Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C

Fit Corner consultancy P.L. C. Is an organization working on Sport. Specially to solve the problem i

11/06/2024

Thanks for being a top engager and making it on to my weekly engagement list! 🎉

Biruk Abera, Shibeshi Nega, Bereke Beyene Bonga

Photos from Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C's post 09/06/2024

ወብና ጽዱ አዲስ አበባን ለመጪው ለትውልድ እናወርሳለን በሚል መሪ ቃል ደማቅ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተካሄደ።
ሰኔ 2/2016 ዓ.ም፤
ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ /አዲስ አበባ/
🏃‍♀🏃**🏃🏃‍♀

ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ጋር በመተባበር ወብና ጽዱ አዲስ አበባን ለመጪው ለትውልድ እናወርሳለን በሚል መሪ ቃል ደማቅ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተካሂዷል።

በዝግጅቱ ላይ የፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንስትራክተር ነፃነት ካሣ፤ የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳዊት ትርፉ፥ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አይዳ አወል፤ የአዲስ አበባ ከተማ አካበቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ዲዳ ድሪባ ፤ ሌሎች እንግዶች በተገኙበት እና በርካታ የከተማዋ ነዋሪወች በተገኙበት በድምቀት ተከናውኗል።

ከተማችንን ውብ እና ፅዱ የማድረግ ተግባር (እንቅስቃሴ) ራሱ ጤናን ለመጠበቅም እንደሚረዳ ገልፀው፤ ፅዳትንና
የአካል ብቃት እንቅስቃሴን ባህሉ ያደረገ ሕብረተሰብ መፍጠርና ጤናማ ሀገር ተረካቢ ትውልድ እንዲኖር ማስቻል አስፈላጊ መሆኑንና ለዚህም ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን መወጣት እንደሚገባቸው ኢንስትራክተር ነፃነት ካሣ ገልፀዋል።

ዝግጅቱ በሌሎች ስፖርታዊ ፌስቲቫሎችም ታግዞ በድምቀት ተከናውኗል።
🏃‍♀🏃//🏃🏃‍♀
➧ በማሕበራዊ ሚዲያ ቤተሰብ ይወዳጁን!!!
Telegram=>
Youtube=>http://bit.ly/subscribe_netsisport
https://www.facebook.com/netsisport

Photos from Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C's post 06/06/2024

ከአዳማ ጋርመንት ኢንዱስትሪ የስራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች ጋር ደማቅ የማስ-ስፖርት እንቅስቃሴ ተከናወነ፤
ግንቦት 29/2016 ዓ.ም፤ አዳማ
*****//*****
ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ከመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር በግዙፉ የአዳማ ጋርመንት ኢንዱስትሪ ውስጥ ከስራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች ጋር ደማቅ እና አካታች /Inclusive/ የማስ-ስፖርት እንቅስቃሴ በዛሬው ዕለት ከማለዳው 12፡00 ሠዓት ጀምሮ ተከናውኗል፡፡ በዚህ ልዩ ዝግጅት ላይ ኮ/ል መኮነን በየነ - የመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን ም/ስራ አስፈፃሚ፣ ኮ/ል ተመስገን ይሰሐቅ - የአዳማ ጋርመንት ኢንዱስትሪ ዋና ስራ አስኪያጅ ፣ ኢንስትራክተር ነፃነት ካሣ - የፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ መስራችና ዋና ስራ አስኪያጅ እንዲሁም ታዋቂው አርቲስት ተስፋለም ታምራት ተገኝተውበታል፡፡
በተለይም የሰራተኞች በአካል ብቃት እንቅስቃሴ እንዲያዘወትሩና ጤናቸውን በመጠበቅ የኢንዱስትሪውን ምርታማነት ለማሻሻል እንዲችሉ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ኮ/ል ተመስገን ገልፀዋል፡፡ የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎች በተለይም በስራ ቦታዎች ላይ የሚዘጋጁት አካታች /Inclusive/ 👩🏿‍🦽🏃🏿‍♀️👩🏿‍🦼🏃🏿‍♂️ እንዲሆኑ ዲዛይን ማድረግና የአካል ጉዳት ያለባቸው እህት ወንድሞቻችንም ተሳታፊ እንዲሆኑ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ኢንስትራክተር ነፃነት ገልፀዋል፡፡
የአዳማ ጋርመንት ኢንዱስትሪ የመከላከያ ሰራዊትና የፖሊስና ትጥቆችን ከማምረት ባለፈ የውጭ ምንዛሬን የሚጠይቁ ምርቶችን ሃገር ውስጥ በማዘጋጀት ለሃገር ኢኮኖሚ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡
===========//============
#ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ
#የመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን
#አዳማ ጋርመንት ኢንዱስትሪ

Photos from Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C's post 02/06/2024

የአልቲየስ ጂም ሩጫና የወወክማ ኤሮቢክስ እንቅስቃሴ ፌስቲቫል በድምቀት ተካሄደ።
ግንቦት 25/2016 ዓ.ም
🏃‍♀️🏃‍♂️🏃‍♀️🏃‍♂️👯‍♀️
በዛሬው እለት እሁድ ከማለዳው ጀምሮ አልቲየስ ጂም ባዘጋጀው ሩጫ ላይ ከተሳተፉ በኋላ አራት ኪሎ በሚገኘው የትምህርትና ስልጠና ማዕከል ላይ በተካሄደው የኤሮቢክስ ፌስቲቫል ላይ የተገኙት የፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንስትራክተር ነፃነት ካሣ እሁድን ውጤታማ ዝግጅቶች መከናወናቸውን ገለፁ።

ኢንስትራክተር ነፃነት አያይዘውም የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ በሁለቱም ዝግጅቶች ላይ በመገኘት ለሙያው ያሳዩትን ክብር አድንቀዋል። በተለይም የቢሮው ኃላፊ አቶ በላይ ደጀን ለዕለቱ ዝግጅት ድምቀት ለነበሩት የስፖርት ባለሙያወች፣ አሰልጣኞችና ዳኞች ላሳዩት ፍቅር፣ አክብሮትና አጋርነት በመላ የስፖርት ባለሙያወች ስም ምስጋናቸውን ለኃላፊው አቅርበዋል።
ሁሉም የስፖርት ሙያተኞች ሙያው በሚፈልገን ጊዜና ቦታ ሁሉ በመገኘት ኃላፊነታችንን መወጣትና ለስፖርት ልማት ተባብረን መስራት አለብን ሲሉ አሳስበዋል።
በዝግጅቶቹ ላይ ተሳታፊ ለነበሩ ቡድኖችና ውድድሩን ለመሩት ዳኞች የእውቅና የምስክር ወረቀት እና የሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

*🏃‍♀🏃🏃‍♀🏃*
#ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ
#የአ/አ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ
#አራት ኪሎ የትምህርትና ስልጠና ማዕከል
#አልቲየስ ጂም

Photos from Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C's post 01/06/2024

በኢትዮጵያ - የመካከለኛ ክብደት የወንዶች የሰውነት ቅርፅ ውድድር የኤግል ፊትነስ ተወዳዳሪው አሸናፊ ሆነ::
ግንቦት 24/2016 ዓ.ም

*//*

ከመላ ኢትዮጵያ ከሚገኙ የአካል ብቃት ማዕከሎች (ጂምናዚየሞች) የተውጣጡ ወንዶች የሰውነት ቅርፅ /body building/ ተወዳዳሪወች በየዓመቱ ለ'' Bodybuilding & Bikini Show - Mister Ethiopia'' ይፎካከራሉ። ይህንን ውድድር ከአለም አቀፉ የሰውነት ግንባታ /International Federation of Bodybuilding/ ጋር በጥምረት የሚያዘጋጀው ነው። በዚህ ውድድር ላይ ታዋቂው የአካል ብቃት አሰልጣኝ እዮብ አሰፋ በባለቤትነት የሚያስተዳድረውን 'ኤግል ፊትነስ'ን ወክሎ የተወዳደረው እስከዳር ካሳየ በአንደኛነት በማጠናቀቅ 'Mister Ethiopia' ተብሏል።
የኤግል ፊትነስ ባለቤት አሰልጣኝ እዮብ አሰፋ እና ''Body builder'' እስከዳር (Mr. Ethiopia) ላስመዘገቡት ስኬት የፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንስትራክተር ነፃነት ካሣ እንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክቱን አስተላልፏል።
===//===
Corner Sport Consultancy
fitness
Federation of Bodybuilding

TikTok · Netsi Sport 16/05/2024

Follow us on tiktok...

TikTok · Netsi Sport 87 likes, 4 comments. “FIT CORNER SPORT consultancy Spor”

Photos from Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C's post 26/04/2024

“ንቁና ብቁ ትውልድ ለሃገር መሰረት!!”
የተማሪዎች የማለዳ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተጠናክሮ በመቀጠል በአድዋ የመ/ደ/ት/ቤት በድምቀት ተከናወነ::
ሚያዚያ 18/2016 ዓ.ም፣ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ
🏃🏿‍♀️🏃🏿‍♂️🏃🏿***🏃🏿🏃🏿‍♂️🏃🏿‍♀️
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ከፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ጋር በመተባበር በከፍተኛ ትኩረት እያከናወኑት የሚገኘው የተማሪዎች የማለዳ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተጠናክሮ በመቀጠል ዛሬ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ በሚገኘው የአድዋ የመ/ደ/ት/ቤት “ንቁና ብቁ ትውልድ ለሃገር መሰረት!!” በሚል መሪ ቃል በድምቀት ተከናውኗል፡፡
በዚህ ፕሮግራም ላይ የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሲሳይ እንዳለ፣ የት/ቢሮ ም/ኃላፊ አቶ አሊ ከማል፣ የፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንስትራክተር ነፃነት ካሣ፣ ት/ቤቱ ር/መ/ር አቶ ወርቅነህ ለቺሳ፣ የት/ቤቱ መምህራንና ተማሪዎች ተሳትፈውበታል፡፡
ተማሪዎችን የአካል ብቃት እንቅስቃሴን ባህል እዲያደርጉና ተነሳሽነት እንዲኖራቸው በኢንስትራክተር ነፃነት ካሣ የተመራና ሌሎች አሰልጣኞች እና የስፖርት ሳይንስ መምህራን የተሳተፉበት አነቃቂና አሳታፊ እንቅስቃሴዎች ተከናውነዋል፡፡
➧ በማሕበራዊ ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!!!
Telegram=>
Youtube=>http://bit.ly/subscribe_netsisport
https://www.facebook.com/netsisport
🏃🏿‍♀️🏃🏿‍♂️🏃🏿=//=🏃🏿🏃🏿‍♂️🏃🏿‍♀️
#ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ
#የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ
#አድዋ የመ/ደ/ት/ቤት

Photos from Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C's post 21/04/2024

በመቀሌ ዩኒቨርስቲ ዋናው ካንፓስ(ዓዲ ሓቂ ካምፓስ) ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ::
ሚያዝያ 13/2016 ዓ.ም
መቀሌ ከተማ፤
ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ

🏃🏿‍♀️🏃🏿‍♂️🏃🏿*//🏃🏿🏃🏿‍♂️🏃🏿‍♀️
በዛሬው ዕለት በመቀሌ ከተማ - በዋናው ካንፓስ (ዓዲ ሓቂ ካምፓስ)ሲሰጥ የነበረው የአካል ብቃት ስልጠና ተጠናቀቀ:: በስልጠናው ላይ ከተለያዩ የትግራይ ከተሞች የተመረጡ የስፖርት ሳይንስ መምህራንና የመቀሌ ዩኒቨርስቲ መምህራን ተሳትፈዋል::

🏃‍♂️=================🏃‍♂️🏃‍♀️
ስልጠናው በንድፈ ሀሳብና በተግባር የተደገፈ በሳይንሳዊ መንገድ አተገባበር ላይ ያተኮረ ስልጠና ተደራሽ መደረጉን ተሳታፊዎች ገልፀዋል፡፡

ከስልጠናው ጎን ለጎን ኢንስትራክተር ነፃነት ካሳ ከትግራይ ክልል ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ተኽላይ ፍቃዱ ና ከክልሉ የአካል ብቃት አሰልጣኞች ጋር በቀጣይነት አብሮ በመስራት ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ውይይት አድርገዋል::
🏃‍♀️🏃‍♂️🧘🏽‍♀️🏊‍♀️
#ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ

➧ በማሕበራዊ ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!!!
👇👇👇👇 Facebook=>https://www.facebook.com/netsisport
Telegram=>

Photos from Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C's post 03/04/2024

ለከተማው ስፖርት እንቅስቃሴ መስፋፋት ላደረጉት አስተዋፅዖ አቶ በላይ ደጀን ከኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ የምስክር ወረቀትና ምስጋና ተበረከተላቸው::

ለስፖርቱና ለወጣቱ የተፈጠሩ መንታ መሳይ የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፍዎች:: አቶ በላይ ደጀንና አቶ ማቲዮስ ሶቦቃ እንኳን ደስ አላችሁ::
ለስፖርቱ ዕድገትና ለወጣቱ ተጠቃሚነት በጋራ መስራት ወሳኝ ነው::

Photos from Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C's post 02/04/2024

የተማሪዎች የማለዳ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን ዛሬም “በህብረት ችለናል!” በሚል መሪ ቃል ተከናውኗል፡፡
መጋቢት 24/2016ዓ.ም
ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ
🏃🏿‍♀️🏃🏿‍♂️🏃🏿//🏃🏿🏃🏿‍♂️🏃🏿‍♀️
የህዳሴው ግድብ መሰረት የተጣለበትን 13ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ “በህብረት ችለናል!” በሚል መሪ ቃል የማዳ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በአዲስ ምዕራፍ ቅድመ አንደኛና አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ተካሄደ፡፡
ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ እና የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ በመተባበር የሚያከናውኑት የተማሪዎች የማለዳ የአካል ብቃት ብቃት እንቅስቃሴ በዛሬው ዕለትም ቀጥሎ ከማለዳው 12፡00 ሰዓት ጀምሮ የት/ቤቱ መምህራን፣ ር/መምህራንና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ተከናውኗል፡፡
#ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ
#የአዲስ አበባ ከተማ ትምህት ቢሮ
#የአዲስ አበባ ከተማ ወጣችና ስፖርት ቢሮ
#የአዲስ ምዕራፍ ቅድመ አንደኛና አንደኛ ደረጃ ት/ቤት
➧ በማሕበራዊ ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!!!
Telegram=>
Youtube=>http://bit.ly/subscribe_netsisport

01/04/2024
Photos from Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C's post 31/03/2024

በሸገር ከተማ ታላቁ የጎዳና ላይ ሩጫ እና የማስ-ስፖርት በድምቀት ተካሄደ፡፡
መጋቢት 22/2016 ዓ.ም
ሸገር ከተማ፤ ኮዬ ፈጨ
🏃🏿‍♀️🏃🏿‍♂️🏃🏿*//🏃🏿🏃🏿‍♂️🏃🏿‍♀️
በዛሬው ዕለት በሸገር ከተማ - ኮዬ ፈጨ ከማለዳው 12፡00 ሰዓት ጀምሮ የታላቁ ሩጫና የማስ ስፖርት በድምቀት ተከናውኗል፡፡ በዝግጅቱ ላይ የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና አመራሮች፣ የሸገር ከተማ የስራ ኃላፊዎችና አመራሮች፣ በርካታ ነዋሪዎች፣ የአትሌቲክስ ክለቦችና ጥሪ የተደረጉላቸው እንግዶች በተገኙበት ተከናውኗል፡፡
በፕሮግራሙ ላይ የኦሮሚያ ክልል ም/ፕሬዚደንት አቶ አወሉ አብዱ፣ የህዳሴው ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሄራዊ ምክር ቤት ፅህፈት ቤት ኃላፊ ዶ/ር አረጋዊ በርሄ፣ የሸገር ከተማ ከንቲባ ዶ/ር ተሸመ አዱኛ፣ የኦሮሚያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ማቴዎስ ሰቦቃ፣ የሸገር ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ኃላፊ አቶ ናስር ፣ የፊት ኮርነር ስፖርት አማሪ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንስትራክተር ነፃነት፣ ነዋሪዎች፣ የመንግስትና የግል ሰራተኞች እና አትሌቶች ተሳትፈውበታል፡፡
ታላቁ ሩጫ በሸገር ከተማ “ሕዳሴ ግድባችን የትውልድ አሻራ ነው!” በሚል መሪ ቃል የተከናወነ ሲሆን በሩጫው ላይ ከ1ኛ እስከ 3ኛ ለወጡ ተወዳዳሪዎች ሜዳሊያና ዋንጫ ዳጎስ ካለ የገንዘብ ሽልማት ጋር ተሰጥቷቸዋል፡፡

➧ በማሕበራዊ ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!!!
Telegram=>
Youtube=>http://bit.ly/subscribe_netsisport

Photos from Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C's post 24/03/2024

የአካል ብቃት እንቅስቃሴ የሚያዘወትሩ ሴቶች የተስተካከለ ቁመና እንደሚኖራቸው ተገለጸ

መጋቢት 15 2016 ዓ.ም ፊት ኮርነር

🏃‍♀️🏃‍♂️=================🏃‍♂️🏃‍♀️

ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ከአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፓርት ቢሮ እና ከአዲስ አበባ ሴቶችና ማህብራዊ ጉዳይ ቢሮ ጋር በመተባበር 113ኛውን የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ በነጋዋ ሴት የክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከሉ ደማቅ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ አካሄደ

#ዛሬ ከማለዳው 12:00 ሰዓት ጀምሮ የሴቶች ቀን ምክንያት በማድረግ በተካሄደው የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ላይ በአዲስ አበባ ምክር ቤት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ ዘይነባ ሹክር፣ የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ወይንሸት ዘሪሁን የማዕከሉ አመራሮች ከሁሉም ክፍለ ከተማ የተውጣጡ ሴቶች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተው ዝግጁቱን አድምቀውታል

የፊት ኮርነር አማካሪና ስራ አስኪያጅ ኢንስትራክተር ነጸነት ካሳ በማስ ስፖርት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት አካል ብቃት ማዘውተር ጤናማ ልብ እና ሳንባ፤ ጠንካራ አጥንት እና ጡንቻ፤ የተሻለ የአእምሮ ጤና የተስተካከል የሰውነት ክብደት እእንዲኖር ያስችላል ብለዋል።

የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ የሚሰጠውን ዘርፈ ብዙ ጥቅም በመረዳት ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማዕከሉ ደረጃውን የጠበቀ ጂም ማስገንባታቸውን የገለጹት ኢንስትራክተር ነጻነት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በማዘውተር በአዕምሮችን ንቁ በአካላችን ጠንካራ መልካም ስብዕና የተላበስን መሆን እንችላለን ብለዋል

የዘንድሮው ዓለም አቀፍ #የሴቶች ቀን_ማርች_8 በዓለ አቀፍ ደረጃ ለ113ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ለ48ኛ ጊዜ ሴቶችን እናብቃ ሰላምና ልማትን እናረጋግጥ በሚል መሪ ቃል እየተከበረ እንደሚገኝ ተመልክቷል

Photos from Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C's post 26/02/2024

የጤና ቡድኑ ላይ በተከሰተው የትራፊክ አደጋ የሰው ህይወት መጥፋቱ ይታወቃል።

ፈጣሪ ብርታቱን ይሰጣችሁ ወገኖቼ::
ነብስ ይማር!!!!!

Photos from Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C's post 20/02/2024

ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ከኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ጋር በመተባበር የሚከናወነው የማስ ስፖርት ፕሮግራም መከናወኑን ቀጥሎ በዛሬው ዕለትም በድምቀት ተከናውኗል፡፡
የካቲት 12/2016 ዓ.ም (ሳር ቤት - ተስፋ ሜዳ)
*🏃🏿‍♀️🏃🏿‍♂️🏃🏿🏃🏿‍♀️🏃🏿‍♂️🏃🏿*
የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ እና ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ጋር የሚያዘጋጁት የኦሮሚያ ክልል የመንግስት ሰራተኞች የማስ-ስፖርት እንቅስቃሴ በኦሮሚያ ፕሬዚደንት ጽ/ቤት አስተናጋጅነት በዛሬው ዕለት የካቲት 12/2016 ዓ.ም በድምቀት ተከናውኗል፡፡
በፕሮግራሙ ላይ በም/ፕሬዚደንት ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ ክላስተር አስተባባሪ አቶ አብዱልሃኪም ሙሉ፣ የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ማቴዎስ ሰቦቃ፣ የኦሮሚያ ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ደረጀ አብደኖ ፣ የፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንስትራክተር ነፃነት ካሣ፣ የመንግስት ሰራኞችና ሌሎች የስራ ሃላፊዎች ተሳትፈውበታል፡፡
ይህ የማስ ስፖርት እንቅስቃሴ አካላዊና አዕምሯዊ ጤናን፣ የሰራተኞችን የእርስ በእርስ ግንኙነትን እና አብሮነት የማሻሻል አላማ ያነገበ መሆኑን አቶ ማቴዎስ ሰቦቃ ገልፀዋል፡፡
የፕሮግራሙ ሂደት በግዙፍ የአደባባይ ስክሪን ላይ በቀጥታ የተላለፈ ሲሆን ዝግጅቱ አካላዊና አዕምሯዊ ጤናን፣ የሰራተኞችን የእርስ በእርስ ግንኙነትን እና አብሮነት የማሻሻል አላማ ያነገበ መሆኑን አቶ ማቴዎስ ሰቦቃ ገልፀዋል፡፡
===//===
#ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ
#የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ
➧ በማሕበራዊ ሚዲያ በሚከተሉት አማራጮች ይከታተሉን!
Facebook=>https://www.facebook.com/netsisport
Telegram=>
Youtube=>http://bit.ly/subscribe_netsisport

Photos from Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C's post 07/02/2024

በብቸኛው የጎልፍ ክለብ የጦር ጀነራሎች እና ሌሎች የጦር መኮነኖች በተገኙበት የአካል ብቃት እንቅስቃሴና የጎልፍ ጨዋታ ተደረገ፡፡
ጥር 29/2016 ዓ.ም (አዲስ አበባ - ጎልፍ ክለብ)
🇪🇹🇪🇹🏌️‍♂️⛳️🏌️‍♂️🏃🏿🏃🏿‍♀️🏌️‍♂️⛳️🏌️‍♂️🇪🇹🇪🇹
ከ1940ወቹ ጀምሮ በተመሰረተውና እስካሁንም “አንድ ለእናቱ” ሆኖ በማገልገል ላይ በሚገኘው የጎልፍ ክለብ ውስጥ የጦር ጀነራሎች 🎖🏅🎖 🏅🎖 እና ሌሎች የጦር መኮነኖች 🎖🏅🎖 በተገኙበት ከኢንስትራክተር ነፃነት ካሳ ጋር የአካል ብቃት እንቅስቃሴና የጎልፍ ጨዋታ በዛሬው ዕለት ማለትም ጥር 29/2016 ዓ.ም ተደረጓል፡፡

በዚህ ልዩ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ የጦር አዛዥ ሜ/ጄኔራል ጡሩየ አሰፋ፣ ብ/ጄኔራል ደረጀ መገርሳ፣ ኮሎኔል ጌትነት አዳነ፣ ኮሎኔል አሸናፊ አሊ፣ እና ሌሎች አንጋፋ መኮንኖችና ኢንስትራክተር ነፃነት ካሣ ተሳትፈውበታል፡፡

🇪🇹🏌️‍♂️⛳️🏌️‍♂️⛳️🏌️‍♂️🏌️‍♂️⛳️🇪🇹
#ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ
#የአዲስ አበባ ጎልፍ ክለብ
➧ በማሕበራዊ ሚዲያ በሚከተሉት አማራጮች ይከታተሉን!
Facebook=>https://www.facebook.com/netsisport
Telegram=>
Youtube=>http://bit.ly/subscribe_netsisport

Photos from Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C's post 07/02/2024

ኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ከፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ጋር በመተባበር የጤና ማስ-ስፖርት በድምቀት ተከናወነ፡፡
ጥር 29/2016 ዓ.ም (ሳር ቤት - ተስፋ ሜዳ)
🏃🏿‍♀️🏃🏿‍♂️******//******🏃🏿‍♀️🏃🏿
የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ እና ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ጋር በመተባበር ያዘጋጁትና የኦሮሚያ ጤና ቢሮ በኃላፊነት የመራው የሰራኞች የማለዳ የአካል ብቃት እቅስቃሴ ሳር ቤት በሚገኘው “ተስፋ ሜዳ” በትናንትናው ዕለት (ጥር 28/2016 ዓ.ም) በድምቀት ተከናውኗል፡፡

እንደ ከዚህ በፊቱ ሁሉ የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በፕሮግሙ ላይ በመገኘት ለሰራተኞቻቸው ጤና በትኩረት እንደሚሰሩ በተግባር አረጋግጠዋል፡፡ በዚህ የጤና ማስ ስፖርት ፕሮግራም ላይ በም/ፕሬዚደንት ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ ክላስተር አስተባባሪ አቶ አብዱልሃኪም ሙሉ፣ የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ማቴዎስ ሰቦቃ፣ የኦሮሚያ ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ደረጀ አብደኖ እና የፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንስትራክተር ነፃነት ካሣ ተሳትፈውበታል፡፡

የጤና ማስ ስፖርት ፕሮግራም በግዙፍ የአደባባይ ስክሪን ላይ በቀጥታ የተላለፈ ሲሆን ዝግጅቱ በከፍተኛ ድምቀት ተጠናቋል፡፡
===//===
#ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ
#የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ
➧ በማሕበራዊ ሚዲያ በሚከተሉት አማራጮች ይከታተሉን!
Facebook=>https://www.facebook.com/netsisport
Telegram=>
Youtube=>http://bit.ly/subscribe_netsisport

Photos from Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C's post 04/02/2024

የተቸገሩ ህሙማንን ለመርዳት የሚውል የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር በስኬት ተከናወነ።
ጥር 26/2016 ዓ.ም (HELP ETHIOPIA)
🏃‍♀️🏃‍♂️*🧘🏿‍♀️
ለተቸገሩ ህሙማንን ለመርዳት የሚውል የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር በቅዱስ ዮሴፍ ት/ቤት ግቢ ውስጥ ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ታጅቦ በስኬት ተከናውኗል።
ይህንን የበጎ አድራጎት የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ያዘጋጀው 'HELP ETHIOPIA' የተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን የተቋቋመው በ2021 እ.ኤ.አ ሲሆን ዶ/ር ፈርዖን ጌታቸው በኘሬዚደንትነት እንደሚመሩት ተገልጿል።

HELP ETHIOPIA የተመሰረተበት ዋና ዓላማ የተቸገሩ ህሙማንን መርዳት፣ ተማሪወችን በመሪነት ማብቃት፣ የጤና ስርዓቱን ማሻሻል መሆኑንና ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሪፈር ተደርገው በኢኮኖሚ ችግር መታከም ለማይችሉ፤ በሐኪም የታዘዙ መድሀኒቶችን፣ የላቦላቶሪ እና ኢሜጂንግ ምርመራወችን ወጪ በመሸፈን እንዲሁም ነፃ አገልግሎቶችን እንዲያገኙ በማድረግ ባለፋት ሦስት አመታት ከ750 በላይ ታካሚወችን መርዳቱን ዶ/ር ኢየሩሳሌም ኮከቤ ገልፀዋል።

በዛሬው እለት የተካሄደው የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ላይ የጋራ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ፣ የእግር ኳስ ውድድርና አጫጭር ጨዋታወች የተካተቱበት ሲሆን ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪን ጨምሮ በርካታ ድርጅቶችና ግለሰቦች ተሳትፈውበታል።
በቀጣይም ተመሳሳይ አላማ ያላቸው የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራሞች በስፖርታዊ እንቅስቃሴወችና ውድድሮች ታጅበው እንደሚከናወኑ HELP ETHIOPIA ገልጿል።
=====//======
#ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ
ETHIOPIA

Photos from Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C's post 18/01/2024

ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ከኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ጋር በመተባበር የማለዳ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተከናወነ፡፡
ጥር 08/2016 ዓ.ም (ሳር ቤት - ተስፋ ሜዳ)
🏃🏿‍♀️🏃🏿‍♂️//🏃🏿‍♂️🏃🏿‍♀️
የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ከፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ጋር በመተባበር ለሰራኞች የማለዳ የአካል ብቃት እቅስቃሴ ሳር ቤት በሚገኘው ውብ ሁኖ በተገነባው “ተስፋ ሜዳ” በድምቀት ተከናውኗል፡፡
ለኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ሰራተኞች በተዘጋጀው በዚህ ማራኪ የማለዳ የአካል ብቃት እቅስቃሴ ላይ የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ማቴዎስ ሰቦቃ፣ የኦሮሚያ ክልል ም/ፕሬዚደንት አቶ አወል አብዱ፣ በም/ፕሬዚደንት ደረጃ የማህበራዊ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አብዱልሃኪም ሙሉ፣ የጨፌ ኦሮሚያ ጽ/ቤት ም/ኃላፊ አቶ ኤሊያስ ኡመታ፣ የባህልና ስፖርት ም/ዲኤታ አቶ መስፍን ቸርነት እና የፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንስትራክተር ነፃነት ካሳ ተሳትፈውበታል፡፡
ይህ ልዩ ፕሮግራም ከፍተኛ ዝግጅት የተደረገበትና የተለያዩ የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎች በኢንስትራክተር ነፃነት ካሣ እየተመራ የተከናወነ ሲሆን በተጨማሪም የሰላም ምልክት የሆኑት እርግቦችን 🕊🕊 በመልቀቅ ሁሉም ነዋሪዎች ለሰላምና ለአብሮነት እዲሰራ ተግባራዊ መልዕክት ተላልፏል፡፡
ዝግጅቱም በግዙፍ የአደባባይ ስክሪን ላይ በቀጥታ የተላለፈ ሲሆን በዝግጅቱ ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማቸው ገልፀዋል፡፡
==//==
#ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ
#የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ
➧ በማሕበራዊ ሚዲያ በሚከተሉት አማራጮች ይከታተሉን!
Facebook=>https://www.facebook.com/netsisport
Telegram=>
Youtube=>http://bit.ly/subscribe_netsisport

Photos from Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C's post 03/01/2024

# የአንድ ሰዓት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለሚሊዮኖችና ለአብሮነት በሚል መሪ ቃል በድምቀት ተከበረ፡፡
ታህሳስ 24/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ
*********//********
ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ እንደወትሮው ሁሉ ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር እና ከአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ጋር በመተባበር “የአንድ ሰዓት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለሚሊዮኖችና ለአብሮነት” በሚል መሪ ቃል ዛሬ የተከናወነው የአካል ብቃት እቅስቃሴ በመምራትና በማስተባበር እውን እንዲሆን አድርጓል፡፡
በዚህ በደማቅ ሁኔታ በተከናወነው የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ላይ የሃገራችን ከፍተኛ አመራሮች፣ ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎችና የቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል ታራሚዎች ተሳትፈውበታል፡፡

# የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለጤናችንና ለአብሮነታችን!
➧ በማሕበራዊ ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!!!
Telegram=>
Youtube=>http://bit.ly/subscribe_netsisport

Photos from AMN-Addis Media Network's post 31/12/2023

Morning workout with leaders of the city.

‘’ Get your body ready to start the day by working out.’’

Photos from Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C's post 29/12/2023

የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ከፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ጋር በመተባበር እየተከናወነ የሚገኘው የተማሪዎች የማለዳ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለፀ፡፡
ታህሳስ 19/2016 ዓ.ም፤
ትንቢተ ኤርሚያስ የመ/ደ/ት/ቤት ፤ አዲስ አበባ
**********//**********
የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ከፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ጋር በመተባበር እየተከናወነ የሚገኘው የተማሪዎች የማለዳ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን በዛሬው ዕለት በትንቢተ ኤርሚያስ የመ/ደ/ት/ቤት በደማቅ ሁኔታ ተከናውኗል፡፡

በዚህ መርሃ ግብር ላይ የፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ዋ/ስራ አስኪያጅ ኢንስትራክተር ነፃነት ካሳ፣ የአ/አበባ ት/ቢሮ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሲሳይ እንዳለ፣ የአ/አ/ወ/ስፖርት ቢሮ የማ/ስፖርት/ማስፋፊያ ተሳትፎ ዳይሬክተር አቶ እንግዳዎርቅ ዳንዔል ፣ የት/ቤቱ ርዕሰ መ/ር፣ መምህራንና ተማሪዎች ተሳትፈውበታል፡፡

ይህ መርሃ ግብር የተማሪዎችን አካላዊ፣ አዕምሯዊና ማህበራዊ ጤና ለመጠበቅና በትምህርታቸው ውጤታማ ሁነው ብቁ፣ ኃላፊነት የሚሰማቸውና ለሃገር አንድነት የሚተጉ የሃገር ተረካቢዎችን ለማፍራት እንደሚረዳ ተገልጽዋል፡፡

የተማሪዎች የማለዳ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የዜና ቻናል (EBC News) እና መዝናኛ ቻናል (EBC Entertainment) ላይ በመተላለፍ ላይ ይገኛል፡፡
==========//=========
#ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ
#የአዲስ አበባ ከተማ ትምህት ቢሮ
#የአዲስ አበባ ከተማ ወጣችና ስፖርት ቢሮ
#በትንቢተ ኤርሚያስ የመ/ደ/ት/ቤት
➧ በማሕበራዊ ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!!!
Telegram=>
Youtube=>http://bit.ly/subscribe_netsisport

Photos from Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C's post 07/12/2023

የተማሪዎች የማለዳ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በተስፋ ኮከብ አንደኛና መካከለኛ ት/ቤት በድምቀት ተከናወነ::
“በአካልና በአዕምሮ የዳበረ ትውልድ ለሀገር እድገት!”
ሕዳር 27/2016 ዓ.ም ፤ ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ
*************************************************
ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ጋር በመተባበር እያከናወኑት የሚገኙት የተማሪዎች የማለዳ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን ዛሬ ማለዳ በተስፋ ኮከብ አንደኛና መካከለኛ ት/ቤት በድምቀት ተከናውኗል፡፡

በእንቅስቃሴው ላይ የፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንስትራክተር ነፃነት ካሳ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ጽ/ቤት አቶ ሲሳይ እንዳለ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ማኔጅመንት አባላት፣ የልደታ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ እጅጋየሁ አድማሱ፣ የትምህርት ቤቱ ር/መምህራን፣ መምህራንና ተማሪዎች ተሳትፈውበታል፡፡

ኢንስትራክተር ነፃነት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ መስራት ለአዕምሮና ለአካል ጤንነት ያለውን አስፈላጊነት አብራርተው የት/ቤቱ የሰውነት ማጎልመሻ (HPE) መምህራን ተማሪዎቻቸውን አዘውትረው የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በማሰራታቸውና ለሰጡት ትኩረት ምስጋናቸውን ገልፀዋል፡፡

አቶ ሲሳይ በበኩላቸው “በአካልና በአዕምሮ የዳበረ ትውልድ ለሀገር እድገት!” በሚል መሪ ቃል እየተከናወነ ያለው የማለዳ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለተማሪዎች ትምህርት ውጤታማነት ጠቃሚ መሆኑን አውስተው በሁሉም ት/ቤቶች እንዲተገበርና ሁሉም ተማሪዎች ባህል እንዲያደርጉት እየተሰራ ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡

ሙሉ ፕሮግራሙ በኢ.ቢሲ /EBC/ “ኢትዮ-ጤናና ብቃት” ፕሮግራም ላይ እንዲሁም በዩቱብ Netsi Sport “https://www.youtube.com/” ላይ ይተላለፋል፡፡
================//==============
#ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ
#የአዲስ አበባ ከተማ ትምህት ቢሮ
#ተስፋ ኮከብ አንደኛና መካከለኛ ት/ቤት
➧ በማሕበራዊ ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!!!
Telegram=>
Youtube=>http://bit.ly/subscribe_netsisport

Photos from Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C's post 02/12/2023

የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ከፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ጋር በመተባበር 18ኛውን የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በድምቀት ማክበራቸው ተገለፀ።
ህዳር 22/2016 ዓ.ም
ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ (ባቱ /ዝዋይ)
*****//*****
የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ከፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ጋር በመተባበር 18ኛውን የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ቀን ሁሉም የሕብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት ጠዋት ከማለዳ ጀምሮ በአካል ብቃት እንቅስቃሴና በሌሎች ዝግጅቶች ታጅቦ በድምቀት መከበሩ ተገልጿል።

በኦሮሚያ ክልል በባቱ-ዝዋይ ከተማ በተዘጋጀው በዚህ ህዝባዊ በዓል ላይ የፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንስትራክተር ነፃነት ካሳ፣ የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ማቲዮስ ሰቦቃ፣ የመንግስት ኃላፊወች እና ሁሉም የሕብረተሰብ ክፍል በነቂስ ወጥቶ አክብሮታል።

አቶ ማቲዮስ ''ስፖርት የማህበረሰብ ጤና መሰረት መሆኑን ገልፀው፤ ቀኑ ሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች በእኩልነትና በአንድነት እየኖሩ መሆኑን የሚያመላክት መሆኑን ገልፀዋል።

ኢንስትራክተር ነፃነት በበኩላቸው ''የአካል ብቃት እንቅስቃሴን በየትኛውም ጊዜና ቦታ ማዘውተር ለማህበረሰብ ጤና መሻሻል ቁልፍ መሆኑን ገልፀው፤ ጤናማ ትውልድ በመፍጠር የሃገራችንን አንድነትና የህዝባችንን አብሮነት ማስጠበቅ እንችላለን'' ሲሉ ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ቀን በሁሉም ኢትዮጵያዊያን -- በሁሉም የሃገሪቱ ክፍሎች እንደሚከበር ይታወቃል።
===============//===============
#ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ
#የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ
➧ በማሕበራዊ ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!!!
Telegram=>
Youtube=>http://bit.ly/subscribe_netsisport

የሦስት ወር ነፃ የጂም ፓኬጅ የሚሸለሙበት ቪዲዮ! እስከ መጨረሻው ይመልከቱት! ይሸለሙ! 30/11/2023

ህዳር 20/2016 ዓ.ም
ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ፤
*****************
ቃል በገባነው መሠረት መጀመሪያ ''Shape-Up'' ብለው የፃፋ አምስት ግለሰቦች የሦስት ወር የጅም ፓኬጅ ተሸላሚ ሆነዋል።
አሸናፊ የሆናችሁና በውስጥ መስመር የተገለፀላችሁ ተከታታዮች ቅዳሜ ፥ ህዳር 22፥ ከጠዋቱ 3:00 ሳር-ቤት በሚገኘው የ Shape Up Gym እንድትገኙና ስልጠናችሁን እንድትጀምሩ እንገልፃለን።

የሦስት ወር ነፃ የጂም ፓኬጅ የሚሸለሙበት ቪዲዮ! እስከ መጨረሻው ይመልከቱት! ይሸለሙ! ይህንን ሊንክ 👉👉 http://bit.ly/subscribe_netsisport በመጫን ሰብስክራይብ ያድርጉ ለሌሎችም ሼር ያድርጉ@supersoprtlive2688

Photos from Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C's post 23/11/2023

የማለዳ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በሁሉም ት/ቤቶች ባህል ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ፡፡
ሕዳር 13/2016 ዓ.ም ፡
#ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ
#የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ
#የአዲስ አበባ ከተማ በወጣቶችና ስፖርት ቢሮ
====================================
በፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ፣ በአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ እና በወጣቶችና ስፖርት ቢሮ በኩል በትብብር እየተከናወነ ያለው የማለዳ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በየካ ክፍለ ከተማ በሚገኘው ወንድይራድ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት በደመቀ ሁኔታ ተካሄደ፡፡

በፕሮግሙ ላይ የወጣችና ስፖርት ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳዊት ትርፉ፣ የፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንስትራክተር ነፃነት ካሳ፣ ሌሎች የቢሮ ኃላፊዎችና የት/ቤቱ ማህረሰብ አባላት በሙሉ ተሳፈውበታል፡፡

በዕለቱ አቶ ዳዊት የማለዳ የአካል ብቃት እንቅስቃሴውን ባህል ማድግ እደሚገባ የገለፁ ሲሆን ኢንስትራክተር ነፃነት ደግሞ እንቅስቃሴው የሚያስገኘውን አዕምሯዊ፣ አካላዊ፣ ማህበረሰባዊና አብራርተው፣ ይህም ለትምህርት አቀባበል የላቀ አስተዋፅዖ እንዳለው ገልፀዋል፡፡

➧ በማሕበራዊ ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!!!
Telegram=>
Youtube=>http://bit.ly/subscribe_netsisport

Photos from Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C's post 22/11/2023

ተማሪዎችን በአካል፣ በአእምሮና በስነ ልቦና ለማጎልበት የሚከናወነው የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ፡፡
ሕዳር 12 ቀን 2016 ዓ/ም
# ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ
# አ/አ ት/ት ቢሮ
# ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ
============================================
የፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ፣ የአ/አ ከተማ ትምህርት ቢሮ እና ወጣቶችና ስፓርት ቢሮ በሦስትዮሽ በመተባበር በጄነራል ታደሰ ብሩ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተማሪዎች የአካል ብቃት እንቅስቃሴ መርሃ ግብር በከፍተኛ ድምቀት አካሂደዋል፡፡
ዛሬ ማለዳ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ በተካሄደው የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ከት/ቤቱ ር/መምህራን፣ መምህራንና ተማሪዎች በተጨማሪ የወጣቶችና ስፓርት ቢሮ፣ የትምህርት ቢሮ አመራሮች የጉለሌ ክፍለ ከተማ አመራሮች ተሳትፈውበታል፡፡

የዕለቱን የማለዳ የአካል ብቃት የመሩት ኢንስትራክተር ነፃነት ካሣ በበኩላቸው የማለዳ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተማሪዎች አካላዊ፣ አዕምሯዊ እና ስነ ልቦናዊ ብቃታቸውን በማሳደግ ለትምህርት ያላቸውን ዝግጁነት ከማሳደጉም በተጨማሪ ተነሳሽነታቸውን በማሳደግ የአዕምሮ ንቃታቸው ከፍ በማድረግ መማር ማስማሩን ሂደት የተሳካ እንዲሆን ያደርጋል ሲሉ ለተሳታፊዎች ሙያዊ ገለፃ አድርገዋል፡፡

ይኽ እንቅስቃሴ በሁሉም ት/ቤቶች እንዲዘወተር እየተሰራ መሆኑን የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፓርት ቢሮ አማካሪ አቶ ታሪኩ እሸቴ ገልፀዋል።

የተማሪዎች የማለዳ የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎች በኢ.ቢ.ሲ /EBC/ “የኢትዮ ጤናና ብቃት ፕሮግራም” ላይ የሚተላለፍ ሲሆን በተጨማሪም በፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ የዩቱብ ገጽ ላይ እንደሚለጠፍ ተመላቷል፡፡

➧ በማሕበራዊ ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!!!
Telegram=>
Youtube=>http://bit.ly/subscribe_netsisport

Photos from Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C's post 18/11/2023

ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ከአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ጋር በመተባበር ሲሰጥ የነበረው የመጀመሪያ ደረጃ የአሰልጣኞች ስልጠና የመዝጊያ ዝግጅት ተከናወነ፤
ሕዳር 08/2016 ዓ.ም፤ አዲስ አበባ
*********************************************
ላለፉት 15 ቀናት ያኽል በከፍተኛ ሙያዊ ስነምግባር በሳይንሳዊ መንገዶች ሲሰጥ የነበረው የመጀመሪያ ደረጃ የአሰልጣኝነት ስልጠና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በተገኙበት የመዝጊያ ዝግጅት በማድረግ ተጠናቀቀ፡፡

በዚህ ስልጠና ላይ ከባህር ዳር፣ ከድሬዳዋ፣ ከአርባ ምንጭና ከአዲስ አበባ የተውጣጡ 70 ሰልጣኞች ተሳትፈውበታል፡፡

በመዝጊያ ስነስርዓቱ ላይ ስልጠናውን በበላይነት ለመሩት ለኢንስትራክተር ነፃነት ካሣ እና ለአሰልጣኝ ኢዮብ አሰፋ የ27000 ብር ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን ለሰልጣኞች ደግሞ 73,000 ብር ማበረታቻ ከዶ/ር እመቤት ገዛኸኝ ተበርክቶላቸዋል፡፡

የስልጠናው ተሳፊዎች በበኩላቸው አሰልጣኞች ላበረከቱላቸው ሁለገብ አስተዋጽዖ እዲሁም ያለመሰሰት ለሰጧቸው እውቀትና ክህሎት ምስጋናቸውን ለመግለጽ ስጦታ አበርክተውላቸዋል፡፡

ሰልጣኝ መማር ተሸለ (ከባህር ዳር)፣ ሰልጣኝ ኤብል በዛብህ (ከአርባ ምንጭ) እና በረከት ደስታ (ከአዲስ አበባ) ስልጠናው ከጠበቁት በላይ እውቀትና ክህሎት እንዳገኙበት ገልፀው ወደፊት ስራቸውን በሳይንሳዊ መንገድ ለመምራት እንደሚረዳቸው ጠቅሰዋል፡፡

በዕለቱ በክብር እግድነት ለተገኙ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላትና ሌሎች እንግዶች የአካ ብቃት እንቅስቃሴ መስሪያ የዮጋ ምንጣፍ (Yoga mat) ስጦታ ከፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪና ከአ/አ ወጣችና ስፖርት ቢሮ በኩል ተበርክቶላቸዋል፡፡
---------//--------
#ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ
#የአዲስ አበባ ስፓርት ለሁሉም ጽ/ቤት

➧ በማሕበራዊ ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!!!
👇👇👇👇 Facebook=>https://www.facebook.com/netsisport
Telegram=>
Youtube=>http://bit.ly/subscribe_netsisport

የሦስት ወር ነፃ የጂም ፓኬጅ የሚሸለሙበት ቪዲዮ! እስከ መጨረሻው ይመልከቱት! ይሸለሙ! 16/11/2023

ነገ ዓርብ ህዳር 07/2016 ዓ.ም ከረፋዱ 4:00 ጀምሮ ይከታተሉ....

የሦስት ወር ነፃ የጂም ፓኬጅ የሚሸለሙበት ቪዲዮ! እስከ መጨረሻው ይመልከቱት! ይሸለሙ! ይህንን ሊንክ 👉👉 http://bit.ly/subscribe_netsisport በመጫን ሰብስክራይብ ያድርጉ ለሌሎችም ሼር ያድርጉ@supersoprtlive2688

ልብ፣ ሳንባና ጡንቻ በእጅጉ የተፈተኑበት፤ የኢ.ቢ.ሲ ዋና ስራ አስኪያጅ ከነፂ ጋር! 16/11/2023

➧ቀጥታ ስርጭት ይከታተሉን......

ልብ፣ ሳንባና ጡንቻ በእጅጉ የተፈተኑበት፤ የኢ.ቢ.ሲ ዋና ስራ አስኪያጅ ከነፂ ጋር! ይህንን ሊንክ 👉👉 http://bit.ly/subscribe_netsisport በመጫን ሰብስክራይብ ያድርጉ ለሌሎችም ሼር ያድርጉ@supersoprtlive2688

Want your business to be the top-listed Gym/sports Facility in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Videos (show all)

የኤርገንዶ ምርቶች የሆኑትን ምቹና ተመራጭ የሆኑ የተለያዩ ምንጣፎች (Mats) ይዘንላችሁ ቀርበናል። 1ኛ:- ምቹና አስተማማኝ የጅምናዚየም ወለል ምንጣፍ (Gym mats)2ኛ:- የህፃናት ወለ...
ታህሳስ 24/ 2014 ዓ.ም #ቀጥታ_ከመስቀል_አደባባይ #መስቀል_አደባባይ በትውልደ ኢትዮጵያዊያን ፣ በኢትዮጵያ ወዳጆችና በከተማዋ ነዋሪዎቿ ከማለዳው 12:00 ሰዐት ጀምሮ #በማስ_ስፖርት ደ...
Coming Soon on EBC News channel
ሚያዚያ 10 / 2013 ዓ.ም #ቀጥታ_አቃቂ_ቃሊቲ_ክፍለ_ከተማ #10ኛው_ከተማ_አቀፍ_የአካል_ብቃት እንቅስቃሴ የኮቪድ 19 ፕሮቶኮል መመሪያንና አሰራርን በጠበቀ መልኩ በአዲስ አበባ ከተማ አ...
የዓለም የስፖርት ቀንን ስናከብር ሁላችንም በአቅማችን ልክ መደበኛ በሆነ መንገድ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እንስራ።
መጋቢት 26 / 2013 ዓ.ም #ቀጥታ_አምቦ_ከተማ ።#አብሮነታችን_ለሀገራችን ! ለሰላማችን ፣ለአንድነታችንና ለወንድማማችነት በሚል መሪ ሀሳቦች #በአምቦ_ከተማ ከማለዳው 12:00 ሰዐት ጀምሮ...
የካቲት 28 / 2013 ዓ.ም #ቀጥታ_መስቀል_አደባባይ ##የሴቶች_ቀን  #ማርች_8  የሴቶች ተሳትፎ ለሁለንተናዊ #ብልፅግና በሚል መሪ ሀሳብ በመስቀል አደባባይ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ...
የካቲት 07 / 2013 ዓ.ም #ቀጥታ_አዲስ_ከተማ ።#6ኛው_ዙር_ከተማ_አቀፍ_የአካል ብቃት እንቅስቃሴ  በልዩ በድምቀት እና ልዩ ልዩ  ዝግጅቶች ከማለዳው 12:00 ሰዐት ጀምሮ #መድሀኒዐለም...
የካቲት 07 / 2013 ዓ.ም #ቀጥታ_አዲስ_ከተማ ።#6ኛው_ዙር_ከተማ_አቀፍ_የአካል ብቃት እንቅስቃሴ  በልዩ በድምቀት እና ልዩ ልዩ  ዝግጅቶች ከማለዳው 12:00 ሰዐት ጀምሮ #መድሀኒዐለም...
የካቲት 06 / 2013 ዓ.ም #ቀጥታ_ደብረ_ብርሃን ከተማ#አብሮነታችን_ለሀገራችን በሚል መሪ ቃል ማህበረሰብ አቀፍ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ #ማስ_ስፖርት ለለሁሉም ዜጋ በሁሉም ቦታ ዛሬ ከማ...
ታህሳስ 18 / 2013 ዓ.ም #ቀጥታ_ለሚ_ኩራ ክፍለ ከተማ#ለሀገሬ_ሰላም_ዘብ_እቆማለሁ_ለመከላከያ_ሰራዊት ቅድሚያ እሰጣለሁ! በሚል መሪ ሀሳብ #ከተማ_አቀፍ የሰላም ንቅናቄ #የአካል_ብቃት ...
ታህሳስ 03 / 2013 ዓ.ም #የደመቀ_ዝግጅት ተጠናቀቀበቲንሻ ሁለገብ ስታዲየም ከማለዳው 12:00 ሰዐት ጀምሮ #በፊት_ኮርነር_አማካሪ ስራ አስኪያጅ በኢንስትራክተር ነፃነት ካሳ መሪነት #የ...

Telephone

Address


Addis Ababa
Other Personal Trainers in Addis Ababa (show all)
Next Fitness Next Fitness
Bole
Addis Ababa

Fitness, Health, food, Pt #addissababa � Nutritionist � Personal Trainer � Fitness Instructor � Blogger � [email protected]

Shassy Shassy
Bole
Addis Ababa, 0000

+251936761354 ይደውሉልን ቴሌግራም https://t.me/joinchat/WKFZIyxeZFWrtHMD

Bahar Bahar
Addis Ababa

This page is helps to build body

Coaching by Marine Coaching by Marine
Addis Ababa

Certified Personal Trainer - Addis Abeba Online Personal Trainer - English/French Gymnastics Instruc

What did u workout today? What did u workout today?
Addis Ababa

ውፍረትን በመቀነስ ጤነኛ ሰውነት ይያዙ። lose that stubborn belly fat eas

Addis Trainer Addis Trainer
Bole
Addis Ababa

AT provides personal training - whether you want to lose or gain weight, or simply build up your condition, I will provide you a dedicated training

Eyob Ashenafi job Eyob Ashenafi job
Addis Ababa

THIS PAGE IS NEW AND REAL I KNOW REAL IS RARE BUT TRUST IS BLESSED

Fitness & Athletics Coach MIKI Fitness & Athletics Coach MIKI
Addis Ababa

ማንኛውም ሰው ጤናማ፣ ጠንካራና ፣ ያማረ የሰውነት አቋም ሊኖረው ይገባል!!!

Lion heart Lion heart
Addis Ababa

Fitness is lifestyle