Wolaita Zone Plan& Development Dept/ የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ

Wolaita zone plan department is a Newly organized Governmental structure in May 2020 as one of the

Photos from Wolaita S**o City Chief Administration's post 11/12/2023
06/12/2023

በጥራት አቅደን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብና ሁለንተናዊ አገራዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ
እንተጋለን !!

Photos from የወላይታ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት- Wolaita Prosperity Party office's post 06/12/2023
Photos from Wolaita Zone Plan& Development Dept/ የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ's post 06/12/2023

በወላይታ ዞን በሶዶ ከተማ አስተዳደር የፕላንና ልማት ጽ/ቤት ለሴክተር መ/ቤት ኃላፊዎች እና ለልማት ዕቅድ ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጠ።

ኅዳር 26/2016 ዓ.ም
ወላይታ ሶዶ

በጽ/ቤቱ በተደረገው የግንዛቤ ማስጨበጫና የሥልጠና መድረክ ከዞን ፕላንና ልማት መምሪያ የተጋበዙ የልማት ዕቅድ ዝ/ክ/ግ እና የስታትስቲክስ እና ዳታ ዳይ/ት ከፍተኛ ባለሙያዎች በተለያዩ ወቅታዊ የዕቅድ ዝግጅትና ሪፖርት አቀራረብ ስርዓት እንዲሁም በመረጃ ጥራትና ክፍተቶች ላይ የተዘጋጀ ሰነድ አቅርበዋል ።

በዚሁም መሰረት በቀረበው ሰነድ ዙርያ የከተማ አስተዳደሩ ም/ካንቲባ አቶ ስሳይ ሞገስ ችግር ፈቺ ዕቅዶችን ለይተን በማቀድ ከየትኛውም ጊዜ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባ አስረድተዋል ።

በመቀጠልም የፕላንና ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ሕይወት ዮሐንስ በበኩላቸው ዕቅድ የተግባር ሁሉ ምሶሶ መሆኑን በመጥቀስ አሁን ካለንበት ነባራዊ ሁኔታዎች አንጻር ለሌሎች ተሞክሮ ልሆን የሚችል የዕቅድና ሪፖርት ስርዓት በመዘርጋት ተግባራችንን ከወትሮው በተለየ አግባብ ለማከናወን ያሉብን ችግሮች ገባ ብለን በማየት በጋራ ለመስራት ቁርጠኛ አቋም መያዝ እንደሚገባ ገልፀዋል ።

በመድረኩ የተሳተፉ አካላት ላነሱት በርካታ ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠት የጋራ አቋም ተይዞ ማጠናቀቅ ተችሏል ።

Photos from FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)'s post 30/11/2023
Photos from Wolaita Zone Plan& Development Dept/ የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ's post 29/11/2023

የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ በ18ኛዉ የኢትዮጵያ ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በተዘጋጀው ሰነድ ዙሪያ ውይይት አካሄደ ።

ወ/ሶዶ:- ህዳር 19/2016

የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ "ሕብረ ብሄራዊ ፌደራል ስርዓት እና የሰላም ግንባታ" በሚል ሰነድ ዙሪያ የ18ኛዉ የኢትዩጵያ ብሄር፤ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን አስመልክቶ ተወያይቷል።

በውይይት መድረኩ ላይ ከብዝሃ ማንነት ለሚመነጩ ፍላጎቶችና ጥያቄዎች ህጋዊ፣ ፖለቲካዊ እና አስተዳደራዊ ምላሽ የመስጠት አስፈላጊነት፤ፌደራሊዝም የአብሮነት ፍልስፍና መሆኑን በመምሪያው ኃላፊ አቶ ኃይሌ ስላስ የመወያያ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል ።

በውይይት መድረኩ የፌደራሊዝም ብዝሃነትን የሚያስተናግድ መሆኑ በተለይም ህብረ-ብሄራዊ ፌደራል ስርዓት እንደ ሃገራችን ባሉ ብዝሃነት መገለጫቸዉ በሆኑ ሃገራት በጣም ተመራጭና ለመተግበርም ምቹ መሆኑና ሌሎችም ተያያዥ ጉዳዮች በሰራተኞች በኩል ተነስቶ ግንዛቤ ለማደበር ተችሏል ፡፡

በውይይት ሠነዱ በሀገራችን ለህብረ-በሄራዊ ፌደራል ስርዓት እና ለሰላም ግንባታ ያሉ ምቹ ሁኔታዎች በዝርዝር ቀርበው የሕብረ-በሄራዊ ፌደራላዊ ሰርዓታችን በትክክለኛ እና በተሟላ ሁኔታ ለመተግበር ያሉብን ዉስንነቶች በዝርዝር በመወያየት ከመድረኩ ምላሽ የተሰጠ ሲሆን በውይይቱ ሂደት ከሰራተኛኞች እንደ ጥያቄ የተነሱ ከፍ ያለ ምላሽ የሚፈልጉ ጉዳዮች ለቀጣይ መድረክ እንደሚቀርቡ በመግባባት የዕለቱ አጀንዳ ተጠናቋል ።

31/10/2023

የስብሰባ ጥሪ!!

ነገ ረቡዕ ጥቅምት 21/02/2016 ዓ.ም የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ በ2016ዓ.ም 1ኛ ሩብ ዓመት ተግባር አፈፃፀም እና በ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ ዙሪያ የሚመክር መድረክ ስለሚኖር፦
1. የወረዳ/ከተማ አስተዳደር ፕላንና ልማት ጽ/ቤት ኃላፊዎች የ1ኛ ሩብ ዓመት ተግባር አፈፃፀም ፣ የ2016 ዓ.ም የተከለሰ ዕቅድ እና መገጣጠሚያ ደብዳቤ በመያዝ ከጧቱ ልክ 2:30 በዞን አስተዳደር አዳራሽ እንድትገኙ እናሳስባለን።

ወላይታ ዞን ብልጽግና ፓ/ጽ/ቤት
የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ
ጥቅምት 19/2016ዓ.ም
ወላይታ ሶዶ

Photos from Wolaita Zone Plan& Development Dept/ የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ's post 20/10/2023

ወላይታ ሶዶ ጥቅምት 9 /2016 ዓ.ም
በዛሬው ዕለት የፕላንና ልማት መምሪያ የፓርቲ አባላት የህዋስ ውይይት አድርገዋል።
በመምሪያው በተደረገው የህዋስ ውይይት መድረክ ቀደምሲል በዞኑ አመራር ደረጃ ዉይይት የተደረገባቸው ሁለት አጀንዳዎች ማለትም የቡና ግብይት ምርትና ምርታማነት እና የበጋ መስኖ ልማት ተግባር በተመለከተ ለህዋሷ አባለት ሰፊ ዉይይት አድርገዋል፤
የወይይቱ ተሳታፊ አባላት በሲዳማ “ሲ” ተጃምሎ ለዉጪ ገበያ ይላክ የነበረዉ ቡናችን በታላቁ የወላይታ ህዝብ ስያሜ “የወላይታ ቡና” የሚል የራሱ ብራንድ አግኝቶ የዓለም አቀፉን ገበያ መቀላቀል መቻሉ በፈጠረዉ ከፍተኛ መነቃቃት መነሻ በማድረግ የተገኘዉን ድል በዘላቂነት ለመስቀጠል የበኩላቸውን ድርሻ መወጣት እንዳለባቸው ከመድረኩ የተገለጸ ሲሆን በአንጻሩ አሁን ካለው የድጋፍና ክትትል መቀዛቀዝ በመንቃት ሁሉም ባለድርሻ አካላት በበጋ መስኖ ልማት ተግባራት ላይ የራሱን አሻራ በማሳረፍ የሀገራችን ብልጽግና የሚረጋገጥበት አግባብ ለመፍጠር እንደሚረባረብ ቃል በመግባት በሁለቱም አጀንዳዎች ላይ በሰፊው በመወየየት ሃሳብ አስተያየት ታክሎበት የጋራ አቋም ተይዞ የዕለቱን አጀንዳ ለማጠናቀቅ ተችሏል ::

Photos from Wolaita Zone Plan& Development Dept/ የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ's post 13/10/2023

የወላይታ ዞን ፕላን መምሪያ ከሴክተር መ/ቤቶች፤ ከበጎ አድራጎ ማህበራትና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት የሥነ- ሕዝብ ቴክኒክ ኮሚቴ አባላትጋር ውይይት አደረገ፡፡

ቀን 02/02/2016 ዓ.ም
ወላይታ ሶዶ፤

በወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ የሥነ ሕዝብ ዳይሬክቶረት ቡድን መሪ አቶ ግርማ በርገነ እና የመምሪያ ኃላፊ ተወካይ አቶ ሚልክያስ ፋሪሶ ከዞኑ የሥነ ሕዝብ ቴክኒክ ኮሚቴ አባላት/ከጤና: ከግብርና :ከትምህርት : ከሠራተኛና ማህበራዊ: ከውሃ: ከአከባቢ ጥበቃ :ከሥራ ዕድል ፈጠራና እንተርፕራይዝ ልማት :ከሴቶችና ሕፃናት :መምሪያዎች ከወልማ ከጠረጴዛ ልማት ማህበር እና ከዞን ሐይማኖት ተቋማት ጉባዔ/ ከመጡ የሥነ ሕዝብ ባለሙያዎች ጋር በመሆን በአሥር ዓመት የሥነ ሕዝብ ፕሮግራም ዕቅድ መነሻ የ2016 ዓ/ም ዕቅድ ስትራቴጂክ ግቦች ማለትም #1 የሕዝብ ዕድገት ምጣኔውን ከኢኮኖሚ ጋር ማጣጣም
#2 የተፈጥሮ አከባቢ ጥበቃ መጠበቅና ማልማት
#3 ምርትና ምርታማነት በማሳደግ የምግብ ዋስትና በቤተሰብ ደረጃ ማረጋገጥ
#4 አጠቃላይ የኅብረተሰብ ጤና አጠባበቅ ማሳደግ
#5 ሴቶች ወጣቶች ልዩ ድጋፍ የሚሹ የማህብረሰብ ክፍሎች በኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉደይ ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማስቻል በተቀመጡ ግቦችና በዞኑ አስር ዓመት የሥነ ሕዝብ ዕቅድ መነሻ መታቀዳቸውን በጋራ በመገምገም የተለዩ ችግሮችን ለይቶ በቀጣይ የሩብ ዓመት ዕቅድ አካል እንዲያደርጉ እና በጥንካሬ የተገመገሙትን አጠናክሮ በሁለተኛ ሩብ ዓመት ማጠቃለያ ላይ የተሻለ ሥራ ሠርተው እንዲገኙና የሥነ ሕዝብና ልማት ሥራ ሁላችንም ባለቤት ሆነን በመንቀሳቀስ በሁሉም ዘርፍ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የበኩላችንን ኃላፊነት ለመወጣት በመግባባት የዕለቱ መድረክ ተጠናቋል።

Photos from Wolaita Zone Plan& Development Dept/ የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ's post 10/10/2023

ሁሉም ኢትዮጵያውያን ሀገራችሁ ያላትን ሃብት ማየት፣ ማውጣት፣ ማስተዋወቅ እና ማገልገል ይጠበቅባችኋል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ሃሳብ፥ ብዙ ታሪክ፣ ቅርስ፣ ባህል፣ የተፈጥሮ ስጦታዎች፣ አዕዋፍ፣ የዱር አራዊት እና ሊጎበኙ የሚችሉ ድንቅ ሁነቶች እንዳሉን ግምት ውስጥ በማስገባት ከኢኮኖሚው ዘርፍ ዋና ምሦሦዎች አንዱ የቱሪዝም ዘርፉ ነው ብለዋል።
ዛሬ የተከፈተው ሀገር አቀፍ የቱሪዝምና ሆስፒታሊቲ አውደ ርዕይ ጎብኚዎች ኢትዮጵያን ምቹ መዳረሻ የሚያደርጋትን በናሙና እንዲያዩ ዕድል እንደሚሰጥም ነው የገለጹት።
ያለንን ዐቅም ለማውጣት፣ ኢትዮጵያን የብዙ ውበቶችና ግኝቶች መዳረሻ አድርጎ ለማስተዋወቅና ለማገልገል ሁሉም ኢትዮጵያውያን ሀገራችሁ ያላትን ሀብት ማየት፣ ማውጣት፣ ማስተዋወቅና ማገልገል ይጠበቅባችኋል ሲሉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

Photos from Wolaita Zone Plan& Development Dept/ የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ's post 10/10/2023

በወላይታ ዞን በብላቴ ማስልጠኛ ተቋም እየተገነባ ያለው የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ በተቀመጠው ጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ እየተሰራ እንደሚገኝ ተገለጸ
ወላይታ ሶዶ፤ መስከረም 29/2016 የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ሂደት ያለበት ደረጃ ጎብኝተዋል።
ግንባታው በተለያዩ ምክንያት እየተጎተተ ቢሆነም አሁን በተቀመጠው ጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል።
የአውሮፕላን ማረፊያው በ2 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር የሚገነባ ሲሆን በአጠቃላይ የ75 ኪሎ ሜትር የውስጥ ለውስጥ አስፓልት መንገድን ያካተተ መሆኑን ተገልጿል።
ከብላቴ ማስልጠኛ እስከ ዲምቱ ከተማ ድረስ እየተሰራ ያለው 25 ኪ.ሜ ኮንክሪት አስፓልት መንገድ በዚህ ዓመት ሙሉ በሙሉ ይጠነቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ግንባታው ቶሎ በማጠናቀቅ ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጥ የዞኑ መንግስት ከራሱ የምጠብቀውን ድጋፍ እንደሚያደርግ የወላይታ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አሳምነው አይዛ ገልጸዋል።
ይህ ልማት ለአካባቢው ህብረተሰብ ብሎም ለወላይታ ዞን እጅግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደለውም አቶ አሳምነው ጠቅሰዋል።
መሠረት ድንጋዩን የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር ዶክተር አብርሃም በላይ፣ የኢፌድሪ ጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ቩም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላና የቀድሞ ደቡብ ክልል ርእስ መስተዳር ርስቱ ይርዳው በጋራ ማስቀመጣቸው ይታወሳል።

Photos from Wolaita Zone Plan& Development Dept/ የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ's post 06/10/2023

በወላይታ ዞን ጉኑኖ ሐሙስ ከተማ አስተዳደር እየተሰራ ያለው የውስጥ ለውስጥ አስፋልት መንገድ ግንባታ አሁናዊ ገጽታ በፎቶ፤

Photos from Wolaita Zone Plan& Development Dept/ የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ's post 06/10/2023
Photos from Wolaita Zone Plan& Development Dept/ የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ's post 06/10/2023

የተገልጋይ እርካታ ለማምጣት፣ ተገልጋይ ተኮር አገልግሎት ለመሰጠትና ቅንጅታዊ አሰራርን ለማሳለጥ በሁሉም ዘርፍ የተሰማሩ ባለድርሻ አካላት እንደሚተጉ ተናገሩ

በወላይታ ዞን ማዕከል ያሉ ሴክተር መሥሪያ ቤቶች የመንግስታዊ ሥራና የፓርቲ ተግባር የ2016 ሩብ ዓመት የእስካሁን ሥራ አፈጻጸምና ከመስከረም 15 እስከ ታህሣሥ 25/2016 ዓ.ም የመቶ ቀናት ዕቅድ ዙሪያ የውይይት መድረክ አካሄዱ።

ወላይታ ሶዶ ፦ መስከረም 25/2016ዓ/ም (ወ/ዞ/መ/ኮ/ጉ/መምሪያ)

ተቋማቱ በየደረጃው ባሉ የሴክተር ሥራዎችን በመንግሥት ፖሊሲና ስትራቴጂ ላይ ተመሥርተው በተቀናጀና ሁሉ አቀፍ በሆነ ዕቅድ በመዘርጋት የመቶ ቀናት ዕቅድ በማዘጋጀት የበጀት ዓመቱ ዕቅድ ውጤታማ ለማድረግ እንደሚሰራ ተጠቁሟል

በበጀት ዓመት የታቀደው ዕቅድ ሳይዛነፍ ለመፈጸም በሁሉም ዘርፍ የተመደበው አካላት ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት መንቀሳቀስ እንዳለበት ተጠይቋል ።

ፖለቲካዊ፣ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ትኩረት በማድረግ የታቀደው ዕቅድ ለማሳካት ትኩረት ማድረግ እንደሚገባ ተብራርቷል ።

ተገልጋይ እርካታ ለማምጣት ተገልጋይ ተኮር አገልግሎት ለመሰጠትና ቅንጅታዊ አሰራርን ለማሳለጥ በሁሉም ዘርፍ የተሰማሩ ባለድርሻ አካላት እንደሚተጉ አስተያየት ሰጪዎች ጠቁሙዋል።

በቀጣይ መቶ ቀናት በሚሰሩና ሊሰሩ የታቀዱ ጉዳዮች፣ አፈጻጸም ከፍ ለማድረግ በሩብ ዓመቱ የተከናወኑ ጠንካራና ደካማ ጎኖች በመለየት የተሻለ ሥራ ለመሥራት ባለድርሻ አካላት መግባባት ላይ ተደርሷል ።

በሥራ ሂደት ላይ የሚገጥመው ችግሮችን በወቅቱ በመቅረፍ፣ የተቀላጠፍ ተግባር ለመፈጸም ባለድርሻ አካላት ንቃት ሕሊና ዝግጅት እንደሚጠይቅ ተጠቁሟል ።

በሁሉም ሴክተር መስሪያ ቤቶች ያሉ ህዋሳት የተግባር አፈጻጸም ግምገማ እና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ የውይይት ተገምግመዋል ።

በመድረኩም የየሴክተር መስሪያ ቤቶች የተግባር አፈፃፀም እየተገመገመ ሲሆን ተቋማዊ አሰራርን የበለጠ በማጠናከር የተጣለበትን ኃላፊነት በብቃት መወጣትና ተግባራትን በዕቅድ መፈጸም እንደሚገባ ተጠቁሟል።

በአገልጋይነት መንፈስ የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት በመፍጠር ለህዝቡ ተገቢውን አገልግሎት መስጠት እንደሚገባም ተገልጿል።

ተግባራትን በቅንነት በመስራት የህዝባችንን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት መስራት አማራጭ የሌለው ጉዳይ በመሆኑ በተነሳሽነት ማከናወን እንደሚገባ የጋራ መግባባት ተደርሷል።

በወላይታ ዞን ማዕከል ያሉ ሴክተር መሥሪያ ቤቶች የመንግስታዊ ሥራና የፓርቲ ተግባር የ2016 ሩብ ዓመት የእስካሁን ሥራ አፈጻጸምና ከመስከረም 15 እስከ ታህሣሥ 25/2016 ዓ.ም የመቶ ቀናት ዕቅድ ዙሪያ የውይይት መድረክ ተካሂዷል ።

Photos from Wolaita Zone Plan& Development Dept/ የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ's post 06/10/2023

የፕላንና ልማት መምሪያ የፓርቲ አባላት የህዋስ ውይይት ተደረገ።
***********************
ወላይታ ሶዶ መስከረም 25/2016 ዓ.ም

በዛሬው ዕለት የፕላንና ልማት መምሪያ የፓርቲ አባላት የህዋስ ውይይት አድርገዋል።

በመምሪያው በተደረገው የህዋስ ውይይት መድረክ የ1ኛ ሩብ ዓመት የህዋሷ የዕቅድ አፈጻጸምና የ100 ቀን ዕቅድ ተገምግሟል።

የወይይቱ ተሳታፊ አባላት በፓርቲ መርህ ላይ ተመስርተው ለሁለንተናዊ ብልፅግና እንዲረባረቡ የአባላት የግንባታ መድረኮችና የህዋስ ስብሰባዎች ወሳኝ ስለመሆኑ በመጠቆም ህዋሱ ይበልጥ መጠናከር እንዳለበትና በቀጣይ የፓርቲ ውስጠ ደንብ መመሪያዎች ላይ አባላቱ ስልጠና ማግኘት እንዳለበት የመምርያው ኃላፊ አቶ ኃይሌ ስላስ አሳስበዋል ::

በተጨማሪም የህዋሷ ሰብሳቢ አቶ ኡፎ ቦንጋ ብልፅግና ፓርቲ ዓላማ እና መዳረሻን የተረዳ አባልን ማፍራት እና ህዋስን ማጠናከር ለሁለንተናዊ ብልፅግና ሚናው ከፍተኛ እንደሆነ በመግለጽ የ1ኛ ሩብ ዓመት አፈፃፀም በማስገምገም እንዲሁም የፓርቲ 100 ቀን ዕቅድ ገምግሞ በማፅደቅና ከአባላቱ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠት ለቀጣይ ተግባራት መዘጋጀት እንዳለበት ተገልጸዋል ።

መድረኩ በመንግሥታዊ ተግባራት አንፃር በተለይም የሴክተሩ የ100 ቀን ዕቅድ ገምግሞ ማፅደቅ ፥በቀጣይ የሚከናወኑ ተግባራት ዙርያ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በሰፊው ተወያይቶ ሃሳብ አስተያየት ታክሎበት የጋራ አቋም ተይዞ የዕለቱን አጀንዳ ለማጠናቀቅ ተችሏል ::

Photos from Wolaita Zone Plan& Development Dept/ የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ's post 22/09/2023

የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ የፓርቲ አባላት የህዋስ ውይይት አድርጉ።
************************🇪🇹
ወላይታ ሶዶ መስከረም 11/2016ዓ.ም
በዛሬው ዕለት የፕላንና ልማት መምሪያ የፓርቲ አባላት የህዋስ ውይይት አድርገዋል።

በመምሪያው በተደረገው የህዋስ ውይይት መድረክ ክልላችን ታሪካዊ የሆነዉን የክልል አደረጃጀት ርፌሬንዲየም ምርጫ አጠናቆ ወደ ተግባር መሻገሩ የሚታወቅ ሲሆን ሁሉም አባል እና አመራሩ ህዝቡ የሰጠዉን ኃላፊነት በየደረጃው በታማኝነት እና በቅንንነት ለማገልገል መዘጋጀት እንደሚገባ ተጠቁሟል ::

በተጨማሪም የብልፅግና ፓርቲ ዓላማ እና መዳረሻን የተረዳ አባልን መሰረታዊ ፓርቲ እና ህዋስን ማጠናከር ለሁለንተናዊ ብልፅግና ሚናው ከፍተኛ እንደሆነ ተገልጿል ::

ይህ በእንዲህ እንዳለ አባላቱ መርህ ላይ ተመስርተው ለሁለንተናዊ ብልፅግና እንዲረባረቡ የአባላት የግንባታ መድረኮችና የህዋስ ስብሰባዎች ወሳኝ ሳለመሆኑ በመጠቆም ህዋሱ ይበልጥ መጠናከር እንዳለበት የመምርያው ኃላፊ አቶ ኃይሌ ስላስ አሳስበዋል ::

መድረኩ በተለያዩ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ እና ሃሳብ አስተያየት አክለዉበት የጋራ አቋም ተይዞ እንደሚጠናቀቅ ለማዎቅ ተችሏል ::

15/09/2023
Photos from Wolaita Zone Plan& Development Dept/ የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ's post 15/09/2023

የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መመሪያ የመምሪያው ኃላፊ አቶ ኃይሌ ስላስ እና የህዋስ አመራር የሴክተሩን ህዋስ የማጠናከር ውይይት አድርገዋል ።

በተደረገው መድረክ ቀደም ሲል የነበሩ ጠንካራ ጎኖችን በማበረታታትና ውስንነቶች ላይ በመስራት በቀጣይ የሴክተሩ ህዋስ የላቄ ውጤት ማስመዝገብ እንዳለበት ሰፋ ያለ ውይይት ተደርጓል ።

Photos from Wolaita Zone Plan& Development Dept/ የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ's post 14/09/2023

👉የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ አዲስ የተሾሙ የመምሪያ ኃላፊ አቶ ኃይሌ ስላስ ከመምሪያው የማነጅመንት አባላት ጋር የትወውቅ መድረክ አድርገዋል ።

መስከረም 3/2016 ዓ.ም
ወላይታ ሶዶ፣
👉የዞኑ ፕላንና ልማት መምሪያ አዲስ የተሾሙ የመምሪያ ኃላፊ አቶ ኃይሌ ስላስ ከመምሪያው ከማነጅመንት አባላት ጋር የትውውቅ መድረክ ያካሄዱ ሲሆን በመድረኩ በየዳይረክቶሬቱ የሚከናወኑ ተግባራት ላይ ግንዛቤ በመፍጠር የማስታወቅና በቀጣይ በሴክተሩ የሚከናወኑ ተግባራት በተነቃቃ መንፈስ ለማከናወን መዘጋጀትና ለመምሪያው በአዋጅ የተሰጡ ተግባራት አከዋወን ዙርያ ውይይት በማድረግ እንዲሁም በ2016 በጀት ዓመት የሚከናወኑ ዘርፈ ብዙ ተግባራት ወቅቱን ጠብቀው በጥራት የሚከናወኑበት አቅጣጫ ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

👉በመቀጠልም እያንዳንዱን ተግባር ለቅመን በመተግበር እንደ ዕቅድ መስሪያ ቤት የዞኑን አጠቃላይ ዕቅድ ክንውን በመገምገም ፣የዞኑን ካፕታል ፕሮጀክቶች ያሉበት ሁኔታ በመከታተልና ግብረ መልስ በመስጠት የአፈፃፀም ርፖርት ወቅቱን ጠብቆ ለአስፈፃሚው አካል የማድረስ ጉዳይ ትኩረት ልያገኝ እንደሚገባ የመምሪያ ኃላፊ አቶ ኃይሌ ስላስ ገልጸው በቀጣይ በአጭር ጊዜ የሚከናወኑ ተግባራት ተለይተው እንዲቀርቡና ለዞናችን ልማትና የጋራ ስኬት መረባረብ እንደሚገባ ለመምሪያው ማኔጀመንት አባላት አሳስበዋል ።

11/09/2023

በወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ በዛሬው ዕለት የተሾሙ የመምሪያው ኃላፊ አቶ #ኃይሌ #ስላስ አዲሱ ዓመት የሠላም የደስታና የስኬት ዓመት እንዲሆንላችሁ የመልካም ምኞት መግለጫ አስተላልፈዋል።

Photos from Wolaita Zone Plan& Development Dept/ የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ's post 30/08/2023

የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ የወላይታ ዞን አትላስ ምረቃ ሥነ ሥርዓት ከዞን፥ ከወረዳና ከተማ አስተዳደር ከተውጣጡ አስፈፃሚ አካላት ጋር እያካሄደ ይገኛል።

ነሐሴ 24/2015 ወላይታ ሶዶ፣

የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ ባደረገው የሥነ ሕዝብ የ10 ዓመት ፕሮግራም ሰነድ ምክክር ጉባኤና የወላይታ ዞን የአትላስና የ10 ዓመት መሪ ዕቅድ ምረቃ ስነ ሥርዓት የዞኑ አትላስ ለረዥም ዓመታት ስለፋበት የነበረ የአትላስ ስራ ተጠናቅቆ መታተሙን በማስታወስ በሀገራችን እስካሁን በዞን ደረጃ ያልተደፈረ ተግባር መሆኑን በማስታወስ ሥራውን ለማጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት በሙሉ የመምሪያው ኃላፊ ዶ/ር ማርቆስ ጩምቡሮ ምስጋና አቅርቦዋል ።

በመቀጠልም የመምሪያው የጂአይ ኤስና ስታትስቲክስ ዳይ/ት ቡድን መሪ አቶ ማኦ ካስትሮ የአትላሱን አሰራርና ጠቀመታውንና ፋይዳውን በመተንተን አቅርበዋል ።

በተጨማሪም የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ የሥነ- ሕዝብ አሥር ዓመት የፕሮግራም ሰነድ የስነ ሕዝብ ልማት ዳይ/ት ቡድን መሪ አቶ ግርማ በርገነ ከዞን ፤ ከወረዳና ከተማ አስተዳደር ለተውጣጡ አስፈጻሚ አካላት አቅርበዋል ።
በመጨረሻም የዞኑ አትላስና የዞኑን የ10 ዓመት መሪ ዕቅድ ለሁሉም ባለድርሻ አካላት ስርጭት በማድረግና በዝግጅቱ ለተሳተፉ አካላት የዕውቅና ሰርቲፍኬት በመስጠት የፕሮግራም መርሃ ግብሩ ተጠናቅቋል ።

07/08/2023

#የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ ሰራተኞች #በደቡብ #ኢትዮጵያ አደረጃጀትጋር በተያዘው ጉዳይ ፓርትያችን #ብልፅግና በሰጠው ምላሽ ዙሪያ ውይይት ተደረገ ።

በመድረኩም በፓርቲያችን ብልፅግና በምርጫው ጊዜ ለህዝብ በገባው ቃል መሰረት የህዝብ ጥያቄ የሆነውን
6ዞኖችና 5 ልዩ ወረዳዎች በጋራ ለመደራጀት ያቃረቡትን ጥያቄ ላይ ቆሞ የተሰጠውን የአደረጃጀት ጥያቄ ምላሽ ዙሪያ ውይይት በማድረግ አብሮ ከተደራጁ ጎረበት ወገኖቻችንና ወደ አከባቢያችን አዲስ የሚመጡ እንግዶች በደስታ በመቀበል የጋራ አሴቶችን በማበልፀግና አብሮነትን ለማጠናከር የሚኖረን ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን በመረዳት የሚጠበቅብንን ኃላፍነት መወጣት እንዳለብን ከመምሪያው ኃላፊ ዶር ማርቆስ ጩምቡሮ ገለጻ ተደረጓል ።

Photos from Wolaita Zone Plan& Development Dept/ የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ's post 03/08/2023

የ2016 በጀት ዓመት 55 ቢሊየን 836 ሚሊየን 723 ሺ 309 ብር
የደቡብ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በ2016 በጀት ዓመት የክልሉ መንግስት ረቂቅ በጀት አዋጅ ላይ ተወያይቶ የውሳኔ አቀረበ

የደቡብ ክልል መስተዳድር ምክርቤት በ26/12/2016 ባካሔደው 254ኛ መደበኛ ስብሰባው በ2016 ረቂቅ በጀት ላይ ውይይት አካሔዷል።
በዚህም መሰረት የ2016 በጀት ዓመት 55 ቢሊየን 836 ሚሊየን 723 ሺ 309 ብር እንዲሆን ነው በክልሉ ምክር ቤት እንዲጸድቅ የውሳኔ ሀሳብ ቀርቧል።

በክልሉ ለ2016 ከቀረበው ረቂቅ በጀት ውስጥ ከፌደራል መንግስት ድጎማ 28 ቢሊየን 748 ሚሊየን 375ሺ 845 እንዲሁም ከክልሉ ገቢ ደግሞ 26 ቢሊየን 740 ሚሊየን 994ሺ 239 ሺ በድምሩ 55 ቢሊየን 836 ሚሊየን 723 ሺ 309 ብር መሆኑን ነው በመስተዳድር ምክር ቤቱ የተገለጸው።

በክልሉ የ2016 በጀት የ20 ነጥብ 6 በመቶ እድገት እንዳለውም ተጠቁሟል።
ምክር ቤቱ በቀረበው የክልሉ መንግስት የ2016 በጀት ረቂቅ አዋጅ ላይ በስፋት ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ክልሉ ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል።

ሐምሌ 26/2015
SNNPRs Government Communication Affairs Bureau

22/07/2023

የወላይታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ የዞኑን የ2015 በጀት ዓመት አፈጻጸም ማጠቃለያ እና የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ በማዘጋጀት በዞኑ ካብኔ ምክር ቤት በማቅረብ አስገምግሟል። ለተጨማሪ መረጃ
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=585589467080610&id=100068886862788&mibextid=Nif5oz

Want your organization to be the top-listed Government Service in Sodo?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Videos (show all)

Telephone

Address


S**o
S**o
Other Government Organizations in S**o (show all)