Wolaita District Customer Service and GrivanceRedorsal
Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Wolaita District Customer Service and GrivanceRedorsal, Government Organization, አብርሃም ሆቴል አጠገብ, Sodo.
በወላይታ ዲስትሪክት የደንበኞች አገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል ይሰጥ የነበረው ስልጠና ዛሬ ተጠናቀቀ ።
ከ02/06/2013 እስከ 04/06/2013
ለክቡራን ደንበኞቻችን በሙሉ
************
ዛሬ ህዳር 15 ቀን 2013 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ጀምሮ ባጋጠመን የቴክኒክ ችግር ምክንያት በኢትዮጵያ በአብዛኛው አካባቢ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጧል፡፡
በቴክኒክ ችግር የተቋረጠውን ኃይል ለመመለስ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የቴክኒክ ሠራተኞች ከፍተኛ ርብርብ በማድረግ ላይ ይገኛሉ።
በመሆኑም ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንን ተገንዝባችሁ ተቋሙ ችግሩ ሙሉ ለሙሉ እስኪፈታው ድረስ በትግዕስት እንድትጠባበቁ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ፤ ፈጣን መረጃ ያግኙ።
https://t.me/eeuethiopia
ደቡብ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከቀን 14/3/13 እስከ 15/3/13 ድረስ የ4 ወራት አፈጻጸም ግምገማ እና በቀጣይ ተግባር አስመልክቶ ውይይት አካሄደ ።
በውይይቱም ያህል ዲስትሪክት ኃላፊዎች ፣የዲስትሪክት ደንበኞች አገ /ኃላፊዎች እና ዲስትሪቪዪሽን ኃላፊዎች ተካፍለዋል ።
የወላይታ ዲስትሪክት ማኔጅሜንትና ሠራተኞች ስብሰባ አካሄደ
የስብሰባዉ ትኩረት
1_ የ2013 በጀት ዓ.ም ሩብ ዓመት አፈፃፀም ግምገማ እና የቀሪ ወራት ተግባራት ላይ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል
_አስተማማኝና ያልተቆራረጠ ኤሌክትሪክ ለዘጎች ማድረስ
_አዲስ ኃይል ጠያቂዎችን በማስተናገድ የደንበኛን ቁጥር መጨመር
_የገንዘብ ስብሰባ ማሣደግ
_በመሠረተ ልማት ላይ እየደረሰ ያለው ጉዳት መከላከል
በእነዚህ አጀንዳዎ ሠፊ ውይይት:አስተያየቶች ተካሂዷል
በተጨማሪም በርካታ ጥያቄዎች ተነስቶ ሁሉም የሥራ ኃላፊዎ ምላሽ ሰጥተዋል ::
መጨረሻም በበጀት ዓመቱ ቀሪ ወራቶች የተጣለብንን ለመፈፀም ሁሉም የዲስትሪክቱ ማኔጅሜንትና ሠራተኞች ቃል በመግባት የአቋም መግለጫ በማሰማት ስብሰባ ተጠናቅቋል ::
በኢ/ኤ/ አ ለወላይታ ዲስትሪክት ሠራተኞችና ማናጅሜንት አባላት በሙሉ:_
ዲስትሪክታችን በ2013 ዓ/ም የተጣለበት ተቋማዊ ብሎም ሀገራዊ ግዴታዎችን እንዲሁም ሀላፊነቱን ለመወጣት ከመቼውም ጊዜ በላይ ርብርብ በማድረግ ላይ እንደሚንገኝ ይታወቃል :: ከዚህ ጋር በተያያዘ በበጀት የ1ኛ ሩብ ዓመት ወይም የዝግጅት ምዕራፍ አፈፃፀም እና የቀሪ ትግበራ ምዕራፍ በተመለከተ ውይይት ለማድረግ ዝግጅት አጠናቅቀናል ::
ስለሆነም ጥቅምት 07/2013 ከጧት 2:30 ሠዓት በወላይታ ጉተራ አዳራሽ እንድትገኙ እያሳሰብን ሁሉም ተሰብሳብ ከወቅታው ወረርሽ ከሆነው ኮሮና /COVID19/ ቫይረስ ራሱን/ሷ ለመጠበቅ አገርቷ ያወጣችው ደንብ እና የጤና ሚንስተር ያወጣው አዋጅና መመሪያ በማክበር "ርቀትዎን በመጠበቅ :የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ /ማስክ/ እንዲትገኙ ጥሪ እናስተላልፋለን ::
ለተሻለ አገልግሎት የተዘጋጀ ሠራዊት ለማፍራት በሚደረገው ተቋማዊ እንቅስቃሴ የበኩላችንን አሻራ እናሳርፋለን::
የታቀደ የቆጣሪ ንባብ ብዛትና የአንባቢ ብዛት ፤
· በድርጅቱ በጸደቀው እና በሰው ሀብት ስራ አስፈፃሚ በቀን የካቲት 15/2009 ዓ.ም በደብዳቤ ቁጥር 68.4/289/09 በተላለፈው መሠረት አንድ አንባቢ በቀን 100 ወይም በወር 2200 ቆጣሪዎችን በአማካይ ማንበብ አለበት፡፡
· ከቆጣሪ ንባብ በተጨማሪ ቆጣሪውንና ተዛማጅ እቃዎች ደህንነታቸውን የተጠበቀ እና ህገወጥ ተግባር ያልተፈጸመባቸው መሆኑን በየስምሪቱ ማረጋገጥ እና ድርጊቱ መፈጸሙን ሲጠራጠር ወዲያውኑ ለሚመለከተው አካል ሪፖረት ማድረግ አለበት፡፡ እያንዳንዱ አንባቢ በማእከሉ ስር ያሉ በወቅቱ ቢላቸውን ያልከፈሉ ደንበኞችን በየግሩፑ በመለየት የቆረጣ ቅጠላ ስራን ሰነድ በማዘጋጀት ቆረጣ ቅጠላ ስራ ትዕዛዝን ለማዕከል ኃላፊው በማፀደቅ ማከናወን አለበት፡፡
· በተጨማሪም የማዕከሉን የቢል ሽያጭ እና ገንዘብ ስብሰባ አፈፃፀም በየወሩ መከታተል እና ቆረጣ ቅጠላ ስራ በየወሩ ትኩረት በመስጠት የቢል ሽያጭ አፈፃፀም እንዲጨምር የራሱን አስተዋፅዎ ማድረግ አለበት፡፡
ስለሆነም የቆጣሪ ንባብ አወሳሰድ ድርጅቱ ተግባራዊ በሚያደረገው የመተግበሪያ SOFT WARE/APPLICATION/ በተጫነለት የቆጣሪ ንባብ መውሰጃ መሳሪያ/ CMRI (Common Meter Reading Instrument) ቴክኖሎጂ ብቻ መሆን አለበት በተባለው መሰረት በማዕከላት ላይ በስታንዳርዱ መሰረት የተሟላ የአንባቢ ቁጥር መኖር አስፈላጊ በመሆኑ ከዲስትሪክት የተላከውን መረጃ ከዚህ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡ በመሆኑም ዲስትሪክቶች የተጓደሉትን የአንባቡ ቁጥር በመለየት በዲስትሪክታቸው የሰው ኃይል አስተዳደር ጋር በኩል በአፋጣኝ የሚሟላበት ሁኔታ እንዲፈጠርና ትግበራው እንዲጀመር በማለት እንጠያቃ
ውድ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ደንበኞች በሙሉ:-
የምንም ጊዜ አገልጋያችሁ የሆነው ተቋማችን ለደንበኞቹ ጊዜ ቆጣቢ እና ዘመናዊ የክፍያ አማራጭ ይዞ ቀርቧል ::
በዚህ አማራጭ ጊዜያችሁንና ጉልበታችሁ በመቆጠብ እንዲትጠቀሙ እያሳሰብን
1_በሲቢኢ ብር ባሉበት ሆነው መክፈል
2_ከባንክ አካዉንትዎ ቀጥታ እንዲከፈል ማድረግ
እና ሌሎች አማራጮችን ለክቡራን ደንበኞች እነሆ ብሏልና ተገልገሉበት እንላለን ::
ውድ ጊዜዎት በአግባቡ ይጠቀሙ
ወዲደአሽግሪ
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Website
Address
S**o
Ligaba
S**o
በብቃት እና በጥረት የተካኑ ወጣቶችን ለማፍራት እንተጋለን !