Arada FM 95.1 - አራዳ ኤፍኤም 95.1

This is the official page of AradaFm 95.1 Infotainment Radio station.

18/04/2024

ጆ ባይደን በቻይና የብረት ምርቶች ላይ የሚጣለው ቀረጥ ከፍ እንዲል ጠየቁ

ሚያዝያ 10፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ወደ አሜሪካ በሚገቡ የቻይና የተወሰኑ ምርቶች ላይ የሚጣለው ቀረጥ ከፍ እንዲል ጥሪ አቀረቡ።

ባይደን በቻይና የተወሰኑ የብረት እና አሉሚኒየም ምርቶች ላይ የሚጣለው ቀረጥ በሦስት እጥፍ ከፍ እንዲል ጥሪ አቅርበዋል።

ባይደን ቻይና የብረትና አሉሚኒየም ምርቶቿን ወደ አሜሪካ ገበያ በርካሽ ዋጋ በገፍ ታስገባለች የሚል እምነት አላቸው።

ይህ መሆኑ ደግሞ የዋሺንግተንን አምራች ኩባንያዎች ገበያና የሥራ እድል ፈጠራን በከፍተኛ ሁኔታ እየጎዳ ነው በሚል በተደጋጋሚ ትችት ሲያቀርቡ ይስተዋላል።

ለዚህም አስፈላጊው ቁጥጥር ሊደረግ ይገባል በሚል የቀረጥ ጭማሪ ምክረ ሃሳባቸውን አቅርበዋል።

ኋይት ሃውስጥ በፕሬዚዳንት ባይደን የቀረበው ሃሳብ የአሜሪካን ገበያ እና የሥራ እድል ፈጠራ ከአላስፈላጊ የገበያ ውድድር ለመጠበቅ ያለመ መሆኑን ገልጿል።

በፔንሲልቫኒያ ለብረት ኢንዱስትሪ ማህበር ሰራተኞች ባደረጉት ንግግርም፥ ቻይና ምርቶቿን የምታቀርብበት ዋጋ “ባልተገባ መልኩ በጣም ዝቅተኛ” ነው ሲሉ ኮንነዋል።

መንግስታቸው ትርፍን ሳያስብ የብረት ኢንዱስትሪውን ቢደጉምም ቻይና ተገቢ ባልሆነ የገበያ ፉክክር ጉዳት እያስከተለች ነው ሲሉም ኮንነዋል።

በገበያው “እነርሱ መርህን አያከብሩም” ያሉት ባይደን “ጥፋቱንም እዚሁ በአሜሪካ እያየነው ነው” ሰሉ በምሬት ገልጸዋል።

በፈረንጆቹ 2000 መጀመሪያ ላይም የቻይና የብረት ምርቶች ወደ አሜሪካ በብዛት መግባታቸውን ተከትሎ በኢንዱስትሪው በመቶ ሺህዎች ሥራ መፍታታቸውን አስታውሰዋል።

አሁን ላይ ይህ በድጋሚ እንዲሆን አንፈቅድም ብለዋል ባይደን በንግግራቸው።

ቻይና በበኩሏ በአሜሪካ የሚቀርብባትን ውንጀላ በተደጋጋሚ ስታስተባብል ቆይታለች።

በዋሺንግተን የቻይና ኤምባሲም በባይደን የቀረበውን ምክር ሃሳብ ተቃውሞታል።

የኤምባሲው ቃል አቀባይ ሊዩ ፔንግዩ ይህን መሰሉ እርምጃ የሃገራቱን ግንኙነት ብሎም ዓለም አቀፉን ኢኮኖሚ የሚጎዳ ነው በሚል ሃሳቡን ተቃውመዋል።

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም መሰል ውጥረቶች የዓለም ኢኮኖሚን የሚጎዳና የዋጋ ግሽበትን ወደ አላስፈላጊ አቅጣጫ የሚወስድ አደገኛ አካሄድ ነው ሲል አስጠንቅቋል።

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

Photos from Arada FM 95.1 - አራዳ ኤፍኤም 95.1's post 18/04/2024

ቤተልሔም ወልዴ በማንዴላ አፍሪካን ቦክሲንግ ሻምፒዮና አሸነፈች

ሚያዝያ 10፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) በማንዴላ አፍሪካ ቦክሲንግ ካፕ ሻምፒዮና ከደቡብ አፍሪካ አቻዋ ጋር የተጫወተችው ቤተልሄም ወልዴ ተጋጣሚዋን በበቃኝ አሸንፋለች።

የመላው አፍሪካ ሻምፒዮኗ ቤተልሄም ወልዴ በሁለተኛ ዙር ላይ ተጋጣሚዋ ላይ ሀይለኛ ቡጢ በማሳረፍ በዳኛ ውሳኔ አሸናፊ መሆኗን የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመላክታል።

በወንዶች ምድብ ኢትዮጵያን የወከሉት አቡዱሰላም አቡበከር፣ አቡበከር ሰፋን እና ኤርሚያስ መስፍን በተጋጣሚዎቻቸው ተሸንፈዋል።

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

Photos from Arada FM 95.1 - አራዳ ኤፍኤም 95.1's post 18/04/2024

በቻምፒየንስ ሊጉ ባየርሙኒክ እና ሪያል ማድሪድ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቀሉ

ሚያዝያ 10፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) በአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የሩብ ፍፃሜ የመልስ ጨዋታዎች
ምሽት ተካሂደዋል።

ወደ አሊያንዝ አሬና ያቀናው አርሰናል በባየርሙኒክ ተሸንፎ ከግማሽ ፍጻሜው ቀርቷል።

ጨዋታውን ጆሹዋ ኪሚች ባስቆጠራት ጎል ሙኒክ 1 ለ 0 አሸንፏል።

ውጤቱን ተከትሎም ሙኒክ በድምር ውጤት 3 ለ 2 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል።

በሌላው የምሽቱ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ እና ሪያል ማድሪድ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።

በድምር ውጤት አራት አቻ መሆናቸውን ተከትሎ ወደ መለያ ምት አምርተው ሪያል ማድሪድ 4 ለ 3 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል።

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

17/04/2024

ኢትዮጵያ ከፍተኛ የተባለ የኮሌራ ወረርሽኝ እያስተናገደች መሆኗን የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ

ሚያዝያ 9፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) ኢትዮጵያ በታሪኳ ከፍተኛ የተባለ የኮሌራ ወረርሽኝ እያስተናገደች እንደምትገኝ የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ።

የዓለም ጤና ድርጅት በኢትዮጵያ ለሚያካሂደው ሥራ አስቸኳይ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያስፈልገውም ገልጿል።

የድርጅቱ ዳይሬክተር ቴድሮስ አድሐኖም ድጋፉ የማይገኝ ከሆነ ድርጅታቸው በሀገሪቷ የሚያከናውነውን ከጤና ጋር የተገናኝ ሥራ ለመቀጠል እንደሚቸገር ተናግረዋል።

ዶክተር ቴድሮስ የተስፋፋ ድርቅና በሽታ በሚሊየን የሚቆጠሩ አትዮጵያውያንን ሕይወት አደጋ ላይ መጣሉንም አስረድተዋል።

በተለይም በትግራይ፣ አማራ፣ ኦሮሚያና ሌሎች አካባቢዎች የተፈጠረው ግጭት እና ጦርነት የከፋ ጉዳት አድርሷል ነው ያሉት።

በርካታ የጤና ተቋማት እና መሰረተ ልማቶች ላይ ውድመት መከሰቱን አስታውሰው የተለያዩ ወረርሽኞች መከሰታቸውንም ጠቅሰዋል።


የዓለም ጤና ድርጅት በኢትዮጵያ በሥምንት ክልሎች 41 ሺህ ሰዎች በኮሌራ በሽታ መያዛቸውንም ገልጿል።

በሽታው በዚህ ልክ በኢትዮጵያ ሲከሰት በታሪኳ ከፍተኛው እንደሆነም ነው ድርጅቱ የገለጸው።

ወባና ኩፍኝም ሌሎቹ ወረርሽኞች መሆናቸውን የጠቀሰው ድርጅቱ፥ በኢትዮጵያ ለሚያከናውነው የበሽታ መከላከልና ጤና አጠባበቅ ሥራ አፋጣኝ የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግለት ጥሪ አቅርቧል።

በበየነ ወልዴ

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

17/04/2024

የሚኒስትሮች ምክር ቤት የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲን አጸደቀ

ሚያዝያ 9፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 30ኛ መደበኛ ስብሰባው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።

ምክር ቤቱ በሀገሪቱ በተለያዩ ዘመናት የተከሰቱ እና የቀጠሉ ተደራራቢ እና ሰፊ የተጎጂና የአጥፊ ወሰን ያላቸው የሰብአዊ መብት ጥሰቶች፣ የእርስ በእርስ ግጭቶች፣ ያልጠሩ ትርክቶች እና በደሎችን ለመፍታት የተለያዩ ሙከራዎች መደረጋቸውን አስታውሷል።

ሆኖም እነዚህ አሰራሮች በእውነት፣ በዕርቅ፣ በምህረት እና በፍትሕ ላይ የተዋቀረ እና በግልፅ ፖሊሲ የሚመራ ሁለንተናዊ የሽግግር ፍትሕ ስልትን አካታች፣ሰብአዊ መብት ተኮር በሆነ እና በተሰናሰለ መንገድ ባለመተግበራቸው የሚፈለገውን ዘላቂ መፍትሔ ማምጣት አልቻሉም ብሏል።

ስለሆነም የሽግግር ፍትሕ ሂደቱን በተደራጀ፣ በተቀናጀ እና ውጤታማ በሆነ መልኩ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመምራትና ለመተግበር እንዲቻል ረቂቅ ፖሊሲ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል።

ምክር ቤቱም በዛሬው እለት ባደረገው ስብሰባ በረቂቅ ፖሊሲው ላይ ከተወያያ በኋላ ግብዓቶችን በማከል ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ በሥራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል።
ምክር ቤቱ ከዚህ በተጨማሪም የመንግስት ሠራተኞች አስተዳደርን ነጻ፣ ገለልተኛ፣ ቀልጣፋ፣ ተደራሽነት እና ተጠያቂነት ላይ የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት፥ እንዲሁም ከጊዜው ጋር የሚራመድ የአሰራር ስርአት ለመዘርጋት የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ ላይ ተወያይቶ ለህዝብ አንደራሴዎች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል።

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

17/04/2024

21ኛው የባህል ስፖርቶች ውድድርና 17ኛው የባህል ፌስቲቫል በአዲስ አበባ ይካሄዳል

ሚያዝያ 9፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) 21ኛው የባህል ስፖርቶች ውድድርና 17ኛው የባህል ፌስቲቫል በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ አስተናጋጅነት ይካሄዳል።

በውድድሩና በፌስቲቫሉ ላይ ከ300 በላይ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች እንደሚሳተፉ ተገልጿል።

በ21ኛው የኢትዮጵያ ባህል ስፓርቶች ውድድር እና 17ኛው የባህል ፌስቲቫል ላይ ከ300 በላይ በጎ ፈቃደኞች ይሳተፋሉ ተብሏል።

ዝግጅቱ ከሚያዝያ 12 እስከ ሚያዝያ 20 ቀን ድረስ ነው የሚካሄደው።

በተስፋወርቅ ልዑልሰገድ

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

17/04/2024

የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከ27 ሚሊየን ብር ከቅጣት መሰብሰቡን አስታወቀ

ሚያዝያ 9፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 27 ሚሊየን 194 ሺህ 567 ብር ከቅጣት ገቢ ማግኘቱን ገልጿል።

ገቢው በዘጠኝ ወራት ውስጥ በከተማዋ ከተፈጸሙ የተለያዩ የደንብ ጥሰቶች የተሰበሰበ መሆኑን አራዳ ሰምቷል።

በዚህ ጊዜ ውስጥ በድምሩ ከ34 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ያገኘ ሲሆን፥ በ7 ሚሊየን 228 ሺህ 686 ብር ደግሞ የመንግስት ግዢ መፈጸሙን አስታውቋል።

ባለስልጣኑ ህገወጥ ግንባታ፣ ህገወጥ የመሬት መስፋፋት፣ ህገ ወጥ እንስሳት ዝውውርና እርድ እንዲሁም አዋኪ ድርጊቶች ላይ ቁጥጥር እያደረገ መሆኑን አመላክቷል።

በእንቁጣጣሽ ኃይለማርያም

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

Photos from Arada FM 95.1 - አራዳ ኤፍኤም 95.1's post 17/04/2024

ጠንካራ ፉክክር የሚታይባቸው የቻምፒየንስ ሊግ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎች ምሽት ይደረጋሉ

ሚያዝያ 9፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) በአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የሩብ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት ይደረጋሉ።

በምሽቱ ሁለት ተጠባቂ ጨዋታዎች በጀርመን እና እንግሊዝ ሲካሄዱ፥ ባየር ሙኒክ ከአርሰናል እንዲሁም ማንቼስተር ሲቲ ከሪያል ማድሪድ ጋር የሚያደርጉት ፍልሚያ ይጠበቃል።

የሰሜን ለንደኑ ክለብ ወደ ጀርመን አቅንቶ ከባቫሪያኑ ክለብ ባየር ሙኒክ ጋር ከባዱን ጨዋታ ያደርጋል።

ጨዋታው ከአርሰናል ወቅታዊ አቋም እና ከባየርሙኒክ የካበተ የቻምፒየንስ ሊግ ልምድና በጥሎ ማለፉ ያለው የአሸናፊነት ታሪክ አንጻር ከባድ ፍልሚያ ይደረግበታል ተብሎ ይጠበቃል።

በመጀመሪያው ጨዋታ ኢሚሬትስ ላይ ጨዋታው ሁለት አቻ ሲጠናቀቅ የሙኒክ ልምድና በተለይ ጠንካራ የነበረው የአርሰናል ተከላካይ ክፍል ተደጋጋሚ ስህተቶች የተንጸባረቁበት ነበር።

ሁለቱ ክለቦች በተገናኙባቸው አጋጣሚዎች የጀርመኑ ክለብ የተሻለ የአሸናፊነት ታሪክ ያለው ሲሆን፥ ያለፉት ሦስት ተከታታይ ጨዋታዎችም በተመሳሳይ በሙኒክ የ5 ለ 1 አሸናፊነት የተጠናቀቁ ነበሩ።

በምሽቱ ጨዋታ በሙኒክ በኩል በመጀመሪያው ጨዋታ ያልተሰለፈው ቶማስ ሙለርን ጨምሮ መጠነኛ ጉዳት አለባቸው የተባለት ማኑዌል ኑዌር እና ሊሮይ ሳኔ እንደሚሰለፉ ይጠበቃል።

በተቃራኒው የግራ መስመር ተከላካዩ አልፎንሶ ዴቪስ በተመለከተው የማስጠንቂያ ቢጫ ካርድ ምክንያት እንዲሁም ሳር፣ ቦይ፣ ኪንግስሊ ኮማን እና ናብሪ በጉዳት ምክንያት አይሰለፉም ተብሏል።

በአንጻሩ በአርሰናል በኩል ወሳኝ ተጫዋቾቹ ማርቲን ኦዴጋርድ እና ቡካዮ ሳካ በጉዳት ምክንያት መሰለፍ አለመሰለፋቸው እስካሁን አልታወቀም።

በቡንደስሊጋው የ11 ዓመታት የሻምፒዮንነት ጉዞው የተገታው ሙኒክ ቻምፒየንስ ሊጉ ብቸኛ የዋንጫ ተስፋው ሲሆን፥ በአንጻሩ አርሰናል በፕሪሚየር ሊጉ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ሆኖ የዛሬውን የመልስ ጨዋታ ያደርጋል።

‘ኳስ እረፍት አልበራትም’ በተባለበት የመጀመሪያው የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ በርናባው ላይ ሦስት አቻ የተለያዩት ሪያል ማድሪድ እና ማንቼስተር ሲቲ በሌላኛው የምሽቱ ጨዋታ መርሐ ግብር በኢቲሃድ ይፋለማሉ።

ሁለቱ ክለቦች እስካሁን በዚህ መድረክ ዘጠኝ ጊዜ ሲገናኙ ሲቲ አራት ጊዜ ሲያሸንፍ ማድሪድ ሦስት እንዲሁም ቀሪ አራት ጨዋታዎችን በአቻ ውጤት አጠናቀዋል።

ማንቼስተር ሲቲ ሪያል ማድሪድን በደርሶ መልስ 5 ለ 1 በማሸነፍ ዋንጫውን በታሪኩ ለመጀመሪያ ዘጊ ያሳካበት ውጤት የቅርብ ጊዜ የክለቦቹ የመጨረሻ ግንኙነት ነበር።

በወቅቱ በማድሪድ ሜዳ ባደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ ሲለያዩ በመልሱ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ 4 ለ 0 በማሸነፍ በድምር ውጤት 5 ለ 1 በሆነ ውጤት ለፍጻሜ መቅረቡ ይታወሳል።

ቀደም ባለው ዓመት በነበራቸው ግንኙነትም በግማሽ ፍጸሜው ተገናኝተው በሜዳቸው ሁለቱም ሲያሸንፉ፥ ሪያል ማድሪድ በደርሶ መልስ ውጤት 6 ለ 5 በማሸነፍ የፍጻሜ ተፋላሚና ሻምፒዮን መሆኑ አይዘነጋም።

ማንቼስተር ሲቲ በዛሬው ጨዋታ አሸንፎ ሪያል ማድሪድን ከመንገዱ ማስቀረት ከቻለ፥ ማድሪድን በጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች በተከታታይ የጣለ ሁለተኛው ክለብ ይሆናል።

ከዚህ ቀደም የጣሊያኑ ኤሲ ሚላን ማድሪድን በግማሽ ፍጻሜ (1988-1989) እና በጥሎ ማለፍ ሁለት (1989-1990) ተከታታይ ዓመታት ከመንገዱ በማስቀረት ቀዳሚው ክለብ ነው።

በጨዋታው በሪያል ማድሪድ በኩል ኦረሊየን ቹዋሜኒ በተመለከተው ተከታታይ የማስጠንቀቂያ ቢጫ ካርድ ምክንያት በጨዋታው አይሰለፍም።

በመጀመሪያው ጨዋታ ተጠባባቂ የነበረው ኤደር ሚሊታኦ ወይም ናቾ ፈርናንዴዝ በዛሬው ጨዋታ ከአንቶኒዮ ሩዲገር ጋር ቹዋሜኒን ተክተው ሊጣመሩ ይችላሉ እየተባለ ነው።

በማንቼስተር ሲቲ በኩል በመጀመሪያው ጨዋታ ‘በህመም’ ምክንያት ተጠባባቂ የነበረው አማካዩ ደ ብሩይነ ዛሬ እንደሚሰለፍ ታውቋል።

ከዚህ ባለፈም በጉዳት ከጨዋታ ውጭ የነበሩት ናታን አኬ እና ካይል ወከር እንዲሁም ግብ ጠባቂው ኤደርሰን ወደ ቡድኑ መመለሳቸው ለማንቼስተር ሲቲ መልካም ዜና ሆኗል።

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

17/04/2024

ለኢትዮጵያ ሰብአዊ ድጋፍ የሚውል ከ600 ሚሊየን ዶላር በላይ ቃል ተገባ

ሚያዝያ 9፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ለኢትዮጵያ ሰብአዊ ድጋፍ የሚውል ገንዘብ ለመሰብሰብ ባካሄደው ዝግጅት ከ600 ሚሊየን ዶላር በላይ ቃል ተገብቷል።

ተመድ በኢትዮጵያ ለአስቸኳይ ጊዜ ሰብአዊ ድጋፍ የሚሆን 1 ቢሊየን ዶላር ለማሰባሰብ አቅዶ ነበር የተነሳው።

ይሁንና ትናንት በጄኔቫ በተካሄደው ዝግጅት ላይ ቃል የተገባው ከ630 ሚሊየን ዶላር የተሻገረ አይደለም ተብሏል።

የተመድ ሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (ኦቻ) የአስቸኳይ ጊዜ ድጋፉ በድርቅ፣ በጎርፍና በጦርነት ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች የሚውል ነው ብሏል።

ኦቻ እንዳለው ከሆነ በጦርነት እና በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ ከ21 ሚሊየን በላይ ኢትዮጵያውያን ሰብአዊ ድጋፍ ይፈልጋሉ።

ከመጪው ሐምሌ እስከ መስከረም ባሉት ወራት 10 ነጥብ 8 ሚሊየን ዜጎች የከፋ የምግብ ችግር ሊያጋጥማቸው እንደሚችልም ቢሮው ገልጿል።

ይህን ከወዲሁ ለመከላከል በተደረገው የገቢ ማሰባሰብ አሜሪካ 253 ሚሊየን ዶላር፣ ብሪታንያ 124 ነጥብ 58 ሚሊየን ዶላር እና የአውሮፓ ሕብረት 46 ነጥብ 6 ሚሊየን ዶላር ቃል በመግባት ቀዳሚ መሆናቸውን የሬውተርስ ዘገባ መረጃ ያመላክታል።

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1



ሚያዝያ 9፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ለኢትዮጵያ ሰብአዊ ድጋፍ የሚውል ገንዘብ ለመሰብሰብ ባካሄደው ዝግጅት ከ600 ሚሊየን ዶላር በላይ ቃል ተገብቷል።

ተመድ በኢትዮጵያ ለአስቸኳይ ጊዜ ሰብአዊ ድጋፍ የሚሆን 1 ቢሊየን ዶላር ለማሰባሰብ አቅዶ ነበር የተነሳው።

ይሁንና ትናንት በጄኔቫ በተካሄደው ዝግጅት ላይ ቃል የተገባው ከ630 ሚሊየን ዶላር የተሻገረ አይደለም ተብሏል።

የተመድ ሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (ኦቻ) የአስቸኳይ ጊዜ ድጋፉ በድርቅ፣ በጎርፍና በጦርነት ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች የሚውል ነው ብሏል።

ኦቻ እንዳለው ከሆነ በጦርነት እና በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ ከ21 ሚሊየን በላይ ኢትዮጵያውያን ሰብአዊ ድጋፍ ይፈልጋሉ።

ከመጪው ሐምሌ እስከ መስከረም ባሉት ወራት 10 ነጥብ 8 ሚሊየን ዜጎች የከፋ የምግብ ችግር ሊያጋጥማቸው እንደሚችልም ቢሮው ገልጿል።

ይህን ከወዲሁ ለመከላከል በተደረገው የገቢ ማሰባሰብ አሜሪካ 253 ሚሊየን ዶላር፣ ብሪታንያ 124 ነጥብ 58 ሚሊየን ዶላር እና የአውሮፓ ሕብረት 46 ነጥብ 6 ሚሊየን ዶላር ቃል በመግባት ቀዳሚ መሆናቸውን የሬውተርስ ዘገባ መረጃ ያመላክታል።

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

17/04/2024

ዓለም በጉጉት የሚጠብቀው የህንድ ጠቅላላ ምርጫ ከነገ በስቲያ ይጀመራል

ሚያዝያ 9፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) የህንድ ጠቅላላ ምርጫ ከነገ በስቲያ ዓርብ ይጀመራል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ለሦስተኛ ዙር የሥልጣን ዘመን በሚወዳደሩበት ምርጫ ወደ 1 ቢሊየን የሚጠጉ ህንዳውያን ድምፅ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ለ44 ቀናት የሚዘልቀው ምርጫ በሰባት ደረጃዎች በሚካሄድ የድምፅ አሰጣጥ፥ 543 የሎክ ሳብሃ (የህንድ የታችኛው ምክር ቤት) አባላት ምርጫ ይካሄዳል።

በምርጫው ከሃገሪቱ ኢኮኖሚ ከፍ ያለውን ሃብት ያመነጫል የሚባለው የደቡብ ህንድ ክፍል ከፍ ያለ ተፅዕኖ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።

ይህ ክልል ከህንድ ጠቅላላ የሃገር ውስጥ ምርት እድገት ውስጥ 30 በመቶውን እንደሚያመነጭ መረጃዎች ያመላክታሉ።

ከዚህ አንጻርም በዚህ አካባቢ የተሻለ ድምፅ ያገኘ ተወዳዳሪ ቀጣዩን የሃገሪቱን መንግስት አስተዳደር የመመስረት እድሉ የሰፋ እንደሚሆን ነው ከድምጽ አሰጣጡ በፊት ከህዝብ የተሰበሰቡ አስተያየቶችን ዋቢ ያደረጉት አልጀዚራና ቢቢሲ ያስነበቡት።

የህንድ 20 በመቶ ህዝብ በሚገኝበት በዚህ ክልል ታሚል ናዱ፣ ካርናታካ፣ አንድራ ፕራዴሽ፣ ኬራላ እና ቴላንጋ ግዛቶች የሚገኙ ሲሆን፥ የጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ባሃራቲያ ጃንታ ፓርቲም በዚህ አካባቢ ተቀባይነቱ ከፍ ያለ መሆኑን ዘገባው አመላክቷል።

በፈረንጆቹ ሰኔ 1 ቀን የሚጠናቀቀው ድምፅ አሰጣጥ ውጤት ከሦስት ቀናት በኋላ ይፋ የሚደረግ ሲሆን፥ ህንድ ካላት ከ2 ሺህ 500 በላይ ፓርቲዎች ውስጥ 86 በመቶው የምክር ቤት መቀመጫ በ10 ፓርቲዎች ብቻ መያዙን ዘገባው ጠቅሷል።

በምርጫው የጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ፓርቲን ጨምሮ በዋናነት አምሥት ተቀናቃኝ ፓርቲዎች ብርቱ ፉክክር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የሞዲ 'ባሃራቲያ ጃንታ ፓርቲ' ዓለም ላይ 180 ሚሊየን አባላት ያሉት ትልቁ ፓርቲ ሲሆን፥ ጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲም የሂንዱ እምነት ተከታዮች በሚበዙባት ሰሜናዊ ፕራዴሽ ግዛት በምትገኘው ቫርናሲ ከተማ ይወዳደራሉ።

‘የህንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች አያት’ የሚባለውና በ1885 የተመሰረተው 'ኢንዲያን ናሽናል ኮንግረስ ፓርቲ' በምርጫው ሌላው ተፎካካሪ ሲሆን፥ ህንድን ከነጻነት በኋላ ረዘም ላለ ጊዜ የመራና በአብዛኛው በነጻ አስተሳሰብ የሚመራ እና ሐይማኖታዊ ዕሳቤን መሰረት ያደረገ እንደሆነ ይነገርለታል።

ሌላኛው 'ዓም ዓዳሚ ፓርቲ' ዋነኛው ተፎካካሪ ሲሆን፥ በፈረንጆቹ 2011 ከተነሳው የህንድ የፀረ ሙስና እንቅስቃሴ የተገነጠለና ጠንካራ የሐይማኖት አስተምህሮ ባላቸው ፖለቲከኞች እንደሚመራ ይነገራል።

'ድራቪዳ ሙነትራ ካዣጋም' ፓርቲም በምርጫው ተፎካካሪና በፓርላማው ሦስተኛው በርካታ የመቀመጫ ወንበር ያለውና በደቡባዊ የሃገሪቱ ክፍል ጠንካራ ድጋፍ ያለው መሆኑ ነው የሚነገረው።

አራተኛው ግዙፍ ፓርቲ ነው የሚባለው 'ኦል ኢንዲያን ትሪናሙል ኮንግረስም' በዚህ ምርጫ ጠንካራ ዕጩዎች ያሉትና በተለይም በቤንጋል ግዛት የናሬንድራ ሞዲ ፓርቲ መቀመጫ እንዳይኖረው ያደረገ መሆኑ ዘገባው ያመላክታል።

ህንድ ካላት የህዝብ ቁጥር፣ እያደገ ካለው ኢኮኖሚዋ፣ አማራጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ከመሆኗ እና ትልቅ የገበያ ፍላጎት ያለባት ከመሆኗ አንጻር በርካታ ሃገራት በአጋርነት ይፈልጓታል።

በተጨማሪም የሃገሪቲ ጂኦ ፖለቲካዊ አቀማመጥ፣ የቆዳ ስፋትና እየተገበረች ያለውን አማራጭ የኢንቨስትመንት ማበረታቻ ተከትሎ፥ የዓርቡ ምርጫ ዓለም ላይ አይንና ጆሮ መሳቡ አይቀሬ ነው።

ከዚህ ባለፈም ህንድ ከፖለቲካዊ ዕሳቤ አንጻር የሰፋ ልዩነት አላቸው የሚባሉ ሃገራትን በእኩል በማስተናገድ ወዳጅና አጋር አድርጋ መያዟም ካላት የህዝብ ቁጥርና የገበያ ፍላጎት ጋር ተዳምሮ መዳረሻ ሊያደርጉ የሚፈልጉ ሃገራት ምርጫውን በጉጉት ይጠብቁታል።

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

17/04/2024

የአሜሪካ እና የቻይና መከላከያ ሚኒስትሮች ከወራት በኋላ ተወያዩ

ሚያዝያ 9፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) የአሜሪካ እና የቻይና መከላከያ ሚኒስትሮች ከወራት በኋላ የመጀመሪያቸው ነው የተባለውን ውይይት አድርገዋል።

የአሜሪካው መከላከያ ሚኒስትር ሎይድ ኦስቲን እና የቻይናው አቻቸው ዶንግ ጁን በ18 ወራት ውስጥ የመጀመሪያ ውይይታቸውን በቪዲዮ ኮንፈረንስ አካሂደዋል።

በውይይታቸው ወቅትም የሃገራቱን ወታደራዊ ግንኙነት ማደስ በሚቻልበት አግባብ ላይ መምከራቸውን አልጀዚራ ዘግቧል።

ሎይድ ኦስቲን ከደቡባዊ ቻይና ባህር ጋር በተያያዘ ዓለም አቀፉን ህግ ባከበረ መልኩ በአካባቢው የመንቀሳቀስ መብትን ማክበር ያለውን ጠቀሜታ በተመለከተ ገለጻ አድርገዋል።

የቻይናው መከላከያ ሚኒስትር ዶንግ ጁን በበኩላቸው፥ ዋሺንግተን የቤጂንግን ሉዓላዊነት፣ የባህር ኃይል ነጻነትን እና በደቡባዊ ቻይና ባህር ያላትን ጥቅምና ፍላጎት ልታከብር ይገባል ብለዋል።

ከዚህ ባለፈም የቀጠናውን ሰላም ለማረጋገጥ ተጨባጭ እርምጃ ልትወስድ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

ቻይና ሉዓላዊ ግዛቴ ናት ከምትላት ታይዋን ጋር በተያያዘም አሜሪካ ያላትን አቋም ልታጤነው እንደሚገባ አሳስበዋል።

የታይዋን ጉዳይ የቻይና ውስጣዊና የራሷ ጥቅምና የፍላጎት ጉዳይ እንጅ፥ አሜሪካን የሚመለከት አይደለም ሲሉም ነው የገለጹት።

አሜሪካ እና ቻይና ከደቡባዊ ቻይና ባህር እና በታይዋን ጉዳይ ከረር ያለ ዲፕሎማሲያዊ ፍጥጫ ውስጥ መግባታቸው ይነገራል።

ቻይና ደቡባዊ ቻይና ባህርም ሆነ ታይዋን የቻይና ግዛት አካል እና የቤጂንግ ውስጣዊ ጉዳይ ነው በሚል አሜሪካ ያላትን ጣልቃ ገብነት ታቆም ዘንድ በተደጋጋሚ ጠይቃለች።

አሜሪካ በበኩሏ ቻይና የራሷን ፍላጎት በሌሎች ላይ በመጫን አላስፈላጊ መስፋፋት እያደረገች ነው በሚል ‘ዓለም አቀፍ ህጎች ይከበሩ’ ስትል ትደመጣለች።

ደቡባዊ ቻይና ባህርን ብሩነይ፣ ማላይሲያ፣ ፊሊፒንስ እና ቬትናም የግዛታችን አካል ነው በሚል የባለቤትነት ጥያቄ ያነሱበታል።

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

17/04/2024

አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት በኢራን ላይ አዲስ ማዕቀብ ሊጥሉ ነው

ሚያዝያ 9፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት በኢራን ላይ አዲስ ማዕቀብ እንደሚጥሉ አስታወቁ።

ማዕቀቡ ቴህራን እስራዔል ላይ የፈጸመችውን ጥቃት ተከትሎ የሚጣል መሆኑንም ገልጸዋል።

የአሜሪካ ግምጃ ቤት ኃላፊ ጃኔት ያለን አሜሪካ በመጪዎቹ ቀናት በቴህራን ላይ አዲስና ተጨማሪ ማዕቀብ ትጥላለች ብለዋል።

በቀጣዮቹ ቀናት ማዕቀብ እንጥላለን ብለን እንጠብቃለን ያሉት ኃላፊዋ፥ “ኢራን ለሽብር የምታደርገውን ድጋፍ ማቋረጥ የሚያስችሉ ሁሉም አማራጮች እጃችን ላይ አሉ” ብለዋል።

አያይዘውም የኢራን የድፍድፍ ነዳጅ ሽያጭ ሊታይ የሚገባው መሆኑን ጠቅሰው፥ አሁንም ኢራን ድፍድፍ ነዳጅ እያቀረበች በመሆኑ በዚህ ላይ ሊሰራ የሚገባው ሥራ ይኖራልም ነው ያሉት።

የአውሮፓ ህብረት የውጭ ጉዳዮች እና ደህንነት ኃላፊው ጆሴፍ ቦሬል በበኩላቸው፥ ህብረቱ ተጨማሪ አዲስ ማዕቀብ ለመጣል እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በኢራን ላይ ማዕቀብ እንዲጣል የሚጠይቀው የአባል ሃገራቱ ፍላጎትም እየጨመረ መሆኑን አስረድተዋል።

እስራዔል ቅዳሜ ሌሊት ከተፈጸመባት ጥቃት በኋላ አጋር ሃገራት ኢራን ላይ ማዕቀብ እንዲጥሉ ስትጠይቅ ቆይታለች።

የእስራዔል ጦር ኢታማዦር ሹም ሌተናንት ጄኔራል ኸርዚ ሃልቬይ፥ የኢራን ጥቃት ምላሽ ያሻዋል ሲሉ ተደምጠዋል።

ቴል አቪቭ ሃገራት በኢራን ላይ ከዚህ ቀደም ከጣሉት በተጨማሪነት አዳዲስ እና ሰፋ ያሉ ማዕቀቦች እንዲጣሉ እየወተወተች ሲሆን፥ የኢራን ብሔራዊ አብዮታዊ ዘብም በአሸባሪነት እንዲፈረጅ ጠይቃለች።

ከዚህ ቀደም ተመድን ጨምሮ አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት በኢራን የድፍድፍ ነዳጅ ሽያጭ እና የሚሳኤል ፕሮግራም ላይ ማዕቀብ ቢጥሉም፥ ማዕቀቡ የተፈለገውን ያክል ውጤታማ እንዳልሆነ ይነገራል።

ለዚህ ደግሞ ኢራን በተዘዋዋሪ የነዳጅ ሽያጭ ማከናወኗ እና ከእይታ ውጭ በሆነ መንገድ የሚሳኤል ፕሮግራሟን ማበልጸግ መቀጠሏ ምክንያት መሆኑ ይነገራል።

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

17/04/2024

ንግድ ባንክ ያለአግባብ ተወስዶ ከነበረው ገንዘብ ውስጥ 95 በመቶውን ማስመለሱን አስታወቀ

ሚያዝያ 9፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መጋቢት 7 ቀን 2016 ዓ.ም ከተከሰተው የሲስተም ችግር ጋር በተገናኘ ያለአግባብ ተወስዶ ከነበረው ገንዘብ ውስጥ 95 በመቶ የሚሆነውን ማስመለሱን አስታውቋል።

ባንኩ ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ ጋር በተገናኘ በተጠቀሰው ዕለት በተፈጠረ ችግር ምክንያት 801 ሚሊየን 417 ሺህ 747 ብር ከ81 ሣንቲም ያለአግባብ ተወስዶ እንደነበር መገለፁ ይታወሳል።

ከተወሰደው ገንዘብ ውስጥ 762 ሚሊየን 941 ሺህ 341 ብር ማስመለስ መቻሉን ባንኩ በማኅበራዊ ትስስር ገፁ ባወጣው መረጃ አስታውቋል።

ይህም መሰብሰብ ከነበረበት ገንዘብ ውስጥ 95 በመቶ የሚሸፍን ሲሆን ቀሪውን 38 ሚሊየን 474 ሺህ 938 ብር የማስመለስ ሥራ እንደሚቀጥልም ገልጿል።

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

Photos from Arada FM 95.1 - አራዳ ኤፍኤም 95.1's post 17/04/2024

ዶርትመንድ እና ፒ ኤስ ጂ የግማሽ ፍጻሜ ተፋላሚ ሆነዋል

ሚያዝያ 9፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) በአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የሩብ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታዎች ትናንት ምሽት ተደርገዋል።

በካምፕ ኑ ፒ ኤስ ጂን ያስተናገደው ባርሴሎና የፓርክ ደ ፕሪንሱን ውጤት ሳያስጠብቅ ከሩብ ፍጻሜው ቀርቷል።

ከሳምንት በፊት ፓሪስ ላይ 3 ለ 2 ያሸነፉት ብሉናግራዎች ትናንት ምሽት በሜዳቸው 4 ለ 1 ተሸንፈዋል።

በጨዋታው ሮናልድ አራኡሆ ቡድኑ እየመራ በነበረበት ሰዓት በሰራው ጥፋት በቀይ ካርድ ከሜዳ መውጣቱ የባርሴሎና አጨዋወት ላይ የራሱን ተፅዕኖ አሳርፏል።

ራፊንሃ ለባርሴሎና የቀዳሚነቷን ጎል ሲያስቆጥር፥ ኦስማን ደምበሌ፣ ፖርቹጋላዊው አማካይ ቪቲንሃ እና ኪሊያን ምባፔ (2) ለፒ ኤስ ጂ የድል ጎሎቹን አስቆጥረዋል።

በመጀመሪያው ጨዋታ ባርሴሎና 3 ለ 2 ከሜዳው ውጭ ያሸነፈ ሲሆን፥ ፒ ኤስ ጂ በድምር ውጤት 6 ለ 4 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል።

በሌላኛው የምሽቱ ጨዋታ ደግሞ በሜዳው አትሌቲኮ ማድሪድን ያስተናገደው ቦሩሲያ ዶርትመንድ ግማሽ ፍጻሜውን መቀላቀሉን አረጋግጧል።

ዶርትመንድ የምሽቱን ጨዋታ 4 ለ 2 ሲያሸንፍ፥ ጁሊያን ብራንዲት፣ ኢያን ማትሰን፣ ኒክላስ ፈልክረግ እና ማርሴል ሳቢትዘር የዶርትመንድን ጎሎች አስቆጥረዋል።

ማትህ ሃመልስ (በራሱ መረብ) እንዲሁም አንሄል ኮሬዓ የአትሌቲኮ ማድሪድን ማስተዛዘኛ ጎሎች ሲያስቆጥሩ፥ ውጤቱን ተከትሎ ዶርትመንድ 5 ለ 4 በማሸነፍ የግማሽ ፍጻሜ ተፋላሚ መሆኑን አረጋግጧል።

ቦሩሲያ ዶርትመንድ እና ፒ ኤስ ጂም በግማሽ ፍጻሜው እርስ በእርስ መገናኘታቸውን አረጋግጠዋል።

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

16/04/2024

ቡናን የሚያጠቁ በሽታዎች ወደ አራት ከፍ ማለታቸው ስጋት ደቅኗል ተባለ

ሚያዝያ 8፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) በሀገሪቱ ከፍተኛ የምንዛሬ ምንጭ የሆነውን ቡና የሚያጠቁ በሽታዎች ቁጥር ወደ አራት ከፍ ማለታቸውን በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢስቲትዩት ስር የሚገኘው የጅማ ምርምር ማዕከል ገለፀ።

መንግስት በዘርፉ ለሚሰሩ ስራዎች ትኩረት ካልሰጠ ኢትዮጵያ ቡና ልታጣ ትችላለች ሲሉ በምርምር ማዕከሉ የቡና በሽታ ተመራማሪው ጋቢሳ ግዴሳ ለአራዳ ተናግረዋል።

ተመራማሪው ከ15 ዓመታት በፊት በሃገሪቱ ቡናን የሚያጠቁ ዋና ዋና በሽታዎች ሦስት ብቻ እንደነበሩ ጠቅሰው፥ አሁን ላይ ቁጥሩ ወደ አራት ከፍ ማለቱ በሀገሪቱ ዋነኛ የምንዛሬ ምንጭ በሆነው የቡና ምርት ላይ ስጋትን ደቅኗል ብለዋል።

በሀገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች ቡናን የሚያጠቁ በሽታዎች የቡና ፍሬ አበስብስ፣ የቡና ግንድ አድርቅ እንዲሁም የቡና ቅጠል በሽታ፥ ሲሆኑ በቅርቡ ደግሞ ወደ ዋነኛ በሽታነት የተሸጋገሩት የቡና ቅርንጫፍ ፍሬና ቅጠል በሽታ እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል።

እነዚህን በሽታዎች ለመቋቋም እና በምርት ላይ የሚያደርሱትን ኪሳራ ለመቀልበስ ከፍተኛ የጥናትና ምርምር ስራዎችን ቢጠይቅም በመንግስት የተሰጠው ትኩረት አነስተኛ መሆኑን አስረድተዋል።

አያይዘውም በተፈጠረው የአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ወደፊት ስጋት ሊሆኑ የሚችሉ ተብለው የተመደቡ የቡና በሽታዎች ወደ ዋነኛ በሽታነት እየተሸጋገሩ መሆኑንም ነው የተናገሩት።

በታሪኩ ጋሹ

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

16/04/2024

የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃ ሥርጭት እየተባባሰና ጥፋት እያስከተለ ነው - የመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን

ሚያዝያ 8፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃ ሥርጭት እየተባባሰና ጥፋትም እያስከተለ መሆኑን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን አስታወቀ።

ባለስልጣኑ የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃ ሥርጭት ያለበትን ሁኔታ የተመለከተ የዳሰሳ ጥናት ሪፖርት ይፋ አድርጓል።

የሪፖርቱ ዓላማ የማኅበራዊ ሚዲያ አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች በአዋጁ መሠረት ግዴታቸውን በምን ያህል መጠን እየተወጡ መሆናቸውን ማመላከት መሆኑ ተገልጿል።

በዚሁ መሠረት የሪፖርቱ መረጃዎች ከፌስቡክ፣ ቲክቶክ፣ ቴሌግራም፣ ዩ-ቲዩብ እና ኤክስ በናሙና እንዲሁም የሕዝብ አስተያየት ማካተት በማስፈለጉ በአምሥት ክልሎች በመጠይቆችና በነፃ የስልክ መስመር መረጃዎች መሰብሰባቸው ታውቋል።

በዚህ መሰረትም የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃ ሥርጭት እየተባባሰና ጥፋትም እያስከተለ መሆኑ ተመላክቷል።

የባለሥልጣኑ የመገናኛ ብዙኃን አቅም ግንባታ ዴስክ ኃላፊ ኤደን አማረ በሰጡት ማብራሪያ፥ የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃ እየተስፋፋ መሆኑን ከመረጃው መረዳት ችለናል ብለዋል።

የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃ መስፋፋቱ ደግሞ በተለይም በግለሰቦችና አጠቃላይ በኅብረተሰብ ደኅንነት ላይ አደጋ ደቅኗል ነው ያሉት።

ከጥላቻ ንግግር ምንጮች መካከልም በዋነኝነት አንዳንድ የሃይማኖት አባቶች፣ ማህበራዊ አንቂዎች፣ ፖለቲከኞች፣ የማኅበራዊ ይዘት አመንጪዎችና ግለሰቦች መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

በጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃ ሥርጭት ቀደም ሲል የብሔር ተኮር ማንነቶች ላይ በስፋት ያነጣጠረ እንደነበር አስታውሰው፥ ከቅርብ ወራት ወዲህ ደግሞ ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ማተኮሩን አስረድተዋል።

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

16/04/2024

ከፍትህ ሚኒስቴር ውጪ ያለ ልዩ ዐቃቤ ሕግ እንዲቋቋም የሚጠይቅ ረቂቅ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀረበ

ሚያዝያ 8፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) የሽግግር ፍትህን ተፈፃሚ የሚያደርግ ልዩ ፍርድ ቤትና ዐቃቤ ሕግ እንዲቋቋም የሚጠይቅ ረቂቅ ወደ ሚኒስትሮች ምክር ቤት ተላከ።

የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት እና የሕግ ባለሙያዎች በሽግግር ፍትህ ገለልተኛ ተፈፃሚነት ላይ እምነት እንደሌላቸው ለጣቢያችን ገልፀዋል።

የምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ደስታ ዲንቃ እንዳሉት ፖሊሲው እየረቀቀ ያለው በፍትህ ጉድለት ውስጥ ሚና አለው ተብሎ በሚታሰበው ፍትህ ሚኒስቴር መሆኑ ጉዳዩን ተዓማኒ እንዳይሆን አድርጎታል ብለዋል።

የተነሳው ስጋት የፖሊሲውን ሰነድ ለማዘጋጀት ግብዓት ሲሰበሰብ በበርካታ አካላት መነሳቱን የፍትህ ሚኒስቴር ለአራዳ ኤፍ ኤም ገልጿል።

ይህን ታሳቢ በማድረግ እውነት አፈላላጊ ኮሚሽን እንደሚቋቋምና ከፍትህ ሚኒስቴር ውጪ ያለ ልዩ ዐቃቤ ሕግ እንዲቋቋም ረቂቅ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት እንደላከ አራዳ ከፍትህ ሚኒስቴር ሰምቷል።

ከመደበኛው ውጭ የሆነው ይህ ዐቃቤ ሕግ ምርመራና የክስ ሂደቶችን የሚያጣራ ሲሆን የራሱ ዐቃብያነ ሕግና መርማሪዎች በሕዝብ የተሳትፎ እንዲመረጡ እንደሚደረግም፥ በፍትህ ሚኒስቴር የሕግ ጥናት ማዕቀፍ እና ማጠቃለል ዳይሬክቶሬት ከፍተኛ ዐቃቤ ሕግ አቶ ጠገነኝ ትርፌ ተናግረዋል።

በተመሳሳይ ግብዓት የሰጠው ሕዝብ አሁን ባሉት ፍርድ ቤቶች ላይ እምነት የለንም በማለቱ ከነባሮቹ ልዩ የሆነ ፍርድ ቤት እንዲቋቋም የሚጠይቅ የባለሙያዎች ረቂቅ ወደ ሚኒስትሮች ምክር ቤት ተልኮ ምላሽ እየተጠበቀ ነው ብለዋል።

በእንቁጣጣሽ ኃይለማርያም

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

16/04/2024

በበርካቶች ዘንድ ቅሬታና ትችት የቀረበበት የቤጂንግ የግማሽ ማራቶን ውድድር አጨራረስ

በእሑዱ ውድድር ኢትዮጵያዊው አትሌት ደጀኔ ኃይሉ እና ሁለቱ ኬንያውያን አትሌቶች ቻይናዊው አትሌት ውድድሩን እንዲያሸንፍ ሆን ብለው ውጤት ለቅቀዋል በሚል የቤጂንግ ግማሽ ማራቶን አዘጋጆች ምርመራ እያደረጉ መሆኑ ይታወሳል።

በውድድሩ ኬንያውያኑ እና ኢትዮጵያዊው አትሌት ወደ መጨረሻው መስመር ሲደርሱ ፍጥነታቸውን በመቀነስና ቻይናዊው አትሌት ቀድሞ እንዲገባ ሲጠቁሙ ይታያል።

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

16/04/2024

ፕሪሚየር ሊጉ ከ23ኛ ሣምንት ጀምሮ በሐዋሳ ይካሄዳል

ሚያዝያ 8፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በኢትዮጵያ ዋንጫ ጨዋታዎች ምክንያት ከተቋረጠ በኋላ ከ23ኛ ሣምንት ጀምሮ በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም እንደሚካሄድ ተገለጸ።

የ2016 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከ16ኛ እስከ 22ኛ ሣምንት በድሬዳዋ ከተማ እየተካሄደ መሆኑ ይታወቃል።

ከቀጣዩ መርሐ ግብር ጀምሮ በኢትዮጵያ ዋንጫ ጨዋታዎች ምክንያት ሊጉ ከተቋረጠ በኋላ ሲመለስ ከዚህ በፊት በወጣው መርሐ-ግብር መሰረት ከ23ኛ ሣምንት ጀምሮ የሊጉ ውድድር የሚካሄደው በሐዋሳ ከተማ ሐዋሳ ዩንቨርሲቲ ስታዲየም መሆኑን የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማኅበር አስታውቋል።

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

16/04/2024

"የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ምሽትን በአራዳ ሜዳ"

ተወዳጁ አራዳ ሜዳ የቻምፒየንስሊጉን ተጠባቂ ጨዋታ ይዞላችሁ ይቀርባል!

የ2023/24 የአውሮፓ ቻምፒየንስሊግ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎች ዛሬም ሲቀጥሉ ባርሰሎና ከ ፓሪሰንት ዠርማ ጋር የሚያደርጉትን ተጠባቂ የመልስ ጨዋታ ከምሽት 03:00 ጀምሮ በአራዳ ኤፍ ኤም 95.1 በቀጥታ ስርጭት ወደእናንተ እናደርሳለን።

◤◢◤◢◤◢◤◢◤◢◤◢◤
ተወዳጁን የአውሮፓ ቻምፒዮንስሊግ
ምሽትን በአራዶቹ መንደር
ያሳልፋ!
◢◤◢◤◢◤◢◤◢◤◢◤◢◤

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

Photos from Arada FM 95.1 - አራዳ ኤፍኤም 95.1's post 16/04/2024

የጀርመን መንግስት ለሥምንት ሆስፒታሎች የ3 ነጥብ 6 ሚሊየን ዩሮ የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ

ሚያዝያ 8፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) የጀርመን መንግስት በጀርመን ልማት ባንክ አማካኝነት ለሥምንት የማስተማሪያ ሆስፒታሎች የ3 ነጥብ 6 ሚሊየን ዩሮ የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

ድጋፍ የተደረገላቸው ጥቁር አንበሳ ስፔሻላዝይድ ሆስፒታል፣ ድል ጮራ ሪፈራል ሆስፒታል፣ አዳማ ሪፈራል ሆስፒታል፣ ደሴ ሪፈራል ሆስፒታል፣ ፈለገ ህይወት ሪፈራል ሆስፒታል፣ ጂማ ዩኒቨርሲቲ ሜዲካል ማዕከል፣ አይደር ሪፈራል ሆስፒታልና አርባ ምንጭ ሪፈራል ሆስፒታሎች ናቸው።

ለሆስፒታሎቹ ከሕክምና ቁሳቁስ በተጨማሪ የአቅም ግንባታ ስልጠናና የቴክኒክ ድጋፍ እንደሚደረግም ተገልጿል።

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

16/04/2024

በኮሪደር ልማት ዝግ ሆነው የቆዩ መንገዶች ለተሽከርካሪ ክፍት ሆኑ

ሚያዝያ 8፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) በአዲስ አበባ ከተማ በተወሰኑ አካባቢዎች እየተከናወኑ በሚገኙ የኮሪደር ልማት ሥራዎች ምክንያት ዝግ ሆነው የቆዩ መንገዶች ለተሽከርካሪ ክፍት መደረጋቸውን ፖሊስ አስታወቀ።

በዚህም

ከደጃች ውቤ በአፍንጮ በር ወደ ራስ መኮንን ድልድይ

ከባሻወልዴ ችሎት በቱሪስት ሆቴል ራስ መኮንን ድልድይ አፍንጮ በር

ከዳኑ ሆስፒታል እስከ ቱሪስት ሆቴል በመውጣት ወደ ራስ መኮንን ድልድይ አፍንጮ በር

ከአራዳ መስተዳደር ወደ ዳኑ ሆስፒታል መውረጃ በአንድ አቅጣጫ ብቻ አሽከርካሪዎች መጠቀም እንደሚችሉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

ከዚህ ጋር ተያይዞ እየተከናወኑ ባሉ የልማት ሥራዎች ምክንያት ለአጭር ሆነ ለረጅም ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ክልክል መሆኑንም ነው ያስታወቀው።

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

16/04/2024

በፓኪስታን እና አፍጋኒስታን በጎርፍ አደጋ ከ100 በላይ ሰዎች ለህልፈት ተዳረጉ

ሚያዝያ 8፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) በፓኪስታን እና አፍጋኒስታን በጎርፍ አደጋ ከ100 በላይ ሰዎች ለህልፈት መዳረጋቸው ተሰማ።

በፓኪስታን ከ50 በላይ ሰዎች ለህልፈት ሲዳረጉ፥ በሃገሪቱ ሰሜን ምዕራብ ክልል ከፍተኛ ዝናብ ያስከተለው ጎርፍ እና የመሬት መንሸራተት የመሰረተ ልማት ውድመት ማስከተሉን አልጀዚራ ዘግቧል።

በፑንጃብ ግዛት የ21 ሰዎች ህልፈት የተመዘገበ ሲሆን በመዲናዋ ኢስላማባድም ከፍተኛ ውድመት ደርሷል ነው የተባለው።

በተመሳሳይ በአፍጋኒስታን 50 ሰዎች ለህልፈት የተዳረጉ ሲሆን፥ በርካታ መኖሪያ ቤቶች በጎርፍ አደጋ መውደማቸውንም ዘገባው አመላክቷል።

የሃገራቱ ባለስልጣናት በአካባቢው እየጣለ ያለው ከባድ ዝናብ ከመቀጠሉ ጋር ተያይዞ በጎርፍ አደጋ የሚደርሰው የህልፈትና የመሰረተ ልማት ጉዳት መጠን ያሻቅባል በሚል ስጋታቸውን እየገለጹ ነው።

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

16/04/2024

የእናቶችና ሴቶች ጤና ላይ ትኩረቱን ያደረገ በጎ አድራጎት ድርጅት ሥራ ጀመረ

ሚያዝያ 8፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) የእናቶችና ሴቶች ጤና ላይ ትኩረቱን ያደረገ በጎ አድራጎት ድርጅት በዛሬው እለት ሥራ መጀመሩ ተነግሯል።

ሄዋን የሴቶች ጤና ድጋፍ በጎ አድራጎት ድርጅት በ2015 ዓ.ም በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሆስፒታል ኮሌጅ፥ በማህጸን እና ፅንስ ክፍል ባሉ ሀኪሞች የተቋቋመ ነው።

የነፍሰ ጡር እናቶች መድሃኒት መግዣ ማጣት፣ ተመላልሶ ለመታከም የትራንስፖርት እና ሌሎች ወጪዎች ገንዘብ ማጣት ለሴቶች እና እናቶች ችግር እየሆነ መምጣቱ ነው የተነገረው።

ድርጅቱ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚኖሩ ሴቶችን፣ በተለያየ ምክንያት ለተሰደዱ ህጻናትና ሴቶች፣ የህክምና ወጪያቸውን መሸፈን ለማይችሉ እናቶች፣ በዝቅተኛ ደረጃ በመንግስት መስሪያ ቤት የሚሰሩ ሴቶችን ለመርዳት ትኩረት እንደሚያደርግ ተገልጿል።

የወሊድ ማቆያ ስፍራ መገንባት፣ የሴቶችን ጤና ለማጎልበት የተከለከሉ ድርጊቶችን ለመቅረፍ እና መገለልን ለመቀነስ ሀገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመስራት የሴቶች እና እናቶች ጤና ማሻሻል የሚያከናውናቸው ተግባራት ናቸው።

ሄዋን በቀጣይ የሴቶች አዳሪ ትምህርት ቤት እና የማገገሚያ ማዕከል ለማቋቋም እቅድ እንዳለው አስታውቋል።

በአናንያ ንጉሱ

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

16/04/2024

ንዴትና ቁጣን ለማስወገድ

ሚያዝያ 8፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) ንዴትና ቁጣ በጤናም ሆነ በማህበራዊ ህይወት ግንኙነት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደሚያሳርፍ ይነገራል።

መንስኤ፦ የንዴትም ይሁን የቁጣ የመጀመሪያው መንስኤ እንደ ሁኔታዎች ቢለየያም ነገሮች እኔ ባሰብኩት መንገድ ብቻ ካልሆነ የሚል የግል አመለካከት ዋናው ምክንያት መሆኑን የሥነ ልቦና ባለሙያዎች ይገልጻሉ።

ምናልባት ነገሮች ለቁጣና ንዴት የሚዳርጉ ቢሆን እንኳን ሁልጊዜም ያችን አጋጣሚ ችሎ ማሳለፍ የመጀመሪያው እርምጃ ሊሆን ይገባልም ነው የሚሉት።

ንዴት ምን ያስከትላል?

ሲናደዱ ሰውነትዎ አድሬናሊን እና ኮርቲሶልን አብዝቶ ስለሚረጭ ያልታሰበ ፍርሃት፣ ድንገተኛ ጭንቀት እና ቅፅበታዊ ደስታ ሊፈጠር ይችላል።

ከፍተኛ ራስ ምታት፣ የሥርዓተ ምግብ መስተጓጎል (ሆድ አካባቢ የሚፈጠር ችግር)፣ የእንቅልፍ ዕጦት፣ የፍርሃት፣ ጭንቀትና የድብርት ስሜት፣ የደም ግፊት፣ ድንገተኛ የልብ ህመም እና የጭንቅላት ውስጥ ደም መፍሰስ እንዲሁም ድንገተኛ የቆዳ ላይ መቆጣትና መጉረብረብ በዚህ ጊዜ ይከሰታል።

በተጨማሪም ሰውነትዎ ለተዘጋጀበት አካላዊ ምላሽ ዝግጁ ይሆን ዘንድም ደም ከአዕምሮ ወደ ጡንቻ ይሄዳል።

በዚህ ጊዜ ትንፋሽ እና የደም ዝውውር ሲጨምር ምናልባት የደም ግፊት ከፍ የማለት ዕድሉም የበዛ ነው።

ምን ማድረግ ይገባዎታል?

ምክንያቱን ማወቅ፦ ንዴት ብዙ ጊዜ ወዳልተፈለገ አቅጣጫ በማምራት ብጥብጥና ሁከት በመፍጠር ወደ አካላዊ ድብድብ የማደግ እድሉ ሰፊ ነው።

ለንዴት እና ቁጣ የዳረገዎትን ጉዳይ መለየትና ማወቅ እንዲሁም ለጉዳዩ ምላሽ የሰጡበትን መንገድ መለየት የመጀመሪያ እርምጃ ሊሆን ይገባል።

ከዚህ በኋላ ደግሞ ለንዴት የዳረገዎትን ምክንያት መለየትና አጠቃላይ ሁኔታዎቹን በማስታወሻ መያዝ።

በዚህ ወቅት የሚሰማዎትን ስሜት እና ንዴቱን ተከትሎ የሚመጣን ሁኔታ መለየት እና ማወቅ፣ ትዕግስትዎን የሚፈታተኑና ንዴትዎን የሚያባብሱ ነገሮችን ለይቶ መዘርዘር እንዲሁም ለጉዳዩ የሰጡትን ምላሽ ማስተዋል።

ስሜትን መቆጣጠር፦ ለሆነው ነገር ተገቢ ያልሆነ ምላሽ በመስጠት ነገሮችን ከማባባስ ይልቅ ስሜትን መቆጣጠር እና ነገሩን ለማርገብ መሞከር።

የሚሆነውን ነገር መከታተል፣ በጥሞና አይቶ ማለፍ እና ስሜትን መቆጣጠር መቻል መልካም ነው።

የተፈጠረውን ስሜት ለመርሳት መሞከር እና በደቂቃዎች ውስጥ ከተፈጠረው ክስተት መውጣትና ወደ ነበሩበት ነባራዊ ሁኔታ መመለስ።

አዎንታዊ አስተሳሰብ ማዳበር፦ ሰዎች ትክክል ያልሆነ ነገር አድርገዋልና ሊቀጡ ይገባል በሚል ራስን በበቀል ስሜት ማበሳጨትና መናደድ ተገቢ አይደለም።

ከዛ ይልቅ ጥፋታቸውን በይቅርታና በትምህርት ማሳለፍ።

በተጨማሪም በተናደዱ ጊዜ በተቻለ መጠን እስከሚረጋጉ ድረስ ከሁኔታውና ከቦታው መራቅ፣ ስሜቱን የተለመደ ነው ብለው መቀበል መቻል፣ በትክክል የተበሳጩበትን ሁኔታ መለየት፣ ከዚህ በኋላ በምን መልኩ መቀረፍ አለበት ለሚለው መፍትሄውን ብቻ ማሰብ፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ እና የቅርብ ከሚሉት ሰው ጋር ተወያይቶ ማለፍን ይልመዱ።

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

16/04/2024

በአዲስ አበባ የሚገኙ እድሮች እንዲመዘገቡ የሚያስገድድ ረቂቅ መመሪያ ወጣ

ሚያዝያ 8፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) የአዲስ አበባ ሴቶች፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ በከተማዋ ውስጥ የሚገኙ እድሮች እንዲመዘገቡ የሚያስገድድ ረቂቅ መመሪያ መውጣቱን አስታውቋል።

በአዋጅ ቁጥር 74 /2014 የወጣውን የእድሮች አዋጅ በ84/2016 ተሻሽሎ ለማስፈፀሚያ መመሪያ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቶለታል።

መመሪያው እድሮች ቀብር ከማስፈፀም ባለፈ አባሎቻቸውን እንዲያገለግሉ፣ ከመንግስት ጋር በቅርበት እንዲሰሩ፣ አባሎቻቸውን እንዲያበዙ እና ህጋዊ ሆነው እንዲንቀሳቀሱ ያግዛል ተብሏል።

እድር ያለው ማህበራዊ ፋይዳ ትልቅ በመሆኑ በዩኔስኮ ለማስመዝገብ ይሰራልም ነው የተባለው።

የእድሮችና የእድር ምክር ቤቶች የምዝገባና የእድሳት አሰጣጥ መመሪያ 151/2016 ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።

በባንቺአየሁ አሰፋ

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

16/04/2024

እስራዔል ለተፈጸመባት ጥቃት አፀፋዊ ምላሽ እንደምትሰጥ አስታወቀች

ሚያዝያ 8፣ 2016 (አራዳ ኤፍ ኤም) እስራዔል በኢራን ቅዳሜ ሌሊት ለተፈጸመባት ጥቃት አፀፋዊ ምላሽ ለመስጠት እያሰበች መሆኑን ወታደራዊ ምንጮች ገልጸዋል።

የእስራዔል የጦር ካቢኔ በቴህራን ለተፈጸመው ጥቃት ምላሽ መስጠት በሚቻልበት አግባብ ላይ መክሯል።

ካቢኔው በጉዳዩ ላይ ከመምከሩና ‘የኢራን ጥቃት በቸልታ የማይታለፍና ምላሽ የሚያስፈልገው’ መሆኑን ከመጥቀስ ባለፈ ግን በጥቃቱ ዙሪያ ዝርዝር መረጃዎች አለማውጣቱን ምንጮችን ዋቢ ያደረገው የቢቢሲ ዘገባ ያመላክታል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁም ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ኢራንን እንዲያወግዝና ከቴህራን በተቃራኒው እንዲቆም ጠይቀዋል።

የእስራዔል ጦርም የቴህራን ጥቃት አፀፋዊ ምላሽ እንደሚፈልግ ሲገልጽ፥ የጦሩ ቃል አቀባይ “የእስራዔልን ደህንነት ለማስጠበቅ አጋጣሚው በፈቀደና በመረጥነው ጊዜ ሁሉ ጥቃት እንፈጽማለን” ሲሉ ተደምጠዋል።

ሁኔታው ያሳሰባቸው ሃገራት ደግሞ ሁለቱ አካላት ፍጥጫውን ወደ ለየለት ጦርነት ውስጥ ከሚያስገባና ቀጠናውን ወደ ትርምስ ከሚያስገባ አካሄድ እንዲቆጠቡ እየጠየቁ ይገኛል።

የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሁሴን አሚር አብዶላሂያን በበኩላቸው፥ በእስራዔል ላይ የተፈጸመውን ጥቃት “ራስን የመከላከል መብት ነው” በሚል ገልጸውታል።

ሃገራቸው በማንኛውም ሁኔታ ጥቅሟን ለማስከበር ማንኛውንም ነገር ከማድረግ ወደ ኋላ እንደማትልም አስረድተዋል።

ይሁን እንጅ የቅዳሜ ሌሊቱ ጥቃት ‘ኢራን ለተፈጸመባት ጥቃት የሰጠችው ምላሽና ጉዳዩም የተዘጋ ፋይል ነው’ በማለት ወደ ከፋ ግጭት ውስጥ የመግባት ፍላጎት እንደሌላቸው ጠቁመዋል።

አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት!

Telegram:https://t.me/Arada_Fm

Website:https://aradafm.com/

Facebook: https://www.facebook.com/aradafm95.1/

Youtube:https://www.youtube.com/.1

Tiktok:https://www.tiktok.com/.1

Want your business to be the top-listed Media Company in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Videos (show all)

በበርካቶች ዘንድ ቅሬታና ትችት የቀረበበት የቤጂንግ የግማሽ ማራቶን ውድድር አጨራረስ በእሑዱ ውድድር ኢትዮጵያዊው አትሌት ደጀኔ ኃይሉ እና ሁለቱ ኬንያውያን አትሌቶች ቻይናዊው አትሌት ውድድሩ...
83 ዓመታት በአንድ ሌሊት - ለይለተል ቀድር
AradaFm 95.1
AradaFm 95.1 #1minute #የኢትዮጵያ #ዜና #habesha #radiostation #Entertainment
AradaFm95.1
4-3-3 ፕሮግራም  ስፖርት በአራዳ 95.1 የማንቹሪያን ደርቢ ጨዋታ!#sportnews #manchesterunited #manchestercityfc
የኢትዯፒካሊክ እና የማንያዘዋል ፍጥጫ በአራዳ ኤፍ ኤም 95.1 በቅርብ ቀን!#aradafm95.1 #Ethiopia
የሰው ልጆችን ለማጥፋት እቅድ አላችሁ ተብለው የተጠየቁት የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ  ሮቦቶች ምላሽበተመድ በተካሄደው የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ጉባኤ ላይ የተሳተፉት ኤ አይ ወይንም ሰውሰራሽ አ...
ዝናብ በጣለ ቁጥር እራሳቸውን ወደ ትንንሽ ሀይቅነት የሚቀይሩት የአዲስ አበባ ጎዳናዎች ! ሰሚት አካባቢ በዚህ ሰአትTelegram:https://t.me/Arada_FmWebsite:https://a...
“በንብ መንጋ የሚመሰለው የሺቡያ እግረኞች መገናኛ"በጃፓን ቶኪዮ የሚገኘው የሺቡያ መሻገሪያ "በአለም ላይ ካሉ በጣም የተጨናነቁ የእግረኞች መገናኛ" መሻገሪያ አንዱ ነው። በቦታው ላይ በቀን ...
በሰንበት ለተለያዩ ጉዳዮች ሱፍ ለብሰው መውጣት የሚያስቡ አብዛኛዎቹ ወንዶች ክራቫት ማሰር ራስ ምታት ስለሚሆንባቸው አስቀድመው ክራቫት ማሰር በሚችል ወዳጃቸው ሸብ ያስደርጋሉ።  ይህን የማይፈ...

Category

Telephone

Address


Kazanchis, Bloom Tower Building, 4th Floor, Addis Abeba
Addis Ababa
Other Radio Stations in Addis Ababa (show all)
HYPNOTIZED Afro FM 105.3 HYPNOTIZED Afro FM 105.3
Piazza
Addis Ababa

The official page for the Afro FM Hypnotized show Listen live on www.afro105fm.com

SHEGER FM 102.1 RADIO SHEGER FM 102.1 RADIO
Addis Ababa Bahirdar Road
Addis Ababa

SHEGER 102.1FM 'Yenanetew Radio' is the first private radio station in Ethiopia. We are proud to be Ethiopian and we love our country more than anything! Hear us live on www...

The Vibe Afro FM 105.3 The Vibe Afro FM 105.3
Bole
Addis Ababa

Welcome To The Official Fan Page for The ViBE(The French Hr) Afro FM 105.3 - 10am - 11am Weekdays 11

Abresh Saddam Digital entertainment Ethiopia Abresh Saddam Digital entertainment Ethiopia
Addis Ababa

Man proposise, God disposise.

Awal show Awal show
Addis Ababa

Like tuqi

Hodan Media Hodan Media
Hodan@gmail. Com
Addis Ababa

ከሀ እስከ ፐ  Ke Ha Eske Pe ከሀ እስከ ፐ Ke Ha Eske Pe
Addis Ababa

ስፖርታዊ ክንውኖችን በቀጥታ የሚስተላልፍ ፕሮግራም

ሐበሻ ጣዕም/Habesha Taem ሐበሻ ጣዕም/Habesha Taem
Addis Ababa

ሐበሻ ጣዕም ስለ ሁሉም የሚያወራ ስለ ሁሉም የሚያነሳሳ #የመዝናኛ ,#የመረጃ ,እና, #የቁምነገር ሬዲዮ ፕሮግራም ነው