Kolfe W05 youth league press

የኮልፌ ወረዳ 05 የብልፅግና ወጣቶች ሊግ

Photos from Kolfe W05 youth league press's post 12/06/2024

የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ማጠቃለያ ኮንፍረንሱን ማካሔድ ሊጀምር ነው።

ኮልፌ ኮሙኒኬሽን ሰኔ 05/2016ዓ.ም

ኮንፍረንሱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣የክፍለ ከተማና ወረዳ አመራሮች፣የክብር እንግዶችና የሊጉ አባላት በተገኙበት ከጥቂት ደቂቃ በኋላ በክፍለ ከተማው አዳራሽ ይጀምራል ።

በኮንፍረንሱ የክብር እንግዶች መልዕክት የሚያስተላልፉ ሲሆን የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ እቅድ አፈፃፀም ላይም ውይይት እንደሚደረግ ይጠበቃል።

12/06/2024

የኮልፌ የቀራንዮ ክፍለ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ማጠቃለያ ኮንፍረንስ

Photos from Kolfe W05 youth league press's post 06/06/2024

"ወጣቶች የነገ ሀገር ተረካቢ ብቻ ሳይሆኑ የዛሬ ሀገር ባለቤቶችም ጭምር ናቸው":- አቶ ሙሉጌታ ጉልማ የክፍለ ከተማው የዲሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ሀላፊ
በዛሬው እለት የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወጣቶች ከአጎራባች ሸገር ሲቲ መልካ ኖኖ ክፍለ ከተማ ወጣቶች ጋር በመተባበር ወንድማማችነትና እህትማማችነት በሚያፀኑ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሄደዋል።

በመድረኩም የገዢ ትርክት ግንባታና ምንነት እንዲሁም የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትና ማጠናከር ላይ ያተኮረ አጭር ሰነድ በክፍለ ከተማው ምክትል ፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ አቶ አደም መሀመድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

በመድረኩ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የክፍለ ከተማው ዲሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበርያ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ሙልጌታ ጉልማ ወጣቶች የነገ ሀገር ተረካቢ ብቻ ሳይሆኑ የዛሬ ሀገር ባለቤቶች በመሆናቸው ወንድማማችነትና እህትማማችነት በማፅናት ሀላፊነታቸው እንዲወጡ አሳስበዋል።

ውይይቱን የመሩት የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ምክትልና ፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ አቶ አለማየሁ ፍቃዱ በትብብርና በጋራ በመስራት የህዝባችን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻልና የወጣቱ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የክፍለ ከተማ ወጣቶች ሊግ ሰብሳቢ ወጣት ቤተልሄም ትዳሩ በበኩሏ የበለፀገች ኢትዮጵያ እውን ለማድረግ የወጣቱ ሚና ከፍተኛ መሆኑን በመግለፅ መሰል ግንኙነቶች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቃለች።

የውይይቱ ተሳታፊዎችም አንድነትና አብሮነት በሚያጠናክሩ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በቅንጅትና በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

Photos from Kolfe W05 youth league press's post 16/05/2024

የወጣቶች ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ከፓርቲው ጋር ተቀራርቦ መሥራት ከአባላት ይጠበቃል!

በወረዳችን አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ወጣቶች ሊግ የ9 ወራት ኮንፈረንስ ተካሂዷል።

በዛሬው ግንቦት 8/2016 የተካሄደው ኮንፈረንሱ የአባላቱን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አንድ እርምጃም ነው ተብሏል።

በመድረኩም የ9 ወራት ሪፖርት ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን ወጣቶች ከፓርቲው ጎን በመቆም ድጋፍ እንዲያደርጉ ተጠይቋል።

በኮንፈረንሱ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የወረዳችን ብልፅግና ፓርቲ ምክትልና ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ደምሱ መተኪያ እንደገለፁት በ9 ወራት የተከናወኑትን እንደ ወረት በመያዝ በቀሪ ሁለት ወራት ደግሞ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በማረም ለተግባራዊነታቸው ርብርብ እንዲደረግ ጠይቀዋል።

በሊጉ ሰብሳቢ በወጣት የሲሩ ላሂምና በምክትል ሰብሳቢው በወጣት ፍራኦል አበራ መሪነት የቀረበው የ9 ወር ሪፖርቱ ወጣቱ በአረንጓዴ አሻራ፣በበጎ ፍቃድና በሰው ተኮር ስራዎች እንዲሁም በማህበራዊ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ አላማ የመጠቀም ስራዎች ላይ አስተዋፅኦው የጎላ ነበር ተብሏል።

ተቀራርቦ መሥራት ለውጤታማነት ያበቃል ያሉት የሊጉ ሰብሳቢ ወጣት የሲሩ ላሂም ፓርቲያችን ለወጣቱ የሰጠውን ትኩረት በማገዝ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ያስፈልጋል ብለዋል።

በኮንፈረንሱም አዳዲስ የተመለመሉ አባላትና የ9 ስራ አስፈፃሚዎች በዝርዝር ቀርበው የፀደቁ ሲሆን በቀጣይ ቀሪ ወራት ፓርቲውን ከፍ የሚያደርጉ ስራዎች መሠራት አለበትም ተብሏል።

በመጨረሻም በኮንፈረንሱ ላይ ተገኝተው የማጠቃለያ መልዕክት ያስተላለፉት የክፍለ ከተማችን ወጣት ሊግ ሰብሳቢ ወ/ሪት ቤተልሄም ትዳሩ እንደገለፁት ብልፅግና የወጣቶች ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ እያከናወነ ያለው ተግባር ከፍ ያለ ነው ብለዋል።

በፓርቲ አሰራርና ደንብ መሠረት የተቀመጡ አቅጣጫዎችን በማክበር መንቀሳቀስ ያስፈልጋል ያሉት ሰብሳቢዋ በህዋስና መሰል ውይይቶች በመሳተፍ አቅምን መገንባት ተገቢነት አለው ብለዋል።

የፓርቲያችን ኃላፊ አቶ አሸናፊ ኩምሳ በበኩላቸው የወጣት ሊግ አባላት ለፓርቲያችን መሠረት መሆናቸውን ገልፀው መዋቅሩ እንዲጠናከር እና በአዳዲስ ፈጠራ የታጀበ ስራ መሠራት አለበት ብለዋል። ለዚህም መሳካት ፓርቲያችን በሚፈጥራቸው መድረኮችና ሴሚናሮች እየተገኙ መሳተፍ ይጠበቃል ያሉት አቶ አሸናፊ እንደ ፓርቲ አባል ሞዴል ሆኖ መታዬት እንዲቻልም አባላቱ ራሳቸውን ዝግጁ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

Photos from Kolfe W05 youth league press's post 16/05/2024

የወረዳችን አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ወጣቶች ሊግ የ9 ወራት ኮንፈረንስ መካሄድ ጀምሯል።

Photos from Kolfe W05 youth league press's post 15/05/2024

የኮልፌ ወረዳ 05 ወጣቶች ሊግ ኮንፍረንስ የነገው ኮንፍረንስ ቅድመ ዝግጁት

09/04/2024

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1445ኛው አመተ ሂጅራ ኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

ረመዳን የመረዳዳት እና የአብሮነት ከመሆኑም በላይ በአማኙ ዘንድ ከፈጣሪው ጋር ያለውን መስተጋብር ከሌሎች ጊዜያት በበለጠ የሚያ ጠናክር ሆኖ በማለፍ ታላቅ ሀሴትን ፈጥሮ አልፏል።

ህዝበ ሙስሊሙ ለፈጣሪው ያለው መተናነስ በእጅጉ ጎልቶ የታየበትና ከሌሎች ወቅቶች በበለጠ የመስጠት እና የመተዛዘን ወቅት ሆኖ ያለፈበት ነበር የረመዳን ወር!

ቀድሞም የነበረና በዚህ ወር የተጠናከረውን የአብሮነትና የመተዛዘን ተግባር የበለጠ በማስቀጠል አንድነትን ማጠናከርም ይገባል።
ኮልፌ ወረዳ 05 ወጣቶች ሊግ ሀላፊ አቶ የሲሩ ላሒም❤️❤️❤️❤️❤️🌙🌟عيد مبارك تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال كل عم وأنتم بخير🌙🌟ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1445ኛው አመተ ሂጅራ ኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

ረመዳን የመረዳዳት እና የአብሮነት ከመሆኑም በላይ በአማኙ ዘንድ ከፈጣሪው ጋር ያለውን መስተጋብር ከሌሎች ጊዜያት በበለጠ የሚያ ጠናክር ሆኖ በማለፍ ታላቅ ሀሴትን ፈጥሮ አልፏል።

ህዝበ ሙስሊሙ ለፈጣሪው ያለው መተናነስ በእጅጉ ጎልቶ የታየበትና ከሌሎች ወቅቶች በበለጠ የመስጠት እና የመተዛዘን ወቅት ሆኖ ያለፈበት ነበር የረመዳን ወር!

ቀድሞም የነበረና በዚህ ወር የተጠናከረውን የአብሮነትና የመተዛዘን ተግባር የበለጠ በማስቀጠል አንድነትን ማጠናከርም ይገባል።
ኮልፌ ወረዳ ዜሮ 05 የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ሰብሳቢ አቶ የሲሩ ላሒም❤️❤️❤️❤️❤️🌙🌟عيد مبارك تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال كل عم وأنتم بخير🌙🌟

09/04/2024

!!

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1 ሺ 445ኛው የኢድ- አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳቹህ/ አደረሰን!!

የኮ/ቀ/ክ/ከተማ ወጣቶች ሊግ ሀላፊ ወጣት ቤተልሔም ትዳሩ

https://www.facebook.com/KolfeProsperityPartyYouthLeague

Photos from Kolfe W05 youth league press's post 15/03/2024

Congratulations to the Honorable Dr. Adanech Abebe for being awarded Africa's Best Female Leader at the African Leadership Magazine Awards.

Photos from Kolfe W05 youth league press's post 09/03/2024

የአዲስ አበባ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ አስተባባሪ ኮሚቴ መደበኛ የስራ አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ።
የሊጉ አስተባባሪ ኮሚቴ በመደበኛ የስራ አፈጻጸም ግምገማ መድረኩ የውስጠ ፓርቲ ስራዎች እና የወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ የንቅናቄ ስራዎች ያሉበት ደረጃ ገምግሟል ።በውይይቱም ጠንካራ ፓርቲ በመገንባት ሂደት ውጤታማ የፓለቲካና የአደረጃጀት ስራዎች መከናወናቸውን ገምግሟል ።ከወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ ንቅናቄ ተግባራት አንጻርም ስራ ፈላጊ ወጣቶች ልየታና ስልጠና በተሻለ ሁኔታ እየተመራ መሆኑ በማየት ስራ ፈላጊ የሆኑ የከተማዋ ወጣቶች ባሉ የስራ ዕድሎች ላይ ያለምንም ስራ ማማረጥ ዋነኛ ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማስቻል ሊጉ የማስተባበር ሚናውን በአግባቡ እንዲወጣ የስራ አቅጣጫ ተቀምጧል።

19/02/2024

የኮልፌ ወረዳ 05 ወጣቶች ሊግ ም/ሰብሳቢ ወጣት ቃልኪዳን ዱፌራ የወረዳ 4እና 7 የምግብ ና መድሀኒት ቁጥጥር ባለስልጣን አስተባባሪ ሆነው ተሹመዋል።

መልካም የስራ ዘመን

Photos from Kolfe W05 youth league press's post 17/02/2024

"እኔ ለአገሬ የሰላም ዘብ ነኝ"

የአዲስ አበባ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ አመራሮች እና አባላት '' እኔ ለአገሬ የሰላም ዘብ ነኝ" በሚል መሪ ቃል ከብሎክ ጀምሮ ሲደረግ የቆየውን ውይይት የማጠቃለያ መድረክ አካሂደዋል።

የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ምክትል ፕሬዚዳንት አባንግ ኩመዳን በከተማ ደረጃ በተደረገው የማጠቃለያ መድረክ ባስተላለፉት መልዕክት ውይይቱ በመላ አገሪቱ እየተካሄደ መሆኑን ጠቅሰው በህብረ -ብሔራዊቷ አዲስ አበባ ብዝሀ ማንነቶች ያሏቸው ወጣቶች በአንድ መድረክ የመምከር ዕድል ስላላቸው ዕድለኞች መሆናቸውን ገልፀዋል።

ኢትዮጵያ በወጣቶች ቅብብሎሽ ከዚህ የደረሰች ናት ያሉት ወ/ሪት አባንግ በበርካታ ፈተናዎች ውስጥ እያለፈች ጭምር እየተመዘገቡ ባሉ ከአሁን በፊት ተመዝግበው የማያውቁ አንፀባራቂ ድሎች ላይም የወጣቶች አሻራ ላቅ ያለ መሆኑን አስገንዝበዋል።

እንደ ትናንቱ ሁሉ ዛሬም ህዝባችንን በመከፋፈል ኢትዮጵያ ባሏት የመልማት ፀጋዎች ልክ እንዳታድግ የሚጥሩ አካላት መኖራቸውን ያመላከቱት ምክትል ፕሬዝዳንቷ የአገራችን ሰላምና ልማት በዋነኛነት በወጣቱ ትከሻ ላይ በመሆኑ ለአገሬ ሰላም ምን አደረግሁ ? በቀጣይስ ከእኔ ምን ይጠበቃል ? የሁሉም ወጣት የሁል ጊዜም ጥያቄዎች ሊሆኑ እንደሚገባ አስረድተዋል።

የወጣቶችን የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጭምር ተቋቁሞ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ያስገነዘቡት ወ/ሪት አባንግ ወጣቶች ከስራ ጠባቂነት እና ስራን የማማረጥ አስተሳሰብ በመቆራረጥ የሚገኙ አማራጮችን በአግባቡ ሊጠቀሙ እንደሚገባ በአፅንዖት ገልፀዋል።

የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሀላፊ አቶ በላይ ደጀን የሁላችንም ከተማ ፣ የአፍሪካ መዲና በሆነችው አዲስ አበባ የወጣቶች ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት እንዲጐለብት የተለያዩ ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልፀው ድህነትን ድል ለማድረግ በተጀመረው የአርበኝነት ጉዞ ላይ ወጣቶች እራሳቸውንና አገራቸውን ለመለወጥ የሚያደርጉትን ጥረት እንዲያጠናክሩ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ፕሬዝዳንት ወጣት መለሰ አባተ "እኔ ለአገሬ የሰላም ዘብ ነኝ " በሚል መሪ ቃል ከብሎክ ጀምሮ በተካሄደው ውይይት ከ 500 ሺህ በላይ የከተማችን ወጣቶች በከተማችን ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ጉዳዮች እንዲሁም በወጣቶች ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ላይ መምከራቸውን ገልፀዋል።

ፅንፈኛ አካላት አዲስ አበባን የሁለትና ብጥብጥ መሞከሪያ ለማድረግ ተደጋጋሚ ሙከራዎችን ቢያደርጉም የከተማችንና የአገራችን የሰላም ዘብ የሆኑት የከተማችን ወጣቶች እኩይ እሳቤያቸውን በማክሸፍ ከምንጊዜውም በላይ ህብረብሔራዊ አንድነታቸውን ከፍ እያደረጉ መሆናቸውን የሊጉ ፕሬዝዳንት አስረድተዋል።

የወጣቶችን የስራ ዕድል ተጠቃሚነት ለማበራከት የከተማ አስተዳደሩ ያሉትን አቅሞች በመጠቀም እና ለግሉ ዘርፍ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ ብዙዎች ተጠቃሚ እየሆኑ ቢሆንም ካለው ሰፊ የስራ አጥ ቁጥር አንፃር ብዙ ስራ ስለሚጠይቅ ማነቆዎችን ሁሉ በመፍታት በጋራ ለመረባረብ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ወጣት መለሰ አስገንዝበዋል።

ብሔራዊ ማንነትን እና አገራዊ አንድነትን እኩል ማስኬድ ላይ የነበሩትን ክፍተቶች ለመሙላት ፓርቲያችን ህብረ -ብሔራዊ አንድነትን ለመገንባት ጥረት እያደረገ መሆኑን እና ሰዎች በተቀያየሩ ቁጥር ከዜሮ የሚጀምሩ ተቋማት እንዳይኖሩ በፅኑ መሰረት ላይ ለማነፅ አበረታች ስራዎች መጀመራቸው፣ ምርትንና ምርታማነትን ለማሳደግም የስንዴ ምርትን ጨምሮ አንፀባራቂ ድሎች እየተመዘገቡ መሆኑ ወጣት መለሰ ባቀረቡት የመወያያ ሰነድ ተጠቅሷል።

Photos from Kolfe W05 youth league press's post 04/02/2024
Photos from Kolfe W05 youth league press's post 03/02/2024

የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ በአዳማ ከተማ ተጀምሯል።

በመርሀ ግብሩ መክፈቻ ላይ የሊጉ ፕሬዚዳንት ወጣት አክሊሉ ታደሰ የሊጉ ምክትል ፕሬዚዳንት ወጣት አባንግ ኩመዳን የዘርፉ ምክትል ሀላፊ ክቡር አቶ ፓል ቱት እንዲሁም የወጣቶች ሊግ ስራ አስፈፃሚ እና ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ተገኝተዋል።

ኮሚቴው በ3 አጀንዳዎች ላይ ውይይት የሚያደርግ ሲሆን የመዋያያ ርዕሰ ጉዳዮችን በአብላጫ ድምፅ በማፅደቅ በይፋ መድረኩ ተጀምሯል።

የኮሚቴውን ቆይታ በመክፈቻ ንግግር የከፈቱት የሊጉ ፕሬዚዳንት ወጣት አክሊሉ ታደሰ ሊጉ የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማስፋት ስትራቴጂክ ሀሳቦች እና የለውጥ ምህዋሮች የሚዘወርበት እንዲሆን ሰፊ ስራዎችን እንደተሰሩ አንስተዋል።

በተለይም ባለፉት 6 ወራት በሀገር አቀፍ ደረጃ የወጣቶችን የማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ተሳትፎ ልህቀት በተላበሰ ደረጃ ለማሳደግ ተግባራዊ የተደረጉ እንቅስቃሴዎች ውጤታማ እንደነበሩ ገልፀዋል።

በመርሀ ግብሩ ላይ በሊጉ ምክትል ፕሬዚዳንት በወጣት አባንግ ኩመዳን የሊጉ የ6ወራት አፈፃፀም ሪፖርት የቀረበ ሲሆን ከእቅድ ዝግጅት እስከ ትግበራ ምእራፍ የነበሩ የአፈፃፀም ሂደቶች ተዳሰዋል።

በዚህም በበጎፍቃድ እንቅስቃሴዎች፣በንቅናቄ ተግባራት፣የሚሰጡ ወቅታዊ ተልእኮዎችን በመፈፀም፣በሀገራዊ ተልእኮዎች ወጣቶችን በማስተባበር ረገድ አመርቂ ውጤቶች መመዝገባቸው ተነስቷል።

በሊጉ እና በዋና ፓርቲው ጉባኤዎች የተላለፉ ውሳኔዎች በአግባቡ ተፈፃሚ እንዲሆኑ የተደረጉ ጥረቶች ፍሬያማ እንደነበሩ እና በቀጣይም የታዩ ክፍተቶችን ለማረም ምልአተ ወጣቱን በማስተባበር ሰፋፊ ስራዎች መሰራት እንደሚገባቸው ተጠቅሷል።

የማእከላዊ ኮሚቴው ቆይታ ለተከታታይ 2 ቀናት የሚካሄድ ሲሆን ውይይቶች የተሞክሮ ልውውጥ መድረኮች እንዲሁም ለቀጣይ የስራ አቅጣጫ አቅም መፍጠር የሚችሉ ውሳኔዎች እንደሚተላለፉበት ይጠበቃል።

Photos from Addis Ababa Prosperity Party Youth's - ብልፅግና's post 30/01/2024
25/01/2024

የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ኮምንኬሽን ፅ/ቤት የ6 ወር እቅድ አፈፃፀም ለባለ ድርሻ አካላት እውቅና ሰጠ። በዚህም የኮልፌ ወረዳ 05 የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ 🏆🏆🏆🏆በ1 ደረጃ 🥇🥇🥇🥇 በመውጣት የምስጋና ሰርተፍኬት ተበረከተለት።
ለወረዳችን የወጣት ሊግ አባላት አመራሮች እንኳን ደስ አላችሁ ደስ አለን

18/11/2023

ሙስናና የስነ ምግባር ጉድለትን ተደራጅተን በመታገል መልካም አስተዳደርን እናስፍን!!

አቶ አለማየሁ ፍቃዱ
የብልፅግና ፓርቲ ኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ቅ/ጽ/ቤት ምክትልና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ!!

በሃገራችን በኢትዮጵያ አሁን ያለው የለውጡ መንግስት ከ2010 ጀምሮ ስልጣን ከተቆጣጠረ ጀምሮ ቀጣይነት ያለው ማሻሻያ በማድረግ ላይ ይገኛል።

ኢትዮጵያን የበለፀገች ሀገር ለማድረግ አልሞ እየሰራ ሲሆን የህዝብን ክብር፣ የሃገርን ጥቅም እና ሉዓላዊነትን ለማስከበር ከፍተኛ እርብርብ በማድረግ የላቀ ውጤቶችንም ማሳካት ተችሏል፡፡

ይሁን እንጂ የለውጡ ሂደት በርካታ ፈተናዎች ሲያጋጥሙት የቆዩ ሲሆን አብዛኞቹ ፈተናዎች ከቀድሞው ኋላ ቀር አሰራሮች እና እሳቤዎች የተያያዙ አሁን መስተካከል ያለባቸው ጉዳዮች ናቸው። አብዛኞቹ ተግዳሮቶች በአንድም ይሁን ከሙስናና ብልሹ አሰራር ብሎም ከመልካም አስተዳደር ችግሮች ጋር የተያያዙ ናቸው።

ዜጎች በህዝብ ተቋማትና እና በፖለቲካዊ ተቋማት ላይ ያላቸውን እምነት ከሚያሳድጉባቸው ጉዳዩች መካከል የአገልግሎቶች ጥራት፤ ሙስናና ብልሹ አሰራር የጸዳ አገልግሎት ወዘተ…ጋር በተያያዘ ያላቸው ግምገማ ጋር የተዛመዱ በመሆናቸው በተለይም የአመራርና ባለሙያ የብቃት ማነስ፣ ቀልጣፋና ውጤታማ ያልሆነ የክትትልና ግምገማ ሥርዓት፤ ምላሽ ሰጭነት ችግር፤ የመረጃ ተደራሽነት ችግሮች፤ የመልካም አስተዳደርን ውጤታማነት አለማሻሻል፤ ሙስናና ብልሹ አሰራር መኖር ወዘተ አገልግሎት አቅራቢዎችና አገልግሎት ተቀባዮች መካከል ያለው የተጨባጭ እውነታ ልዩነት የዜጎች አለመርካትን ያመጣል፡፡

ስለሆነም ችግሮችን ለመቅረፍ እና በአስተማማኝነት በመልካም አስተዳደርና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የህዝብ አመኔታን ለማስፈን የመንግስት ሰራተኛው፤ የግል ሴክተሩ፤ የሲቪክ ማህበራትና ሚዲያው ተናበው መስራት ይኖርባቸዋል፡፡

ይህ የማይሆን ከሆነ እና የህዝብና የፖለቲካ ተቋማት ተቋማዊ እምነት ማጣት የህዝቡን አመኔታ መሸርሸርና የመንግስትን ህጋዊነትና ቅቡልነት ማሳጣት ሊያስከትል ስለሚችል ነው። ይህ ደግሞ እንደ አንዳንድ ሃገራት ወደ አልተፈለገ ችግር በማስገባት ሃገራችን የጀመረችውን ሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ በማደናቀፍ በድህነት አዙሪት እንድንቆይ ያደርገናል፡፡

16/11/2023
16/11/2023

"ሁሉንም የልማት ዕድሎች እና አቅሞ በማስተባበር አዲስ አበባን ተወዳዳሪና ተመራጭ ከተማ የማድረግ ራዕያችንን እናሳካለን።"

ከንቲባ አዳነች አቤቤ
መልካም ቀን ይሁንለዎ!

Photos from Kolfe W05 youth league press's post 05/11/2023

[ Album ]
የተከልናቸው ችግኞች ዛፍ ሆነው ጥቅም መስጠት ይገባቸዋል። ችግኝ መትከል በራሱ ብቻውን ግብ አይደለም ግቡ የተተከሉትን እንድፀድቁ አድገው ዛፍ እንድሆኑ ማድረግ ነው።
በዛሬው 25/02/2016 እለት የብልፅግና ፓርት ኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ቅ/ጽ/ቤት ወጣቶች ሊግ ከክ/ከተማው አስተዳደር የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በክረምት የተተከሉ ችግኞችን ተንከባክቧል።
በክ/ከተማው ወረዳ 06 ህዳሴ ፓርክ ኑር ሰፈር በክረምት የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ ሰርተዋል። በፕሮግራሙ ላይ የክፍለ ከተማና ወረዳ አመራሮች፣ ከሁሉም ወረዳዎች የተውጣጡ ወጣቶችና የሴፍቲኔት ተጠቃሚዎች በተገኙበት ችግኞችን የመከባከብ ንቅናቄ ተካሂዷል።
አቶ ዛየደ ቢወጣ የክፍለ ከተማው የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ፅ/ቤት ኃላፊ እንዳሉት በክረምት አረንጓዴ አሻራ መርሀ-ግብር ከ1,643,000 በላይ ችግኞች ተክለናል። ከተማችን ውብ፣ አረንጓዴ፣ ለኑሮ አመቺ እንዲሁም በቱሪስቶች ቀዳሚ ተመራጭ እንድትሆን ችግኞችን መንከባከብ ይገባል ብለዋል።
ወጣት ቤቴልሔም ትዳሩ የብልፅግና ፓርት ኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ቅ/ጽ/ቤት ወጣቶች ሊግ ኃላፊ እንዳሉት በአለም አቀፍ ደረጃ ተፅዕኖው እየጨመረ የመጣውን የአየር ንብረት ለውጥ ለመከላከል ወጣቱን የማህበረሰብ ክፍልን የተተከሉ ችግኞችን መንከባከብ ይገባዋል። የክ/ከተማችን የወጣቱ መዋቅር ያስጀመረውን አርዓያነት ያለው ተግባር ሌሎችም ወጣታችን በማሳተፍ የበለጠ መስራት ይጠበቅብናል።

21/10/2023

መደመር የሚገለጥባቸው 3 ባህሪዎች፦

1ኛ. ማሰባሰብ
ዛሬ ላይ የሚገኙትን ሀሳቦች፣ ሀብቶችና አቅሞች ማገናኘት ነው።

2ኛ. ማከማቸት
በትናንት ሀሳብ፣ አቅምና ሀብት ላይ የዛሬን መጨመር ማለት ነው።

3ኛ. ማካበት
ለለውጥና ብልፅግና የሚያበቃ ወረት ማጠራቀም መቻል ነው።

21/10/2023

የአገር ብሄራዊ ክብር ከግል ፍላጎት በላይ መሆኑን ኢትዮጵያውያን በሀገር ግንባታ ሂደት ያጋጠማቸውን አደጋዎች በመቀልበስ ያረጋገጡ ህዝቦች ናቸው!

የብሔር፣ የቋንቋ፣ የሀይማኖት እና የባህል ብዝሀነቶች ቢኖሩንም በአገር ጉዳይ ደግሞ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ እንደ አንድ ልብ መካሪ መሆናችን ጥያቄ ውስጥ የሚገባ አይደለም።

በአራቱም ማዕዘን የሚገኙ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች በተደጋጋሚ በአገራችን ሉዓላዊነት ላይ የተቃጡ ማንኛውም አይነት ፈተናዎችን በጋራ በመስዋዕትነታቸው በመቀልበስ ኩሩ አገር ያወረሱን የፖለቲካና ሌሎች የሀሳብ ልዩነቶች ሳይኖራቸው ቀርቶ ሳይሆን አገርን እና ህዝብን በማስቀደማቸው ነው።

ዛሬም ኢትዮጵያውያን ለመጪው ትውልድ የበለፀገች ኢትዮጵያን ለማውረስ ተባብረው አገራቸውን እየገነቡ ሲሆን ጉዟችንን ለማደናቀፍ ከአገር ጥቅም በተፃራሪ በመቆም የግል ፍላጎታቸውን ለማሟላት በአገርና በህዝብ ላይ የሚቆምሩ ግለሰቦች ከህዝባችን የተደበቁ አይደሉም።

የጀመርነው የብልፅግና ጉዞ አልጋ በአልጋ አይደለም። ባለፉት ዓመታት ምንአልባትም አገራችን ካሳለፈቻቸው ዋና ዋና ፈተናዎች ውስጥ በታሪክ የሚጠቀሱ ውስብስብ ችግሮችን አልፈናል።

ህዝባችንን ከጎናችን በማሰለፍ ጥበብ በሞላበት አመራር ችግሮችን መሻገር ብቻም ሳይሆን እጅን ከአፍ የሚያስጭኑ ስኬቶችንም በመፍጠንና በመፍጠር አስመዝግበናል።

የኢትዮጵያን መለወጥ እና መበልፀግ እንደ መልካም ዕድል ሳይሆን እንደ ስጋት የሚቆጥሩ ሀይሎች እና ተላላኪዎቻቸው ዛሬም ነገም በእኩይ እንቅስቃሴዎቻቸው ቢቀጥሉ እንኳን ህብረብሔራዊ አንድነታችንን ይበልጥ በማጠናከር የሰነቅነውን ሁለንተናዊ ብልፅግናን የማረጋገጥ ራዕይ ዕውን እናደርጋለን።

ሲበርደን የምንደርባት፣ ሲሞቀን ደግሞ የምናወልቃት ልብስ ሳትሆን አገር ማለት አንተም አንችም ሁላችንም በመሆናችን እንደ አባቶቻችን ሁሉ ዛሬም ሆነ ነገ የግል ፍላጎቶቻችንን ከብሔራዊ ጥቅማችን አናስቀድምም።

Photos from Kolfe W05 youth league press's post 19/10/2023



በዛሬው መድረክ ላይ የ2016ዓ.ም የሩብ አመት አፈጻጸም የቀረበ ሲሆን በመጨረሻም የ2016 በጀት አመት እቅድ በብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ም/ሰብሳቢ ወጣት ቃልኪዳን ዱፌራ ቀርቦ ውይይት ከተደረገ በኃላ ገንቢ ሀሳቦች በግብዓትነት ከመድረክ ተሰጥቶበት ጠንካራ የመሰረታዊ ፓርቲ አመራሮች በአባላት ተመርጠው እንዲፀድቁ ተደርጓል።

ወጣት ቃልኪዳን ዱፌራ የኮልፌ ወረዳ 05 ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ምክትል ሰብሳቢ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቱ ሀገር ተረካቢ ሳይሆን የሀገር ባለቤት እንዲሆን እየሰራ ያለ ፓርቲ ነው እናንተ ኢትዮጵያን እያስቀጠላችሁ ህፃናት የሚያድጉበት፤ወጣቶች የሚሰሩበት አረጋውያን በአግባቡ የሚጦሩበት ትውለድ የሚቀጥልበትን ሀገር ለመፍጠር ኃላፊነት እንድትወጡ በሚል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

የወረዳው ወጣቶች ሊግ ፀሐፊ ወጣት ፍራኦል አበራ ሊጉ በድንበር ተሻጋሪ በጎ ፍቃድ ተግባራት፤ በዲጂታል ሚዲያ ዘመቻዎች ስራዎችን መስራታቸውን ገልፀው ‹‹እኛ ወጣቶች በጊዜያችን ተጠቅመን ለሀገር እድገት ኃላፊነታንን እንወጣለን!!››ሲሉ አስታውቀዋል፡፡

Photos from Kolfe W05 youth league press's post 18/10/2023

ወጣትነት ለሀገር ግንባታ መሠረት የሚጣልበት የእድሜ ክልል ነው። ወጣት ሀገር ይገነባል፤ ወጣት ብልፅግናን ያረጋግጣል።

በዛሬው 06/02/2016 እለት የብልፅግና ፓርቲ ኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ቅ/ጽ/ቤት ወጣቶች ሊግ የ2015 እቅድ አፈፃፀምና የ2016 እቅድ ላይ ውይይት አካሄደ። የ2016 ሩብ አመት እቅድ አፈፃፀም ላይ እንዲሁ ውይይት ተካሂዷል።

አቶ ወርቅነህ ሞርካ የብልፅግና ፓርቲ ኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ በውይይቱ ተገኝተው እንዳሉት ወጣት የሀገር ተስፋ ነው። የብልፅግና ወጣቶች ሊግ ደግሞ በርካታ ኃላፊነት ያለባቸው ናቸው። ኃላፊነታቸውን የሚወጡ ለሌላው ወጣት አርዓያ የሚሆኑ ለተጠቃሚነታቸው የሚተጉ ናቸው። መሪ የምናፈራው ከሊጉ ነው። ወጣት ሊግ የአመራር ቋት ነው። የወጣት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጥር ሀይል ነው። እንደ ክ/ከተማችን አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ነን ብለዋል።

ወጣት ቤተልሄም ትዳሩ የብልፅግና ፓርቲ ኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ቅ/ጽ/ቤት ወጣቶች ሊግ ኃላፊ እንዳሉት በ2015 በርካታ ስራዎች በተቋማችን ተግብረናል። ወጣት በተደራጀና በተቀናጀ ከተመራ ለሀገር ያለው ፋይዳ የማይተካ መሆኑን አይተናል። በ2016 የወጣቱን ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፓለቲካዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ስራዎችን እንሰራለን። በሩብ አመቱ የሰራናቸው በርካታ ስራዎች እቅዳችንን ለማሳካት የሚያስችል አቅም እንዳለን ነው። የአረንጓዴ አሻራ ተግባር ላይ ወጣት ሊጉ ነፃ ወጣቶችን ጭምር በማስተባበር በርካታ ወርቃማ ተግባር ፈፅሟል። በሰበዓዊነት ተግባርም የቤት እድሳት፣ የደም ልገሳ፣ የማዕድ ማጋራት በሰፊው የሰራንበት ነው ብለዋል።

ወጣት ቤተልሄም እንዳሉት ወጣቱ ለሀገሩ በርካታ አሻራዎቹን እያስቀመጠ ነው። ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የምናደርገውን አስተዋፅኦ እስኪጠናቀቅ አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል። በዛሬው እለትም በውይይቱ የተገኙት የዘጠኝ ስራ አስፈፃሚ፣ የመሠረታዊ ፓርቲ አመራሮች ማስጀመሪያው ላይ የድርሻቸውን ተወጥተዋል።

በእለቱ ለሁሉም ወረዳዎች የተሳትፎ የምስክር ወረቀት ተበርክቷል። ከአንድ እስከ ሶስት ደረጃ ይዘው 2015ን ያጠናቀቁ ወረዳዎች እውቅና ተሰጥቷቸዋል። ወረዳ 1፣ 7ና 4 ከ1ኛ - 3ኛ ደረጃ ይዘው አጠናቀዋል። የተሻለ የሚዲያ ተሳትፎ ለነበራቸው የሊግ አመራሮችም እንዲሁ እውቅና ተሰጥቷል።

Photos from Kolfe W05 youth league press's post 16/10/2023

የኮልፌ ወረዳ05 ብልፅግና ፖርቲ ወጣቶች ሊግ አመራሮች የተተከሉ ችግኞችን በቀጠና 6 ሚኒሊክ ካባ በመገኝት እንክብካቤ አድርገዋል፡፡

Photos from Kolfe W05 youth league press's post 10/09/2023

የአሁኑ ትውልድ ለቀጣዩ ትውልድ የበለፀገች ኢትዮጵያን ማስረከብ ሀላፊነት አለበት።

ወጣት አባንግ ኩመዳን የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የፅ/ቤት ሀላፊ

በብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ መሪነት በአዲስ አበባ ከተማ ከሁሉም ክፍለ ከተሞች የተወጣጡ ወጣቶችን በማስተባበር ለአብረሆት ቤተ መፅሀፍት ከ3000 በላይ የመፅሀፍ ድጋፍ ተደረጓል።

በርክክብ ስርአቱ ላይ የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ምክትል ፕሬዚዳንት እና የፅ/ቤት ሀላፊ ወጣት አባነወግ ኩመዳን፣ ከ300 በላይ የሚሆኑ ወጣቶች፣ የቤተመፅሀፍቱ ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ውብአየሁን ጨምሮ የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ፅ/ቤት ሀላፊ መለስ አባታ ተገኝተዋል።

በመድረኩ ላይ እንደ ሀገር በጳጉሜ ወር በታወጀው በትውልድ ቀን ይህን አይነት ትውልድ ተሻጋሪ የሆነ ተግባር በሊጉ አስተባባሪነት መፈፀሙ እጅግ የሚበረታታ እንደሆነ ተጠቅሷል።

በመርሀ ግብሩ ላይ መልእክት ያስተላለፈችው የሊጉ ምክትል ፕሬዝዳንት ወጣት አባንግ ኩመዳን የአሁኑ ትውልድ ለቀጣዩ ትውልድ የበለፀገች ኢትዮጵያን የማስረከብ ሀላፊነት እንዳለበት በመግለፅ በዚህ በጎ ተግባር ላይ የተሳተፉ አካላትን አመስግናለች።

Photos from Kolfe W05 youth league press's post 09/09/2023

የክፍለ ከተማው ዴሞክራሲያዊ ስርኣት ግንባታ ወጣቶች ሊግ አዘጋጅነት አቅም ለሌላቸው የማህበረሰብ ክፍሎች የማእድ ማጋራት ስነ ስርዓት አካሄደ፡፡

ኮልፌ ኮሙኒኬሽን ጳጉሜ 4/2015ዓ.ም

ወጣት ሊጉ በዛሬው ዕለት የክፍለ ከተማው ነዋሪ ለሆኑ አቅመ ደካሞች የማዕድ ማጋራት አካሂዷል፡፡

በስነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የክፍለ ከተማው ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ የሆኑት አቶ ሙሉጌታ ጉልማ ባስተላለፉት መልዕክት በጎነትን ሁልግዜም ባህል በማድረግ ወደ ውስጣችን በማስረጽ ለወገኖቻችን አጋርነታችንን ማሳየት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡

ሀላፊው አክለውም ቀጣዩን አዲስ ዓመት የመረዳዳት ባህላችንን የምናሳድግበት መልካም አዲስ አመት እንዲሆን ምኞታቸውን ገልፀዋል፡፡

Photos from Kolfe W05 youth league press's post 07/09/2023

ኢትዮጵያ በጀግኖች መስዋዕትነት ለዘላለም ፀንታ ትኖራለች።

በዛሬው 02/13/2015 እለት የብልፅግና ፓርቲ ኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ቅ/ጽ/ቤት ወጣቶች ሊግ የመስዋዕትነት ቀንን በማስመልከ
የደመ ልገሳ ፕሮግራም ና በጦር ኃይሎች ሆስፒታል ደሞ ምሳ የማብላት ፕሮግራም አከናውኗል።

በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት አቶ ሙሉጌታ ጉሉማ የብልፅግና ፓርቲ ኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል። በመልዕክታቸውም ቅደመ አያቶቻችን፣ አያቶቻችን፣ አባቶቻችን መስዋትነት ከፍለው ያቆዩልን ሀገር አለችን።። አሁን ወጣቶቻችን ሀገር ለማፅናት ዋጋ ከፍለዋል። በአስፈለገ ጊዜ አስፈላጊውን መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ናቸው። ዛሬ ለሀገር መስዋዕትነት የከፈሉ ወገኖቻችንን የምናመሠግንበት እለት ነው። ይህን ፕሮግራሙን ያስተባበሩ የወጣት ሊግ አመራር አባላት አመሠግናለሁ ብለዋል።
በፕሮግራሙ ላይ የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ወጣቶቾ ሊግ ኃላፊ ወጣት ቤተልሔም ትዳሩ ለሀገራችን በበርካታ ዘርፍ መስዋዕትነት ለከፈሉ ዜጎች ከጎናቸው መሆናችንን ና ሰራዊቱ የከፈለው መስዋዕትነት ሁሌም ሲዘከር እንደሚኖር ገልፀዋል።
በእለቱ አቶ አለማየሁ ፍቃዱ የብልፅግና ፓርቲ ኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ቅ/ጽ/ቤት ምክትልና ፓለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ተገኝተዋል።

Want your organization to be the top-listed Government Service in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Telephone

Website

Address

ኮልፌ ቀራንዮ ክፈለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር
Addis Ababa
Other Political Organizations in Addis Ababa (show all)
African Union African Union
Addis Abeba
Addis Ababa, 1111

A UNITED & STRONG AFRICA

Qabsoo Bilisummaa Qabsoo Bilisummaa
Finfinne
Addis Ababa, 2560

Injifannoon Kan Abbaa dhugaati

GMN Grand Media Network GMN Grand Media Network
Addis Ababa

Manegment

Bole Wereda 1 Prosperity Party ብልጽግና Bole Wereda 1 Prosperity Party ብልጽግና
Bole Michael
Addis Ababa, G.P.O

ይህ በቦሌ ክ/ከተማ ስር በሚገኘው በወረዳ 1 ብልጽግና ፓርቲ የ?

Anwar Tuti Anwar Tuti
Somaliya
Addis Ababa, HADLIYAAAA

Addis Ketema Woreda 6 Prosperity Party-ብልፅግና Addis Ketema Woreda 6 Prosperity Party-ብልፅግና
Addis Ketema
Addis Ababa

ለሁሉም ዜጋ ብልፅግናን ለማረጋጋጥ እንሰራለን

Free state movement for Addis ababa Free state movement for Addis ababa
Addis Ababa

Political

Imala Haqaa Imala Haqaa
Addis Ababa

Kaayyoon Kenya haqaa dhokate basne baketi mulisudhaa kanafu nu hordofun haqaa cina dhabachun eru nun

Paartii Badhaadhinaa Kutaa Magaalaa Araadaa Paartii Badhaadhinaa Kutaa Magaalaa Araadaa
Belay Zeleke Street, Pissa Road
Addis Ababa, 251,56

providing facts of prosperity party

Abdallaa  Zeenu Abafogi .Follow Abdallaa Zeenu Abafogi .Follow
Jiimmaa
Addis Ababa