የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/

Wolaita ethiopia

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 01/03/2024

በወላይታ ሶዶ ከተማ 79 ኪ.ሜ የመካከለኛ እና 80 ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመር መዘርጋቱንና 4 ሺህ 772 የኮንክሪት ምሰሶዎች ተከላ መከናወኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ

የ6ቱ ከተሞች መልሶ ግንባታና አቅም ማሳደግ ፕሮጀክት 87 በመቶ ማጠናቀቁን ገልጸዋል።

ተቋማችን በዲስትረቡሽን መስመሮች እርጅና ምክንያት በከተሞች አካባቢ የሚስተዋለውን የኃይል መቆራረጥና መዋዥቅ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት መጠነ ሰፊ የዲስትሪቡሽን መስመሮች መልሶ ግንባታና አቅም ማሳደግ ስራዎች እያከናወነ ይገኛል፡፡

ከእነዚህም መካከል በወላይታ ሶዶ፣ በሐረር፣ በሻሸመኔ፣ በደብረማርቆስ፣ በጎንደር እና በኮምቦልቻ ከተሞች እየተከናወነ የሚገኘው የ6ቱ ከተሞች መልሶ ግንባታና አቅም ማሳደግ ፕሮጀክት 87 በመቶ ተጠናቋል፡፡

በሐረር ከተማ 28 ኪ.ሜ የመካከለኛ እና 40.75 ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመር ተዘርግቷል፤ 3 ሺህ 549 የመካከለኛ እና የዝቅተኛ መስመር ተሸካሚ የኮንክሪት ምሰሶዎች ተተክለዋል፡፡

በወላይታ ሶዶ ከተማ 79.20 ኪ.ሜ የመካከለኛ እና 80.66 ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመር ተዘርግቷል፤ 4 ሺህ 772 የኮንክሪት ምሰሶዎች ተከላ ተከናውኗል፡፡

በፕሮጀክቱ በሻሸመኔ ከተማ 5 ሺህ 666 የኮንክሪት ምሰሶዎች በመትከል 76 ኪ.ሜ የመካከለኛ እና 46.17 ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመር ለመዘርጋት ተችሏል፡፡

በተመሳሳይ በደብረማርቆስ ከተማ 3 ሺህ 550 የኮንክሪት ምሰሶዎችን በመትከል 28.52 ኪ.ሜ የመካከለኛ መስመር የተዘረጋ ቢሆንም የዝቅተኛ መስመር ስራ አልተጀመረም፡፡

እንዲሁም በጎንደር ከተማ ለፕሮጀክቱ ከሚያስፈልገው አጠቃላይ 6 ሺህ 278 ምሰሶዎች ውስጥ 5 ሺህ 095 ምሰሶዎች ተተክለዋል፤በዚህም 65 ኪ.ሜ የመካከለኛ እና 29.45 ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመር ተዘርግቷል፡፡

በአንፃሩ በኮምቦልቻ ከተማ የመካከለኛ እና የዝቅተኛ መስመር ዝርጋታ ያልተጀመረ ቢሆንም፤ 190 የመካከለኛና የዝቅተኛ መስመር ተሸካሚ የኮንክሪት ምሰሶዎች ተተክለዋል፡፡

ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ከከተሞቹ እድገት ጋር ተያይዞ ይስተዋል የነበረውን የኃይል መቆራረጥና መዋዥቅ ችግር በዘላቂነት ይፈታል ተብሎ ይታመናል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 01/03/2024

በወላይታ ዞን በ2016 ምርት ዘመን በአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ 76 ሺህ 973 ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ

#ላሾቄራ ፤ የካቲት 22/2013 በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን በ2016 ምርት ዘመን በአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ 76 ሺህ 973 ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑ የዞኑ ግብርና መምሪያ ገለጸ፡፡

በአፈርና ውሃ ጥበቃ የስነ-አካላዊ ስራ በሁሉም የዞኑ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ከጥር 27/2016 ዓ/ም ጀምሮ ለተከታታይ 30 ቀናት በተመረጡ 361 ንዑስ ተፋሰሶች ላይ በህብረተሰብ ንቅናቄ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ መስራት እንደተጀመረ የዞኑ ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊና የተፈጥሮ ሀብት ዘርፍ ኃላፊ አቶ መስፍን መድኔ ተናግረዋል፡፡

ባለፉት 20 ቀናት ውስጥም በአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 90 በመቶ የሚሆነውን ማልማት እንደተቻለ ምክትል መምሪያ ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡

ሁሉም አርሶ አደሮች የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራን በጥሩ ተነሳሽነት እየሠሩ እና ተፋሰሶችን እየተንከባከቡ ያገኙትን ጥቅም በመረዳት ለንቅናቄ ስራው ፈቃደኛ በመሆን ወደ ስራ ገብተዋለል፡፡ እስከ አሁን ድረስም በስራ ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡

የአፈር ለምነትን በመጠበቅ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በለሙ ተፋሰሶች ላይ ወጣቶች ተደራጅተው ንብ በማነብ እንዲሁም እንስሳት በማድለብ ስራ ላይ ተሰማርተው እንደሚገኙ አቶ መስፍን አብራርተዋል፡፡

በዞኑ አሁንና ከዚህ በፊት የተሰሩ የተፋሰስ ልማት ስራዎችን በሥነ-ሕይዎታዊ ዘዴ ለማጠናከር ችግኞችን የማዘጋጀት ስራ በትኩረ እየተሰራ እንደሚገኝ አቶ መስፍን ገልፀዋል።

በወላይታ ዞን ሶዶ ዙሪያ ወረዳ ደልቦ ወገኔ ቀበሌ ነዋሪና የዘይሴ ንዑስ ተፋሰስ አርሶ አደሮች በበኩላቸው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ መሥራታቸው በእርሻ መሬታቸው ላይ የአፈር ለምነት እንዲጨምር በማድረግ ምርትና ምርታማነታቸው እንዲያድግ ማድረጉን ተናግረዋል።

የተፈጥሮ ሃብት ሥራ በተሠሩ ቦታዎች ላይ ከሰብል ልማት፣ ከአትክልት እና ፍራፍሬ በተጨማሪ የእንስሳት መኖ በማልማት ተጠቃሚ መሆናቸውንም አርሶ አደሮቹ አስረድተዋል።

የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ከመስራታቸው በፊት የእርሻ መሬታቸው የተራቆተና በአካባቢያቸውም የጎርፍ አደጋ በተደጋጋሚ ያጠቃቸው እንደነበር የገለፁት አርሶ አደሮቹ አሁን ላይ ግን በተሠራው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ የሚታይ ለውጥ መምጣቱን ገልፀዋል።

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 01/03/2024

ቀበሌያትን በ18ቱ የጤና ኤክስቴንሽን ፓኬጅ ሞዴል በማድረግ ህብረተሰቡን የጤና አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ

#ላሾቄራ ፣ ካቲት /2016 ዓ.ም በወላይታ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ ከዞን ጤና መምሪያ የመጡ ከፍተኛ ኤክስፔርት ባለሙያዎች (Verification team) ተዘዋውረው ምልከታ በማድረጉ የአድስ ዋሙራ ቦሮኮሽ ቀበሌ ሞዴል መሆን የሚያስችል ውጤት ማግኘቱ ተረጋግጧል።

ከዞን ጤና መምሪያ የመጡ ከፍተኛ ኤክስፔርት ባለሙያዎች በግብረ መልሳቸዉም በጤና ኬላ፣ በልማት ቡድን በተቋማትና በቀበሌ የተሰሩ ስራዎች በእጅጉ እንዳስደሰታቸውና ይህ የተሰራዉ ስራ ለሌሎች ተሞክሮ የምሆን ተግባር እንደሆነ ተጠቁመዋል።

ቀበሌያትን በ18ቱ የጤና ኤክስቴንሽን ፓኬጅ ሞዴል በማድረግ ህብረተሰቡን የጤና አገልግሎት ተጠቃሚ የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።

ማጣሪያ(Verification) የተደረገው በ18ቱ ጤና ኤክስቴንሽን ፓኬጆች አፈጻጸም መሠረት ስሆን በማህበረሰብ ደረጃ፤ በትምህርት ቤቶች፤ በሃይማኖት ተቋማትና በጤና ኬላዎች ደረጃ መሆኑ ተገልጿል።

በሴቶች ልማት ቡዱን የሚሰሩ ተግባራቶችን እና በተቋማት ላይ የተሰሩ ሥራዎችን በቡድን ሆነው በChecklist ምልከታ ካደረጉ በኋላ አድስ ዋሙራ ቦ/ቀበሌ በ18ቱ ጤና ኤክስቴሽን ፓኬጅ ሞዴል ሆኖ ሊመረቅ እንደምችል አረጋግጠዋል።

#ዘገባው ፦የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ህዝብ ግንኙነት እና ሚዲያ ዘርፍ ነው‼️

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 29/02/2024

በወላይታ ዞን በድጉና ፋንጎ ወረዳ የተጀመረው የበጋ ስንዴ ምርት አሰባሰብ ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል።

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 29/02/2024

በካዎ ኮይሻ ወረዳ ሴቶች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የፖለቲካ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ የሚረዳ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሂዷል ።

#ላሾቄራ ፣ የካቲት 21/2016 ዓ ም በካዎ ኮይሻ ወረዳ የሴቶችን ሚዲያ ተሳትፎና አጠቃቀም ለማሳደግ የሚረዳ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሂዷል።

በመድረክ ተገኝቶ ግንዛቤ የሰጡት የካዎ ኮይሻ ወረዳ ህዝብ ግንኙነትና ማህበራዊ ሚዲያ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሞጎስ ካጮ ባስተላለፉት መልክት ሴቶች ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ ዓላማ፣ ለሠላም፣ ለልማት፣ ለዕድገት እና ለህብረብሔራዊ አንድነት በሚያጎላ መልኩ በመጠቀም የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ተጠይቋል።

የዘመኑ ቴክኖሎጂ ሁሉም ሰው በፅሁፍም ሆነ በተንቀሳቃሽ ምስል መረጃዎችን የሚያስተላልፍበትን ዕድል ስለፈጠረ ትክክለኛ መረጃዎችን ተደራሽ ለማድረግ እና የተሳሳቱትን ለማረም የማህበራዊ ሚዲያ ፕላትፎርሞችን እንደየዝንባሌአቸው በአግባቡ ሊጠቀሙባቸው እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል።

ኢትዮጵያን የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ የጀመርናቸው ውጥኖች በሁሉም መስክ ፍሬአማ እንዲሆኑ ሴቶች የድርሻቸውን እንደሚወጡ ተጠይቋል።

የካዎ ኮይሻ ወረዳ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ብሩቱካን ዳዊት እንደገለጹት ሴቶች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ያላቸውን ተሳትፎ በማሳደግ የመሪነት ሚናቸውን እንዲወጡ ለማስቻል እንዲሁም በየእርከኑ ያሉ የመንግስትና የፓርቲ ፔጆችን እንዲቀላቀሉና እንዲደግፉ ለማስቻል መሆኑን አስረድተዋል።

በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የአከባቢያችንና የተቋማችን መልካም ገፅታ ለመገንባት በሚዲያ ላይ ንቁ ተሳትፎ ማድረግ ወሳኝ በመሆኑ ሴቶች በጠንካራ ቁመና ለሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በዘርፉ ጠንክሮ መሳተፍ ያስፈልጋል ብለዋል።

የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ሊግ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሪት ተስፋነሽ ቶረጫሶ በበኩላቸው የተጠናከረ የሚዲያ እና የኮሙዩኒኬሽን ስራዎችን በአግባቡ ማከናወን በመረጃ የዳበረ ዜጋ ለመፍጠር እና ህዝቡ በልማትና በዲሞክራሲ ግንባታ ላይ ዋና ተዋናይ እንዲሆን በማስቻል ረገድ የሚዲያና የኮሙዩኒኬሽን ሚና የላቀ መሆኑ አመላክተዋል።

ሴቶች ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ ተግባር በመጠቀም ሀገርና ህዝብን ማሻገር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች ልፈጥሩ እንደሚችሉ የተገለፀ ስሆን በተለይ በዘርፉ ላይ ያለውን ትኩረት ለመሳብ በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ ክህሎትን ለማሳደግና የተሻለ ግንዛቤ ለመጨበጥ መልካም ሁኔታዎችን እንደሚፈጥር ጠቁመዋል።

29/02/2024

በዞኑ በኢንቨስትመንት ዘርፍ መዋለ ንዋይ ለማፍሰስ ለሚሹ ባለሀብቶች ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል

በዞን በኢንቨስትመንት ዘርፍ መዋለ ንዋይ ለማፍሰስ ለሚፈልጉ ባለሀብቶች ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን የወላይታ ዞን አስታወቀ፡፡

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ፎላ እንደገለጹት፤ ወላይታ ዞን ሰባት በር መወጫና መግቢያ ያለው ሲሆን ከፍተኛ የንግድ እንቅስቃሴ ያለበትም ነው፡፡

ዞኑ ከፍተኛ የንግድ እንቅስቃሴ ያለበት መሆኑ በተለይ በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ ላይ ለተሰማሩ ባለሀብቶች ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ነው ብለዋል፡፡ መንግሥት በአሁኑ ጊዜ ኢኮኖሚውን ለማሳደግ እየተጠቀመባቸው ካሉ ዘርፎች አንዱ ቱሪዝም ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው፤ በወላይታ ዞንም የቱሪዝም መዳረሻ የሆኑ እንደ ዳሞታ ተራራ፣ አጆራ ፏፏቴ፣ ጊቤ ሰው ሠራሽ ሐይቅና የተለያዩ ዋሻዎችን ጨምሮ ብዙ የቱሪስት መስህቦች የሚገኙበት አካባቢ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪም አካባቢው በመሠረተ ልማት የተሻለ በመሆኑ ለውጭም ሆነ ለሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ምቹ ሁኔታ መኖሩን ጠቁመው፤ በዞኑ ባሉ ሰባት መውጫና መግቢያ በሮች በስድስቱ ደረጃቸውን የጠበቁ የአስፋልት መንገድ እንዲሁም አንዱ መንገድ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ በጠጠር ተገነባ ነው ብለዋል፡፡

የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትን በተመለከተ ለአካባቢው ተብሎ 45 ሜጋ ዋት የቀረበ ሲሆን በዚህም የትኛውም ባለሀብት በዞኑ በየትኛውም ዘርፍ መዋለ ንዋዩን ቢያፈስ በኃይል አቀርቦት ረገድ ምንም ዓይነት ስጋት አይኖርም ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ሌላው በዞኑ በርካታ ቁጥር ያላቸው የተማረ የሰው ኃይል ያለበት ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው፤ ይህም በግሉ ዘርፍ ወደ ዞኑ መጥቶ ኢንቨስት ለማድረግ የተማረ ሰው እጥረት እንደማያጋጥመው ተናግረዋል፡፡

አቶ ሳሙኤል በዋናነት አንድ ባለሀብት ወደ አንድ አካባቢ ሄዶ ኢንቨስት ለማድረግ የሰላም ሁኔታው ወሳኝ ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡
በዚህም ዞኑ ሰላም ያለበት በመሆኑ የተለያዩ ባለሀብቶች ወደ ዞኑ በመምጣት ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎችን እንዲሁም ሌሎች የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን በመገንባት ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡

የዞኑና የከተማ አስተዳደርም በዞኑ ኢንቨስት ለማድረግ ፍላጎት ላላቸው የግል ባለሀብቶች የመሬት አቅርቦት በበቂ ሁኔታ በማመቻቸት ረገድ ሰፊ ሥራዎችን እየሠራ ይገኛል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው፤ ባለሀብቶችም ያለውን ዕድል በመጠቀም ወደ ዞኑ መጥተው ኢንቨስት እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

(ኢፕድ)

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 29/02/2024

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ፕሬዝዳንት ዊልያም ሩቶ በኬንያ ሱስዋ ናሮክ ወረዳ የሚገኘውን እና ከኢትዮጰያ በኩል ከወላይታ ሶዶ የ500 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ ኃይል መለወጫ ጣቢያ መስመር ማብቂያ የሆነውን የኬትራኮ ኮንቨርተር ስቴሽንን ጎብኝተዋል።

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 29/02/2024

የወላይታ ቴሌቪዥን ከተቋቋመበት አጭር ዕድሜ ያስቆጠረ ቢሆንም የማህበረሰቡን ባህል፣ቋንቋና ታሪክ በማስተዋወቅና የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን በማሳለጥ እየሰራ ያለውን አበረታች ተግባር አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ተናገሩ

#ላሾቄራ፤ የካቲት 20/2016የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የወላይታ ቴሌቪዥን አሁናዊ የስራ ሁኔታ ጎብኝተው ገንቢ አስተያየት ሰጥተዋል።

ወላይታ ቴሌቪዥ የወላይታን ባህል፣ ቋንቋና ታሪክ ከማስተዋወቅ አንጻር እያበረከተ ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን የጠቆሙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ይህም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።

የተቋሙን አቅም በመገንባት የሚፈለገውን መረጃ በተገቢው ለማህበረሰቡ እንዲደርስና ካለፈ ጊዜ ተቋሙ ይበልጥ እንዲጠናከር ሁለንተናዊ ድጋፍ እንደሚያፈልጋልም ተናግረዋል።

ከቴሌቪዥን ጣቢያው ጥሩ ግብአት ያገኙ እንደሆነ የጠቆሙት የምክር ቤት አባላት አሁንም ህብረተሰቡ የሚያነሳቸው የመልካም አስተዳደር ችግሮች ላይ ጣቢያው ትኩረት አድሮጎ መስራት ይጠበቅበታል ብለዋል።

ከአገልግሎት አሰጣጥ እና ከመልካም አስተዳደር ጥያቄ ጋር ተያይዞ በሕዝቡ ዘንድ ቅሬታ የሚፈጥሩ ጉዳዮች ላይ እውነታውን ፈልፍሎ በማውጣት ወደ ሕዝቡ እንዲደርስ የማድረግ ስራ ከጣቢያው የሚጠበቅ አሁናዊ ተግባር መሆኑ ተነስቷል።

የወላይታ ቴሌቪዥን ጣቢያ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሴባ ናና የወላይታ ሕዝብን የወከሉ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ያደረጉት ጉብኝት ለሥራ የሚያነሳሳ ገንቢ ሀሳብ የተገኘበት እንደሆነ ጠቁመዋል።

ተቋሙ ይበልጥ ጠንክሮ መስራት የሚጠበቅ መሆኑ የተጠቆመ ሲሆን ሕዝቡም በባለቤትነት መደገፍና ጠቃሚ መረጃን በመስጠት ለለውጥ መስራት ያስፈልጋል ተብሏል።(ወቴቪ)

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 28/02/2024

በካዎ ኮይሻ ወረዳ ለተከታታይ ሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የስድስት ወራት ፓርቲና መንግስት ሥራዎች አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ተጠናቋል ።

#ላሾቄራ ፣ የካቲት 20/2016 ዓ.ም በወላይታ ዞን በካዎ ኮይሻ ወረዳ ለተከታታይ ሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የስድስት ወራት ፓርቲና መንግስት ሥራዎች አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ተጠናቋል።

በግምገማ መድረኩ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች አፈታት ቅልጥፍና፣ የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት አሰጣጥ ፣ ህብረተሰቡን ያሳተፈ የመሠረተ ልማት ተደራሽነትና ጥራት፣ የወጣቶች ሥራ ዕድል ፈጠራ ልየታና ሥምሪት ፣ የመንግስት ከተማ መሬት አያያዝና አጠቃቀም ፣ የንግድ ሥርዓት ማዘመንና ህገ ወጥ ንግድ መከላከል በተመለከተመ ሰፊ ሀሳብና አስተየት ተሰጥቶበት በጥልቀት ተገምግሟል።

በተጨማሪም የገቢ አማራጭ መለየትና መሰብሰብ ፣ የፐብሊክ ሰርቫንት አገልገሎት አሰጣጥ መከታተል መቆጣጠር ፣ የወጣቶችና ሴቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ማሳደግ፣ የአስፈፃሚ አካላት አቋምና አቅም መፈተሽና ወቅቱ በሚፈልገው ልክ ማሰለፍ ፣ የወረዳው ፀጥታ በህዝባዊ ንቅናቄ መምራትና አስተማማኝ ከማድረግ ሰፊ ግምገማ ተካሂዷል።

በማጠቃለያው ላይ የወላይታ ዞን ውኃና ማዕድናት መምሪያ ም/ኃላፊ አቶ ታረቀኝ ባዳቾ እንደገለጹት አመራሩ አመለካከትን በማጥራትና ከተግባር ጋር በማጣመር ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ መትጋት ያስፈልጋል ተብለዋል።

አያይዘውም አመራሩ የመፍጠርና የመፍጠን ክህሎት በማዳበር ለሚያጋጥሙ ችግሮች መፍትሔ ለማበጀት ህዝቡን ወደ ምንዳ ለማሸጋገር ትኩረት ማድረግ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

የወላይታ ዞን ሥራ ዕድል ፈጠራ እና ኢንተርፕራይዞች መምሪያ ም/ኃላፊ አቶ ማቱሳል ፎሻ የተገኙ ሲሆኑ ባለፉት 6 ወራት ውስጥ በጥንካሬ ጎን የተገመሙ ሥራዎችን በማጠናከር፤ የታዩ ምርጥ ተሞክሮዎችን እንደዕድል መውስድ እና የተስተዋሉ ድክመቶችን ፈጥኖ በማረም ለኮሚሽኑ ተቆጥረው የተሰጡ ተልዕኮዎች በተሟላ አኳኃን እንዲፈፀሙ በቀጣይ ከፍተኛ ርብርብ ሊደረግ እንደሚገባ ተገምግሟል ፡፡

የአካልዊ ግምገማዉን መነሻ በማድረግ የኮሚሽኑ አመራር አካላት በኮሚሽኑ ምዘና መመሪያ መሠረት የተመዘኑ ሲሆን የምዘናው ውጤት ለቀሪ ሥራዎች የሚያነሳሳ ሊሆን እንደሚገባም አሳስበዋል ፡፡

የካዎ ኮይሻ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሕዝቅኤል ጎቶሮ በበኩላቸው ምዘናው የአመራሩን ቁመና በማስተካከል በወረዳው ለቆዩና ለተወዛዘፉ ችግሮች መፍትሄ እንዲሆን አቅም የሚፈጥር መሆኑን አብራርተዋል።

ወረዳችን አንድ ጀረጃ ከፍ ለማድረግ እያንዳንዱ ተቋማትና ግለሰቦች ለቀጣይ ጊዜ የለሽ መንፈስ ሊሰራ እንደሚገባም አሳስበዋል።

አክለውም ባሳለፍናቸው ወራት የተስተዋሉ ጉድለቶችን በማረም እና ጥንካሬዎችን በማጉላት የመንግስትንና ፓርቲ ተግባራትን ከግብ ለማድረስ መረባረብ እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል።

የፓርቲውን ራዕይ እና ዕሴት በሚገባ ተረድተው ጠንካራ ተቋማትንና አባላትን ለማፍራት አመራሩ ከወትሮ በተለየ ሁኔታ በትኩረት መስራት እንዳለበትም ጥሪ ቀርበዋል።

አመራሩ በአስተሳሰብ፣ በአመለካከትና በተግባር አንድ ሆኖ የተጀመሩ ለውጥ ሥራዎችን በማስቀጠል የህዝብ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሚገባም ተጠቁመዋል።

#ዘገባው ፦የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ህዝብ ግንኙነት እና ሚዲያ ዘርፍ ነው‼️

28/02/2024

ባለ 2 ሺህ 144 ክፍሎች ያሏት ቻይና የሰራችው 2ኛው ግዙፍ መርከብ በፈረንጆቹ 2026 ለአገልግሎት ይበቃል ተባለ

መርከቡ በአጠቃላይ 142 ሺህ ቶን ክብደት፣ ርዝመቱ 341 ሜትር፣ ስፋቱ 37 ነጥብ 2 ሜትር እና 2 ሺህ 144 ክፍሎች ያሉት በመሆኑ ከመጀመሪያው መርከብ በክብደት፣ ርዝመትና ስፋት የሚበልጥ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

#ላሾቄራ፣ የካቲት 20፣ 2016 በቻይና 2ኛው በሀገር ውስጥ የተገነባ ግዙፍ የመዝናኛ መርከብ በመገጣጠም ላይ ሲሆን በፈረንጆቹ 2026 መጨረሻ እንደሚጠናቀቅ የሻንጋይ ዋይጋኦኪዮ መርከብ ግንባታ ኩባንያ አስታውቋል።

በፈረንጆቹ 2026 መጋቢት ወር መጨረሻ ላይ ከወደብ እንደሚነሳ፣ የሙከራ ጉዞውም በፈረንጆቹ ሰኔ 2026 እንደሚጀምር ኩባንያው ገልጿል።

የመርከቧ ስም እና አቅርቦትም ዓመቱ ከመገባደዱ በፊት እንደሚከናወንም አመላክቷል።

በቻይና ለመጀመሪያ ጊዜ በሀገር ውስጥ ከተሰራው ግዙፍ የመዝናኛ መርከብ “አዶራ ማጂክ ከተማ” ጋር ሲነፃፀርም አዲሱ መርከብ በርዝመት፣ በስፋት እና በክብደት እንደሚበልጥ ተገልጿል፡፡

መርከቡ በአጠቃላይ 142 ሺህ ቶን ክብደት፣ ርዝመቱ 341 ሜትር፣ ስፋቱ 37 ነጥብ 2 ሜትር እና 2 ሺህ 144 ክፍሎች ያሉት በመሆኑ ከመጀመሪያው መርከብ በክብደት፣ ርዝመትና ስፋት የሚበልጥ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

አዲሱ መርከብ ምንም እንኳን አዶራ ማጂክ ከተማ ከተሰኘችው የመጀመሪያዋ መርከብ መጠኑ ከፍ ያለ ቢሆንም፣ አጠቃላይ የግንባታው ሰዓት ከመጀመሪያው በ20 በመቶ እንደሚቀንስ የሀገሪቱ ከፍተኛ የመርከብ አምራች ገልጿል።

መርከቡን የማስዋብ ስራ ሰኞ ዕለት መጀመሩን የገለፀው ኩባንያው፤ የዚህ ወሳኝ ምዕራፍ ምቹ ሂደት የመርከቡን አጠቃላይ የግንባታ እና የማጓጓዣ መርሃ ግብር ለማረጋገጥ መሰረት ይጥላል ማለቱን ሲጂቲኤን ዘግቧል።

አዶራ ማጂክ ከተማ የተሰኘችው የመጀመሪያዋ መርከብም ለሰባት ቀን እና ለስድስት ሌሊት ከ1 ሺህ 800 ኪሎ ሜትር በላይ የባህር ላይ ጉዞ ካከናወነ በኋላ በፈረንጆቹ ጥር ወር ላይ የመጀመሪያ የንግድ ጉዞውን ማጠናቀቁም ተመላክቷል።

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 28/02/2024

የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምን በመግራት ለበጎ ዓላማና ለህብረ-ብሔራዊ አንድነት ማዋል እንደሚገባ ተጠቆመ

#ላሾቄራ፤ የካቲት 20/2016 ዓ.ም በወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ሊግ አማካይነት በማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ዙሪያ ለሴቶች ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል።

ሴቶች አሁን ያለው ድህረ እውነት መረጃ በውል በመረዳት የነቃ የማህበራዊ ሚዲያ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ያለመ መድረክ መሆኑን ተገልጿል።

ግንዛቤ ማስጨበጫው መድረክ ሴቶች ማህበራዊ ሚዲያን በተመለከተ ያላቸውን እውቀትና ክህሎት ለማሳደግ እንደሆነም ተጠቁሟል።

የማህበራዊ ሚዲያ ድረገጾችን ሴቶች እየለዩ መጠቀም እንዳለባቸው የተመለከተ ሲሆን ሀሰተኛና የተዛቡ መረጃዎች የመመከትና የማረም ስራ መስራት እንዳለባቸውም ተመላክቷል።

ሴቶች ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ ዓላማ፣ ለሠላም፣ ለልማት፣ ለዕድገት እና ለህብረብሔራዊ አንድነት በሚያጎላ መልኩ በመጠቀም የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ተጠይቋል።

የዘመኑ ቴክኖሎጂ ሁሉም ሰው በፅሁፍም ሆነ በተንቀሳቃሽ ምስል መረጃዎችን የሚያስተላልፍበትን ዕድል ስለፈጠረ ትክክለኛ መረጃዎችን ተደራሽ ለማድረግ እና የተሳሳቱትን ለማረም የማህበራዊ ሚዲያ ፕላትፎርሞችን እንደየዝንባሌአቸው በአግባቡ ሊጠቀሙባቸው እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል።

ኢትዮጵያን የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ የጀመርናቸው ውጥኖች በሁሉም መስክ ፍሬአማ እንዲሆኑ ሴቶች የድርሻቸውን እንደሚወጡ ተጠይቋል።

በወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ሊግ መሪነት ሴቶች በማህበራዊ ሚዲያ የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ያለመ ዞናዊ የሚዲያ አጠቃቀም ላውንችግ ፕሮግራም ከነገ ጀምሮ እንደሚካሄድ የዞኑ ሴቶች ሊግ ቅ/ጽ/ቤት አስታውቋል።

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 28/02/2024

የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ሥነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት የ2016 በጀት የግማሽ ዓመት የኮሚሽኑ አመራር ግምገማና ምዘና መድረክ ተካሂዷል ።

#ላሾቄራ ፦የካቲት 20/2016 ዓ.ም የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ሥነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት የ2016 በጀት የግማሽ ዓመት የኮሚሽኑ አመራር ግምገማና ምዘና መድረክ ተካሂደዋል ።

በግምገማውና ምዘናው መድረክ ላይ የወላይታ ዞን ሥራ ዕድል ፈጠራ እና ኢንተርፕራይዞች መምሪያ ም/ኃላፊ አቶ ማቱሳል ፎሻ የተገኙ ሲሆኑ ባለፉት 6 ወራት ውስጥ በጥንካሬ ጎን የተገመሙ ሥራዎችን በማጠናከር፤ የታዩ ምርጥ ተሞክሮዎችን እንደዕድል መውስድ እና የተስተዋሉ ድክመቶችን ፈጥኖ በማረም ለኮሚሽኑ ተቆጥረው የተሰጡ ተልዕኮዎች በተሟላ አኳኃን እንዲፈፀሙ በቀጣይ ከፍተኛ ርብርብ ሊደረግ እንደሚገባ ተገምግሟል ፡፡

የአካልዊ ግምገማዉን መነሻ በማድረግ የኮሚሽኑ አመራር አካላት በኮሚሽኑ ምዘና መመሪያ መሠረት የተመዘኑ ሲሆን የምዘናው ውጤት ለቀሪ ሥራዎች የሚያነሳሳ ሊሆን እንደሚገባም አሳስበዋል ፡፡

የግምገማና ምዘና መድረክ ላይ የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ኢንስፔክሽንና ሥነ-ምግባር ኮሚሽኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በቀለ ባለቻ በጋራ መርተዋል፡፡

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 28/02/2024

የክልላችን ህዝቦች ሰላምና ልማት የተረጋገጠ እንዲሆን መንግስት በልዩ ትኩረት እየሰራ ይገኛል:- አቶ ተስፋዬ ይገዙ

#ላሾቄራ፤የካቲት 20/2016 ዓ/ም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጸጥታ ምክር ቤት ምስረታ ጉባኤ በወላይታ ሶዶ ከተማ እየተካሄደ ነው።

የክልሉን ሰላምና ጸጥታን በማጠናከር ልማትና ዕድገትን ለማፈጠን ትልቅ ድርሻ ያለው የክልሉ ጸጥታ ምክር ቤት ምስረታ ጉባኤ በወላይታ ሶዶ ከተማ በመካሄድ ይገኛል።

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የኢንተርፕራይዞች ልማትና ስራ ዕድል ፈጠራ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ይገዙ እንደገለፁት የክልሉን ሠላምና ጸጥታን በተደራጀ መልኩ በህግ አግባብ ለመምራት የጸጥታ ምክር ቤት ልዩ ፋይዳ አለው ብለዋል።

ክልሉ የሰላም የመቻቻልና የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ መንግሥት በልዩ ትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ የገለፁት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ የሚቋቋመው የጸጥታ ምክር ቤት የዚህ አካል መሆኑን አስረድተዋል።

የክልላችን ህዝቦች ሰላምና ልማት የተረጋገጠ እንዲሆን ህግ የማስከበር ስራ መጠናከር አለበት ያሉት ክቡር አቶ ተስፋዬ ይህን እውን ለማድረግ የተቀናጀ አሰራር ያስፈልጋል ነው ያሉት።

የሠላምና የጸጥታ ማስከበር ስራ በከፍተኛ መስዋዕትነት ጭምር የሚከናወን በመሆኑ አላስፈላጊ ዋጋ መክፈል እንዳይኖር ሁሉም ሠላምን ከማስከበር አኳያ የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል።

በመድረኩ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የኢንተርፕራይዞች ልማትና ስራ ዕድል ፈጠራ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ይገዙ፣ የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አለማየሁ ባዉዲ፣ በም/ል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር አበባየሁ ታደሰ፣ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና የዞን አመራሮች፣ ሌሎችም ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 27/02/2024

ላለፉት 2 ቀናት ሲካሄድ የነበረው የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ሥነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት የ2016 በጀት የግማሽ ዓመቱ የኮሚሽኑ አመራር ግምገማና ምዘና መድረክ ማጠቃለያ አግኝቷል።

#ላሾቄራ፤19/06/2016 ዓ.ም የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የኢንስቴክሽንና ሥነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት የ2016 ዓ.ም የዞኑ ኮሚሽን አመራር ግምገማና ምዘና መድረክ ተካሂዷል።

በግምገማውና ምዘናው መድረክ ላይ የዞኑ የኮሚሽን ኮሚቴ አመራር አካላት የተገኙ ሲሆን ባለፉት 6 ወራት ውስጥ በጥንካሬ ጎን የተፈፀሙ ተግባራትን በማጠናከር፤ የታዩ ምርጥ ተሞክሮዎችን በማስፋት እና የተስተዋሉ ድክመቶችን ፈጥኖ በማረም ለኮሚሽኑ ተቆጥረው የተሰጡ ተልዕኮዎች በተሟላ አኳኃን እንዲፈፀሙ በቀጣይ ከፍተኛ ርብርብ ሊደረግ እንደሚገባ በማጠቃለያው ተመላክቷል፡፡

የ6 ወሩ የኮሚሽኑ ሥራዎች ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ በዝርዝር የተገመገመ ሲሆን አፈፃፀሙን መነሻ ያደረገ የአካል ግምገማ ተደርጓል፡፡

የአካል ግምገማዉን መነሻ በማድረግ የኮሚሽኑ አመራር አካላት በኮሚሽኑ ምዘና መመሪያ መሠረት የተመዘኑ ሲሆን የምዘናው ውጤት ለቀሪ ሥራዎች የሚያነሳሳ ሊሆን እንደሚገባም ተመላክቷል፡፡

ምዘናው ከተጠናቀቀ በኋላ የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች በበተለይም በየደረጃው የሚገኘውን የኮሚሽን መዋቅር ማጠናከር፣ የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብና መመሪያዎች ሥራ ላይ መዋላቸውን መከታተል፣ የፓርቲውን የፖለቲካ ጥራት ማረጋገጥ፣ የሥነ-ምግባር ጤናማነት በፓርቲ ውስጥ የማረጋገጥ፣ በፓርቲ ውስጥ የሙስናና ብልሹ አሰራሮች ትግል እየተደረገ መሆኑን ማረጋገጥ፣ የፓርቲው አካላትና አባላት መብቶች መረጋገጣቸውን መከታተል፣ የፓርቲው ሀብቶች በአግባቡ መያዛቸውንና ሥራ ላይ መዋላቸውን መቆጣጠር፣ የአባልነት መዋጮ በትክክል ተሰብስቦ ገቢ መደረጉን መከታተል፣ በየደረጃው ከሚገኙ የፓርቲ አደረጃጀቶች ጋር ቅንጅታዊ አሰራርን ማጎልበት እና የኮሚሽኑን ”አንድ ዕቅድ፣አንድ ሪፖርት፣ አንድ ምዘና” መርህ ተግባራዊ የማድረግ ሥራዎች በቀጣይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶአቸው ሊመሩ እንደሚገባ የተቀመጡ ዋና ዋና አቅጣጫዎች ናቸው።

በመጨረሻም የወረዳና ከተማ መዋቅሮች የግምገማና ምዘና መድረክ የሚከታተሉ የዞን ኮሚሽን አመራር አካላት ሥምሪትና መድረኩ የሚመራበት አቅጣጫ ላይ ኦረንቴሽን ተሰጥቶኣቸው መድረኩ ተጠናቋል፡፡

የግምገማና ምዘና መድረኩን የወላይታ ዞን ዋና አፈጉ-ባኤና የኮሚሽኑ ሰብሳቢ ክብርት ወ/ሮ ወይንሸት ሞላ፣ የኮሚሽኑ ም/ሰብሳቢና የህ/ሥራ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ገቡ እና የዞኑ የኢንስቴክሽንና ሥነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወንድማገኝ አበራ በጋራ መርተዋል፡፡

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 27/02/2024

በወላይታ ዞን በሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደር የስድስት ወራት የመንግስትና የፓርቲ ስራዎች አፈጻጸም ግምገማ መድረክ መካሄድ ጀመረ

#ላሾቄራ፤ የካቲት 19/2016 በወላይታ ዞን በሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደር የ2016 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የመንግስትና የፓርቲ ስራዎች አፈጻጸም ግምገማ መድረክ መካሄድ ጀምሯል።

መድረኩ በዋናነት ባለፉት ስድስት ወራት የተከናወኑ የመንግስትና የፓርቲ ስራዎች ዕቅድ አፈጻጸም በመገምገምና ቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳይ ላይ አቅጣጫ ለማስቀመጥና የአመራሩን የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት በማምጣት በሥነ ምግባር፣ በክሂሎት እንዲሁም በዕውቀት የላቁ አመራሮች ለማፍራት እና የውስጠ ፖርቲ አሠራርና አደረጃጀት ለማጠናከር ያለመ ነው።

በግምገማ መድረኩ ሁሉም አመራሩ የፖርቲ ዲሰፕልን ጠብቆ በንቃት መከታተል እንዳለበት ከመድረኩ አቅጣጫ የተቀመጠ ሲሆን የግምገማ መድረኩም ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ መሆኑ ተገልጿል።

በመድረኩ የወላይታ ዞን ደጋፊ አመራር ፣ የወረዳው ፊት አመራሮች እና አጠቃላይ አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ ።

27/02/2024

የደብብ ኢትዮጵያ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት ዛሬ በበይነ መረብ ባደረገው ስብሰባ በተለያዩ ረቂቅ አዋጆችና ደንቦች ላይ በመወያየት ለክልሉ ምክር ቤት ቀርቦ እንዲፀድቅ ውሳኔ አስተላልፏል።

የመስትዳድር ምክር ቤት አባላቱ ዛሬ ባደረጉት ውይይት ክልሉ ህግን ተከትሎ ስራዎችን መስራት የሚያስችሉ 19 አዋጆችና አንድ ደንብ ላይ ውይይት በማድረግ ለሚመለከተው አካል ቀርቦ እንዲፀድቅ በሙሉ ድምፅ ወስኗል።

በተጨማሪ ምክር ቤቱ የክልሉን የ6 ወር አፈፃፀምም በመገምገም ስብሰባውን አጠናቋል።

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 27/02/2024

የዛሬ ጠዋት ውይይት ሰፊ መጠነ ርዕይ ባላቸው ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ከሶማሌ፣ አፋር፣ ሀረሪ፣ ጋምቤላ፣ ቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልሎች እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከተወጣጡ ተወካዮች ጋር ተደርጓል፡፡ ውይይታችን በልማት፣ ሰላም እና ፀጥታ ጉዳዮች ላይ ያጠነጠነ ነበር፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ( ዶ/ር )

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 27/02/2024

በወላይታ ዞን ከኦፋ ወረዳና ከገሱባ ከተማ የተወጣጡ የኅብረተሰብ ክፍሎች በልማትና በመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ዙሪያ ከክልልና ከፌዴራል የመጡ በወረዳውና በከተማው የህዝብ ተወካዮች አባላት ከወከላቸው ህብረተሰብ ጋር እየተወያዩ ይገኛሉ።

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 27/02/2024

በካዎ ኮይሻ ወረዳ"በላቀ ውጤታማነት ከእዳ ወደ ምንዳ " በሚል መሪ ሀሳብ የ2016 በጀት ዓመት የፓርቲና የመንግስት የ6ወራት የስራ አፈጻጸም ግምገማ መካሄድ ጀመረ ።

#ላሾቄራ ፦የካቲት 19/2016 ዓ.ም በወላይታ ዞን የካዎ ኮይሻ ወረዳ "በላቀ ውጤታማነት ከእዳ ወደ ምንዳ" በሚል መሪ ሀሳብ የ2016 በጀት ዓመት የፓርቲ እና የመንግስት ስራ የ6 ወር የስራ አፈፃፀም አጠቃላይ የወረዳ አመራር በተገኘበት ግምገማ ማካሄድ የጀመረ ሲሆን ግምገማው ለሦስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ መሆኑ ተገልጿል።

ግምገማው ባለፉት ስድስት ወራት በተከናወኑ የመንግስትና የፖርቲ ስራዎች ላይ እንዲሁም ተግባር ላይ ትኩረት አድረጎና ዲሲፕሊን ዙርያ እንደሚካሄድ ከመድረኩ ማብራሪያ ተሰጥተዋል።

በየደረጃው የሚስተዋሉ የአፈጻጸም ሳንካዎችን በመጠገን ለህዝባችን የገባንውን ቃል ወደ ተግባር እንዲቀይሩና ሁሉም አመራር ሥር ነቀል ለውጥ ለማምጣት በእውቀትና በጊዜ የለሽ መንፈስ መሥራት እንደሚገባ ተደምጠዋል።

በመንግሥት እና በፓርቲ ስራዎች ያሉ ጠንካራ እና ደካማ ጎኖችን በመለየት ጉድለቶች እንዲያስተካክሉ አመራሩ የትላንት ድክመቶች በማረምና አቅም በመገንባት ክፍተቶችን የሚሞላ መልኩ መድረክ እንደተካሄደ እንደሆነ ተጠቁሟል።

ህብረ-ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከርና በማፅናት ሀገርን መገንባት የሚሉ እሳቤዎችን ያነገበው መድረክ ሁሉም አመራር የተሳተፉበትና በቀጣይ አመራሩ የታዩበትን ክፍተት በማረም በዉጤት መታጀብ እንዳለባቸው ተገልጿል።

#ዘገባው ፦የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ህዝብ ግንኙነት እና ሚዲያ ዘርፍ ነው‼️

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 26/02/2024

ክልላችን የብልጽግና ተምሳሌት ማድረግ የምንችለው ያለንን ጸጋ ለይተን በማወቅና ገቢን በአግባቡ መሰብሰብ ስንችል ነው:- ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ

#ላሾቄራ፥ የካቲት 18/2016 ዓ.ም "ግንባር ቀደም ግብር ከፋይ የዘመኑ አርበኛ" በሚል መሪ ቃል በተከናወነው ክልላዊ የታክስ ሕግ ተገዢነት ንቅናቄ መድረክ ለግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች ማበረታቻና ዕውቅና የመስጠት ስነ ስርዓት ተከናውኗል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአርባ ምንጭ ከተማ በተዘጋጀው ክልላዊ የታክስ ሕግ ተገዢነት ንቅናቄ መድረክ ላይ የማጠቃለያ ንግግር ያደረጉት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ እንደተናገሩት፤

ግብርን በወቅቱ መክፈል የዜግነት ግዴታን መወጣትና ለሀገር ያለንን ፍቅር ማሳያ ነው ያሉት ክብር ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ ጥላሁን ህጋዊ የግብር ከፋይነትን በማበረታታትና ህጋዊ አሰራርን በማስፈን ግብር ለኢኮኖሚ እድገት የሚያስገኘውን ገቢ ለማሳደግ በትኩረት መስራት ያስፈልጋ ብለዋል።

መታመን ያሸልማል እንዲሁም የህልና እርካታን ያስገኛል ያሉት አቶ ጥላሁን ለዚህም ታማኝ ግብር ፋዮች የመንግስትን ለመንግስት በመስጠት ስላበረከቱት አስተዋጽኦ የክልሉ መንግሰት አድናቆት እና ምስጋናን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል።

ክልላችን የሰላም የመቻቻል እና የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ የተቀመጠው ራዕይ እውን ማድረግ የምንችለው ያለውን ጸጋ ለይተን በማወቅና ገቢን በአግባቡ መሰብሰብ ስንችል ብቻ እንደሆነም አመልክተዋል።

ይህን ዕውን ለማድረግ የግሉ ባለሀብት እና የሁሉም ግብር ከፋዮች ተሳትፎ ያስፈልጋል ያሉት ክቡር አቶ ጥላሁን የትላንት ስብራቶቻችን ጠግነን የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት ሁሉም ዜጋ የበኩሉን ድርሻ መወጣት አለበት ነው ያሉት።

በኢኮኖሚ በልጽገን የራሳችን ፍላጎት ለማሟላት ከውስጥ ገቢያችን 75 በመቶ በላይ ለመሸፈን አቅዶ እየተሰራ እንደሆነ ጠቅሰዋል።

በመድረኩ በ2015 የግብር ዘመን በተለያዩ ደረጃዎች ያሉ ግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች በክቡር ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ ጥላሁን ከበደ እና በተጋባዥ እንግዶች የዕውቅና እና የማበረታቻ ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን ግንባር ቀደም ግብር ከፋዮችም በተሰጠው ዕውቅና መደሰታቸውን ገልፀው በቀጣይም ግብርንና ታክስን በወቅቱ በመክፈል ሀገራዊ ግዴታቸውን በአግባቡ እንደሚወጡ ገልጸዋል።

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 26/02/2024

ለህዝቡ ቃል የተገቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ቀጣይነት ባለው መልክ ለመመለስ ተቀናጅተው መስራት እንደሚያስፈልግ የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ዶ/ር አሰለፈች ኩቼ ተናገሩ

#ላሾቄራ ፤የካቲት 18/2016 በወላይታ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ የህዝቡ የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ዙሪያ ከክልልና ከፌዴራል የመጡ የወረዳው የህዝብ ተወካዮች የወከላቸው ህብረተሰብ ጋር ተወያይተዋል።

የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ክብርት ዶ/ር አሰለፈች ኩቼ ለህዝቡ ቃል የተገቡ የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ቀጣይነት ባለው መልክ ለመመለስ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተቀናጅተው መንቀሳቀስ ያስፈልጋል ብለዋል።

በወረዳ ውስጥ ለህዝቡ ቃል የተገቡ በርካታ የልማትና የመልካም አሰተዳደር ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ መመለሳቸውንና እየተመለሱም መሆናቸውን ተዘዋውሮ መጎብኘቱን ጠቅሰው አሁንም ያልተመለሱ ጥያቄዎችን በዘላቂነት ለመመለስ ከሚመለከታቸው የዘርፋ አመራሮች ጋር ተቀናጅተው መንቀሳቀስ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

የወጣቶችን ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ያለው እንቅስቃሴ በጥሩ ሂደት ላይ መኖሩን የጠቀሱት ዶ/ር አሰለፈች በማህበር ተደራጅተው ለሚመጡ ወጣቶች ጽ/ቤቱ ልዩ ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በጤናው ዘርፍ እየተሰሩ ያሉ ሥራዎች ተሰፋ ሰጭ መሆናቸውን አንስተው ለህብረተሰቡ የተቀላጠፈ አገልግሎት ከመስጠት ጋር ተያይዘው ያሉ ነገሮች በደንብ መፈተሽ ይገባል ብለዋል።

የካዎ ኮይሻ ወረዳ ም/ አስተዳዳሪና ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘለቀ ዛፋ በበኩላቸው ህዝብ የሚያነሳቸው ወሳኝ የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች አቅም በፈቀደ መጠን ሁሉ እየተፈታ መምጣቱን ገልጾ በቀጣይም ያልተመለሱ ጥያቄዎች ከህዝቡ ጋር በመወያየት ተለይቶ እንደሚፈቱ አቅጣጫ ተቀምጧል ብለዋል።

እንደሀገር በትምህርት ላይ የተጀመረው የሪፎርም ሥራዎች አበረታች መሆኑን ገልጾ በዘንድሮው የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ውጤት ጋር ተያይዞ የሚነሱ ጉዳዮችን ለማሻሻል በትምህርት ሥራ ላይ እንደ ወረዳ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

የሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ በተመለከተ በተቋቋመው ግብረ ሀይል በኩል ውጤት እየመጣ መሆኑን አንስተዋል።

የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ለማሳደግ በተያዘው በጀት ዓመት ለህዝቡ ቃል በተገባው መሠረት በቁጥር 10 የውሃ ቦኖዎች በRCBD ፕሮጀክት አማካኝነት የተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።

የግብርና ዘርፍ እየተሰሩ ያሉ ነገሮች አበረታች መሆኑን ጠቅሰው ባሳለፍነው በጀት ዓመት የምርጥ ዘር እና የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት በዋናነት ተግዳሮት የሆኑ ጉዳዮች እንደሆኑ አንስተዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የካዎ ኮይሻ ወረዳ የህዝብ ተወካይ የሆኑት ወ/ሮ ሀና ጨምሮ እንደገለፁት የህዝብ ተወካዮች ከመረጣቸው ህዝብ ጋር በየጊዜው በመምከር የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ ይሰራሉ ብለዋል።

በተመሳሳይም የወረዳ ሕዝብ የሚያነሷቸውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ከመፍታት አኳያ የተጀመሩ ሥራዎች ውጤት እያስመዘገቡ ይገኛል ብለዋል።

በምክር ቤቱ አሠራር መሠረት የህዝብ ተወካዮች በዓመት ሁለት ጊዜ በየተወከሉበት ምርጫ ክልል በመሄድ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍል እና ከየአካባቢው አመራር ጋር ውይይት የሚያካሂዱ መሆኑ ይታወቃል፡፡

የመንገድ ተደራሽነት ጋር በተያያዘ የሚነሱ ችግሮችን አቅም በፈቀደ መጠን ሁሉ ለመሰራት በቀጣይም የተለዩ ቀበልያትን በትኩረት ለመደገፍ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

#ዘገባው፦የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ህዝብ ግንኙነት እና ሚዲያ ዘርፍ

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 26/02/2024

የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ከመራጩ ህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ተወያዩ

#ላሾቄራ፤የካቲት 18/2016 በወላይታ ዞን በጉኑኖ ሐሙስ ከተማ የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና የከተማ መሰረተ-ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ስብሳቢ ክብርት ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ በተገኙበት የልማትና የመልካም አስ/ር ጥያቄዎች ዙሪያ ከማህበረሰቡ ጋር ተወያይተዋል።

የዉይይት መድረኩን የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና የከተማ መሰረተ-ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ስብሳቢ ክብርት ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ፣ የከተማ ከንቲባ የተከበሩ አቶ ብርሃኑ ዋጃ እና የከተማ ምክር ቤት ዋና አፌ-ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ መዘገበች ባራታ በጋራ የመሩ ሲሆን አጠቃላይ ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ጉዳዮች ላይ በስፋት ተወያይተዋል።

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና የከተማ መሰረተ-ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ስብሳቢ ክብርት ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ በበኩላቸው ለህብረተሰቡ መልካም አስተዳደር ጥያቄ ሆኖ የቆየውን የከተማ ውስጥ ለውስጥ አስፋልት ግንባታው እየተገባደደ መሆኑንና በጠንካራ አመራር እና ብርቱ ህዝብ ጋር ያለውን አንድነቱን አመስግነዋል።

አክለውም የከተማ መሠረተ ልማት እያደገ የመጣዉን የህዝብ የመልማት ፍላጎትን መንግስት ቃል በገባዉ መሠረት በአጭር፣ በመካከለኛና በረዥም ጊዜ አቅዶ ህዝብን በሚጠቅም መልኩ እንደሚመልስ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን፣ ከዞን መንግስት ጋር አንድ በመሆን የከተማ መንግስት የመብራት፣ የውሃ፣ የስልክ መስመር እና ተነሺ ቤቶች የካሣ ክፍያ በመክፈል ከህብረተሰቡ፣ ከነጋዴዎች፣ ከተማሪዎች፣ ከተማ ዙሪያ አርሶ አደሮች ድጋፍ በማድረግ የበለጸገች ከተማ ለመፍጠር ሁሉም ድርሻቸውን እየተወጡ እንደሆነ ተናግረዋል።

በዋናነት ከተጠቀሱት አጀንዳዎች መካከል የህዝብን ሰላም በአስተማማኝ ሁኔታ በማስፈን የህብረተሰቡን የልማት እና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ፈትሾ መፍትሄ የመስጠት ጉዳይ ቀዳሚ ድርሻ እንደሚይዝ ጠቅሰዋል።

ከተማዋ የአብሮነት፣ የአንድነትና የመተሳሰብ መገለጫ የሆነችውን ከተማ እንድትሆን እነዚህን ስራዎች በማስቀጠል ለሕብረተሰቡ አመቺ ከተማ ለማድረግ እንደሚገባም አብራርተዋል።

የመንገድ ግንባታ ሂደቱን የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞን መንግስት ዕውን ለማደረግ ህብረተሰቡን በማሳተፍ አበክሮ እየሰራ እንደሆነ አረጋግጠዋል።

በተጨማሪ የወከለው ህዝብ የሚያነሳቸዉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምን እንደሆኑ የመፈተሽ እና አቅም የፈቀደውን ሁሉ በማድረግ ተራ በተራ የመመለስ ሥራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አስገንዝበዋል።

የዉይይቱ ተሳታፊዎች እንደገለፁት መንግስት የስራ አጥነት ችግር በዘላቂነት ለመፍታት አቅጣጫ ቀይሶ የህዝባችንን ሸክም ማቃለል እንዳለበትና እንድሁም በየቀኑ እየጨመረ ያለዉ የኑሮ ውድነት ችግር መፍታት እንዳለበት አንስተዋል።

በተጨማሪ ተሳታፊዎቹ በከተማችን ሁል ጊዜ እንደ መልካም አስተዳደር ጥያቄ ስነሳ የነበረው ውስጥ ለውስጥ አስፋልት ግንባታ ሥራ እየተገባደደ በመሆኑ እንዳስደሰታቸው ገልጸዋል።

በመጨረሻም ከመድረኩ የዉይይቱ ተሳታፊዎች ላነሱት ጥያቄዎች በቂ ምላሽና ማብራሪያ ከተሰጠ በኃላ መድረኩ ተጠናቋል።

በዉይይት መድረኩ ላይ የኢፌዴሪ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና የከተማ መሰረተ-ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ስብሳቢ ክብርት ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ፣ የክልል ህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል የተከበሩ አቶ ቦልጥቾ ኦ፣ የከተማ ፊት አመራሮች፣ ሀይማኖት አባቶች፣ ሀገር ሽማግሌዎች፣ ታዋቂ ሰዎች፣ የንግዱ ማህበረሰብ እና ባለድርሻዎች

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 26/02/2024

ድህነትን በማሸነፍ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ግብርና ታክስን በአግባብ መክፈል ይኖርብናል :- የፌደራል ገቢዎች ሚንስትር ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአርባ ምንጭ ከተማ በክልሉ ገቢዎች ቢሮ በተዘጋጀ ክልላዊ የታክስ ሕግ ተገዢነት ንቅናቄ መድረክ ላይ ንግግር ያደረጉት የፌደራል ገቢዎች ሚንስትር ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ እንደተናገሩት ሀገራችን ከፍተኛ የመልማት አቅም ያላት በመሆኑ ያለንን ፖቴንሺያል አሟጠን ለመጠቀም ገቢን አሟጦ መሰብሰብ ያስፈልጋል።

የግብር አሰባሰብ ስርዓት በማዘመን ለግብር አሰባብ ፈተና የሆኑ ህግ ወጥ አሰራርን ማለትም የታክስ ስወራና ማጭበርበር እንዲሁም ደረሰኝ አለመስጠት ብሎም የኮንትሮባንድ ንግድን ለመከላከል የሁሉም በቅንጅታዊ አሰራር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

አባቶች ሀገርን ከወራሪው ጠብቀው ለእኛ እንዳስረከቡት እኛም ድህነትን በማሸነፍ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ግብርና ታክስን በአግባብ መክፈል ይኖርብናል ብለዋል።

በመድረኩ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፋት የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ አለምነሽ ደመቀ እንደገለጹት በክልሉ ገቢዎች ቢሮ የተዘጋጀው ክልላዊ የታክስ ህግ ተገዥነት ንቅናቄ መድረክ ግንባር ቀደም ግብር ከፋዮችን በማበረታታትና ዕውቅና በመስጠት ህጋዊ አሰራርን ለማጠናከር ነው።

ግብርን መክፈል ለሀገር ሁለንተናዊ ዕድገትና ብልጽግና ቁልፍ ድርሻ እንዳለው የገለፁት የገቢዎች ቢሮ ኃላፊዋ ለህብረተሰቡ ቀልጣፋና ተደራሽ አገልግሎት በመስጠት ፍትሃዊ የአገልግሎት አሰጣጥ እንዲኖር ያስችላል ነው ያሉት።

ግብር ከፋዩ በታማኝነት እና በፈቃደኝነት የሚጠበቅበትን ታክስ እንዲከፍል የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ጠቅሰው በታክስ በመሰወርና በማጭበርበር ተግባር በተሰማሩት ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል።

የታክስ ህጎችን ማክበርና ማስከበር ሀገርን መውደድ እና ህዝብን ማክበር እንደሆነ የገለፁት ወ/ሮ አለምነሽ ለዚህም የንግዱ ማህበረሰብ ሆነ ሸማቹ የበኩሉን ግዴታ መወጣት አለበት ብለዋል።

በመድረኩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ እንዲሁም በክብር እንግድነት የተጋበዙ የፌደራል ገቢዎች ሚንስትር ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ፣ የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበላ ቃባቶ፣ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ባዉዲ፣ የክልሉ ዋና አፌ ጉባኤ ክብርት ጸሐይ ወራሳ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ፣ የዞኑ አመራሮች፣ የንግዱ ማህበረሰብ እና ሌሎችም ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።

26/02/2024

ሰላም የፖለቲካ መረጋጋት ከማረጋገጡም በላይ ለአዎንታዊ የህዝብ ለህዝብ ትስስር ከፍተኛ ሚና አለው፦

ኢትዮጵያ የተለያዩ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦች ፣ ህዝቦች እና ሀይማኖቶች ተዋድደውና ተከባብረው የሚኖሩባት ሀገር ናት።

ሠላም የፖለቲካ መረጋጋትን በማስፈን ውጤታማ አስተዳደር እንዲኖር እና የዴሞክራሲ ተቋማትን መመስረት ያስችላል። ለኢኮኖሚ ዕድገት ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፣ ኢንቨስትመንቶችን ይስባል፣ ለህዝቡ የስራ እድል ይፈጥራል።

በተጨማሪም ሰላም ለሰብአዊ መብቶች መከበር እና መሰረታዊ አገልግሎቶችን እንደ ትምህርት፣ ጤና አጠባበቅ እና የመሰረተ ልማት ዝርጋታ አቅርቦት ወሳኝ ነው።

ኢትዮጵያ ሰላምን በማስቀደም የውስጥ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገዶች ብቻ በመፍታት በሀገር ግንባታ ላይ በማተኮር ለዜጎቿ ብሩህ ተስፋን ለማስፈን ተግታ እየሰራች ትገኛለች።

የኢትዮጵያ ሰላም ከውስጥ ተጠቃሚነት በተጨማሪ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ጠቀሜታ አለው። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ስትራተጂካዊ ቦታ ላይ ስለመትገኝ የኢትዮጵያ ሰላም ለቀጣናችን መረጋጋት ወሳኝ ሚና አለው።

ኢትዮጵያ የድንበሯን ሰላም በማስጠበቅ ለአካባቢው ሰላምና መረጋጋት የበኩሏን አስተዋጽኦ ማድረግ ትችላለች ለዛም እየሰራች ትገኛለች።

ከዚህም በላይ ኢትዮጵያ ለሰላም የሰጠችው ቁርጠኝነት ለሌሎች ተመሳሳይ ፈተናዎች ለሚጋፈጡ ሀገሮች መነሳሳት ሆኖ የሚያገለግል ሲሆን ይህም በውይይት፣ በዕርቅና በሰብዓዊ መብቶች መከበር ግጭቶችን መፍታት እንደሚቻልና ማህበረሰቦችም ሊያድጉ እንደሚችሉ ያሳያል።

በኢትዮጵያ ያለው ሰላም የራሱን ህዝቦች ብቻ ሳይሆን የበለጠ ሰላም የሰፈነበት እና የበለፀገ አለም እንዲሰፍን አስተዋፅዖ ያደርጋል።

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 26/02/2024

በካዎ ኮይሻ ወረዳ የፌዴራል የህዝብ ተመራጮች ምክር ቤት አባላት በልማትና መልካም አሰተዳደር ጥያቄዎች ላይ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው

#ላሾቄራ ፣ የካቲት 18/2016 ዓ.ም በወላይታ ዞን በካዎ ኮይሻ ወረዳ በወረዳዊ፣ክልላዊ እና ሀገራዊ ወቅታዊ ጉዳይ እና በልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ላይ ትኩረት ያደረገው የውይይት መድረክ ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች የተወጣጡ ተወካዮች ጋር እየተካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ ላይ የካዎ ኮይሻ ወረዳ ም/አስተዳዳሪና ግብርና ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘለቀ ዛፉ በበጀት ዓመቱ ባለፉት ጊዜያት መልካም አስተዳደር የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት አፈፃፀም ሪፖርት እያቀረቡ ናቸው።

በየአካባቢው የሚነሱ ጥያቄዎችን ለሚመለከተው አካል ማድረስ ቀጣይነት ያለውና የህዝብ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ መንግስት ትኩረት ተሰጥተው እንደሚሰራ ተገልጿል።

በዉይይት መድረኩ ላይ ፌዴራል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት ዶ/ር
አሰለፈች ኩቼ፣የክልል ህዝብ ተወካይ ወ/ሮ ሀና ጩመሮ ፣የወረዳው ፊት አመራር ጨምሮ የወረዳ እና የቀበሌ አመራሮች፣ የቀበሌ የምክር ቤት አባላት፣ 3ቱም ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ ታዋቂ ሰዎች፣ ሀይማኖት አባቶች፣ ሀገር ሽማግሌዎች እና የንግዱ ማህበረሰብና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ናቸው።

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 26/02/2024

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክልላዊ የታክስ ሕግ ተገዢነት ንቅናቄ መድረክ መካሄድ ጀመረ

#ላሾቄራ፤ የካቲት 18/2016 ዓ.ም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክልላዊ የታክስ ሕግ ተገዢነት ንቅናቄ መድረክ በአርባ ምንጭ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።

የመድረኩ ዓላማ የግብር ከፋዩን ህብረተሰብ ለማበረታታትና ህጋዊ አሰራርን በማስፈን ህገ ወጥነትን ለመከላከል ነው።

በዚህም ለግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች ዕውቅና በመስጠት ማበረታታትና ለንግዱ ማህበረሰብ እንዲሁም ለሸማቹ ግንዛቤን በመፍጠር ህጋዊ አሰራር ተከትለው እንዲሰሩና ታክስ እና ግብርን በወቅቱ በመክፈል ኃላፊነታቸውን በተገቢው እንዲወጡ ለማስቻል መሆኑንም ተገልጿል።

በመድረኩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ እንዲሁም በክብር እንግድነት የተጋበዙ የፌደራል ገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ፣ የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበላ ቃባቶ፣ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ባዉዲ፣ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የዞኑ አመራሮች፣ የንግዱ ማህበረሰብ እና ሌሎችም ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ለግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች ዕውቅናና ማበረታቻ እንደሚበረከትላቸው ይጠበቃል።

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 26/02/2024

"ዲቻ እግር ኳስ ክለብ ወላይታን በተለያዩ መድረኮች በመወከል አምባሳደራችን በመሆኑ እንደአይናችን ብሌን እንጠብቀዋለን" አቶ ሳሙኤል ፎላ

#ላሾቄራ ፣ የካቲት 17/2016 የወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ልዑክ አባላት በድሬዳዋ ለሚያደርጉት ጨዋታ ሽኝት ተደረገላቸው።

በሽኝት ሥነ ሥርዓቱ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት ክቡር እንግዳ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ እና የክለቡ የበላይ ጠባቂ አቶ ሳሙኤል ፎላ ዲቻ እግር ኳስ ክለብ
ወላይታን በተለያዩ መድረኮች በመወከል አምባሳደራችን በመሆኑ እንደአይናችን ብለን እንጠብቀዋለን ብለዋል።

በጨዋታ የተገኘው ውጤት የህዝቡም ጭምር ነው ያሉት አስተዳዳሪው የዞኑ መንግስት ለጨዋታው ምቹ መደላድል ለመፍጠር የዞኑ መንግስት ከየትኛውም ጉዳይ ቅድሚያ በመስጠት የፋይናንስ ችግሮችን ለመፍታት ይሠራል ብለዋል።

"Nunaara diyage ubbaa xooniyagaa!" "(ከኛ ጋር ያለው ሁሉን አሸናፊ ነው)"መርሃችን ነው በማለት በይቻላል መንፈስ በቡድን መንፈስ ለድል እንድትጫወቱ ሲሉ ለተጫዋቾች መልዕክት አስተላልፈዋል።

የዲቻ ስፖርት ክለብ ትልቁ የኢንቨስትመንት ኢንዱስትሪ ነው ያሉት አቶ ሳሙኤል ወጣቶቻችን የሥራ ዕድል የሚያገኙበት ዘርፍ በመሆኑ በልዩ ትኩረት ይመራል ብለዋል።

የአመቱ ማጠቃለያ በውጤት እንደሚታጀብ ተስፋ አለኝ ያሉት አስተዳዳሪው ቀጣይ ዕድል የሰመረ እንዲሆን ተመኝተዋል።

አቶ ያሬድ ገመቹ የክለቡ አሠልጣኝ ስፖርት ክለቡ ከአመራ ጋር በቅንጅት እየሠራ እንደሆነ አንስተዋል።

በወጣቶች ላይ ትኩረት አድርገው እየሠሩ እንደሆነ የገለጹት አሠልጣኙ የተሻለ ውጤት ለማምጣት እንደሚሠሩ ተናግረዋል።

የእግር ኳስ ክለቡ አምበል ወጣት ቢንያም ገነቱ እኛ በሥራችን ላይ ትኩረት አድርገን እንጫወታለን በማለት ለመጫወት አቅም እንዳለን አሳይተናል፤ በቀጣይም ውጤት ለማምጣት እንተጋለን ሲል ገልጿል።

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 26/02/2024

በድጉና ፋንጎ ወረዳ በተከሰተው ድንገተኛ የትራፊክ አደጋ የ8 ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን በ13 ሰዎች ከባድ ጉዳት ደርሷል

#ላሾቄራ፤ የካቲቲ 17/2016 ዓ/ም በድጉና ፋንጎ ወረዳ በተከሰተው ድንገተኛ የትራፊክ አደጋ አሸከርካሪውን ጭምሮ የ 8 ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን በ13 ሰዎች ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል።

ዛሬ 12 :30 ገደማ መነሻውን ከአርባምንጭ ከተማ ወደ ሀዋሰ ከተማ በመጓዝ ላይ ያሉ ለግል ጤንነታቸው በማለት ከተለያዩ ከመንግሥት ሰራተኞች ፣ ከባለሀብት የተወጣጡ ስፖርተኞች በድንገተኛ የመኪና አደጋ ፋንጎ ኮይሻ ቀበሌ ልዩ ስሙ ዞንጋ ተብሎ በሚጠራበት አከባቢ ሕይወታቸው አልፏል ።

በአደጋው በሰው ህይወትና ንብረት ላይ አደጋ ደርሷል እስካሁን ባለው መረጃ የሟቾችና የተጎጂዎቹ ቁጥር ታውቋል።

አደጋው የተፈጠረው የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 A 01784 ሲሆን አጠቃላይ ተሳፋሪ ብዛት 27 ሲሆኑ የሞቱ 8 ሰዎች በህይወት የተረፉ 19 ከባድ ጉዳት 13 ቀላል የአካል ጉዳት 6 መሆናቸው ከቦታው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

Photos from የካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/kawo koisha woreda prosperity party office/'s post 25/02/2024

በየካ ክፍለ ከተማ ሕዝባዊ ውይይት ተካሔደ!!

"ሀብት የመፍጠር ጉዟችን፣ ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እና ቀጣይ አቅጣጫዎች" በሚል መሪ ሀሳብ በየካ ክፍለ ከተማ ሕዝባዊ ውይይት ተካሔሒዷል።

ውይይቱን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳዳር እንደሻው ጣሰው፣ የገንዘብ ሚኒስተር አህመድ ሽዴ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ጃንጥራር አባይ መርተውታል።

የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ባቀረቡት የውይይት መነሻ ሰነድ ውይይቱ የሀገርን አንድነት ለማስቀጠል እንዲሁም መላውን ህብረተሰብ ከእዳ ወደ ምንዳ ለማሸጋገር በሚያስችሉ ወቅታዊ አጀንዳዎች ላይ ምክክር ለማድረግ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህም የተሻለ ግንዛቤ በመፍጠር በሀገሪቱ የብልጽግና ጉዞ ሁሉም ዜጋ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ያስችላል ነው ያሉት።

በህብረተሰቡ የተነሱ ጥያቄዎችን በመመለስ እና ፍትሃዊ ተጠቃሚነቱን በማረጋገጥ የብልፅግና ጉዞችን ማሳለጥ እንደሚገባ ታምኖበታል ብለዋል።

በህዝባዊ ውይይቱ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተወጣጡ የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።

Want your organization to be the top-listed Government Service in Sodo?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Videos (show all)

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ በ9ኛው የከተሞች ፎረም ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ
ደማቋ ከተማ ውቢቷ ወላይታ ሶዶ፤
ፕሮጀክት በተመለከተ   ፦  ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ ( ዶ/ር )
9ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካና የአስተዳደር ማዕከል በሆነችው ወላይታ ሶዶ ከተማ አዘጋጅነት ከየካቲት 9 እስከ 15 2016 ዓ.ም ይካሄዳል።
ደረሰ ደረሰ የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም በወላይታ ሶዶ ከተማ
እሴት በማስረፅ ዘላቂ ሀሴት መፍጠር መቻል አለብን!!የብልፅግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ክቡር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ#prosperity
ተሻጋሪ ምናብ ያላቸው ቡድኖች ከውስን ጊዜ የተሻገረ የፖለቲካ ምልከታ ይኖራቸዋል - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ#prosperity
"ታሪክ መዘን ነገን ማበላሸት የለብንም" - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ#prosperity
በጂኦግራፊ እስረኛ ሆነን ከዚህ በላይ መቀጠል አንችልም:: የህዝብ ቁጥራችን በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ነው::  በድርድር፤በቢዝነስ ህግ፤በሰላማዊ መንገድ በተሞላ አካሄድ ሀገራችን ኢትዮጵያ የቀ...
የወላይታ ሶዶ ከተማ በምታስተናግደው የደቡበ ኢትዮጵያ ክልል ይፋዊ ምስረታ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ላይ የከተማው ነዋሪ አሻራውን እንዲያሳርፍ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ፎላ ጥ...

Telephone

Address

S**o
Other Political Organizations in S**o (show all)
Dddd Dddd
S**o

Dddd is an unknown political organization

Wolaita Soddo City Prosperity Party Office Wolaita Soddo City Prosperity Party Office
S**o

ይህ በሶዶ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት መሪነት የተከናወኑ ተ?

S**o Town DiliBegerera Amba Kebele Prosperity S**o Town DiliBegerera Amba Kebele Prosperity
Woliata S**o
S**o

To promote socioeconomic development and political issues of the community.