Yeka Sub city Small Tax payers branch Office
Revenue for societal infrastructure and facilities
በ 08/03/2016 ዓ.መ በየካ ክ/ከተማ ውስጥ በሚገኙ በመተባበር፤ በዘፍመሽ እና በማራቶን ህንፃ ላይ ለሚገኙ ግብር ከፋዮች የሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያ አጠቃቀም እና አገልግሎት ለማግኘት መደረግ የሚገባቸውን ቅድመ-ሁኔታዎች በተመለከተ የታክስ ከፋዮች ትምህርትና ድጋፍ ቡድን አስተባባሪ የሆኑት አቶ አለማየሁ ሞገስ ገለጻ ያደረጉ ሲሆን በመጨረሻም ከግብር ከፋዮች ለተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ተገቢውን ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት የእለቱ ስልጠና ተጠናቋል፡፡
ለደረጃ ''ሀ "' ግብር ከፋዮች እንዲሁም ለተጨማሪ እሴት ታክስ እና ለተርንኦቨር ታክስ ተመዝጋቢዎች በሙሉ ካለው የግብር ከፋይ መብዛት ጫና ምክንያት በነገው እለት ማለትም በ 01/03/2016 ዓ.ም የመክፈያ ጊዜ የተራዘመ እና ሙሉቀን የሚሰራ መሆኑን እናስታውቃለን::
ታክስ ለዜጎች ያለዉ ጠቀሜታ
ግብር ለአንድ ሃገር እድገት የጀርባ አጥንት ነዉ፣ ግብር የመንግስት ዋንኛ የፋይናንስ ምንጭ ነዉ ፡፡ በህብረተሰቡ ዘንድ ፍታዊ የሆነ የሃብት ክፍፍል እንዲኖር ለማድረግ፣ ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት እና እድገትንና ልማትን ለማፋጠን የሚያገለግል መሳሪያ ነዉ በተለይ እንደ ኢትዮዽያ ያሉ ታዳጊ ሀገራት መንግስት ማህበራዊ አገልግሎቶችን ለማስፋፋት ለመመከላከያ እና ለደህንነት፣ለፍትህ መስፈን፣ ለአካባቢ ጥበቃ፣ ለኢኮኖሚ ልማት፣ ለባህል እድገት፣ በአጠቃላይ ለህዝብ ኑሮ መሻሻል ከፍተኛ ድርሻ አለዉ ፡፡ በመሆኑም እርስዎ በሚያደርጉት የንግድ ልዉዉጥ ሂደት ግዥ ሲፈፅሙ ደረሰኝ በመቀበል ሽያጭ ሲያከናዉኑ እና አገልግሎት ሲሰጡ ደረሰኝ በመስጠት የታክስ አሰባሰቡን ስርዓት ፍታዊ በማድረግ ሃገራችን ሁሌ እርዳታ እና ብድር ጠባቂ እንዳትሆን ሁላችንም ሃላፊነታችን መወጣት አለብን!!!
የየካ ክፍለ ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት
በየካ ክ/ከተማ አስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት ስር ለሚገኙ አዳዲስ ግብር ከፋዮች ስለ ግብር ታክስ ምንነት እና የግብር ከፋዮች መብትና ግዴታዎችን በተመለከተ በዛሬው ዕለት ማለትም በ 22/02/2016 ዓ.ም ስልጠና የተሰጠ ሲሆን የታክስ ከፋዮች ትምህርትና ድጋፍ ቡድን አስተባባሪ የሆኑት አቶ አለማየሁ ሞገስ ገለጻ ያደረጉ ሲሆን በመጨረሻም ከግብር ከፋዮች ለተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች የታክስ ከፋዮች ትምህርት ድጋፍና የህግ ተገዥነት የስጋት ስራ አመራር የስራሂደት አስተባባሪ የሆኑት አቶ ካሱ ፈልሚ ተገቢውን ማብራሪያ በመስጠት የእለቱ ስልጠና ተጠናቋል፡፡
በየካ ክ/ከተማ አስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት ስር ለሚገኙ አዳዲስ ግብር ከፋዮች ስለ ግብር ታክስ ምንነት በዛሬው ዕለት ማለትም በ 15/02/2016 ዓ.ም ስልጠና የተሰጠ ሲሆን የታክስ ከፋዮች ትምህርትና ድጋፍ ቡድን አስተባባሪ የሆኑት አቶ አለማየሁ ሞገስ ገለጻ ያደረጉ ሲሆን በመጨረሻም ከግብር ከፋዮች ለተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች የታክስ ከፋዮች ትምህርት ድጋፍና የህግ ተገዥነት የስጋት ስራ አመራር የስራሂደት አስተባባሪ የሆኑት አቶ ካሱ ፈልሚ ተገቢውን ማብራሪያ በመስጠት የእለቱ ስልጠና ተጠናቋል፡፡
ለአዳዲስ ግብር ከፋዮች ስልጠና ተሰጠ
በዛሬው ዕለት ማለትም በ 25/01/2016 ዓ.ም በየካ ክ/ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት ስር ለሚገኙ በተለያየ ዘርፍ ላይ ለተሰማሩ አዳዲስ ግብር ከፋዮች ስለ ግብር ታክስ ምንነትና የግብር ከፋዮች መብትና ግዴታዎችን በተመለከተ በታክስ ከፋዮች ትምህርትና የህግ ተዥነት ስጋት ስራ አመራር የስራሂደት አስተባባሪ በሆኑት በአቶ መላኩ ደርሶ ስልጠና የተሰጠ ሲሆን አስፈላጊውን ገለፃ እና ማብራሪያ የተደረገ ሲሆን ከግብር ከፋዮች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተገቢውን ምላሽ በመስጠት የእለቱ ስልጠና ተጠናቋል፡፡
የ 2016 ዓ.ም የዕቅድ ስምምነት ፊርማ
በዛሬው ዕለት ማለትም በ 14/01/2016 ዓ.ም በየካ ክ/ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት ስር የሚገኙ ስራአስኪያጅ የዘርፍ ም/ስ/አስኪያጆች የክ/ከተማ እንዲሁም የወረዳ የስራሂደቶች በ 2016 በጀት ዓመት በእቅድ ግቦች ላይ የጋራ ስምምነት ያደረጉ ሲሆን የቅርንጫፉ ስራአስኪያጅ አቶ እንዳለ መንግስቱ ከ3ቱ የዘርፍ ም/ስ/አስኪያጆች እና ከየወረዳ የስራሂደት መሪዎች ጋር እንዲሁም የዘርፍ ም/ስ/አስኪያጆች በየዘርፋቸው ከሚገኙ የስራሂደቶች ጋር በእቅዱ ላይ በመግባባት እቅዱን ከግብ ለማድረስ የጋራ ስምምነት ላይ የደረሱ ሲሆን ይህንንም በፊርማ ስነ-ስርአት አረጋግጠዋል፡፡
በየካ ክ/ከተማ አ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት የወረዳና የክ/ከተማ የስራሂደቶችና አመራሮች የነሐሴ ወር ዕቅድ አፈጻጸም ገመገሙ በ 10/07/2016 ዓ.ም የወረዳው እንዲሁም የክ/ከተማው የስራሂደት መሪዎችና አመራሮች በተገኙበት በየካ ክ/ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት የዕቅድና በጀት ዝግጅት ክትትልና ግምገማ የስራሂደት መሪ የሆኑት አቶ አድሀኖም አስገለ የነሐሴ ወር 2015 ዓ.ም ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን ለመሰብሰብ የታቀደው 167.4 ሚሊዮን ቢሆንም 181.9 ሚሊዮን ብር በመሰብሰብ የዕቅዱን 108.6% ማሳካት የተቻለ ሲሆን ከባለፈው አመት ገቢ ጋር ሲነጻጸር የ 152% ብልጫ ያለው መሆኑን ገልጸዋል:: በተጨማሪም የሐምሌ እና የነሐሴ ወር 2015 ዓ.ም የ 2 ወር ዕቅድ 776.22 ሚሊዮን ሲሆን የዕቅዱን 741.93 ሚሊዮን ብር በመሰብሰብ የዕቅዱን 96% ማሳካት የተቻለ ሲሆን ከባለፈው ዓመት እቅድ አፈፃፀም ጋር ሲነፃፀር የ 129% ብልጫ ያለው መሆኑን ገልፀዋል::በዚህም መሰረት ከባለፉት ወራቶች ዕቅድ አፈጻጸም አንጻር የነበሩ ችግሮችን በመለየት እና በመፍታት ከዚህ የበለጠ በመስራት በመስከረም ወር 2016 ዓ.ም እቅዳችንን ማሳካት እና ውጤታማ መሆን እንደሚጠበቅብን አቅጣጫ በማስቀመጥ የዕለቱ ውይይት ተጠናቋል፡፡
በ 10/01/2016 ዓ.ም በየካ ክ/ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት ስር ለሚገኙ በብረታብረት ንግድ ዘርፍ ላይ ለተሰማሩ ግብር ከፋዮች በገቢ አሰባሰብ እና በሀሰተኛ ደረሰኝ ግኝት ዙሪያ የታክስ ከፋዮች ትምህርት ድጋፍ እና የህግ ተገዥነትና ስጋት ስራ አመራር የስራሂደት መሪ የሆኑት አቶ መላኩ ደርሶ ስልጠና የሰጡ ሲሆን ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ተገቢውን ምላሽ በመስጠት የእለቱ ስልጠና ተጠናቋል፡፡
በዛሬው ዕለት ማለትም በ 07/01/2016 ዓ.ም የየካ ክ/ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት ሁሉም ሰራተኞችና አመራሮች የመስቀል በአል እና የእሬቻ በአል አከባበር በተመለከተ የታክስ ከፋዮች ትምህርት ድጋፍና ህግ ተገዥነት ስጋት ስራ አመራር የስራሂደት መሪ የሆኑት አቶ መላኩ ደርሶ ሁለቱም በአላት ከሀገር አልፎ በአለም በቅርስነት የተመዘገቡ እንዲሁም ከሀይማኖት ባሻገር ባህላዊ ይዘት ያላቸውና በአደባባይ የሚከበሩ ታላላቅ በአላት በመሆናቸው ሁላችንም ባህሉንና እሴቱን ጠብቀን በሰላማዊ መንገድ እንድናከብር ተገቢውን ገለፃ ያደረጉ ሲሆን ከቤቱ ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የታክስ ስራዎች ዘርፍ ም/ስ/አስኪያጅ የሆኑት ወ/ሮ ፀሀይ ለማ ተገቢውን ማብራሪያና ምላሽ በመስጠት የእለቱ ፕሮግራም ተጠናቋል ፡፡
በየካ ክ/ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት በዛሬው ዕለት ማለትም በ 01/13/2015 ዓ.ም የአገልግሎት ቀን ሲከበር የተቋሙ አመራሮችና ሰራተኞች እንዲሁም ግብር ከፋዮች በተገኙበት በደመቀ ሁኔታ የተከበረ ሲሆን የቅ/ጽ/ቤቱ ስራአስኪያጅ የሆኑት አቶ እንዳለ መንግስቱ እንኳን ለአገልጋይነት ቀን በሰላም አደረሳችሁ በማለት የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል፡፡ የአገልግሎት ቀን ሲከበር ብቻ ሳይሆን ቀጣይ ባሉትም ጊዜያት እስካሁን የነበሩትን ስኬቶች ለማስቀጠል ሁላችንም የየበኩላችንን ድርሻና ኃላፊነት መወጣት ይገባናል ምክንያቱም የተቋማችን መሪ ቃል የሆነውን ‹‹ ውጤታማ ተግባቦት ለላቀ ገቢ አፈጻጸም ›› የሚለውን መተግበር የሁላችን ግዴታ ነው፡፡ ‹‹ የላቀ ገቢ ለከተማችን ሁለንተናዊ ብልፅግና ›› በመቀጠል የዳቦ ቆረሳ የተካሄደ እና ከየስራሂደቱ የተሻለ የስራ አፈፃፀም እና የሰአት አከባበር ለነበራቸው ሰራተኞች የምስጋና ወረቀት ተሰጥቷል፡፡ በመጨረሻም የቅ/ጽ/ቤቱ ሞደርናይዜሽንና ኮርፖሬት ስራዎች ዘርፍ ም/ስ/አስኪጅ የሆኑት ወ/ሮ ትእግስት አሰፋ ሁላችንም ሰራተኞች ለአገልግሎት የሚመጡ ግብር ከፋዮችን እንደ ቤተሰቦቻችን በማየት በአግባቡ ልናስተናገዳቸው ይገባል እንዲሁም የተሻለ አገልግሎት በመስጠታቸው እና ሰአት አከባበራቸው የተሻለ ሆኖ በመገኘቱ ለተሸለሙት ሰራተኞች እንኳን ደስ አላችሁ እያልኩ ሁላችንም ለጋራ ለውጥ መረባረብ ይገባናል ሲሉ የእለቱ ፕሮግራም ተጠናቋል፡፡
የየካ ክ/ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት አመራሩም ሆነ ሁሉም ሰራተኞች በተገኙበት በዛሬው ዕለት ማለትም በ 24/12/2015 ዓ.ም የ 2015 ዓ.ም ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና የ 2016 በጀት አመት መሪ ዕቅድ ላይ ውይይት የተካሄደ ሲሆን የክ/ከተማው የእቅድና በጀት ዝግጅት ክትትልና ግምገማ የስራሂደት መሪ የሆኑት አቶ አድሀኖም አስገለ ገቢውን በመሰብሰብ ረገድ የነበሩ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በዝርዝር በማቅረብ በ 2015 ዓ.ም ለመሰብሰብ ከታቀደው ብር 2,255.27 ቢሊዮን ውስጥ የእቅዱን 2,017.57 ቢሊዮን ብር በመሰብሰብ 90% ማሳካት መቻሉን እንዲሁም የ 2016 አመታዊ የገቢ ዕቅድ 2.730 ቢሊዮን ሲሆን ከዚህም ውስጥ የሐምሌ ወር ዕቅድ ብር 608.7 ሚሊዮን መሆኑን ገልፀው ብር 559.9 ሚሊዮን በመሰብሰብ የዕቅዱን 92% ማሳካት እንደተቻለ ገልፀዋል:: በመቀጠል የቅ/ጽ/ቤቱ ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ እንዳለ መንግስቱ በ 800 ሰራተኛ መሰራት የነበረበት ስራ በ 433 ሰራተኞች እየተሰራ ይህ ውጤት ሊመጣ መቻሉን ገልጸው ተሳታፊዎች የነበሩ ችግሮች ወደ ቀጣይ አመት እንዳይተላለፉ በግልጽ ያሉ ችግሮችን እንዲያቀርቡ በሰጡት እድል መሰረት ከቤቱ አጠቃላይ የነበሩ እጥረቶችን እና የተለያዩ ጥያቄዎችን አቅርበው በበላይ አመራሩ ተገቢውን ማብራሪያ እና ምላሽ የተሰጠበት ሲሆን በመጨረሻም የቅ/ጽ/ቤቱ ስራአስኪያጅ የሆኑት አቶ እንዳለ መንግስቱ በከተማ ደረጃ ሊሰበሰብ ከታቀደው 100 ቢሊዮን ውስጥ እኛም መሰብሰብ የሚጠበቅብንን ብር 2.730 ቢሊዮን ለመሰብሰብ ጠንካራ ጎኖቻችንን በማስቀጠል ድክመቶቻችንን በማረም ለ 2016 ዓ.ም የገቢ ዕቅድ መሳካት ሁላችንም የበኩላችንን ሚና እንድንወጣ እያሳሰብኩ ለዕቅዱ መሳካት ሁላችንም ቃል እንገባለን በማለት ከሁሉም ሰራተኛ ጋር የጋራ መግባባት ላይ ተደርሶ የእለቱ ውይይት ተጠናቋል::
በየካ ክ/ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት በዛሬው ዕለት ማለትም በ 09/12/2015 ዓ.ም በውቅታዊ የሀገራችን ጉዳይ ማለትም ከአማራ ክልል ጋር ተያያይዞ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ እና ችግሩን ለመቅረፍ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አፈፃፀም በተመለከተ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ስራአስኪጅ የሆኑት አቶ እንዳለ መንግስቱ አስፈላጊውን ገለጻና ማብራሪያ ያቀረቡ ሲሆን ከቅ/ጽ/ቤቱ ሰራተኞኝ ለተነሱ የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተገቢውን ምላሽ እና ማብራሪያ በመስጠት የእለቱ ውይይት ተጠናቋል፡፡
በየካ ክ/ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት የ 2015 ዓ.ም የዓመታዊ ግብር እና የ 3 ወር ቫትና ቲኦቲ ወርሀዊ ለማሳወቅ ለመጡ ግብር ከፋዮች በታክስ ከፋዮች ትምህርትና ድጋፍ ኦፊሰሮች ወ/ሮ እንያት አላምረው እና ወ/ሮ እታበዝ ተገኝ አማካኝነት ‹‹ ታክስ ለዜጎች ያለው ጠቀሜታ ›› በሚል ርዕስ ዙሪያ ገለፃ የተደረገ ሲሆን ከግብር ከፋዮች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተገቢውን ማብራሪያና ምላሽ የተሰጠ ሲሆን በዚህ ርዕስ ዙሪያ የተዘጋጀውን ፓምፕሌት ለግብር ከፋዩ ለእያንዳንዱ እንዲደርስ ተደርጓ ል፡፡
በ 12/11/2015 ዓ.ም በየካ ክ/ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት በሲሚንቶ፣ ጣውላ ፣ ጀሶ እና ብረታብረት የንግድ ስራ ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ግብር ከፋዮች ከሀሰተኛ ከደረሰኝ ጋር በተያያዘ የውውይት መድረክ የተዘጋጀ ሲሆን ከሀሰተኛ ደረሰኝ ጋር የተያያዙ ችግሮች በጣም ብዙ ሲሆኑ ጥቂቶቹ፡- ደረሰኝ ለማሳተም ወይም ሽ/መ/መሳሪያ ለመግዛት ፈቃደኛ አለመሆን፤ ደረሰኝ የሚጠቀሙ ግብር ከፋዮች ያለደረሰኝ ግብይት ማከናወን፤ ከዋጋ በታች ደረሰኝ መቁረጥ/ከዋጋ በላይ ደረሰኝ መቁረጥ፤ ለግዥ እና ተመላሽ ሰነድ ሀሰተኛ ደረሰኝ መጠቀም እና ማሰራጨት፤ በአስመዘገቡት አድራሻ አለመገኘት ወይም ስውር ቦታ መጠቀም በሚል የታክስ ከፋዮች ትምህርትና ድጋፍ ቡድን አስተባባሪ የሆኑት አቶ አለማየሁ ሞገስ የውይይት ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን የህግ ማስከበር ም/ስ/አስኪያጅ የሆኑት አቶ መኮንን ገመቺስ ቀጣይ ባሉት ጊዜያት ግብር ከፋዩ ማህበረሰብ በህጋዊ መንገድ በደረሰኝ ላይ የተመሰረተ ግብይት ብቻ ማከናወን እንዳለባቸው እና ህገወጥነትን ተቀናጅተን በጋራ መከላከል እንደሚገባ በመግለጽ ከግብር ከፋዮች ለተነሱ ጥያቄዎች ተገቢውን ማብራሪያና ምላሽ በመስጠት የዕለቱ ውይይት ተጠናቋል፡፡
በሀገር አቀፍ ደረጃ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በአንድ ጀንበር 500 ሚሊዮን ችግኝ እንትከል ባሉት መሰረት የየካ ክ/ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓ.ም ማንም እቤቱ አይውልም ኢትዮጵያን በ 500 ሚሊዮን ችግኞች አረንጓዴ እናለብሳታለን በሚል መሪ ቃል በደጃዝማች ወንድራድ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ግቢ ውስጥ የችግኝ ተከላ ፕሮግራም ተከናውኗል::
'' ለነገ ዛሬ እንትከል ግብር ለሀገር ክብር!!! ''
በየካ ክ/ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት የ 2015 በጀት ዓመት የግብር ማሳወቂያ የማስጀመሪያ ፕሮግራም ላይ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ስራአስኪጅ የሆኑት አቶ እንዳለ መንግስቱ እንኳን ለ 2015 ዓ.ም የማሳወቂ ጊዜ እንኳን አደረሳችሁ በማለት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር በማድረግ ፕሮግራሙን የከፈቱ ሲሆን በግብር ማሳወቂያ በመጀመሪያው ቀን በመምጣችሁ በተቋሙ ስም ምስጋናዬን እያቀረብኩ በማሳወቂያ ጊዜ በመጀመሪያው ቀን ቀድማችሁ ለመጣችሁ 10 ግብር ከፋዮች የእውቅና ሰርተፊኬት የሚሰጥ ሲሆን ለቀጣይም ባለው ጊዜ ቀድማችሁ እንድትመጡ መልክቴን አስተላልፋለሁ በማለት ከህግ ማስከበር ዘርፍ ም/ስ/አስኪያጅ ከሆኑት አቶ መኮንን ገመቺስ፣ የታክስ ጉዳዮች ም/ስ/አስኪያጅ የሆኑት ወ/ሮ ፀሀይ ለማ፣ የሞደርናይዜሽንና ኮርፖሬት ስራዎች ም/ስ/አስኪያጅ ወ/ሮ ትዕግስት አሰፋ እንዲሁም ከግብር ከፋይ የተወከሉ አንድ ግብር ከፋይ በጋራ በመሆን የዳቦ ቆረሳ በማድረግ የእለቱን ፕሮግራም ያስጀመሩ ሲሆን በመጨረሻም ቀድመው ለተገኙ 10 ግብር ከፋዮች የእውቅና ሰርተፊኬት በመስጠት የዕለቱ ፕሮግራም ተጠናቋል ፡፡
በየካ ክ/ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት የ 2015 በጀት ዓመት የግብር ማሳወቂያ ወቅት የማስፈጸሚያ ዕቅድ ላይ በክ/ከተማው ስር የሚገኙ የስራሂደቶችና ቡድኖች በተገኙበት አጠቃላይ ውይይት ተካሂዷል፡፡
በዕለቱም የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ስራአስኪጅ የሆኑት አቶ እንዳለ መንግስቱ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር በማድረግ ፕሮግራሙን የከፈቱ ሲሆን የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የዕቅድና በጀት ክትትል የስራ ሂደት አስተባባሪ የሆኑት አቶ አስገዶም አስገለ የ 2015 በጀት ዓመት የግብር ማሳወቂያ ወቅት የማስፈጸሚያ ዕቅድ ሰነድ አቅርበው ሰፊ ውይይት በማድረግ ከተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የተሰጡ ሲሆን ከቤቱ ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያቶች የህግ ማስከበር ዘርፍ ም/ስ/አስኪጅ የሆኑት አቶ መኮንን ገመቺስ እንዲሁም የሞደርናይዜሽንና ኮርፖሬት ስራዎች ዘርፍ ም/ስ/ አስኪያጅ የሆኑት ወ/ሮ ትዕግስት አሰፋ ተገቢውን ምላሽ የሰጡ ሲሆን በመጨረሻም የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ስራአስኪጅ የሆኑት አቶ እንዳለ መንግስቱ የከተማው ገቢዎች መሰብሰብ ከሚጠበቅበት 100 ቢሊዮን ውስጥ የእኛ ድርሻ ደግሞ 2.723 ቢሊዮን መሆኑን ገልጸው ይህንንም ዕቅድ ለማሳካት በማቴሪያልም በሰውሀይልም ከባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅተን በመስራት ከተሰጠን አጠቃላይ ዕቅድ ውስጥ 50% የሚሆነውን በግብር ማሳወቂያ ወቅት ለመሰብሰብ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራርን በመጠቀም ግብርከፋዩን ማህበረሰብ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳንል ጠዋት ቀድሞ በመግባት ምሽት አምሽቶ በመስራት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት መስራት እንደሚገባን የስራ መመሪያ በመስጠት የእለቱ ውይይት ተጠናቋል፡፡
ደረሰ ደረሰ ደረሰ!!!
በየካ ክ/ከተማ ለምትገኙ ግብር ከፋዮች በሙሉ እንኳን ለ 2015 ዓ.ም የግብር ማሳወቂያ ጊዜ በሰላም አደረሳችሁ እያልን የ 2015 ዓ.ም ግብር ማሳወቂያው ጊዜ ከሐምሌ 01/2015 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 30/2016 ዓ.ም መሆኑ ይታወቃል፡፡ በዚህም መሰረት ፡- 1ኛ. አመታዊ ገቢያችሁ ከ 500,000 ብር በታች የሆነ ከሐምሌ 01/2015 ዓ.ም እስከ ሐምሌ 30/2015 ዓ.ም፣ 2ኛ. አመታዊ ገቢያችሁ እስከ 1,000,000 ብር የሆነ ከሐምሌ 01/2015 ዓ.ም እስከ ጳጉሜ 05/2015 ዓ.ም፣ 3ኛ. አመታዊ ገቢያችሁ ከ 1,000,000 ብር በላይ የሆነ ደግሞ ከሐምሌ 01/2015 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 30/2016 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ ከአላስፈላጊ ውጣውረድ እንዲሁም ቅጣትና ወለድ ለመዳን በተቀመጠው ጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግብራችሁን እንድታሳውቁ ጥሪያችንን እናስተላልፋን፡፡
በየካ ክ/ከ/አ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት የታክስ ከፋዮች ትምህርትና ድጋፍ ቡድን!!!
በዛሬው ዕለት ማለትም በ 23/10/2015 ዓ.ም የየካ ክ/ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት በአስመጭነትና በኮንስትራክሽን ዘርፍ ላይ ለተሰማሩ ግብር ከሀሰተኛ ደረሰኝ ጋር በተያያዘ ሂሳብ መዝገብ ውድቅ የሚደረግበት እና መፍትሔው ዙሪያ የየካ ክ/ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት የታክስ ከፋዮች ትምህርት ድጋፍና የሕግ ተገዥነት የሥጋት ስራ አመራር የስራ ሂደት አስተባባሪ የሆኑት አቶ መላኩ ደርሶ ተገቢውን ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ከግብር ከፋዮች ለተነሱት ጥያቄዎች እና አስተያየቶች የሕግ ተገዥነት ስራዎች ዘርፍ ም/ስ/አስኪያጅ የሆኑት አቶ መኮንን ገመቺስ ምላሽ እና ማብራሪያ በመስጠት የእለቱ ስልጠና ተጠናቋል ።
በቀን 18/9/2015 ዓ/ም በየካ/ክ/ከ/አ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት በሀሰተኛ ደረሰኝ ዙሪያ አስመጪዎች እና ኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩ ግብር ከፋዮችን ማወያየት ተችሏል፡፡በውይይቱም አቶ መኮንን ገመቺስ የህግ ተገዥነት ም/ስራ አስኪያጅ ፣አቶ መላኩ ደርሶ የስጋት ስራ አመራርና የታክስ ከፋዮች ትምህርትና ድጋፍ የስራ ሂደት እና ወ/ሮ ፅጌ አምባዬ የኢንተለጀንስ የስራ ሂደት ተገኝተው አወያይተዋል በውይይቱም የሚከተለው ገለፃ ተደርጎላቸዋል ፡፡
የሂሳብ መዝገብ በግብር ከፋዮች በራሳቸው የሚሰራ ሲሆን ለሂሳብ ሰነድ በመረጃነት የሚያገለግሉ ሰነዶች በህግ የተፈቀዱ የታተሙ ደረሰኞች ወይም ከሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያ የሚወጡ ሰነዶች ናቸው፡፡ከደረሰኝ ጋር የተያያዙ ችግሮች በጣም ብዙ ሲሆኑ ጥቂቶቹ፡-
ደረሰኝ ለማሳተም ወይም ሽ/መ/መሳሪያ ለመግዛት ፈቃደኛ አለመሆን፤
ደረሰኝ የሚጠቀሙ ግብር ከፋዮች ያለደረሰኝ ግብይት ማከናወን፤
ከዋጋ በታች ደረሰኝ መቁረጥ/ከዋጋ በላይ ደረሰኝ መቁረጥ፤
ለግዥ እና ተመላሽ ሰነድ ሀሰተኛ ደረሰኝ መጠቀም እና ማሰራጨት፤
በአስመዘገቡት አድራሻ አለመገኘት ወይም ስውር ቦታ መጠቀም፤
የሀሰተኛ ደረሰኝ ምንጮች
በታክስ ህጉ እውቅና የሌላቸው ሰነዶች ወይም ያለፈቃድ የታተሙ ደረሠኞች፤
በሀሰተኛ ንግድ ፈቃድ የታተሙ ደረሰኞች፤
በታዋቂ ግለሰቦች/ድርጅቶች የታተሙ ደረሰኞች፤
በሀሰተኛ ማንነት የታተሙ ደረሰኞች
በድግግሞሽ የታተሙ ደረሰኞች
የጠፉ ደረሰኞችን እንደ ሰነድ መጠቀም
የጠፉ እና የተወገዱ ሽ/መ/መሳሪዎች የሚታተሙ ሰነዶች፤
በሀሰት የሚፈጸሙ ድርጊቶች
የእቃ ልውውጥ ሳይኖር ለደረሰኝ ብቻ ሀሰተኛ ግብይት መፈጸም፤
የታክስ ደረሰኝ ለመሸጥ ከተቋቋሙ ድርጅቶች ደረሰኝ መግዛት፤
የማስመሰል ግብይት መፈጸም ማለትም የተወሰነ እቃ ብቻ መግዛት፤
የንግድ ስርዓቱ ውስጥ ያሉ እና በጉዳዩ ያልተሳተፉ ግብር ከፋዮች መንገላታት፤
በሂሳብ መዝገብ ወጪን በማናር ያልተገባ ኪሳራ በማሳወቅ ከግብር መሸሽ፤
በተመላሽ አሰራር ሂደት ያልተገባ ተመላሽ በመጠየቅ ከህዝብ ሀብት መውሰድ፤
የታክስ መርህን በመጣስ የአገሪቱን ኦኮኖሚ ችግር ውስጥ መጣል፤
የመልካም አስተዳደር፣ አገልግሎት አሰጣጥ እና ሙስና መበራከት፤
የዜጎች የገቢ ልዩነት በፍጠር የሀገሪቱን ድህነት ማባባስ እና የኢኮኖሚ ድቀት መፍጠር ወ.ዘ.ተ ናቸው፡፡
የተሳታፊዎች ገጽታ
በቅን ልቦና (AT GOOD FAITH)፡- ትምህርት እና ድጋፍ እንደመፍትሄ፤
በመጥፎ እምነት(AT BAD FAITH)፡- ክትትል እና ምርመራ ተጠያቂነት፤
ችግሩን እንዴት እናስወግድ?
ዘመናዊ ክፍያ ስርዓትን መከተል እና ክፍያን በካሽ አለመክፈል/መቀነስ
ቋሚ አድራሻ ካላቸው ድርጅቶች ግዥ መፈጸም እና የተሻለ የመረጃ ቅርርብ መፍጠር፤
በቂ መረጃ የሌለው ደላላን ማስወገድ/ህጋዊ ወይም የሚታወቅ ደላላ መጠቀም፤
የተቀበሉትን ደረሰኝ ማመሳከር (MAKE INVOICE RECONCILATION )
ምንጊዜም የታክስ ስርዓት አለምአቀፋዊ ሁኔታን ያገናዘበ እና ዘመናዊነትን እየተላበሰ እንደሚሄድ መገንዘብ እና ከገቢው ዘርፍ ጋር ተቀራርቦ መስራት ልምድን ማዳበር አሁን ላይ ያሉ መፍትሄዎች ናቸው በማለት ከግብር ከፋዩም ለተነሱ ጥያቄዎች በጋራ ምላሽ መስጠት ተችሏል፡፡
በየካ/ክ/ከ/አግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት የፓናል ውይይትና የተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድር በቀን 26/8/2015ዓ/ምየመክፈቻ ንግግር በወ/ሮ ቃል ኪዳን ተሻለ በታክስ ጉዳዮች ም/ስራ አስኪያጅ የቅ/ጽ/ቤቱአመራርየ12አንደኛ ደረጃት/ቤቶች ርእሰ መምህራን፣ የታክስ ክበብ ተጠሪ መምህራን፣ 36በት/ቤቶቹየተወዳደሩና የአሸነፉ ተማሪዎች በተገኙበት ተካሂዳል የአሸናፊዎች አሸናፊ በመለየት የፓናል ውይይት ሰነድ ቀርቦ ከቅ/ጽ/ቤቱ የህግ ተገዥነት ም/ስራ አስኪያጅ አቶ መኮንን ገመቺስና የሞደርናይዜሽን ኮርፖሬት ስራዎች ም/ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ትእግስት አሰፋ መወያየትና የሰርተፍኬት ና የሽልማት ፕሮግራም ተካሂዶ ተጠናቃል፡
በቀን 30/6/2015በየካ/ክ/ከ/አ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት በታክስ ከፋዮች ትምህርትና ድጋፍ ቡድን ክፍል በአስመጪ ዘርፍ ለተሰማሩ ግብር ከፋዮች ሂሳብ መዝገብ አያያዝ ላይ ከታክስ ኦዲት ቡድን አስተባባሪዎች ጋር በ በማሰልጠን ከግብር ከፋዮቹ ለተነሱለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት ተችሏል፡፡
የካ/ክ/ከ/አ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤትበቀን 21/06/2015 ዓ/ምበብርሀነ ህይወት አንደኛ ደረጃ ት/ቤት በቀን22/6/2015ዓ/ም በካራ አሎአንደኛ ደረጃ ት/ቤት ጠዋት በመገኘት ስለግብር ምንነትና ጠቃሜታው እናየደረሰኝ ምንነትና ጠቃሜታው በሚል ለተማሪዎች የገፅ ለገፅ ትምህርት ወ/ሮ ሀይማኖት ተሰፋዬ በታክስ ከፋዬች ትምህርትና ድጋፍ ቡድን አስተባባሪ አስተምረዋል
የካ/ክ/ከ/አ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤትበቀን 20/06/2015 ዓ/ምበየካኮተቤ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ጠዋት በመገኘት ስለግብርምንነትና ጠቃሜታው እናየደረሰኝ ምንነትና ጠቃሜታው በሚል ለተማሪዎች የገፅ ለገፅ ትምህርት በወ/ሮ ሀይማኖት ተሰፋዬ በታክስ ከፋዬች ትምህርትና ድጋፍ ቡድን አስተባባሪ መስጠት ተችሏል፡፡
በየካ/ክ/ከ/አ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት በቀን 16/06/2015 አድዋ በር አንደኛ ደረጃ ት/ቤት በደረሰኝ ምንነትና ጠቀሜታው በሚል ለተማሪዎች ገፅ ለገፅ ትምህርት በወ/ሮ እንያት አላምረው በታክስ ከፋዮች ትምህርትና ድጋፍ ከፍተኛ ኦፊሰር መሰጠት ተችሏል፡፡
በቀን 17/06/2015 በየካ/ክ/ከ/አ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት በታክስ ከፋዮች ትምህርትና ድጋፍ ቡድን አዘጋጅነት ግብር ከፋዮችበወ/ሮ ሀይማኖት ተስፋዬ በታክስ ከፋዮች ትምህርትና የድጋፍ ቡድን አስተባባሪ በሂሳብመዝገብአያያዝ በመመሪያ ቁጥር 176/2014 ላይ ስነድንበማቅረብ ስልጠና የተሰጠ እና ከግብር ከፋዮች ለተነሱጥያቄዎች ታክስኦዲት ቡድን አስተባባሪ ከወ/ሮ ህሊና በላይ ጋር በጋራበመሆን ምላሽ ተሰጥታል፡፡
የካ/ክ/ከ/አ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤትበቀን 16/06/2015 ዓ/ምበአብዮት አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ጠዋት በመገኘት የደረሰኝ ምንነትና ጠቃሜታው በሚል ለተማሪዎች የገፅ ለገፅ ትምህርት በወ/ሮ ሀይማኖት ተሰፋዬ በታክስ ከፋዬች ትምህርትና ድጋፍ ቡድን አስተባባሪ መስጠት ተችሏል፡፡
በቀን 14/06/2015 በወጣቶች ገነት አንደኛ ደረጃ ት/ቤትጠዋት በመገኘት በደረሰኝ ምንነትና ጠቀሜታው በሚል ለተማሪዎች ገፅ ለገፅ ትምህርት በወ/ሮ እንያት አላምረው በታክስ ከፋዮች ትምህርትና ድጋፍ ከፍተኛ ኦፊሰር መሰጠት ተችሏል፡፡
በቀን 14/06/2015 በደጃዝማች ወንድይራድ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ጠዋት በመገኘት የደረሰኝ ምንነትና ጠቃሜታው በሚል ለተማሪዎች የገፅ ለገፅ ትምህርት በወ/ሮ ሀይማኖት ተሰፋዬ በታክስ ከፋዬች ትምህርትና ድጋፍ ቡድን አስተባባሪ መስጠት ተችሏል፡፡
በየካ/ክ/ከ/አ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት በቀን 8/6/2015 ሾላ ላይ የንግድ ድርጅትታቸው የተቃጠለባቸው ግብር ከፋዮች ጋር በግብር አከፋፈል ስርዓት ላይ የንግድ እንቅስቃሴ በተመለከተ ከቅ/ጽ/ቤትታችን ስራ አስኪያጅ አቶ እንዳለ መንግስቱ የህግ ተገዥነት ም/ስራ አስኪያጅ አቶ መኮንን ገመችስ መወያየት ችለዋል፡፡ግብር ከፋዮች በምን አይነት ሁኔታ ታክሳቸውን መክፈል እንደሚችሉ ጥያቄ ባነሱት መሰረት እንዳጠቃላይም ግብር ከፋዮ ላነሱት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተመቻቸ እንዲሆን ከፖሊስ መረጃዎች ማቅረብ እንዳለባቸው ህጉ በሚፈቅደው ሁኔታ ማስተናገድ እንችላለን በማለት ምላሽ መስጠት ተችሏል፡፡
በየካ/ክ/ከ/አ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት ወ/ሮ እታፈራው ሲሳይ በገቢዎች ሚኒስቴር ታ/ኦዲት ዳይሬክቶሬት የዋጋ ትልልፍ ኦዲት የስራ ሂደት አስተባባሪ በአ ዲ ስ አ በ ባ ገ ቢ ዎ ች ለየ ካ፣ ለ ለ ሚ ኩ ራ እ ና ለ ቦ ሌ / ክ/ ከ/ አ ግ/ ከ/ ቅ/ ጽ/ ቤ ት በ ኦ ዲ ት ስ ራ ላ ይ
ለ ተ ሰ ማ ሩ ቡ ድ ን አ ስ ተ ባ ባ ሪ ዎ ች ና ሰ ራ ተ ኞ ች 4 ቀ ን የ ቆ የ ስ ል ጠ ና ሰ ጥ ተ ዋ ል፡፡ በ ስ ል ጠ ና ው ም :-
አጠቃላይ የታክስ ኦዲት ምንነት
በ ቀ ን 1.Audit Planning (የኦዲት እቅድ)
በ ቀ ን 2.Audit EX*****ON (የኦዲት ትግበራ ምዕራፍ)
በ ቀ ን 3.Sector based Audit(የዘርፍ ኦዲት አሰራር)
AUDIT COMPLETION (ማጠቃለያ)
- የተግባር ስልጠና
- ኬዝ ቤዝድ(case based የቡድን ውይይት ፕሪዘንቴሽን የ ተ ለ ያ ዩ ዘ ር ፎ ች ን ኮ ን ስ ት ክ ሽ ን ፣ አ ስ መ ጪ ወ.ዘ.ተ ከቀን6/6/2015እስከ9/6/2015 ድረስስልጠና በመስጠት
አጠናቀዋል፡፡
በየካ/ክ/ከ/አ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት በቀን 25/5/2015 አዲስ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ ለሆኑ ግ/ከፋዮች ተጨማሪ እሴት ታክስ ተፈፃሚ የሚሆንበትን አሰራር ዙሪያ ስልጠና መስጠት ተችሏል፡፡ሰነዱም በወ/ሮ እንያት አላምረው የታክስ ከፋዮች ትምህርትና ድጋፍ ከፍተኛ ኦፊሰር ቀርቦ ከግ/ከፋዮች ለተነሱ ጥያቄዎችም ከወ/ሮ ሀይማኖት ተስፋዬ የታክስ ከፋዮች ትምህርትና ድጋፍ ጋር በጋራበመሆን ምላሽ ተሰጥቷል፡፡
በቀን5/05/2015 የሾላ ግብር ከፋዮችንና የነጋዴዎች ፎረም አመራሮችን በቀን5/5/2015 በሾላ ብሎክ ማናጅመንትላይ ስልጠና መስጠት ተችሏል፡፡በእለቱ የተዘጋጀውን ሰነድ በአቶ መላኩ ደርሶ በስጋት ስራ አመራርና በታክስ ከፋዮች ትምህርትና ድጋፍ የስራ ሂደት ቀርቦ በህግ ተገዥነት ዘርፍ ም/ስራ አስኪያጅ በአቶ መኮንን ገመቺስ ከግብር ከፋዩ የተነሱ ጥያቄዎች ላይ በጋራ ምላሽ መስጠት ተችሏል፡፡
በየካ/ክ/ከ/አ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት የ2015 በጀት አመት የ6 ወር ገቢ ዕቅድ አፈፃፀም አመራሮች በተገኙበት ግመገማ ተካሂዷልበ17/05/2015 ዓ.ም አካሄደ በዕለቱ በ6 ወሩ ከቀጥታታክስ 799,064,266.72 ፣ቀጥታ ባልሆኑ ታክሶች455,755,472.64 እና ከማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ 46,956,992.8 ሚሊዮን ብር በአጠቃላይ 1,301,776,732.16 ለመሰብሰብ አቅዶ ብር 1,253,038,938.5 ብር በመሰብሰብ የዕቅዱን 96.26 በመቶ ማከናወን ተችሏል፡፡ ይህ የገንዘብ መጠን በ2014 በጀት ዓመት በተመሳሳይ ከተሰበሰበው ጋር ሲነፃጸር የብር 236,952,049.77 ሚሊዮን (23.32) በመቶ ልዩነት መፈፀሙ በአቶ አድሀኖም የዕቅድ በጀት ክትትልና ግምገማ የስራ ሂደት ሪፖርትበሰነድ አቅራቢነት በዝርዝር ተገልጿል ፡፡
የዕቅድ ግምገማው በቅ/ጽ/ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ እንዳለ መንግስቴ የተመራእና የሁሉንም የስራ ዘርፍና ክፍሎች የዳሰሰ ሲሆንከገቢ አንፃር ሲታይ ከባለፈው አመት ገቢጋር ሲነፃፀር የተሻለ ገቢ ሊሰበሰብ የቻለው ችግሮች የሚታይባቸውን ተግባራትን በየጊዜው በጋራ በመገሙ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ በመሰራቱ፣ ጠንካራ የድጋፍና የክትትል ስራ በመሰራቱ፣ታክስ ከፋዩ ስለታክስ ያለውን ዕውቀት ለማሳደግ የተጠናከረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች በመሰራቱ እና ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ያለው ቅንጅታዊ ስራ ተጠናከሮ በመቀጠሉ የተሻሻለ ገቢ ማግኘት መቻሉ እንደሆነም ተገልጿልበመሆኑም በተሻለ ሁኔታ አጠናክረን በመቀጠል እቅዳችንን በ100++ መተግበር አለብን በማለት ተገልጿል ።
በቀን 21/4/2015 በየካ/ክ/ከ/አ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት ለአዲስ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢዎች በተጨማሪ እሴት ታክስምንነት በዜሮ ምጣኔና ከታክሱ ነፃ የሆኑአቅርቦቶችመካከል ስለአለው ልዩነት ከተ/እ/ታ ምዝገባ ስለመሰረዝ የሚያበቁ መስፈርቶች ስለአስተዳደራዊና የወንጀል ቅጣቶች የተ/እ/ታ የምዝገባ ስርአት የተዘጋጀ ሰነድ በወ/ሮ እንያት አላምረው የታ/ከ/ት/ድጋፍ ከፍተኛ ኦፊሰር የቀረበና ከደንበኞች አገልግሎት ባለሙያዎች ጋር የጋራ ማብራሪያ ምላሽ መስጠት ተችሏል፡፡
በቀን 17/4/2015 የጀመረ በየካ/ክ/ከ/አ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት ለአመራሩና ሰራተኛው በኤች አይቪ እና የጥቃት ቀን በተመለከተማስተማሪያ ሰነድ በማቅረብ የተወያዩበትና ስልጠና መስጠት በአላቱንም በጋራ ማክበር ተችሏል፡፡
Click here to claim your Sponsored Listing.
Videos (show all)
Category
Contact the organization
Website
Address
Addis Ababa
የቦሌ ሥራና ክህሎት ፅ-ቤት Official የፌስቡክ ገፅ ነው፤ እኛን የሚመለከት ጉዳይ ካለዎት ያግኙን።
604 Equatorial Guiene Avenue
Addis Ababa
Serving reliable cadastral services and information
Bole Sub City, Gerji, Amora Building
Addis Ababa
Ethio-engineering Group is a governement owned industrial enterprise established under the laws of the Federal Democratic Republic of Ethiopia /FDRE/ by the decree of the council o...
Kasanchis
Addis Ababa
The Ministry of Irrigation & Lowlands (MILLs) is FDRE's Ministry established in 2021.
2Q29+FQP
Addis Ababa
Permanent Representation of the Republic of Cameroon to the African Union and the United Nations Economic Commission for Africa.