ቢላሉል ሐበሺ - Bilalul Habeshi Community - ኑ ወደ ደግነት
Nearby non profit organizations
Kality
Addis Ababa. Ethiopia
###X
Around
Addis Ababa
Addis Abeba
Basketo Laska
Ethiopa
House
Algeria Street
Addis Ababa
You may also like
ቢላሉል ሐበሺ ጽ/ ቤቱ በአ /አ /ከ አራዳ ክ/ከ የሚገኝ ተቋም ሲሆን ምንጩ ከሀገር ውስጥ በሆነ በጀት ዘርፈ ብዙ የበጎ አድራጎት ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።
ቢላል ሐበሺ የልማትና መረዳጃ እድር የ2016/1445 የዒድ አልአድሐ (ዓረፋ) በዓልን ምክንያት በማድረግ ድጋፍ ለሚሹ ከ986 በላይ የሕብረተሰብ ክፍሎች እና የእርዳታ ተቋማት የእርድ እንስሳትን (ኡድሒያ) በተሳካ ሁኔታ አከፋፍሏል።
********************************************
የቢላሉል ሐበሺ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ባሉበት ሆነዉ በመደገፍ የበኩልዎን ይወጡ፦
የአካዉንት ስም፦ ቢላሉል ሐበሺ የልማትና መረዳጃ እድር
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፦1000468418863
ዘምዘም ባንክ፦ 1762810301
ሒጅራ ባንክ፦ 1000677130001
ሕብረት ባንክ፦ 1959711933992028
ንብ ባንክ፦ 7000009204337
አቢሲንያ ባንክ ፦ 84338214
አዋሽ ባንክ ፦ 01322043751400
በስልክዎ ድጋፍ ለማድረግ
************
በ6833 ላይ ok ብለዉ በመላክ የሚስኪኖች ወገኖቻችን ድጋፍ በማድረግ ከአላህ ዘንድ አጅርን ያግኙ!
አድራሻ፦ ሳርቤት አደባባይ ወደመካኒሳ በሚወስደዉ መንገድ ወደታች ወረድ ብሎ 600 ሜትር ተጉዘዉ ያገኙናል
ለበለጠ መረጃ፦ 09-72-79-79-79
09-72-78-78-78 ብለዉ ይደዉሉልን።
“ ኑ ወደ ደግነት“
የኡድሕያ ድጋፍዎን ለቢላሉል ሐበሺ ያድርጉ!
***************************************
ቢላሉል ሐበሺ የልማትና የመረዳጃ ዕድር
ተቋማችን ለረጅም ዘመናት በአስቸጋሪ እና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ኡለማዎች፣ የቲም ልጆች፣ አካል ጉዳተኞች ፣ አረጋዉያን፣ የተማሪ ቤተሰቦች፣ ወገኖቻችን ከጥገኝነትና ከተረጅነት ለማላቀቅ ብዙ ስራዎችን በመስራት ድጋፍ እያደረገ መምጣቱ የሚታወቅ ሲሆን በተመሳሳይ ከፊት ለፊታችን እየመጣ ያለዉ 1445ኛዉ የኢድ አልአድሃ /አረፋ/ በአል ምክንያት በማድረግ የተቸገሩትን ወገኖቻችን ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ የሁላችሁም እገዛና ድጋፍ ያስፈልጋል፡፡
ቢላሉል ሐበሺ የልማትነና መረዳጃ እድር ባሉበት ሆነዉ በመደገፍ የበኩልዎን ይወጡ፦
የአካዉንት ስም፦ ቢላሉል ሐበሺ የልማትና መረዳጃ እድር
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፦1000468418863
ዘምዘም ባንክ፦ 1762810301
ሒጅራ ባንክ፦ 1000677130001
ሕብረት ባንክ፦ 1959711933992028
ንብ ባንክ፦ 7000009204337
አቢሲንያ ባንክ ፦ 84338214
አዋሽ ባንክ ፦ 01322043751400
በስልክዎ ድጋፍ ለማድረግ
************
በ6833 ላይ ok ብለዉ በመላክ የሚስኪኖች ወገኖቻችን ድጋፍ በማድረግ ከአላህ ዘንድ አጅርን ያግኙ!
አድራሻ፦ ሳርቤት አደባባይ ወደመካኒሳ በሚወስደዉ መንገድ ወደታች ወረድ ብሎ 600 ሜትር ተጉዘዉ ያገኙናል
ለበለጠ መረጃ፦ 09-72-79-79-79
09-72-78-78-78 ብለዉ ይደዉሉልን።
“ ኑ ወደ ደግነት“
በኢትዮ-ሳዑዲ ንግድና ኢንቨስትመንት ፎረም ቢላሉል ሐበሺ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ከፍታ በማሳየት ላይ ይገኛል።
***
የኢትዮ-ሳዑዲ ንግድና ኢንቨስትመንት ፎረም ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።
በሳዑዲ አረቢያ የንግድ ምክር ቤት ፌዴሬሽን የተመራ 79 አባላትን የያዘ ከፍተኛ የኢንቨስትመንትና የንግድ የልዑካን ቡድን ኢትዮጵያን ለመጎብኘት ትላንት ማምሻውን አዲስ አበባ መግባቱ ይታወቃል።
በዛሬው ዕለት በሳይንስ ሙዚየም የተዘጋጀውን የቆዳ፣ ጨርቃጨርቅ፣ ማዕድንና የቱሪዝም መዳረሻዎችን የሚያሳይ አውደ-ርዕይን ጎብኝተዋል።
በዚህ አውደ-ርዕይ ላይ ቢላሉል ሐበሺ ካሰባሰባቸው የኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች ቅርሶች ውስጥ እድሜ ጠገብ ማኒስክርብቶችን፣ ጥንታዊ የመገበያያ ገንዘቦችን፣ ጥንታዊ መስጅዶችን፣ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ሚና የነበራቸው ታላላቅ ኡለሞች፣ ታሪካዊ ሰነዶችና ባህላዊ እቃዎችን በአውደ-ርዕዩ ላይ በማስጎብኘት ኢትዩጵያውያን ሙስሊሞች ለእስልምናው መስፋፋት ያበረከቱትን የጎላ አስተዋፅኦ እንዲያዩት እና እንዲረዱት በማድረግ የኢትዮጵያን ከፍታ ማሳየት ተችሏል፡፡
ፎረሙ በሚካሄድበት ወቅት የአ/አ ዩኒቨርስቲ አረብኛ ቋንቋ ክፍል መስራች እና መምህር የሆኑት ዶ/ር መሐመድ ሰይድ ቢላሉል ሐበሺን በመወከል እስልምና ወደ ሃገራችን የገባበትን እና ከቀሪው የአለም ክፍል ጋር እስልምናን ለማስፋፋት ኢትዮጰያ የነበራትን አስተዋፅኦ በሚገባ በማስረዳት በሁሉም ጎብኝዎች መነቃቃትን ፈጥረዋል።
ጎብኝዎቹ በቢላሉል ሐበሺ የሙዝየም ስራ በጣም መገረማቸውን እንዲሁም ይህ ስራ በተጠናከረ እና ዘመናዊ በሆነ መልኩ እንዲሰራ በማድረግ ረገድ የበኩላቸውን ድጋፍ እንደሚያደረጉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
እነዚህን እና መሰል ስራዎችን ለማበረታታት ቋሚ የሰደቃ አባል ለመሆን
0972787878 ወይም 0972797979
እንዲሁም በአጭር የሞባይል መልክት ላይ 6833 በማለት ከታች ሜሴጅ መፃፊያው ላይ Ok ብለው በመላክ በ1 ብር ዘርፈ ብዙ የቢላሉል ሐበሺ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ይደግፉ።
የባንክ አካውንት፡- ቢላሉል ሐበሺ የልማትና መረዳጃ እድር
- የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000319856898
- ንብ ባንክ SPS 290
- አዋሽ ባንክ 01304043785600
በሚከተሉት አማራጮች ሊያገኙን ይችላሉ
https://www.facebook.com/bilalulhabeshiethio
https://www.youtube.com/channel/UC2uwQa04xTy_sDq-TBdPU_Q
https://t.me/bilalulhabeshi
https://twitter.com/bilalul_habeshi
ክፍት የስራ መደብ ማስታወቂያ
ቢላሉል ሐበሺ የልማትና የመረዳጃ ዕድር ከዚህ በታች ለተዘረዘው የስራ መደብ አመልካቾችን አወዳድ መቅጠር ይፈልጋል፡፡
1.የስራ መደቡ መጠሪያ ፡- ገንዘብ ሰብሳቢ
2.ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡-8ኛ ክፍል ያጠናቀቀ
3.ፆታ፡- ወንድ
4.ተፈላጊ የስራ ልምድ ፡-0 ዓመት
5.ብዛት፡- 2
6.ደመወዝ፡- በስምምነት
7.የቅጥር ሁኔታ፡- በቋሚነት
አመልካቾች የትምህርት ማስረጃችሁን በመያዝ ዋናው መስሪያ ቤት ሳርቤት ቫቲካን ኤምባሲ ፊት ለፊት በሚገኘው ቢላሉል ሐበሺ ማዕከል ማመልከት ትችላላችሁ።
ስታንዳርዱን በጠበቀ ስቱዲዮና የፕሮዳክሽን እቃዎች ጠንካራ ባለሙያዎችን ለማፍራት ከቴክኒክ እና ሙያ እውቅና ባገኘንባቸው ዘርፎች ለ5ተኛ ዙር ለማሰልጠን ዝግጅታችንን ጨርሰናል ይምጡ እኛ ብቁ ባለሙያ እናረግዎታለን!
ለ“ቢላሉል ሐበሺ ሙዝየም” እገዛ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን የከተማው ባህል ኪነ ጥበብ እና ቱሪዝም ቢሮ ገለጸ
★★★★★★★★★★★★★★★★★★
የአዲስ አበባ የባህል ኪነ ጥበብ እና ቱሪዝም ቢሮ በከተማው የሚገኘው “ቢላሉል ሐበሺ ሙዝየም” እገዛ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገለጸ፡፡ የቢሮው ምክትል ኃላፊ ሙዝየሙ አሁን ካለበት የተሻለ ሠፊ ቦታ የሚገባው መሆኑን ጥቆማ ሰጥተዋል፡፡
የከተማው የባህል ኪነ ጥበብ እና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሠፍፀ ፍሬስብሐት፣ ቢላሉል ሐበሺ ሙዝየም በርካታ እስላማዊ ቅርሶችን የያዘ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ምክትል ኃላፊው ለ”ኢትዮጵያን ቢዝነስ ሪቪው” መጽሔት ሲናገሩ፤ ቢሯቸው ሙዝየሙ ከሚሰጠው ጠቀሜታ አንጻር ድጋፍ ያስፈልገዋል የሚል እምነት እንዳለው በመግለጽ፣ ለዚህ እንዲረዳ የሚጠበቅበትን እገዛ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑንም አያይዘው ጠቅሰዋል፡፡
የባህል ኪነ ጥበብ እና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ኃላፊው፣ በቢሮው ቀጥታ የበጀት ድጋፍ ማድረግ ስለማይቻል ድጋፉ ሙዝየሙ የተሻለ ቦታ ላይ እንዲያርፍ ለሚመለከታቸው የፌዴራል ተቋማት ጥያቄ ማቅረብ እንደሚሆን አስረድተዋል፡፡ ሆኖም ከዚሁ ጉዳይ ጋር ተያይዞ እስካሁን ድረስ ከሙዝየሙ ይፋዊ ጥያቄ አልቀረበም ብለዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኘው የቢላሉል ሐበሺ ሙዝየም ተከፍቶ ለጎብኚዎች አገልግሎት መስጠት የጀመረው በ2010 ነው፡፡ ሙዝየሙ በተለይ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች ተበትነው የሚገኙ እስላማዊ ቅርሶችን ሰብስቦ የያዘ ነው፡፡ ሙዝየሙን በ2013 የጎበኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ በከተማው ሊጎበኙ ከሚገባቸው ቦታዎች አንዱ ነው ብለው ነበር፡፡
ቢላሉል ሐበሺ በስፖርቱ ዘርፍ ተሳትፎ አደረገ
======================
ቢላሉል ሐበሺ የልማትና መረዳጃ እድር ዘርፈ ብዙ የበጎ አድራጎት ማለትም በትምህርት፣ በማህበራዊ ጉዳይ እና በሌሎችም የስራ ዘርፎች በመሳተፍ ለተለያዩ ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች ሕይወት መቃናት እና የተሻለ ዜጋ እንዲሆኑ በማድረግ ረገድ የበኩሉን አሻራ እያስቀመጠ ያለ ሃገር በቀል ድርጅት ነዉ፡፡
ይህን ተከትሎ በዛሬዉ እለት በልደታ ክ/ከተማ በወረዳ 04 አስተዳደር ስር ለሚገኙ ወጣቶች፣ ሴቶች እና ሌሎች በስፖርቱ ዘርፍ ተሳትፎ ላላቸዉ አካላት ለስፖርት አገልግሎት የሚዉል 15 ማሊያ በድጋፍ መልክ አበርክቷል፡፡
ድጋፉ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን ማበረታታት ጤናማ እና አምራች የሆነ ትዉልድን ለመፍጠር አይነተኛ ሚና እንዳለዉ በመገንዘብ ወጣቱ ለስፖርት ያለዉን ተነሳሽነት ለማበረታት ታስቦ የተደገረ ሲሆን የወረዳዉ ም/ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ደበላ ዳባ፣ የወጣቶችና ስፖርት ፅ/ቤት ሓላፊ አቶ ሁሴን አብደላ እንዲሁም ሌሎች የወረዳዉ ፅ/ቤት ሓላፊዎች እና ባለሙያዎች በተገኙበት ርክክቡ ተካሂዷል፡፡
የሱና ዩኒቨርስቲ ተመራቂዎች የቢላሉል ሐበሺን ማእከል ጎበኙ
=============================
የሱና ዩኒቨርስቲ አሰተምሮ ያስመረቃቸዉን እና ተመርቀዉ በስራ ላይ ያሰማራቸዉን ኢማሞች ፣ ዳእዮች፣ አስተማሪዎች፣ መሻይኸች እና የዩኒቨርስቲዉ ስታፎች በትናትናዉ እለት ሳር ቤት በሚገኘዉ የቢላሉል ሐበሺ ማእከል በመገኘት ቢላሉል ሓበሺ እየሰራቸዉ ያሉትን ስራዎች ጎብኝተዋል፡፡
በጉብኝቱ ወቅት የዩኒቨርስቲዉ መስራች እና ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶ/ር ሸይኸ መሐመድ ሓሚዲን የተገኙ ሲሆን በጉብኝታቸዉም ቢላሉል ሐበሺን ከበርካታ አመታት በፊት እንደሚያዉቁት እና ለትዉልድ የሚተላለፍ ስራን እየሰራ ያለ ፋና ወጊ ሃገር በቀል ተቋም እንደሆነ አስተያታቸዉን ሰጥተዋል፡፡
በጉብኝቱ በአጠቃላይ 45 የሚሆኑ ኢማሞች ፣ ዳእዮች፣ አስተማሪዎች እና መሻይኸች የተገኙ ሲሆን ኡስታዝ መሓመድ ጀማል ጎናፍር እነዚህን ጎብኝዎች በመቀበል የቢላልን ስራዎች በማስጎብኝት ሁሉም ጎብኝዎች በተሰማሩበት ቦታ እና ስራ ለሃገር እና ለወገን የሚጠቅም ስራ እንዲሰሩ በማሳሰብ ዝግጅቱን በዱአ አጠናቀዋል፡፡
“ሙኽሊስ የሆኑ ወንድሞች እንደዚህ አይነት ለሐገርና ለሙስሊሙ ኡማ ትልቅ ሙዚየም ሲያበረክቱ
እኔም አሻራዮን ማሳረፍ አለብኝ በማለት የአባቴ የነበረ በእጅ የተጻፈ ተንቢሁል አናም የሚባል
ቅርስ ለቢላሉል ሐበሺ ሙዚየም ላበረክት ችያለሁ” አቶ ሙሒብ አብዱልዋሴ አህመድ::
ኢትዮጵያ ለመላው አለም ሙስሊም ባለውለታ መሆንዋን በቢላሉል ሐበሺ ጉብኝት ወቅት ወደ ኡምራ የሚጓዙ ኢንዶኔዥያውያኖች ተናገሩ፡፡
==================================
ቢላሉል ሐበሺ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር ባለው ስምምነት መሰረት የተለያዩ ሐገር ዜጎች ኢትዮጵያ ትራንዚት ሲያደርጉ ቢላሉል ሐበሺ ሙዚየምን ይጎበኛሉ በዚህ ስምምነት የመጡ ወደ ኡምራ የሚጓዙ ኢንዶኔዥያውያን ወጣት ጀምአዎች የቢላሉል ሐበሺ ሙዚየምን ጎበኙ በጉብኝታቸው ወቅት ኢትዮጵያ ለመላው አለም ሙስሊም ባለውለታ መሆንዋን ተናግረዋል፡፡
ቢላሉል ሐበሺ ከየካቲት 22 - መጋቢት 1 (2016) ከHigh Profile ጋር በመተባበር ድጋፍ የሚሹ ወገኖችን ለመደገፍ በማሰብ በኢግዚብሽን ማዕከል ባዘጋጀው ባዛር የተለያዩ የስፖንሰርሺፕ ደረጃዎች ላይ ለተሳተፉ ተቋማት ምስጋና ማቅረብ ይፈልጋል።
ንብ ባንክ ለቢላሉል ሐበሺ የገንዘብ ድጋፍ አደረገ
=====================
መጋቢት 26/2016
ረመዷን 25/1445
ቢላሉል ሐበሺ
የንብ ባንክ የቦርድ አመራሮች እና የባንኩ የተለያዩ ስራ ክፍል ኃላፊዎች በቢላሉል ሐበሺ ማእከል በመዘዋወር ድርጅቱ እየሰራቸዉ ያሉትን ዘርፈ ብዙ የበጎ አድራት ስራዎች:- የማሰልጠኛ ማእከሎቹን / የሚዲያ፣ የጋርመንት፣ የኮምፒተር፣ የቆዳና ቆዳ ዉጤቶች/ እና ሙዝየሙን ጎብኝተዋል፡፡
ቢላሉል ሐበሺ እያደረጋቸዉ ያሉትን ዘርፈ ብዙ የበጎ አድራጎት ስራዎች በተለይ ደግሞ ወላጆቻቸዉን ላጡ እና ለተለያዩ አካል ጉዳተኞች ድጋፍ እንዲሆን በማሰብ የብር 550,000 /አምስት መቶ ሃምሳ ሺ / ድጋፍ አድርገዋል፡፡
የንብ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀመንበር አቶ ሺሰማ ሸዋነካ ባደረጉት ንግግር ቢላሉል ሐበሺ ከባንካችን ምስረታ ጀምሮ አብሮ በመስራት የዘወትር አጋርነቱን ከማረጋገጡም ባሻገር ላለፉት 25 ዓመታት የበርካታ ዜጎችን ችግር በማቃለል ረገድ የበኩሉን ትልቅ አስተዋፅኦ እያደረገ ያለ ተቋም በመሆኑ እነዚህን ስራዎች አጠናክሮ እንዲቀጥል በማሰብ ማህበራዊ ኃላፊነታችንን ለመወጣት እንደ ጅማሪ ይህን የገንዘብ ድጋፍ ስናደርግ በታላቅ ክብር እና ደስታ ነዉ በሚል የገለፁ ሲሆን ድጋፉ ለወደፊቱ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በመግለፅ ንግግራቸዉን አጠናቀዋል፡፡
የቢላሉል ሐበሺ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ አብዱረህማን ኻሊድ የንብ ባንክ አመራሮች ቢላሉል ሐበሺ የማህበረሰቡን ችግር ለመፍታት እያደረገ ያለዉን ዘርፈ ብዙ የበጎ አድራጎት ስራዎች እዉቅና በመስጠት የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ስራዎቻችንን አጠናክረን እንድንሰራ ስላበረታቱን እና አጋርነታቸዉን ስላሳዩን በአመራሩ እና በቢላሉል ሐበሺ ማህበረሰብ ስም እናመሰግናለን በማለት ምስጋናቸዉን አቅርበዋል፡፡
ግራንድ ዒድ ኤከሰስፖ በሚሊኒየም አዳራሽ በድምቀት እየተካሄደ ይገኛል!
=================
ያለፈው ሀሙስ (መጋቢት/19/2014) ጀምሮ በይፋ የተመረቀው ግራንድ ኢድ ኤክስፖ አነሆ የተለያዩ ምርቶችን እና ግብአቶችን በመያዝ እንዲሁም የሀገራችንን ታሪካዊ፣ በህላዊ እና ሃይማኖታዊ ቅርሶችን እና ሃሪማዎችን በማካተት ዝግጅቱን ባማረ እና በደመቀ ሁኔታ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
**
ድርጅታችን ቢላሉል ሐበሺ የተለያዩ ቅርሶችን እና አየሰራቸው ያሉትን ዘርፈ ብዙ የበጎ አድራጎት ስራዎች በመያዝ ለማህበረሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በማሰብ በዝግጅቱ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።
ይምጡ ይሳተፉ ይሸምቱ እንዲሁም እየተዝናናኑ ሙዝየሞቻችንን በመጎብኘት ታሪክዎትን ይወቁ!
ቢላሉል ሐበሺ የልማትና መረዳጃ እድር
ቢላሉል ሐበሺ የኢፍጣር እና ገቢ ማሰባሰብ ፕሮግራም አካሄደ ።
=========
14/7/2016
ቢላሉል ሐበሺ የልማትና መረዳጃ እድር የረመዷን ወር ታሳቢ በማድረግ በዛሬው እለት ከቢላሉል ሐበሺ አጋሮች እና ቤተሰቦች ጋር ባለፈው አመታት የተሰሩትን ስራዎች እና በቀጣይ ለመስራት የታቀዱትን ፕሮጀክቶች በማቅረብ ውይይት አድርጓል።
በውይይቱ ቢላሉል ሐበሺ በጣም በርካታ እና ትላልቅ ፕሮጀክቶችን አቅዶ ለተግባራዊነቱ እየተንቀሳቀሰበት ያለው መንገድ ሊበረታታ እና ሊደገፍ የሚገባው መሆኑ የጋራ መረዳዳት ላይ ተደርሷል ።
በመሆኑም አነዚህን ስራዎች እና እቅዶች ለማስፈፀም ይረዳው ዘንድ በፕሮግራሙ ከታደሙት ውስን አጋሮች የሚያበረታታ ድጋፍ ተደርጎለታል።
ቢላሉል ሐበሺ በዚህ ፕሮግራም ላይ በአካል በመገኘት እና በስልክ በመሳተፍ አሻራቸውን በማስቀመጥ አጋርነታቸውን ላረጋገጡ ተሳታፊዎች በቢላሉል ሐበሺ አመራሮች እና ቤተሰቦች ስም ምስጋና እያቀረብን ኸይር ስራችሁን አላህ ይቀበላችሁ ዘንድ የዘወትር ዱአችን ነው።
በልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 04 ለሚገኙ አቅመ ደካሞች ቢላሉል ሐበሺ የምግብ ድጋፍ አደረገ::
አነዚህን እና መሰል ስራዎችን ለማበረታታት ቋሚ የሰደቃ አባል በመሆን እና 6833 ላይ Ok ብለው በመላክ አጋርነትዎን ያሳዩ።
በሚከተሉት አማራጮች ሊያገኙን ይችላሉ
+251 91 113 2900 / 0987151515
https://bilalulhabeshi.com
https://www.facebook.com/bilalulhabeshiethio
https://t.me/bilalulhabeshi
https://twitter.com/bilalul_habeshi
“ኑ ወደ ደግነት!”- &Support
በኢማን የኢትዩጵያ መስማት የተሳናቸው ልማት ድርጅት ለሚገኙ መስማት ለተሳናቸው ቢላሉል ሐበሺ የረመዷን አስቤዛ ለድጋፍ አደረገ።
አነዚህን እና መሰል ስራዎችን ለማበረታታት ቋሚ የሰደቃ አባል በመሆን እና 6833 ላይ Ok ብለው በመላክ አጋርነትዎን ያሳዩ።
በሚከተሉት አማራጮች ሊያገኙን ይችላሉ
+251 91 113 2900 / 0987151515
https://bilalulhabeshi.com
https://www.facebook.com/bilalulhabeshiethio
https://t.me/bilalulhabeshi
https://twitter.com/bilalul_habeshi
“ኑ ወደ ደግነት!”- &Support
ቢላሉል ሐበሺ የረመዷን አስቤዛ ድጋፍ አደረገ !
========
መጋቢት 8/2016
ቢላሉል ሐበሺ የልማት እና መረዳጃ እድር የ 1445 ኛውን የረመዷን ወርን ምክንያት በማድረግ ከአባላቶቹ፣ ከተቋማት እና ከተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ያሰባሰበውን የረመዷን አስቤዛ 2000 ለሚሆኑ አረጋውያን፣ አካል ጉዳተኞች፣ ወላጆቻቸውን ላጡ፣ ለአቅመ ደካሞች እና ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች አከፋፍሏል።
**
የረመዷኑ አስቤዛ ዱቄት፣ ሩዝ፣ አጃ እና ዘይት ያካተተ ሲሆን ከ ስለኔ በጎ አድራጎት ድርጅት ድጋፍ የተደረገለትን ጨምሮ ከ 4 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ተደርጓል።
ድጋፍ የተደረገላቸው ወገኖችም የተደረገላቸው ድጋፍ መሰረታዊ ፍላጎታቸውን የሚያሟላ እና ወቅቱን ጠብቆ የተደረገ ድጋፍ መሆኑን በመግለፅ ቢላሉል ሐበሺን እና ሌሎች ድጋፍ ያደረጉ አካላትን በማመስገን ዱዓ አድርገዋል።
****
አነዚህን እና መሰል ስራዎችን ለማበረታታት ቋሚ የሰደቃ አባል በመሆን እና 6833 ላይ Ok ብለው በመላክ አጋርነትዎን ያሳዩ።
2ተኛው ዙር የረመዷን ባዛር ዛሬ በይፋ ተጠናቀቀ!
በቢላሉል ሐበሺ እና በሃይ ፕሮፋይል ትብብር ከየካቲት 22-መጋቢት 01/2016 በኢግዚብሽን ማዕከል ሲካሄድ የነበረው የረመዷን ባዛር የተለያዩ የክብር እንግዶች በተገኙበት ዛሬ በይፋ ተጠናቋል።
በመዝጊያ መርኀ ግብሩ የቢላሉል ሐበሺ የቦርድ አመራር አቶ ጀማል አሊ የቢላሉል ሐበሺን አላማ ደግፈው በዚህ ባዛር ላይ በመሳተፍ እና በመጎብኘት የቢላል አጋር መሆናቸውን ላረጋገጡልን አካላት በቢላሉል ሐበሺ ማህበረሰብ ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።
በመዝጊያው መርሀግብሩ በስፖንሰርነት እና በቬንደርነት በመሳተፍ አጋር ለሆኑ ስፖንሰሮች፣ ተቋማት እና ግለሰቦች በክሪስታል የተሰራ የምስጋና ሰርተፊኬት ተበርክቷል።
በመጨረሻም ህዝበ ሙስሊሙ ረመዷኑ የሰላም፣ የጤና፣ የመተሳሰብ እና የመረዳዳት እንዲሆንል በመመኘት ዝግጅቱ በይፋ ተዘግቷል።
ቢስሚላሂ ረህማን ረሂም
ረመዷን ሙባረክ (1445 ዓ.ሂ)
===============
አ.ወ.ወ
ቢላሉል ሐበሺ ዘርፈ ብዙ የበጎ አድራጎት ስራዎችን በመስራት ፋና ወጊ የሆነ አገር በቀል ድርጅት ነው።
እስከ አሁን ድረስ ባዘጋጀናቸው የተለያዩ ኢቭንቶች ማለትም በቢላል የክብር እውቅና፣ በሰልጣኞች ምረቃ፣ በባዛር ዝግጅቶቻችን እና በተለያዩ የድጋፍ አይነቶች ላይ በመሳተፍ አጋርነታቸሁን ላሳያችሁን ሁሉ በቢላሉል ሐበሺ አመራሮች እና በቢላሉል ሐበሺ ማህበረሰብ ስም ምስጋናችንን እናቀርባለን።
ረመዷኑ የሰላም፣ የጤና፣ የመተሳሰብ፣ የመደጋገፍ፣ የኢባዳ እና የመተዛዘን እንዲሆንልን በመመኘት እንኳን ለረመዷን ወር በሰላም አደረሳችሁ ስንል ለሁሉም ህዝበ ሙስሊም መልእክታችንን ለማስተላለፍ እንወዳለን።
በመጨረሻም የታላቁን ረመዷን ወር መሳኪኖችን በማስታወስ እና በመካደም ታሳልፉት ዘንድ አደራ እንላለን። ወ.ወ.ወ
ኡስታዝ መሐመድጀማል አብዱልመሊክ ጎናፍር ( የቢላሉል ሐበሺ የበላይ ጠበቂ)
የፓኪስታን የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የቢላሉል ሐበሺ ማዕከልን ጎበኙ
መጋቢት 01/2016
ሻዕባን 29/1445 ዓ.ሂ
H.E Shehryar Akbar Khan
Ministry of Foreign Affairs of Pakistan
Additional Foreign Secretary for Africa
በዛሬው ዕለት በቢላሉል ሐበሺ ማዕከል ከባለቤታቸው ከ Mrs Sonia Shehryar ጋር በመሆን የቢላሉል ሐበሺ ሙዝየም እና ማእከል ጎብኝተዋል ፡፡
በጉብኝታቸው ወቅት የቢላል የበላይ ጠባቂ ዑስታዝ መሀመድ ጀማል እና የቦርድ አመራሮች የተገኙ ሲሆን ከ ባለቤታቸው ጋር በመሆን የቢላሉል ሐበሺ ሙዝየምን የተለያዩ ጥንታዊ ቅርሶቸን በመጎብኘታቸው መደሰታቸውን በመግለጽ ሙዚየሙን ላቋቋሙት ሰዎች ያላቸውን ክብርና ምስጋና አቅርበዋል ፡፡
ደምቆ ውሏል ረመዷን ባዛር የመዝጊያው ቀን በከፊል ኑ ከወዳጅ ዘመድዎ ጋር ይሸምቱ ይዝናኑ በቅናሽ ዋጋ ቴምር ዱቄት እና የተለያዩ ምርቶችን ያገኛሉ!
1 ቀን ቀረው ረመዷን ባዛር ክንውኑን በከፊል ኑ ከወዳጅ ዘመድዎ ጋር ይሸምቱ ይዝናኑ በቅናሽ ዋጋ ቴምር ዱቄት እና የተለያዩ ምርቶችን ያገኛሉ!
ረመዷን ባዛር ክንውን በከፊሉ ሊጠናቀቅ 3 ቀን ቀረው ኑ ከወዳጅ ዘመድዎ ጋር ይሸምቱ ይዝናኑ በቅናሽ ዋጋ ቴምር ዱቄት እና የተለያዩ ምርቶችን ያገኛሉ
የደም ልገሳ በረመዷን ባዛር ተካሄደ እሁድ መጋቢት 1 ይቀጥላል "በደም እጦት ምክንያት አንድም ሰው መሞት የለበትም"
"በደም እጦት ምክንያት አንድም ሰው መሞት የለበትም"
የልጆች መዝናኛ በረመዷን ባዛር
ረመዷን ባዛር እነሆ ከተጀመረ 2ኛ ቀኑን ይዟል
ነገ እሁድ ደግሞ ለልጆች የተሟላ መጫወቻ የተዘጋጀ ሲሆን
ወላጆች ከልጆቻቸዉ ጋር እየተዝናኑ የሃገራቸዉን ባህላዊ ታሪካዊ እና ሃይማኖታዊ ቅርሶችን የሚጎበኙበት ልዩ ዝግጅት አዘጋጅተናል፡
ቢላሉል ሐበሺ ከሃይ ፕሮፋይል ጋር በመተባበር ከየካቲት 22- መጋቢት 1/2016 ያዘጋጀዉ ባዛር በኤግዝቢሽን ማእከል እየተካሄደ ይገኛል፡፡
ቢላል ሐበሺ ከሃይ ፕሮፋይል ጋር በመተባበር ያዘጋጀዉ ሁለተኛዉ ዙር ረመዳን ባዛር በይፋ ተከፈተ
የካቲት 22/2016
ሻዕባን 20/1445
ቢላሉል ሐበሺ የልማትና መረዳጃ እድር ከሃይ ፕሮፋይል ጋር በመተባበር ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀዉን ባዛር ዶ/ር ሂሩት ካሳው የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ በአዲስ አበባ ኤግዝብሽን ማዕከል በመገኘት በይፋ ከፍተውታል።
በመክፈቻዉ መርኃ ግብሩ የተለያዩ የባንክ የስራ ኃላፊዎች፣ የቢላሉል ሐበሺ የቦርድ አመራሮች፣ የተለያዩ ድርጅቶች፣ ጥሪ የተደረገላቸዉ የክብር እንግዶች እና የባዛሩ ተሳተፊዎች ተገኝተዋል።
የቢላሉል ሐበሺ የቦርድ አባል አቶ ሙስጠፋ መሐመድ ቢላሉል ሓበሺ እየሰራቸዉ ያሉትን ዘርፈ ብዙ የበጎ አድራጎት ስራዎች ከዘረዘሩ በኋላ በዚህ ባዛር ላይ መሳተፍ ከግብይትም በላይ ቢላል የሚሰራቸውን በጎ ስራዎች መደገፍ መሆኑን ገልጸዋል።የባዛሩ ጎብኝዎች ባህላዊ፣ ታሪካዊ እና ሃይማኖታዊ ቅርሶችን በመጎብኘት የሃገራቸዉን እና የማህበረሱን ሁለንተናዊ መስተጋብር በመረዳት አዉቀታቸዉን የሚያዳብሩበት እድል እንዳለም ገልጸዋል።
አቶ ሙስጠፋ አክለውም በባዛሩ ላይ በመሳተፍ የቢላሉል ሓበሺ አጋር ለሆኑ ግለሰቦች እና ተቋማት ምስጋና በማቅረብ ሁሉም ማህበረሰብ በዚህ ባዛር ላይ በመሳተፍ የቢላሉል ሀበሺ አጋር እንዲሆኑ በድጋሚ ጥሪያአቸዉን አስተላልፈዋል፡፡
ይምጡ ፣ ይነግዱ ፣ ይሸምቱ ፣ ይዝናኑ እንዲሁም ቅርሶችን በመጎብኘት እውቀትን ይገብዩ በሚል መርህ ከየካቲት 22 እስከ መጋቢት 01 እንደሚቆይ ታውቋል።፡
Click here to claim your Sponsored Listing.
Videos (show all)
Category
Contact the organization
Website
Address
Addis Ababa
Opening Hours
Monday | 08:30 - 17:00 |
Tuesday | 08:30 - 17:00 |
Wednesday | 08:30 - 17:00 |
Thursday | 08:30 - 17:00 |
Friday | 08:30 - 17:00 |
2Q3W+XV2 Imagine1day, Gabon Street
Addis Ababa, 1000
Educating people to transform themselves, their communities, and the world.
Meskel Square , Lion Building , 9th Floor
Addis Ababa, 1502A.A
OWDA is a charity organization that Promotes conditions of sustainable human development through implementing programs on basic service delivery, economic opportunities, livelihood...
Addis Ababa. Ethiopia
Addis Ababa
WCEO is Charity Society Organization (CSOs) founded to engage in empowering the community particularly women and children through designing different interventions that create econ...
Addis Ababa, ###X
This page is where Jaldu Woreda people will share their ideas, views and discuss on what ever agendas raised
Addis Ababa
To coordinate humanitarian assistance to save lives, restore dignity through psycho-socio rehabilita
SCORE A. A Office
Addis Ababa
We are part of 3000 Spiritans working in over 57 countries. We have been Serving in Ethiopia since 1972. We minister in areas for which the Church has difficulty in finding workers...