰረበት ደረቅ ግንድ እንደለመለመ
🌿ቅዱስ ባስሊቆስ በጸሎቱ ጣዖታትን እንዳጠፋና መሬት እንደተንቀጠቀጠች
🌿ቅዱስ ባስሊቆስ አንገቱን በሰይፍ እንደተቆረጠ
🌿ቅዱስ ባስሊቆስ ያስገደለው መኮንኑ አግዲጢስ በታመመ ጊዜ ቅዱስ ባስሊቆስ የተቀበረበትን አፈር ተቀብቶ እንደዳነ
🙏የሰማዕቱ የቅዱስ ባስሊቆስ ቃልኪዳንና ጸሎት አማላጅነትና፣ረድኤት ከሁላችን ጋር ይሁን🙏

20/01/2022

በዛሬው ዕለት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ ከቅድስት ድንግል ማርያምና ከሐዋርያቱ ጋር የገሊላ ክፍል በሆነችው በቃና በሰርግ ቤት ተገኝቶ ውሃውን ወይን ጠጅ ያደረገበት ነው። ሰርግ ደግሶ የነበረው ዶኪማስ አዘጋጅቶት የነበረው ወይን ጠጅ አልቆ በተጨነቀ ጊዜ ችግሩን ቀርቦ ሳይነግራት ማለቁን አውቃ ልጄ ሆይ ወይን ጠጅ እኮ አልቆባቸዋል በማለት ተናግራ ውሃው ወደ ወይን ጠጅ እንዲለወጥ የማማለድ ተግባር የፈጸመችበት ዕለት ነው።

አምላካችን ጋብቻ ክቡር መሆኑን ዓለም እንዲረዳ ያደረገበት፣ ሰዎች ያዘጋጁት ነገር ተንጠፍጥፎ አልቆ በተጨነቁ ጊዜ እመቤታችን ለልጇ አሳስባ ጎደሏቸው እንዲሞላ ፣ጭንቀታቸው እንዲወገድ የምታደርግበት በዓል ነው።

ጥንቱ ዕለቱ የካቲት 23 ቀን ቢሆንም ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን የውሃን በዓል ከውሃ በዓል ጋር ማክበር ይገባል ብለው የሚጠጡት አልቆባቸው ተጨንቀው የነበሩበት ቃና ዘገሊላ የውሃ በዓል በመሆኑ ከውሃ በዓል ከሆነውና የእዳ ደብዳቤያችን ከተደመሰሰበት ከጥምቀት ጋር እንዲከበር በማድረጋቸው በዛሬው ዕለት እናከብረዋለን።

ዛሬ የዶኪማስ ጭንቀት ብቻ ሳይሆን በጋብቻ ምክንያት የሚከሠት የክርስቲያኖች ሁሉ ጭንቀት የተቃለልበት ዕለት ነው። እመቤታችን ዶኪማስ ሳይለምናት ጭንቀቱን እንዳቃለለችለት ለልጅሽ አሳስቢልን ብለን ብንማጸናት የማይፈጸምልን ነገር፣ የማይወገድልን ጭንቀት አለመሆኑን የተረዳበት ዕለት ነው። በዓሉን ማክበር የሚገባንም ይህን እያሰብን ነው። አምላካችን ከበዓሉ በረከት ይክፈለን።

💚 💛 ❤️

20/01/2022

እንኳን ለቅዱስ ሚካዔል ወርሀዊ ክብረ በዓል እንዲሁም ለቃና ዘገሊላ የጥምቀት ማግስት በሰላም በጤና አደረሳችሁ! ቅዱስ ሚካዔል ይጠብቃችሁ ።

ለከረሞ አንዳችንም ሳንጎደል በሰላም በጤና ሰው ይበለን! አሜን!

Photos from በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ስም የተቋቋመ የአባኮራን ወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበር's post 18/01/2022

ጥር 10 ታቦተ ቅዱስ ዮሐንስ ነጎድጓድን አጅበን ወደ ባሕረ ጥምቀት ጉዞ እያደረግን። እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ። ጌታችን፣ መድኀኒታችን፣ አምላካችን፣ አባታችን፣ ብርሃናችን፣ ፀሐያችን፣ ሕይወታችን፣ እረኛችን፣ የሕይወት እንጀራችን፣ የሕይወት መጠጣችን፣ ንጉሣችን፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ እንወድሃለን እናመሰግንሃለን። የዘመናት አስገኝ ንጉሠ ነገሥት ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ለዓመቱ አድርሰን።

18/01/2022

ጥምቀት ሃይማኖታዊ በዓል ነው።

ታቦታት ከመንበረ ክብራቸው ወደ ባሕረ ጥምቀቱ ለምን ይወርዳሉ? 17/01/2022

1- ታቦታት ከመንበረ ክብራቸው ለምን ወደ ባሕረ ጥምቀቱ ይወርዳሉ?
2- ታቦታት ከባህረ ጥምቀቱ እንደደረሱ ሥርዓተ ጥምቀቱ ለምን አይፈጸምም ?
3 - ለጥምቀቱ የሚሆን ውኃ ለምን ይከተራል?

ለእነዚህ ጥያቄዎች መልስ ያገኙበታል ከሥር Link ተጨነው ይመልከቱ

https://youtu.be/U95Hnlw851M

ታቦታት ከመንበረ ክብራቸው ወደ ባሕረ ጥምቀቱ ለምን ይወርዳሉ?

17/01/2022

📖📖ዜና ገዳማት📖📖
📕ማዕቍዲ ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ📕
☀የቤተ መቅደሱ ውስጠኛው ክፍል ግድግዳው በተአምራት የሚያበራው የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ፍልፍል ዋሻ ቤተ መቅደስ☀
🚍🚍ትግራይ፣ማዕቍዲ ገርዓልታ🚍🚍

16/01/2022

🕛🕛8🕛🕛
🔔🔔ዜና ቅዱሳን🔔🔔
🍒ቅዱስ ማትያስ ሐዋርያ🍒
🌿ቅዱስ ማትያስ በዛ በሚያስተምርበት ሀገር እንደ ታሰረ
🌿ጌታችን ቅዱስ ማትያስን ይፈታው ዘንድ ቅዱስ እንድርያስን እንደላከው
🌿ጌታችን ለቅዱስ እንድርያስ በመርከብ መሪ(Captain) አምሳል እንደተገለጠለት ወደ ቅዱስ ማትያስ እንዳደረሰው
🌿በመርከቡ ላይ ጌታችን ከቅዱስ እንድርያስ ጋር ያደረገው ንግግር
🌿ቅዱስ እንድርያስ ቅዱስ ማትያስንና ሌሎች ታስረው የነበሩትን ከእስር ቤት ነጻ እንዳወጣቸው
🙏የሐዋርያው የቅዱስ ማትያስ ጸሎት አማላጅነትና፣ረድኤት ከሁላችን ጋር ይሁን🙏

16/01/2022

🕛🕛8🕛🕛
🔔🔔ዜና ቅዱሳን🔔🔔
🍒አባ ኪሮስ🍒
❇ለአባ ስምዖንና ለአባ ባውማ ጌታችን እንደተገለጠላቸው
❇አባ ባውማ የአባታችን የአባ ኪሮስን ገድል እንደጻፈ
❇ጌታችን የአባታችንን የፊቱን ላበት በነጭ ሀር እንደጠረገለት
❇...የምሻ እመቤታችን ድንግል ማርያምን አያት ዘንድ ነው...
❇ለአባታችን ለአባ ኪሮስ ንጉሥ ዳዊት ተገልጦለት በገናን እንደረደረለት
❇የአባታችን ነፍሱ ከሥጋው እንደተለየችና በክብር በምስጋና ጌታችን ነፍሱን በእጁ እንደተቀበላት
❇ እግዚአብሔርን ስለሚፈራ ስለ አንድ ሰውና አባ ኪሮስ ስላደረገለት ተአምር
🙏🙏የገዳማውያን መነኮሳት መመኪያቸው የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት፤የአባታችን የአባ ኪሮስ ጸሎትና በረከት፤የቅዱሳኑ የአባ ባውማና የአባ በብኑዳ፣የአባ ሲኖዳና የአባ ለትጹን፣የአባ ሚሳኤል ጸሎት የአበው የነቢያት የሐዋርያት የሰማዕታትና የጻድቃን በረከት የቅዱሳን መላእክት ረድኤት ከሁላችን ጋር ይሁን🙏🙏

Photos from በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ስም የተቋቋመ የአባኮራን ወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበር's post 16/01/2022

🕝8🕝
🔥ዜና ቅዱሳን🔥
🌟🌟አቡነ ተክለ አልፋ ዘዲማ🌟🌟
🌿እንኳን ለአባታችን አቡነ ተክለ አልፋ ወርሀዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ🌿
👉አቡነ ተክለ አልፋ
🌟በአሥራ አራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በኢትዮጵያ የተነሱ፣
🌟ደብረ ድማሕን/ዲማን (ጎጃም) የመሠረቱ፣
🌟በፍጹም ተጋድሎ የኖሩ፣
🌟ምድረ ጎጃምን በስብከተ ወንጌል ያበሩ፣
🌟በሊቅነታቸው የተመሠከረላቸው፣
🌟መልክአ ኢየሱስን እንደደረሱ የሚነገርላቸው፣
🌟ብዙ ተአምራትን የሠሩ (ዛሬም ድረስ የሚሠሩ)ና የሃገራችን ትምክህት የሆኑ ታላቅ ሐዋርያዊ አባት ናቸው።
🙏በአባታችን አቡነ ተክለ አልፋ ጸሎት የሚገኝ በረከት ሁላችንንና ሀገራችን ኢትዮጵያን ይጠብቅ🙏

15/01/2022

⏱⏱ጥር 7🕝🕝
📖📖ዜና ቅዱሳን📖📖
📕📕አጋዕዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ📕
☀እንኳን ለአጋዕዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ☀
⭐አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስም አሉ:-⭐⭐





{{ዜና ሥላሴ ዘጥር}}
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
ልጁን ለላከ ለአብ ምስጋና ይገባል
ለተላከ ወልድም ምስጋና ይገባል
ማኅየዊ ለሚሆን መንፈስ ቅዱስም ምስጋና ይገባል።
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿

🙏🙏የአብ የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ በረከታቸውና ይቅርታቸው በሁላችን ይኑር አሜን🙏🙏

14/01/2022

ግዝረት ከጌታችን ከመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዘጠኙ ንዑሳን በዓላት አንዱ ነው፡፡ እነዚህ ንዑሳን በዓላት የሚባሉትም ስብከት፣ ብርሃን፣ ኖላዊ፣ ግዝረት፣ ቃና ዘገሊላ፣ ልደተ ስምዖን፣ ደብረ ዘይት፣ የመጋቢት መስቀልና መስቀል ናቸው፡፡ ነቢያት ይወርዳል፤ ይወለዳል ብለው በትንቢት ይጠባበቁት የነበረው መሲሕ የዓለም ብርሃን፣ የነፍሳት ጠባቂ መሆኑን አምነን የምናከብራቸው ስብከት፣ ብርሃንና ኖላዊ ይባላሉ፡፡

ከእናቱና ከደቀመዛሙርቱ ጋር በሰርግ ቤት የተገኙበት ቃና ዘገሊላ፣ በአርባ ቀኑ ወደ ቤተ መቅደስ የገባበትና አረጋዊ ስምዖንን የሰላሳ ዓመት ጎልማሳ የሆነበት “ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ ዐይኖቼ ማዳንህን አይተዋልና” በማለት የተናገረበት ልደተ ስምዖን ከንዑሳን በዓላት ይመደባሉ፡፡ የዚህ ጽሑፍ ትኩረት ግዝረት በመሆኑ ሀተታዬን ወደ እሱ እመልሳለሁ፡፡

ፍቅር ወልድን ከዙፋኑ ስቦት ወርዶ ሥጋ ማርያምን ተዋሕዶ፣ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን ማሕፀኗን ዓለም አድርጎ ከቆየ በኋላ ታኅሣሥ ሃያ ዘጠኝ በዘመነ ማቴዎስ ተወለደ፡፡ በተወለደ በስምንተኛ ቀኑ ሥርዓተ ኦሪትን ሊፈጽም ተገረዘ፡፡ ግዝረትን በስምንተኛው ቀን መፈጸሙ፣ በተወለደ በአርባ ቀኑ ወደ ቤተ መቅደስ መሔዱ ሕገ ኦሪትን ሊያጸና፣ ሊፈጽም፣ ምሳሌውን በአማናዊው ሊተካ እንጂ ኦሪትን ሊሽር ላለመምጣቱ እማኝ ምስክር ነው፡፡ የተሻረ ነገር መታሰቢያ የለውም የተፈጸመ፣ በምሳሌና በትዕምርታዊነት የተወከለ ግን ጥንተ ታሪኩን፣ ትንቢቱን ጠይቀን ምሳሌውን ከትርጓሜ መጻሕፍት እንረዳለን፡፡

ግዝረት አይሁድ የአብርሃም ልጅ መሆናቸውን ማረጋገጫ ማኅተም ነው፡፡ በሕግና በሥርዐት የሚመሩ መሆናቸውን አንድ አምላክ ማመናቸውን የገለጡበት ነው፡፡ አይሁድ በግዝረት የአብርሃም ልጅነታቸውን እንዳረጋገጡ፣ ክርስቲያኖችም በጥምቀት የሥላሴ( ልጅነታቸውን ያረጋግጣሉ፡፡ ይህም የሚሆነው ግዝረት የጥምቀት ምሳሌ መሆኑን ያስረዳል፡፡ በሐዲስ ኪዳን ጥምቀት እንጂ መገረዝ፣ አለመገረዝ አይጠቅምም፡፡ በሐዲስ ኪዳን ግዝረት በፍቃድ እንጂ እንደ አይሁድ እኛም የአብርሃም ልጆች እንድንባል የምንገረዝ አይደለም፡፡

ለእኛ ለክርስቲያኖች ከሥላሴ በመንፈስ ቅዱስ መወለድ እንጂ መገረዝ የአብርሃም ልጆች አያሰኘንም፡፡ አለመገረዝ እንደማይጠቅም ቢያውቅም ጌታችን መገረዝ ያስፈለገው ሕገ ኦሪትን ለመፈጸም ሲሆን በእኔ ግን ምስጢረ ጥምቀትን ፈጽሜ አድናችኋለሁ ሲለን( ነው፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ የማይጠቅምና ለነገረ ድኅነት የማያበቃ ነገር ቢያጋጥመን እንኳ በጥበብና በማስተዋል እንድናደርገው ሲያስተምረን ነው፡፡ ሥርዐተ ኦሪታችንን ስላፈረሰብን ለሞት አበቃነው ብለው ምክንያት እንዳያገኙና ይህንን ስበብ አድርገው ከነገረ ድኅነት ተለይተው እንዳይቀሩ የሚያደርጉትን በማድረግ፣ የሚወዱትን በመውደድና አብሯቸው የሥርዐታቸው ተካፋይ በመሆን በፍቅር ስቦ ወደ አማናዊው ድኅነት፣ ወደ ጥምቀትና የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ወደማመን መልሷቸዋል፡፡

የመምህሩን አሰረፍኖት የሚከተለው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በደርቤን በሚያስተምርበት ወቅት ጢሞቴዎስ( ሲከተለው መገረዝ አለመገረዝ ጥቅምም ጉዳትም እንደሌለው እያወቀ የገዘረው( በዙሪያው ብዙ አይሁድ ስለነበሩ እነርሱን ላለማስከፋትና ላለማስደንበር መሆኑን ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ “.. የኦሪት ሕግ ለማዳን ብቁ አለመሆኗን እየደጋገመ በድፍረት ይሰብክ የነበረው መምህረ አሕዛብ ቅዱስ ጳውሎስ እንኳ አይሁድን( ላለማስደንበር ሲል ሥርዐተ ኦሪትን ይፈጽም ነበር፡፡” /1978፣ 29/ በማለት ገልጸዋል፡፡

ግዝረት ለእስራኤል ከአብርሃም ለመወለዳቸው ምልክት ብቻ ሳይሆን የአብርሃምን ሃይማኖት ለመያዛቸውም መታወቂያ ነበረች፡፡ ጌታችንም ምንም እንኳ የባሕርይ አምላክ ቢሆን በሥጋ( የአብርሃም ልጅ ነውና የአብርሃም ልጅነቱን የአብርሃምን ሃይማኖት ማጽናቱን ለማስረገጥ ግዝረትን ፈጸመ፡፡

አንድም በግዝረት ደም ይፈስሳለና አብርሃም በዘጠና ዘጠኝ ዓመቱ በመገረዝና ደሙን በማፍሰስ አበ ሰማዕታት ተብሏልና ግዝረት የሰማዕትነት ምሳሌም ነው፡፡

ጥር ስድስት በሚነበበው ስንክሳር እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አረጋዊ ዮሴፍን ሕፃኑን የሚገርዝ ባለሙያ ፈልጎ እንዲያመጣ እንደነገረችው፣ አረጋዊውም ባለሙያውን ፈልጎ እንዳመጣ ይናገራል፡፡ ባለሙያውም ሕፃንን በደምብ ያዙልኝ ብሎ ለመግረዝ ሲሰናዳ ባለሙያ ሆይ ደሜ ሳይፈስ መግረዝ ትችላለህን ብሎ እንደጠየቀው፣ ከስቅለቱ በፊት ደሙ እንደማይፈስ እንዳስተማረው፣ በዚህም ምክንያት ለመግረዝ የመጣው ባለሙያ፣ አምላክ ወልደ አምላክ መሆኑን አምኖ እንደሰገደለት ለመግረዣ ያዘጋጀው ምላጭም እሳት ላይ እንደተጣደ ቅቤ መቅለጡን ይተርካል፡፡

በመቀጠልም ክርስቶስ ዘር ምክንያት ሳይሆነው እንደተፀነሰ፣ ማኅተመ ድንግልናዋን ሳይለውጥ እንደተወለደ እንደ ነቢዩ ሕዝቅኤል “ሳይከፈት ገብቶ ሳይከፍት እንደወጣ” ስለት ምክንያት ሳይሆነው፣ በግዝረት ምክንያት ደም ሳይፈስ በተአምራት ተገረዘ፡፡

በአጠቃላይ ግዝረት በኦሪት የአብርሃም ልጅነትን፣ የአብርሃምን ሃይማኖት መያዝን ማረጋጋጫ ማኅተም ሲሆን በሐዲስ ኪዳን በጥምቀት ተተክቷል፡፡ ለአማናዊው ግዝረት /ለጥምቀት/ ምሳሌ በመሆኑም በሥራ የአብርሃም ልጅነትን፣ በእምነት የሥላሴ ልጅነትን አግኝተንበታል፡፡ ወርደህ ተወልደህ፣ በነፍስ በሥጋ፣ ከተቆራኘን ባለጋራ አድነን ብለን የተጣራነው ተሰመቶ፣ ሥርዓተ ኦሪትን ፈጽሞ ወደ ሥርዓተ ሐዲስ የሚያሸጋግረን መሆኑን ያመንበት፣ በጥምቀቱ ቦታ በዮርዳኖስ የተቀበረው የባርነታችን ደብደቤ የሚቀደድ መሆኑን በምሳሌ ያወቅንበት ግዝረት ነው፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
💚 💛 ❤️

Photos from በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ስም የተቋቋመ የአባኮራን ወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበር's post 13/01/2022

በወንጌላዊዉ ቅዱስ ዮሐንስ ዐመታዊ ክብረ በዓል ዕለቱን 700 ነዳያንና 100 የአቤት ሆስፒታል ታማሚዎችን በማብላት አሳልፈናል።

በረከቱ በሁላችንም ይደርብን!

Photos from ፍቁረ እግዚእ ሚዲያ Fikure Egzi Media  FEM's post 13/01/2022
Want your organization to be the top-listed Non Profit Organization in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Videos (show all)

እልልልልልልልልል…………ዛሬ  ልዩ ነበር ዳግማዊ ጥምቀት !የወልደ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ እና የመካነ ጎልጎታ ቅድስት ማርያም ታቦታት የጸበል ቦታዉን ወርደዉ ባርከዋል ዳግማዊ ጥምቀት (23/5...
እልልልልልልልልል…………ዛሬ  ልዩ ነበር ዳግማዊ ጥምቀት !የወልደ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ እና የመካነ ጎልጎታ ቅድስት ማርያም ታቦታት የጸበል ቦታዉን ወርደዉ ባርከዋል ዳግማዊ ጥምቀት (23/5...

Telephone

Website

Address

Addis Ababa
55554
Other Charity Organizations in Addis Ababa (show all)
imagine1day imagine1day
2Q3W+XV2 Imagine1day, Gabon Street
Addis Ababa, 1000

Educating people to transform themselves, their communities, and the world.

ናድቢስ ትዉልድ ናድቢስ ትዉልድ
Adiss Abeba
Addis Ababa

Organization for Welfare & Development in Action - OWDA Organization for Welfare & Development in Action - OWDA
Meskel Square , Lion Building , 9th Floor
Addis Ababa, 1502A.A

OWDA is a charity organization that Promotes conditions of sustainable human development through implementing programs on basic service delivery, economic opportunities, livelihood...

Women and Children Empowerment Organization-WCEO Women and Children Empowerment Organization-WCEO
Addis Ababa. Ethiopia
Addis Ababa

WCEO is Charity Society Organization (CSOs) founded to engage in empowering the community particularly women and children through designing different interventions that create econ...

Jaldu Page Jaldu Page
Addis Ababa, ###X

This page is where Jaldu Woreda people will share their ideas, views and discuss on what ever agendas raised

Relief Organization for South Sudan Addis Ababa, Ethiopia Relief Organization for South Sudan Addis Ababa, Ethiopia
Addis Ababa

To coordinate humanitarian assistance to save lives, restore dignity through psycho-socio rehabilita

waldah qurana waldah qurana
Addis Ababa, 1000

الجمعية الخيرية لخدمة القرآن في إثيوبيا �

ኑስራ የበጎ አድራጎት ድርጅት/ Nusra Charitable organization ኑስራ የበጎ አድራጎት ድርጅት/ Nusra Charitable organization
Mesalemia
Addis Ababa

በበጎነት ማህበረሰቡን እናብቃ!!

Spiritan Community Outreach Ethiopia - SCORE Spiritan Community Outreach Ethiopia - SCORE
SCORE A. A Office
Addis Ababa

We are part of 3000 Spiritans working in over 57 countries. We have been Serving in Ethiopia since 1972. We minister in areas for which the Church has difficulty in finding workers...

Abdellah Ibnu Umi Mekhtum-አብደላህ ኢብኑ ኡሚ መኽቱም Abdellah Ibnu Umi Mekhtum-አብደላህ ኢብኑ ኡሚ መኽቱም
Around 6kilo
Addis Ababa

Abdellah Ibnu Umi Mektum Qur’an Association is a certified religious non-governmental organization