Kembata Tembaro zone health dep't Health communication

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ኮሚዩኒኬሽን

29/04/2023

I f you are interested , refer this published study.

Womens_Experiences_and_Reasons_for_Preferences_to_Home_Delivery_A_Phenomenological_Qualitative_Study_in_Tembaro_District_Southern_Nations_Nationalities_and_Peoples_Region_SNNPR_Ethiopia

Photos from Kembata Tembaro zone health dep't Health communication's post 03/04/2023

በጤናው ዘርፍ ጥራት ያለው መረጃ ከሌለ ጥራት ያለው አገልግሎት የለም መርዕ ተግባራዊ ማድረግ በጤናው ሴክተር ጉልህ ሚና እንደሚጫወት ተገለፀ።

በጤናው ዘርፍ ጥራት ያለው መረጃ ከሌለ ጥራት ያለው አገልግሎት የለም መርዕ ተግባራዊ ለማድረግ በተዘጋጀው ውይይት መረጃ በጤና ተቋማት እና በፕሮግራም ክፍሎች መረጃን ለውሳኔ መጠቀም የመረጃን አብዮት ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ‹‹ጥራት ያለው መረጃ ከሌለ ጥራት ያለው አገልግሎት የለም›› በሚል የጤና መረጃ ሳምንት ቀን ተከበረ፡፡

የግሉን ጤና ዘርፍ የጤና መረጃ ተሳትፎ አቅምና ተጠያቂነት ማሳደግ በሚል መሪ ቃል የሚከበረውን የሀገር አቀፍ የመረጃ ሳምንት ከመጋቢት 18-22/2015 መነሻ በማድረግ የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሯል፡፡

በመድረኩ ላይ‹‹ጥራት ያለው መረጃ ከሌለ ጥራት ያለው አገልግሎት የለም›› በሚል የጤና መረጃ ሳምንት በመረጃ ላይ ለውጥን ለማምጣት ታላሚ ያደረገ መሆኑን ተገልጿል፡፡

መድረኩ ከዞኑ ጤና መምሪያ ባለሙያዎችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የተከበረ ሲሆን

የመረጃ ጥራት ላይ ችግሮችን ለማስተካከል ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ኃላፊነት መወጣት እንዳለባቸው የተገለፀ ሲሆን ቀጣይ የተሻለ ለዉጥ ለማስመዝገብ በሁሉም መዋቅሮች ለተግባራዊነቱ ልዩ ትኩረት እንዲሰጥ በማሳሰብ የዕለቱ ውይይት ተጠናቅቋል።

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ኮሚዩኒኬሽን

Photos from Kembata Tembaro zone health dep't Health communication's post 02/04/2023

ማህበረሰቡ የሚፈልገውን የጤና አገልግሎት ለሁሉም ለማዳረስ አዲሱ የጤና ኤክስቴንሽን ፍኖታ ካርታ አተገባበር ዙሪያ በየደረጃው በቂ ግንዛቤ መፍጠር ለትግበራው ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ተገለፀ።

በከምባታ ጠምባሮ ዞን ስር በአዲሎ ዙሪያ ወረዳ ጤና ፅ/ቤት አዲሱን የጤና ኤክስቴንሽን ፍኖታ ካርታ ትግበራ ማጠናከሪያ ግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ

በሸሸራ ጤና ጣቢያ ሁሉም የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት

በተላይም የጤና ኬላዎች በመስፈርቱ መሠረት እንደገና ማጥራት፣ የፍኖታ ካርታ አተገባበር መመሪያ፣ የጤና ኬላ ሪፎርም ስታንዳርዶች ትግበራ፣ በጤና ጣቢያዎች የጤና ኤክስቴንሽን ዩኒት ማደራጀትና ማጠናከር እንዲሁም የተዋሃዱ ጤና ኬላዎች ባሉበት ጤና ጣቢያና ቀበሌ ደረጃ የጤና ኤክስቴንሽን ፓኬጆች አተገባበር ዙሪያ

ሰፋ ያሉ ዝርዝር ጉዳዮች ከወረዳው ጤና ፅ/ቤት በቅርቡ በክልሉ ጤና ቢሮ የጤና ኤክስቴንሽን ፍኖታ ካርታ ማጠናከሪያ ስልጠና በሀላባ ዞን ቁሊቶ ከተማ ወስዳው በተመለሱ ባለሙያዎችና የጤ/ፅ/ቤት ኃላፊዎች አማካይነት ቀርቦ

በተሳታፊዎቹ ለተነሱ ጥያቄዎች በቂ ምላሽ ተሰጥቶ ቀጣይ የሚተገብሩትን አክሽን ፖይንቶችን በማዘጋጀትና ለመተግበር የድርሻቸውን ለመወጣት በመስማማት ተጠናቅቋል።

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ኮሚዩኒኬሽን

Photos from Kembata Tembaro zone health dep't Health communication's post 02/04/2023

እናቶች ህይወት እየሰጡ በደም እጦት ህይወታቸውን እኛ እያለን ማጣት የለባቸውም በሚል የግል ውሳኔ ተማሪዎችና መምህራን ደማቸውን በመለገስ አርኣያ መሆናቸው ተገለፀ።

በከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ስር በዱራሜ ከተማ አስ/ር በህጋ አዳሪ ት/ቤት ተማሪዎችና መምህራን አንድም እናት በወሊድ ሳቢያ በሚፈጠር የደም እጦት መሞት የለባትም በሚል በግላቸው ውሳኔ ደም ለመለገሰ ተስማምተው በአንድ ቀን ብቻ 34 ዩኒት ደም በመለገስ ለሌሎች አከባቢ ተማሪዎችና መምህራን አርአያ መሆናቸውን በተግባር ማረጋገጣቸው በምድር ላይ ታላቅ በጎ ሥራ በመሆኑ እጅግ ልመሰገኑ እንደሚገባ የዱራሜ ከተማ አስ/ር ጤና ፅ/ቤት ዘግቧል።

የከምባታ ጠምባሮ ጤና መምሪያ ኮሚዩኒኬሽን

20/03/2023

አዲሱ የአጠቃላይ ጤና ኬላ የጤና አገልግሎት እንዲሰጥ የታቀደው ጤና ኬላ ይህ ከታች የሚትመለከቱት ስሆን በሁሉም ወረዳዎች ቀጣይ 2016 ዓመት በአንድ ወረዳ በአንድ ዓመት 01 ለመገንባት ባጀት በማስያዝ ከጤና ጣቢያ ራቅ ባለ አከባቢ ከሚገኙና መስፈርቱን የሚያሟላ ጤና ኬላ ወደ ሁሉ አቀፍ ጤና አገልግሎት ሰጪነት ለመቀየር የሁሉም ወረዳ ጤና ፅ/ቤት ኃላፊዎችና ዋና አስተዳዳሪዎች እንዲትረባረቡ እናሳስባለን።

Photos from Kembata Tembaro zone health dep't Health communication's post 20/03/2023

በከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ስር በዱራሜ ከተማ አስተዳደር በዱራሜ ጤና ጣቢያ ባለው የቤተሰብ ጤና ቡድን በላሎና ዘራሮ ቀበሌ በተጋላጭነትና በኢኮኖሚ ዝቅተኛ ደረጃ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች አስቀድሞ ሊየታ ከተሠራ በኃላ ተገቢው የጤና አገልግሎት በጤና ጣቢያ ደረጃና ቤት ለቤት ድረስ በመሄድ የህክምናና የጤና ማጎልባት ተግባራት አገልግሎት እየተሠጠ ይገኛል።

Photos from Kembata Tembaro zone health dep't Health communication's post 20/03/2023

በከምባታ ጠምባሮ ዞን ስር በቀዲዳ ጋሜላ ወረዳ በአድሱ ጤና ኤክስቴንሽን ፍኖተ ካርታ ዙርያ ግንዛቤ ማስጨበጨ ስልጠና በሚመለከታቸው አካላት በበቂ ሁኔታ የተሰጠ ሲሆን

ተሳታፊዎችም ጤ/ኤክስቴንሽኖች፣ የወረዳው ፊት አመራር፣ የወረዳው ካብኔ አካላት፣ የጽ/ቤቱ ባለሙያዎች፣ የጤ/ጣ ኃላፊና ትስስር ፎካሎች እና ሌሎችም ተግባሩ የሚመለከታቸው አጋሮች በድምሩ ከ80 በላይ ተሳታፊዎች በተገኙበት ተካሂዷል።

ተሳታፊዎቹም አስተየየት ሰጥተው ለአፈጻጻሙ ሁላችንም የድርሻችንን መወጠት አለብን ብለዋል ::

የወረዳው ጤና ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ግዛቸውም ጎበና መድረኩን የመሩት ስያጠቃልሉ በተሻሸለው ጤና ኬላዎች መሰረት ህብረተሰባችንን ተጠቃሚ ለማድረግ በየደረጃው ኃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል በማለት አጠቃለዋል::

Mobile uploads 20/03/2023

This is Very Inspiring Public health service expansion acoording to public interest.

Photos from Kembata Tembaro zone health dep't Health communication's post 13/03/2023

በየጊዜው የስራ አፈፃፀም ያለበትን ደረጃ በመገምገም ጠንካራ ጎኖችን የማስቀጠልና ሊሻሻሉ የሚገቡ ጉዳዮችን ፈጥኖ በማረም የጤናውን ሴክተር ትራንስፎርሜሽን ዕቅዶችን ለማሳካት መረባረብ እንደሚገባ ተገለፀ።

በከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ስር የሚገኘው የጠምባሮ ወረዳ በጤናው ዘርፍ የ2015 ዓ.ም የሰባት ወራት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን የተግባራት አፈጻፃም ግምገማ ላይ የወረዳው አስፈጻሚ አካላት፣ ጤና ጽ/ቤት የማኔጅመንት አካላት ፣ የጤና ጣቢያ ኃለፊዎች፣ የጤና ኤክሰቴንሽን ባለሙያዎችና ሌሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካለት በተገኙበት በጥልቀት መገምገሙ ተገልጿል።

የዕቅድ አፈጻጸም መድረኩን የመሩት የጤና ጥባቃ ጽ/ቤት ኃለፊ አቶ ታደሰ መኩሪያ የመድረኩ ዋናው ዓላማ ባለሙያው በፕሮግራሙ አፈጻጸም ያጋጠሙትን ተግዳራቶች በራሱ እንዲለይና ችግሮችን ለመፍታት ምን ማድረግ እንዳለበት ማንም ተነግሮለት ሳይሆን በራሱ የመፍትሄ ባለቤት እንዲሆን ለማብቃት የተዘጋጀ የጋራ መድረክ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

በመድረኩ መክፈቻ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የወረዳው ዋና አስተዳደር አቶ አበራ አርፍጦ እንደገለፁት በእናቶችና በህፃናት በተለያ መልኩ በአየር መዛባት ምክንያት የሚስተዋሉ ወቅታዊ በሆነው በሽታ ከመከላከል የተሰሩ ሥራዎች አፈፃፀም ተጠናክሮ እንዲቀጥል በጤናው ዘርፍ ጤናማና አምራች ዜጋ በመፍጠርና በተሰማራንበት በማንኛውም ሙያ መስክ በቅንነት ህብረተሰቡን ማገልገል ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ገልፀዋል።

በመድረኩ ታዳሚዎችም በሽታን መከላከልና ጤናን ማጎልበት ላይ ያተኮረው የጤና ፖሊሲያችን የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራሙን መተግበር ከጀመረ ወዲህ የማህበረሰቡን የጤና አገልግሎት ተጠቃሚነት በወሳኝ መልኩ በመቀየር ረገድ ጉልህ ድርሻ እንደነበረው ገልፀው በቀጣይ ቀሪ ተግባራትን ለማጠናከር የተሻለ መድረክ መሆኑን ገልፀዋል።

የወረደው የጤናው ዘርፍ ባለፉት ሰባት ወራት በዕቅድ የተያዙትን ተግባራት በተገቢው ሁኔታ ሪፖርት ቀርቦ ከተገመገመ በኋላ ያጋጠሙ ችግሮችን በመለየት እንዳይደገሙ ለማድረግ ጠንካራ ስራ እንደሚሠሩና በጥንካሬ የተለዩ አፈጻጸሞችን ደግሞ ወደ ሁሉም ቀበሌዎች እንዲሰፉ ለማድረግ የሚያስችል አቅጣጫ በማስቀመጥ እንደተጠናቀቀ የጠምባሮ ወረዳ ጤና ፅ/ቤት አሳውቋል።

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ኮሚዪኒኬሽን

Photos from Kembata Tembaro zone health dep't Health communication's post 11/02/2023

እናቶች በደም እጦት ህይወት እየሰጡ ህይወታቸውን ማጣት የለባቸውም በሚል አቋም የመንፈሳዊ ኮንፊራንስ ተሰብሳቢዎች ደማቸውን በመለገስ አርኣያ መሆናቸው ተገለፀ።

በከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ስር በቀን 02/06/2015 በዱራሜ ከተማ አስ/ር አንድም እናት በደም እጦት ምክንያት ህይወት እየሰጠች ህይወቷን ማጣት የለባትም በሚል በአንድ ቀን ብቻ በተደረገዉ መንፈሳዊ ኮንፍራንስ ላይ ከተሳተፉ የህብረተሰብ ክፍሎች 75 ዩኒት ደም መሰብሰብ ተችሏል።

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ወንድሙ ዳንኤል ህበረተሰቡ በደም እጥረት የሚከሰተዉን የእናቶችን ሞት ለመከላከል የሚያደርገዉ ትብብር የሚያስደንቅ መሆኑን ተናግረዋል።

አክለውም ሁሉም አካባቢ ይህንን ልምድ ወስዶ ተግባራዊ ማድረግ እንዳለበት አሳስበው ለተደረገው መልካም ተግባር በዞኑ ጤና መምሪያ ስም ምስጋናቸውን ገልፀዋል።

መከላከል በምንችላቸዉ ም፦ኒያቶች የሚከሰተውን የእናቶችን ሞት በጋራ እንከላከል!!!

የከምባታ ጠምባሮ ጤና መምሪያ ኮሚዩኒኬሽን ፎካል ባለሙያ

02/02/2023

በደቡብ ክልል ዕድሜያቸው ከ12_23 ወራት ላሉ ህፃናት የፀረ አንጀት ጥገኛ ትላትል መከላከያ መድሃኒት እደላ በተመረጡ ወረዳዎች ሊጀመር መሆኑ ተገልጿል
በደቡብ ክልል በተመረጡ 7 ወረዳዎች ዕድሜያቸው ከ12_23 ወራት ላሉ ህፃናት የፀረ አንጀት ጥገኛ ትላትል መከላከያ መድሃኒት እደላ የሙከራ ትግበራ ይፍዊ የማስጀመሪያ መርዓ ግብር በሀላባ ከተማ ተካሄዷል
የደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መንግስት ጤና ቢሮ የእናቶችና ህፃናት ጤናና ስርዓተምግብ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተስፍዬ ሌጆሶ በመልዕክታቸው የሆድ ጥገኛ ትላትሎች ህፃናትንና አዋቂዎችን የሚያጠቁ ቢሆንም በአብዛኛዉ በህፃናት ላይ እንደሚበዛ አውስተዋል ፡፡
ከዚህ ቀደም እድሜያቸው ከ5_19 ዓመት ለሞላቸው ህፃናቶችና እንዲሁም እድሜያቸው ከ15_49 ዓመት ለሚገኙ ሴቶች ይሠጥ የነበረው መድሃኒት በተመረጡ ወረዳዎች ላይ የሙከራ ትግበራው ዕድሜያቸው ከ12 -23 ወራት ያሉ ሕጻናት ተደራሽ እንደሚደረጉ በማንሳት ከዚህ ቀድም ሲከናወኑ የቆዩ ልምድና ተሞክሮዎችን በማካተት ለውጤታማነቱ የጋራ ርብርብ ሊደረግበት እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
የደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መንግስት ጤና ቢሮ የእናቶችና ህፃናት ጤናና ስርዓተምግብ ዳይሬክቶሬት ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት ወ\ሮ ገነት ላቀው በበኩላቸው ንጽህናው ያልተጠበቀ ምግብ መመገብ፣ በግልና አካባቢ ንጽህና ጉድለትና በባዶ እግር መሄድና የመሳሰሉት በሽታው እንዲከሰት የሚያደርጉ ዋነኛ ምክንያቶች መሆናቸው ተናግረዋል።
በሽታው የልጆችን አካላዊና አዕምሯዊ እድገት በማቀንጨር አምራችና ጤናማ ዜጋ እንዳይሆኑ ያደርጋልም ይሁን እንጂ የአንጀት ጥገኛ ትላትሎች መከላከያ መድሃኒት እደላ ውጤታማነት በህጻናት አስተዳደግና የመማር ማስተማር ሂደት ላይ ለያጋጥሙ የሚችሉ ተጽዕኖዎችን ለመግታት ያሥችላል ብለዋል፡፡
በመጨረሻም ከመድረኩ አሳቦች ተነስተው ውይይት የተካሄደባቸው ሲሆን የአንጀት ጥገኛ ትላትል ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት በስፋት የሚከሰት የጤና ችግር መሆኑን ይህም በተለይ የግልና የአካባቢ ንጽሕና ጉድለት ፣ የንጹህ ውሃ አቅርቦት ችግር መኖር በተግዳሮትነት እንደሚወሳ አንስተው ይህንንም ተግዳሮት ለመቅረፍ በተለይም በህጣናት ሁለንተናዊ እድገት ላይ የሚያመጣውን ተፅህኖ ለመመከት የፀረ አንጀት ጥገኛ ትላትል መከላከያ መድሃኒት እደላውን የተሳካ ለማድረግ በዘርፉ የተቀመጡ አደረጃጀቶችን በመጠቀም በጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ባሳተፈ መልኩ ተግባራት እንደሚፈፀሙ ማድረግ ይጠበቃል ብለዋል፡፡
የአንጋጫ ወረዳም ለዚህ ሙከራ ፕሮግራም ተጠቃሚ ለመሆን ስለባቃችሁ እንኳን ደስ አላችሁ።

Photos from Kembata Tembaro zone health dep't Health communication's post 01/02/2023

በሁሉም የጤና አገልግሎት ዘርፎች ደረጃውን የጠበቀ እና ጥራት ያለው አገልግሎት ተደራሽ በማድረግ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለፀ።

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ የ2015 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ስድስት ወራት የጤና ልማት ሥራዎች እቅድ አፈፃፀም ግምገማና ምክክር መድረክ ተካሄደ።

በሽታን መከላከል የሚያስችሉ የጤና ልማት ሥራዎችን በጥራትና በፍትሃዊነት ተደራሽ በማድረግ ጤናማና አምራች ዜጋን ለመፍጠር ትኩረት ሠጥቶ እየሠራ መሆኑን የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ወንድሙ ዳንኤል ገለፁ።

መድረኩን የመሩት የመምሪያው ኃላፊ አቶ ወንድሙ ዳንኤል ጤናው የተጠበቀና አምራች ዜጋን ለመፍጠር በሽታን መከላከል የሚያስችል የጤና ልማት ሥራዎች ለህብረተሰቡ በጥራትና በፍትሃዊነት ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን አብራርተዋል።

ለፍትሃዊ ተጠቃሚነትና ለመልካም አስተዳደር ችግር የሚሆኑ ሙስናን እና ብልሹ አሠራርን በማረምና በማስወገድ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የዘርፉ የሥራ ኃላፊዎች፣ ባለሙያዎች፣ ባለድርሻ አካላትና ማህበረሰቡ ተቀራርቦና ተቀናጅቶ መስራት እንዳለበት አቶ ወንድሙ ዳንኤል አክለው አሳስበዋል።

አቶ ወንድሙ ዳንኤል አያይዘውም በጤና ተቋማት በየዘርፉ የሚሠጠው ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ከቁጥር ባሻገር ደረጃውን የጠበቀ ጥራት ያለው እና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችል መሆን አለበት ብለዋል።

የየዘርፉ የሥራ ሂደት አስተባባሪዎች የበጀት ዓመቱን የስድስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት አቅርበው ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን በግማሽ ዓመቱ የጤና ልማት ሥራዎችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በተደረገው ርብርብ የታዩ ጠንካራ አፈፃፀሞች ይበልጥ አጠናክሮ በማስቀጠል እና የታዩ ክፍተቶችን በማረም በቀጣይ አገልግሎቱን በጥራትና በፍትሃዊነት ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት ተሠጥቶ መሠራት እንዳለበት አቅጣጫ በማስቀመጥ የግምገማው መድረክ ተጠናቅቋል።

በመድረኩ የመምሪያው ማናጅመንት አባላትና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ኮሚዩኒኬሽን ፎካል ባለሙያ

Photos from Kembata Tembaro zone health dep't Health communication's post 24/01/2023

የወባ ኬዞችን በመፈተሽ ወባን የማስወገድ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገለፀ።

በከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ስር በሁሉም መዋቅሮች ለሚገኙ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች የወባ ፍተሻ ተሃዲሶ ስልጠና በሁለት ዙር የሚሰጥ በክላስቴር ደረጃ በዳምቦያ፣ በሀዳሮና ዱራሜ ከተማ እየተሰጠ ይገኛል።

ስልጠናው ጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች የወባ በሽታን ለማስወገድ ለሚሠሩ ተግባራት ዙሪያ የተሻለ ግንዛቤና ልምድ ልውውጥ ለማድረግ እንደሚያግዛቸው ተጠቅሷል።

24/01/2023

ለተቋማዊ መርህ ቃል ማስተካከያ እንዲደረግ ማሳሰቢያ ተሰጠ።

በከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ስር ባሉ በሁሉም ጤና ሴክተር መዋቅሮች ላለፉት ጊዜያት በተለያዩ ጉዳዮችና በደብዳቤዎቻችን ስንጠቀምበት የነበረዉ "አንድም እናት በወሊድ ምክኒያት መሞት የለባትም" የምለዉ መፈክር "መከላከል በምንችላቸዉ ምክኒያቶች የሚከሰቱ የእናቶችን ሞት በጋራ እንግታ" or "Let's end preventable maternal death together" በምል የተቀየረ መሆኑን የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ወንድሙ ዳንኤል አሳውቀዋል።

Photos from Kembata Tembaro zone health dep't Health communication's post 21/01/2023

በከምባታ ጠምባሮ ዞን ቃጫ ቢራ ወረዳ ምስራቅ ሌሾ ቀበሌ በዶ/ር ተሾመ አለምቦ ለሚቋቋመው ዶ/ር ተሾመ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ግንባታ ሥራ ማስጀመሪያ የመሠረት ድንጋይ ተጣለ።

የመሠረት ድንጋዩ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የደቡብ ክልል የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪና የፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ባዩሽ ተስፋዬ እና በከምባታ ጠምባሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ መለሠ አጭሶ ተጥሏል።

Congratulations all!!!
Our zonal Medical tourisim, quality care and private public, partineship should be shifted one step Ihead. Share the experience and let's stand together for our community health!!!!

Photos from Kembata Tembaro zone health dep't Health communication's post 18/01/2023

የወባ በሽታን ለመከላከል ሁል ጊዜ በመኝታ ዙሪያ የአልጋ አጎባር በአግባቡ መጠቀም ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ተገለፀ።

በከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ስር በዱራሜ ከተማ አስተዳደር በአጎበር ስርጭትና አጠቃቀም ዙርያ የቅድመ የኦሬንቴሽን መድረክ ተካሄደ።

በመድረኩም በአጎበር አጠቃቀም፣ ስርጭት፣በወባ መከላከያ ዘዴዎች፣በወባ ትንኝ ባህርያት እንዲሁም አገራዊ የአጎባር ሥርጭት ስልቶች፣ የባለድርሻ አካላት ኃላፊነት እና ተግባር ዙርያ እንዲሁም በሌሎችም ርዕሶች ላይ የዞኑ የጤና መምሪያ የወባ ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ተሰማ ታረቀኝ በኩል
ለተሳታፊዎች ቀርቦ ዉይይት ተደርጓል።

መድረኩን የመክፈቻ ንግግር በማድረግ ያስጀመሩት የላሎ ቀበሌ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ተሰማ ተሾመ እንደገለፁት አጎባርን በአግባቡ በመጠቀም ከበሽታው መከላከል እንደሚገባ ጠቁመው ከዚህ ዉጪ አጎባር ከዓላማው ውጪ በሚጠቀሙ አካላት ተገቢውን እርምጃ በመዉሰድ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ትኩረት መስጠት እንደሚገባ አሳስበዋል።

አክለውም የአጎባር ሥርጭቱ በዋናነት በሽታው የሚበዛባቸው አከባቢዎች ቅድምያ በመስጠት ሊሆን ይገባል ብለዋል።

ህብረተሰቡም አጎበርን በተገቢው መንገድ በመጠቀም ከበሽታው መከላከል እንደሚያስፈልግ በኦሬንቴሽን መድረኩ ላይ ተገልጿል።

በመድረኩም የከተማው አመራር አካላት፣የቀጠና አመራሮች፣የጤና ጽ/ቤት ማኔጅመንት አባላት ፣ሁሉም የከተማው ኤክስቴንሽን አባላት፣የዞኑ ጤና መምርያ የዘርፉ ባለድርሻ አካላትን ጨምሮ የሚመለከታቸው ባለድርሻዎች ተሳታፊ መሆናቸውን የዱራሜ አስተዳደር መንግስት ኮሚዪኒኬሽን ዘግቧል።

17/01/2023

The first private Hospital inauguration in Kambat Tembaro zone Kachabira Woreda In Misrak Lesho will be done in the presence of Elders of Kambata as well as Goverment officials plus highly educated Kambats Doctors and professor on 13/05/15 E.C

Congratulation

Photos from Kembata Tembaro zone health dep't Health communication's post 14/01/2023

በማህበረሰብ የጤና መድህን አፈፃፀም የሀዳሮ ከተማ አስተዳደር 1ኛ ደረጃ በመውጣት የተሻለ አፈፃፀም ስላስመዘገበ ዋንጫና ሴርቲፍኬት ተሸላሚ ሆነ።

በክልላዊ ማዐጤመ ንቅናቄ መድረክ በ2014 በጀት አመት አፈፃፀፈም የሀደሮ ከተማ አስተዳደር 100% በማስመዝገብ በክልሉ ካሉት ወረዳዎች 1ኛ በመሆን ክርስታል ዋንጫና ሰርቲፊኬት እወቅና ተሰጥቶታል።

አቶ ወንድሙ ዳንኤል የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ እንደገለፁት ለተመዘገበው ውጤት፣ እውቅናና ሽልማት ስኬት አስተዋፅኦ ላበረከቱት አካላት በሙሉ የሁላችንም ርብርብ ውጤት በመሆኑ እንኳን ደስ አለን ደስ አላችሁ ብለዋል!!!

አክላውም ለመላው የዞናችን የጤናው ሴክተር አመራሮችና ባለሙያዎች እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል!!

ለበለጠ ስኬት እንትጋ!!

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ኮሚዩኒኬሽን ፎካል ባለሙያ

Photos from Kembata Tembaro zone health dep't Health communication's post 13/01/2023

የማኅበረሰብ ዐቀፍ ጤና መድኅን ከፍለው መታከም የማይችሉትን የኅብረተሰብ ክፍል የጤና አገልግሎት ዋስትና በመሆኑ ተገቢውን ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑ ተገለፀ።

በከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ የ2015 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የማኅበረሰብ ዐቀፍ ጤና መድኅን አፈፃፀም ግምገማ መድረክ በዛሬው ዕለት (05/5/2015) በሺንሽቾ ከተማ አካሒዷል።

የግምገማ መድረኩን የመሩት የከምባታ ጠምባሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ መለሰ አጭሶ በማዐጤመ ዘርፍ በዞን ደረጃ የተመዘገበውን ውጤት ተከትሎ በሀገር ደረጃ የተገኘው ዕውቅናና ማበረታቻ የሚያስደስት እና ለቀጣይ አፈጻጸም ይበልጥ የሚያነሳሳ ነው ብለዋል።

በማኅበረሰብ ዐቀፍ ጤና መድህን ተግባር የምናስመዘግበው ስኬት በራሳቸው ከፍለው መታከም የማይችሉ አባላት የጤና ዋስትና በመሆኑ ተገቢው ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ የገለፁት አቶ መለሰ አጭሶ በየመዋቅሩ የሚስተዋለው ዝቅተኛ አፈፃፀምን ፈጥኖ በማረም የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ልናረጋግጥ ይገባል ብለዋል።

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ወንድሙ ዳንኤል የማህበረሰብ ዐቀፍ ጤና መድህን አፈፃፀም ረገድ በመዋቅሮች መካከል የታየው ልዩነትን በማጥበብ እና በግምገማ የተለዩ ችግሮችን በማረም የሚጠበቀውን የዞኑን አማካይ 80 በመቶ ማድረስ አለብን ብለዋል።

እስካሁን ባለው የተሻለ አፈፃፀም ያስመዘገቡ መዋቅሮች የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር፣ የዳምቦያ ወረዳ አስተዳደር፣ የአዲሎ ዙሪያ ወረዳ አስተዳደር እና ዶዮገና ወረዳ አስተዳደር ናቸው ያሉት አቶ ወንድሙ ዳንኤል በመካከለኛ አፈፃፀም የተመዘገቡ አንጋጫ ወረዳ አስተዳደር፣ ቃጫቢራ ወረዳ አስተዳደር፣ ሀደሮ ከተማ አስተዳደር እና ቀዲዳ ጋሜላ ወረዳ መሆናቸውንም ተናግረዋል።

መክፈል ለማይችሉ አባላት ከየመዋቅሩ የሚጠበቀውን ድርሻ በአግባቡ ያለመፈፀም ችግር የተስተዋለ መሆኑን አቶ ወንድሙ ዳንኤል ገልፀው ዶዮገና ወረዳ፣ ቀዲዳ ጋሜላ ወረዳ እና ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር የሚጠበቅባቸውን 30 በመቶ ድርሻ የፈፀሙ መዋቅሮች ሲሆኑ ሌሎች መዋቅሮች ግን ተግባሩን አለመወጣታቸው ዞናዊ አፈፃፀሙ መድረስ ከሚገባው እንዲያንስ ምክንያት መሆናቸውን ገልፀዋል።

የዕለቱ ተሳታፊዎች የዞን አስተባባሪ ኮሜቴ አባላት፣ ዋና አ/ጉባኤ፣ የወረዳ አስተዳዳሪዎች፣ ፓርቲ ሃላፊዎች፣ ጤና ፅ/ቤት ኃላፊዎችና ማዐጤመ አስተባባሪዎች እንድሁም ዞን ጤና መምሪያ ማነጅመንት አባላትና የሆስፒታል ቦርድ ሰብሳብዎች ስሆኑ በቀሪ ጊዜያት አፈፃፀሙን በተሻለ ደረጃ ለማሳደግ እንደሚሠሩ ቃል ገብተው መድረኩ ተጠናቅቋል።

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ኮሚዩኒኬሽን ፎካል ባለሙያ

Photos from Kembata Tembaro zone health dep't Health communication's post 09/01/2023

የእናቶችን ሞት ለመቀነስ የቤተሰብ ዕቅድ ሚናው ወሳኝ መሆኑ ተገልጿል

የጤና ልማት አጋር ድርጅት የሆነው population service International Ethiopia (PSI Ethiopia) የአፍላ ወጣት ጥንዶች የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎት ተጠቃሚነት የብልዕ ጅምር ፕሮግራም (RISE) ለትግበራ ሂደት
ዕውቅና መስጠቱን የደ/ቡ/ብ/ሕ /ክ /መንግስት ጤና ቢሮ አስታውቋል፡፡

population service International Ethiopia (PSI Ethiopia በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/ መንግስት ውስጥ በሚገኙ 12 ዞኖችና በ 4 ልዩ ወረዳዎች ከመደበኛ የጤና አገልግሎት ጋር አጣምሮ እየሰራ የሚገኘው ‹‹የብልህ ጅምር›› ሮድ ማፕ ፎር ኢንቲግሬቲንግ ስማርት ስታርት ኢን ኢትዮጵያ /RISE/ እ .ኤ .አ በ2023 በተጨማሪ 24 ወረዳዎችን ለመተግበር የሚያስችል ይፋዊ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በወላይታ ሶዶ ከተማ አካሄዷል ፕሮጀክቱ ለሚተገበርባቸው በቆዩ ነባር ወረዳዎችና ዞኖች የዕውቅና ሰርተፍኬት ሰጥቷል፡፡

የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎት 2030 ከ18 አመት በታች ያሉ ልጆች እርግዝና አሁን ካለበት 13 በመቶ ወደ 3 በመቶ፣ የቤተሰብ እቅድን እየፈለጉ ማግኘት ያልቻሉትን ደግሞ አሁን ካለበት 22 በመቶ ወደ 17 በመቶ ለማድረስ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን መረጃዎች ያመላክታሉ ፡፡

የዚህ ተግበራ ዕውን መሆን ድሜያቸው ከ15-19 ዓመት መካከል የሚገኙ ያገቡና እና ያላገቡ ወጣቶች የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎት የአፍላ ወጣቶችን እርግዝና ለመቀነስ ጤና ማሻሻል፣ ወጣቶችን በጤና ፣በማህበራዊና፣ ኢኮኖሚያዊ ረገድ የሚያጋጥሟቸውን ተግዳሮቶች መቅረፍ የሚያስችል መሆኑን ተገልጿል፡

የደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/ መንግስት ጤና ቢሮ የእናቶችና ህፃናት ጤናና ስርሃተምግብ አገልግሎቶች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ሌጅሶ የብልህ ምርጫ ሮድ ማፕ ፎር ኢንቲግሬቲንግ ስማርት ስታርት ኢን ኢትዮጵያ /RISE/ በሚል ስያሜ እየተተገበረ በሚገኘው ያለው ወጣት ጥንዶች በስነ ተዋልዶና በቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ዙሪያ በሚሰጣቸውን ምክር አገልግሎት በመታገዝ በምርጫቸው የቤተሰብ እቅድ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማስቻል በሚያገኙት የምክር አገልግሎት የቤተሰብ በእቅድ በመተግበር በጤናቸው፣ በትምህርታቸውና በኢኮኖሚያቸው የተሻለ ደረጃ ላይ እንዲደርሱ ለማድረግ በቀጣይ ያግዛል ብለዋል፡፡

የመንግስትን አቅጣጫና ፖሊሲ በተከተለ መልኩ አገልግሎቱን እየሰጠ የሚገጀው የጤና ልማት አጋር ድርጅት population service International Ethiopia (PSI Ethiopia) የብልህ ጅማሮ (RISE) የምክክርና የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ወጣት እና አፍላ ወጣቶችና ያገቡ ሴቶች የስነልዶ የቤተሰብ እቅድ አገልግሎትን በማረጋገጥ የእናቶችና የህጻናትን ጤንነት ለመጠበቅ ብሎም የኑሮ ጫናን ለመቀነስ የጎላ ጠቀሜታው ድምር ውጤቱ የእናቶችና ህፃናትን ህመምና ሞት ለመቅረፍ ይረዳል አሳብ አስተያየቶች ፕሮጀክ ተፈጻሚ በመሆን ውጤት በተመዘገባበቸው አካባቢዎች የመጡ ተሳታፊዎች ተናረዋል ፡፡

የደ/ቡ/ብ/ሕ /ክ /መንግስት ጤና ቢሮ

Photos from Kembata Tembaro zone health dep't Health communication's post 05/01/2023

የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ተኮር ድጋፋዊ ክትትል እየተደረገ መሆኑ ተገለፀ።

በጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም አማካይነት ተግባራዊ ሲደረጉ የቆዩ ቁልፍ ተግባራት በዋናነት የሴቶች አደረጃጀት የማጠናከርና ለጤና ተግባራት መጠቀም፣ የሴቶች ልማት ቡድን አደረጃጀት መሪዎችን አቅም ማልበት፣ የወረዳ ትራንስፎርሜሽን ትግበራን ማጠናከር፣ በከተሞች የመሰረታዊ ጤና ክብካቤ አገልግሎት ሪፎርም (ቤተሰብ ጤና ቡድን) ተግባራዊ ማድረግ፣ የህብረተሰቡን ተሳትፎና ባለቤትነት ማረጋገጥ፣ የማህበረሰብ አስተያየት መመዘኛ ካርድን መተግበር፣ ለጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች የሥራ ላይ ማነቃቂያ /IRT/ ሥልጠና መስጠት፣ በጤና ተቋማት እና በማህበረሰብ ደረጃ የጤና አጠባበቅ ትምህርት በመስጠት፣ በትምህርት ቤቶች የጤና ፕሮግራምን (School Health Program) በመተግበር በጤና ሞዴል የሆኑ ትምህርት ቤቶችን መፍጠር እና የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ማጠናከሪያ ፍኖተ ካርታን ተግባራዊ ማድረግ ዙሪያ የተሠሩ ሥራዎችን የክልሉ ጤና ቢሮ የጤና ኤክስቴንሽን ቲም የድጋፋዊ ክትትል በከምባታ ጠምባሮ ዞን በዳምቦያ ወረዳ ከዛሬ 27/04/2015 ጀምሮ እየተካሄደ ይገኛል።

በዚህ ጉብኝት ከጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ለማጠናከር በሙከራ የሚተገበሩ ፕሮግራሞች ባሉባቸው ዱራሜ ከተማ እና ሀዳሮ ከተማ ጭምር እንደሚካሄድ ይጠበቃል።

በድጋፋዊ ክትትሉ የዞን፣ የወረዳና ጤና ጣቢያ ጤና ኤክስቴንሽን ፎካሎች ጭምር ተሳትፈዋል።

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ኮሚዩኒኬሽን ፎካል ባለሙያ

Photos from Kembata Tembaro zone health dep't Health communication's post 05/01/2023

የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ተኮር ድጋፋዊ ክትትል እየተደረገ መሆኑ ተገለፀ።

በኤክስቴንሽን ፕሮግራም አማካይነት ተግባራዊ ሲደረጉ የቆዩ ቁልፍ ተግባራት በዋናነት የሴቶች አደረጃጀት የማጠናከርና ለጤና ተግባራት መጠቀም፣ የሴቶች ልማት ቡድን አደረጃጀት መሪዎችን አቅም ማልበት፣ የወረዳ ትራንስፎርሜሽን ትግበራን ማጠናከር፣ በከተሞች የመሰረታዊ ጤና ክብካቤ አገልግሎት ሪፎርም (ቤተሰብ ጤና ቡድን) ተግባራዊ ማድረግ፣ የህብረተሰቡን ተሳትፎና ባለቤትነት ማረጋገጥ፣ የማህበረሰብ አስተያየት መመዘኛ ካርድን መተግበር፣ ለጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች የሥራ ላይ ማነቃቂያ /IRT/ ሥልጠና መስጠት፣ በጤና ተቋማት እና በማህበረሰብ ደረጃ የጤና አጠባበቅ ትምህርት በመስጠት፣ በትምህርት ቤቶች የጤና ፕሮግራምን (School Health Program) በመተግበር በጤና ሞዴል የሆኑ ትምህርት ቤቶችን መፍጠር እና የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ማጠናከሪያ ፍኖተ ካርታን ተግባራዊ ማድረግ ዙሪያ የተሠሩ ሥራዎችን የክልሉ ጤና ቢሮ የጤና ኤክስቴንሽን ቲም የድጋፋዊ ክትትል በከምባታ ጠምባሮ ዞን በዳምቦያ ወረዳ ከዛሬ 27/04/2015 ጀምሮ እየተካሄደ ይገኛል።

በዚህ ጉብኝት ከጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ለማጠናከር በሙከራ የሚተገበሩ ፕሮግራሞች ባሉባቸው ዱራሜ ከተማ እና ሀዳሮ ከተማ ጭምር እንደሚካሄድ ይጠበቃል።

በድጋፋዊ ክትትሉ የዞን፣ የወረዳና ጤና ጣቢያ ጤና ኤክስቴንሽን ፎካሎች ጭምር ተሳትፈዋል።

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ኮሚዩኒኬሽን ፎካል ባለሙያ

Photos from Kembata Tembaro zone health dep't Health communication's post 04/01/2023

የጤና ሴክተር ትራንስፎርሜሽን ፅቅዶችን በውጤታማነት ለማሳካት የመልካም ተሞክሮ ልምድ ልዉዉጥ ማካሄድ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ተገለፀ፡፡

በከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ በቀን 25/4/2015 ዓ/ም የዞኑ ጤና መምሪያ ከተላያዩ የተመረጡ ጤና ጣቢዎች ከተዉጣጡ ኃላፊዎችና የሆስፒታል ኃላፊዎችና ከዉስን ወረዳና አብዛኞቹ ከተማ አስተደዳር ጤና ጽ/ቤት ኃላፊዎች፤ እንድሁም የዞን ጤና መምሪያ የማኔጅመንት አባላት ተሳታፊ ተጋባዦች ባሉበት በዋሰራ ካቶልክ ጤና ጣቢያ የልምድ ልዉዉጥ ተደረገ።

ይህንን መድረክ የመሩት የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ወንድሙ ዳንኤል የልምድ ልውውጥ አስፈላጊነቱንም ስገልጹ አብዛኞዎቹ የመንግስት ጤና ተቋማት መንግስት በርካታ የአሰራር ህደቶችንና ብቁ ባለሙያዎችን ቀጥሮ ስራዉን እንዲከናወን እያደረገ ቢሆንም ከነባርና ቁርጠኛ ሁነዉ በህሙማን አያያዝ ስርዓትና ድስፒሊን፣ የላቀ አገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት፣ የህክምና ማዕከላትን ንጹህ አድሮጎ በመያዝና ለተገልጋይ የመንፈስ እርካታና ከተላላፊ በሸታ ምንጭ እንዳይሆኑ በማድረግ ከፍተኛ ተምሳሌት ከሆኑት ጤና ጣቢያዎች አንዱ የሆነዉን የዋሰራ ካቶሊክ ጤና ጣቢያን መጎብኘትና ለሌሎች አስተማሪ የሆኑ ስራዎችን በጉብኝቱ ወቅት ለማየት እንደተቻለ ገልፀዋል፡፡

በተጎበኘዉ ዋሰራ ካቶልክ ጤና ጣቢያ የነፍሰጡር እናቶች የሚሰጠዉ የቅድመ ወሊድ ህክምና ክትትል፣ በእርግዝና ምክንያት የሚከሰቱ የጤና መቃወስን ልየታ ስርዓትና ከተለዩም በኋላ የክትትል አግባብ፣ በቅድመ ወሊድ ወቅት ለእናት ተገቢ ምርመራዎችን በበቂ ሁኔታ ማድረግ፣ ከጤና ጣቢያዉ አቅም በላይ ሲሆን ወደ ሆስፒታል የመላክ ሁኔታ፣ የህጻናት ክትባት አሰጣጥና የክትባት የቅዝቃዜ ሠንሰለት አያያዝ፣ የወላዶች ህክምና አሰጣጥና አያያዝ፣ የላቦራቶሪ ምርመራ ክፍል አሰራር፣ የመድሃኒት አቅርቦትና መድኃኒት ለታካሚዎች ከተዘዘላቸዉ በኋላ የሚጠበቀዉን ምክር አሟልተዉ ከማማከር አንጻር ያሉትን መልካም ተሞክሮዎችን ጎብኝዎቹ ልምድ ልዉዉጥ አድርገዉ እንደ መልካም ተሞክሮ ለማየት ችለዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ጤና ጣቢያዉ ከግቢ ንጽህና አያያዝ፣ የህክምና ክፍሎ ንጽህና አያያዝ እና የህክምና መገልገያ መሳሪያዎችን ከበሽታ አምጪ ህዋሳት ነጻ የማድረግን /sterilization / ሂደት፣ የታካሚዎች መረጃ አያያዝ ማለትም ከካርድ ክፍል አንስቶ ያለዉ ነገር እንከን የማይወጣለት እንደሆነ በጉብኝቱ ወቅት ለማየት ተችሎአል፡፡

ከጉብኝቱ በኋላም ከተሳታፊዎች በተሰጠዉ አስተያየቶች ጤና ጣቢያዉ በዞኑ ዉስጥና ዉጭ ላሉት ጤና ድርጅቶች እንደ ልምድ ልዉዉጥና የመልካም ተሞክሮ ማዕከል መሆን እንደሚችልና ከጤና ጣቢያዉ ባለሙያዎች ለስራ ባለቸዉ ተነሳሽነትና ቁርጠኝነት፣ በቡድን ስሜት የመስራት ሂደት፣ ለግቢዉ ጽዳት የተቀጠሩት ሰራተኞች ቢኖሩም የየክፍሉ ሰራተኛ ለያንዳንዱ ክፍል ንጽህና አያያዝ የሰጡትን ትኩረት እጅግ አድንቀዋል፡፡

በማጠቃለያዉም የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ወንድሙ ዳንኤል ሁሉም የጉብኝቱ ተሳታፊዎች ወደየመዋቅሮቻቸዉ ስመለሱ ይህንን መልካም ተሞክሮ በየጤና ጣቢያዎቻቸዉና በየሆስፒታሎቻቸዉ እንዲያሰፉና ባለሙያዎች በመልካም ስነምግባር የተሞሉ ሲሆኑ በርካታ ተግባራትን ማሳካት እንደሚቻልና ለሁሉም ተግባር ቁልፍ ጉዳይ ብሩህ አመለካከት ይዞ ወደ ተግባር መግባትና ተገልጋይ ተኮር የሆነ የባለሙያ ተነሳሽነት መኖር እንዳለበት አሳስበዋል፡፡

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ኮሚዩኒኬሽን ፎካል ባለሙያ

Photos from Kembata Tembaro zone health dep't Health communication's post 31/12/2022

እንኳን ደስ አላችሁ!!!!

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተደረገው የጤና መድህን ጉባኤ ላይ የተሻለ አፈፃፀም በማስመዝገቡ ከኢፌዴሪ ጤና ሚኒስተር የላፕቶፕ ኮምፕውተርና ሰርቲፊኬት እንዲሁም የዳንቦያ ወረዳ የሞተር ሳይክልና ሰርቲፊኬት ተሸላሚ መሆናቸው ተውቋል።

የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ወንድሙ ዳንኤል ለዚህ ተግባር ስኬማነት አስተዋፅኦ ላደረጉ የዞናችን ዋና አስተዳዳሪውንና አመራሮቻቸዉን፣ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች፣ የጤና መምሪያ ማነጅመንትና ባለሙያዎች፣ የወረዳና ከተማ አስተዳዳር ጤና ሴክተር አመራሮችንና ባለሙያዎችን ከልብ ማመስገናቸውን አሳውቀዋል ።

አክለውም ቀጣይም ከዚህ ለበለጠ ስኬት ለመድረስ እንትጋ!! ድሉ ይቀጥላል!! ብለዋል።

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ኮሚኒኬሽን ፎካል ባለሙያ

Photos from Kembata Tembaro zone health dep't Health communication's post 31/12/2022

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ የ5 ቀናት የተቀናጀ የኩፍኝ መከላከያ ክትባት አፈፃፀም በመምሪያው ኃላፊ ቢሮ በዛሬው ዕለት ግምገማ ተደረገ። ታህሣሥ 22/2015፡ ዱራሜ

የኩፍኝ ክትባትና ሌሎች ተግባራት ዘመቻ የ5 ቀን ውሎ አፈፃፀም ኩፍኝ መከላከያ ክትባት 109%፣ ቫይታሚን ኤ 106%፣ ዲወርሚንግ 104% እና ከ5 ዓመት በታች ህፃናት ስነ ምግብ እጥረት ሊየታ 111% የህብረሰብ ክፍሎች በዘመቻው ተጠቃሚ ማድረግ የተቻለ መሆኑ ተውቋል።

የዞኑ የተቀናጀ የኩፍኝና ሌሎች ተግባራት ዘመቻ የ5 ቀናት አፈፃፀሙ የተሻለ መሆኑንና በቀሪ ቀናት የተንጠባጠቡ ህፃናት ለቃማ አገልግሎትና መረጃ የመጥራት ተጠናክሮ ማስቀጣልና ቀሪው ዕቅድ በማሳካት ውጤታማ፣ ፍትሓዊና ጥራቱን ተጠብቆ እንዲሚሠራ የመምሪያው የእናቶችና ህፃናት ጤናና ስርዓተ ምግብ ዳ/ዳይሬክተር አቶ ማርቆስ ጉርማሞ አሳስበዋል።

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ኮሚዩኒኬሽን ፎካል ባለሙያ

Photos from Kembata Tembaro zone health dep't Health communication's post 30/12/2022

ህብረሰቡ በጤና ኬላዎች የጤና ኤክስቴንሽ ፕሮግራም ቀጥተኛ ተጠቃሚነቱን በማመኑ የጤና ኬላዎችን አጥር እያጣረ መሆኑ ልመሳገን እንደሚገባ ተገለፀ።

በከምባታ ጠምባሮ ዞን ስር በቀዲዳ ጋሜላ ወረዳ በደጋ ቀዲዳ ቀበሌ ጋሜላ ጤና ኬላ የተቀናጀ ኩፍኝ ክትባት ዘመቻ በእቅዱ መሠረት እየተሠራ በዚሁ ዘመቻ ጎን ለጎን የማህበረሰብ ተሳትፎ ስራዎችም ተጠናክረው መቀጠላቸው ተውቋል።

የወረዳው ጤና ፅ/ቤት የቀበሌውን አመራር በማስተባበር የአከባቢውን ማህበረሰብ በማነቃነቅ ታህሣስ 20/2015 ማለትም አድስ የተገነባውን የጋሜላ ጤና ኬላ ያለአጥር ባዶ ሜዳ ለይ የሚገኛውን ማህበረሰቡ በራሱ ተነሳሽነት ወጥቶ ጤና ኬላው እንድታጠር ተደረገ።

ከዚህም የተነሳ ህብረተሰቡ ወንድ ሴት ሳይል በቤቱና በማሳው የሚገኘውን ከእንጨት ጀምሮ አስፈላጊውን ቁሳቁስ ይዞ በነቂስ በመወጣት ከ30 ሺህ ብር በላይ ወጪ የሚገመት አጥር ሊታጠር ተችሏል።

በጉዳዩ ይህ ነው የማይባል ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ አካላት ማለትም የጤና ፅ/ቤት ኃላፊዎች፣ የቀበሌው ዋና አስተዳዳሪ፣ የቀበሌው አመራር አካላት፣ የጋሜላ ት/ት ቤት ር/ማምህር እንዲሁም የአከባቢው ማህበረሰብ ልመሳገኑ እንደሚገባቸው የወረዳው ጤና ፅ/ቤት ኮሚዩኒኬሽን ፎካል ባለሙያ አቶ ተሾመ ዮሐንስ ዘግቧል።

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ኮሚዩኒኬሽን ፎካል ባለሙያ

Photos from Kembata Tembaro zone health dep't Health communication's post 30/12/2022

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ከዞኑ ወረዳ ደጋፊ ባለሙያዎች፣ ማኔጅሜንት አባላትና ከክልል ጤና ቢሮ ለድጋፋዊ ክትትል ከመጡ ባለሙያዎች ጋር የ4 ቀናት ውሎ አፈፃፀም በመምሪያው ኃላፊ ቢሮ ግምገማ ተደረገ።

የኩፍኝ ክትባትና ሌሎች ተግባራት ዘመቻ የአራት ቀን ውሎ አፈፃፀም ኩፍኝ መከላከያ ክትባት 86%፣ ቫይታሚን ኤ 88%፣ ዲወርሚንግ 86%፣ ከ5 ዓመት በታች ህፃናት ስነ ምግብ እጥረት ሊየታ 96%፣ የእግር ወደ ውስጥ መቆልመም ሊየታ የተደረጉ ሁሉም 15 ስሆኑ (ከነዚህ ከ5 ዓመት በታች 8፣ ከ2 ዓመት በታች 5)፣ የሽንትና ሠገራ መቀላቀል ችግር ያለባቸው ሴቶች ሊየታ (ከወሊድ ጋር የተያያዘ ፌስቱላ) #2፣ የጎኒዮሽ ጉዳት የታየባቸው #103፣ መደበኛ ክትባት ተጠቃሚ የሆኑ ህፃናት ከ300 በላይ እንዲሁም የኮቪድ 19 መከላከያ ክትባት የወሰዱ ከ1000 በላይ የህብረሰብ ክፍሎች በዘመቻው ተጠቃሚ መሆናቸው ተገለፀ።

የዞኑ የተቀናጀ የኩፍኝና ሌሎች ተግባራት ዘመቻ የአራት ቀናት አፈፃፀሙ የተሻለ መሆኑንና በቀሪ ቀናት የተንጠባጠቡ ህፃናት ለቃማ አገልግሎትና መረጃ የመጥራት ተጠናክሮ ማስቀጣልና ቀሪው ዕቅድ በማሳካት ውጤታማ፣ ፍትሓዊና ጥራቱን ተጠብቆ ለማሳካት እንደሚሠራ የመምሪያው ኃላፊ አቶ ወንድሙ ዳንኤል አሳውቀዋል።

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ኮሚዩኒኬሽን ፎካል ባለሙያ

29/12/2022

በከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ስር በቃጫ ቢራ ወረዳ በተቀናጀ የኩፍኝ መከላከያ ክትባትና ሌሎች ተግባራት ዘመቻ በወንኮ ቀበሌ ቆልማማ እግር ችግር ያለባት የ4 ዓመት ህፃን ፆታዋ ሴት መለየቱን የወረዳው ጤና ፅ/ቤት አሳውቋል።

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ኮሚኒኬሽን ፎካል ባለሙያ

Photos from Kembata Tembaro zone health dep't Health communication's post 29/12/2022

በከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ የተቀናጀ የኩፍኝ ክትባትና ሌሎች ተግባራት ዘመቻ የሦስት ቀን ውሎ አፈፃፀም ከዞኑ ወረዳ ደጋፊ ባለሙያዎች፣ ማኔጅሜንት አባላትና ከክልል ጤና ቢሮ ለድጋፋዊ ክትትል ከመጡ ባለሙያዎች ጋር በመምሪያው ኃላፊ ቢሮ ግምገማ ተደረገ።

የዞኑ የተቀናጀ የኩፍኝና ሌሎች ተግባራት ዘመቻ የሦስት ቀናት ሁሉም ቀበሌያት አፈፃፀም የተገመገመ ስሆን የ3ቱም ቀን የዞኑ አማካይ አፈፃፀም የኩፍኝ መከላከያ ክትባት ሽፋን 65% ስሆን አፈፃፀሙ የተሻለ መሆኑንና በቀጣይ አጠናክሮ ለማስቀጣልና ቀሪው ዕቅድ ለማሳካት እንደሚሠራ የመምሪያው ኃላፊ አቶ ወንድሙ ዳንኤል አሳውቀዋል።

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ኮሚዩኒኬሽን ፎካል ባለሙያ

Photos from Kembata Tembaro zone health dep't Health communication's post 28/12/2022

በከምባታ ጠምባሮ ዞን ስር በቃጫ ቢራ ወረዳ በተቀናጀ የኩፍኝና ሌሎች ተግባራት ዘመቻ ለማስፈፀም በተደረገው ጠንካራ የማህበረሰብ ቅስቄሳ በየቤታቸው የተደበቁ የእግር ወደ ውስጥ መቆልመም ችግር ያለባቸው ህፃናት ሊየታ ተጠናክሮ እየተሠራ መሆኑን የቃጫ ቢራ ወረዳ ጤና ፅ/ቤት አሳውቋል።

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ኮሚዩኒኬሽን ፎካል ባለሙያ

Want your practice to be the top-listed Clinic in Durame?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Category

Telephone

Address

SNNPR
Durame
SBCC
Other Medical & Health in Durame (show all)
KT ZHD_Health promotion and communication KT ZHD_Health promotion and communication
Durame

Halaba Zone_Health Department

Durame Health Center Durame Health Center
Durame
Durame