TOM TOM

i need love and peace

Photos from TOM TOM's post 23/09/2021

እስከ ዶክትሬትነት የዘለቀ
ጏደኝነት ከልጅነት አስከ ጅማ
ዩኒቨርስቲ የህክምና ዶክትሬት::

23/09/2021

መልካም ምሽት

02/09/2021

ማርታ ጎይቶም 😍😍
በተለይ ኪያ የተሰኘው ፊልሟ እስከዛሬ ከሰራቻቸው ፊልሞች ጋር ቢደመሩ የአንድ የሱን ያህል አያክሉም ።
ጎበዝ እና ቆንጃ አክተርስ ።

14/04/2021

‹‹ዘመነ መሳፍንት›› የተባለውን የየግዛት ባላባቶች ዘመን በማስቆም ኢትዮጵያን በአንድ ጠንካራ ማዕከላዊ መንግሥት ስር ለማስተዳደር የሞከሩት ንጉሰ ነገሥት ዳግማዊ አጤ ቴዎድሮስ ያረፉት ከዛሬ 153 ዓመታት በፊት (ሚያዝያ 6 ቀን 1860 ዓ.ም) ነበር፡፡

14/04/2021

አሜሪካ ለተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የ23 ቢሊዮን ዶላር የጦር መሳሪያዎችን ልትሸጥ መሆኗን አስታወቀች

ሽያጩ ይፋ የሆነው ፕሬዝደንት ባይደን ለዩኤኢ የጦር መሳሪያ እንይሸጥ ጥለውት የነበረውን እገዳ በማንሳታቸው ነው፡፡የጦር መሳሪያ ሽያጭ ስምምነቱ በዘመነ ትራምፕ የተደረሰ ነው፡፡

11/01/2021

የቀድሞው የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንትን ጨምሮ ሌሎች በቁጥጥር ስር የዋሉ ዋነኛ የጁንታው አመራሮች አዲስ አበባ ገቡ
የቀድሞው የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንት አባይ ወልዱና ምክትል ፕሬዚዳንትን ዶክተር አብርሃም ተከስተን ጨምሮ አገር ለመበታተን ሲሰሩ ቁጥጥር ስር የሕወሃት ጁንታው አመራሮች አዲስ አበባ ገቡ።
የአገር መከላከያ ሠራዊት፣ የፌዴራል ፖሊስና የብሔራዊ መረጃና ደህንነት ጥምር ሃይል አገር በመከላኪያ ሰራዊት ላይ ጥቃት በማድረስ አገር ለመበታተን ሲሰሩ የነበሩ የአሸባሪው ህወሃት አባላትን ለሕግ የማቅረብ ተልዕኮ እንደቀጠለ ነው።
ኢቢሲ

Photos from TOM TOM's post 10/01/2021

በማዳም ልጅ በጥይት ተመትታ የነበረችው ኢትዮጵያውያን ሰደተኛዋ እህታችን ሀብታሟ ይመር ስጦታው

512 ሺህ ብር ካሳ ተከፈላታል::

ክዌት 🇰🇼

በኩዌት የኢፌዲሪ ኤምባሲ ሀብታሟ ይመር ስጦታው የተባለች ዜጋችንን የግማሽ ሚሎዮን ብር የጉዳት ካሳ በዛሬው ዕለት (ጥር 2 ቀን 2013 ዓ.ም እንዲከፈላት አድርጓል።

ዜጋችን ጠፍታ በምትራበት ቤት እያለች መስከረም 25 ቀን 2013 ዓ.ም በአሰሪዋ ልጅ በሽጉጥ ተመትታ ጉዳት ደርሶባት ነበር።

በዚህም ምክንያት በፈርዋንያ ሆስፒታል ህክምና ስትከታተል የነበረ ሲሆን፣ ለደረሰባት ጉዳት ከሳ እንዲከፈላት ለማድረግ ኤምባሲው ከፖሊስ ጋር በመሆን ጉዳዩን በጎ ፈቃደኛ ጠበቃ አቁሞ ክትትል ሲያደርግ ቆይቷል።

በመሆኑም ጥር 2 ቀን 2013 ዓ.ም በዋለው የፍርድ ቤት ቀጠሮ በመገኘት KWD 4000.00 ( ETB 512,000.00 (አምስት መቶ አስራ ሁለት ሽህ ብር) እንዲከፈል አድርጓል።

የጉዳት ካሳ እንዲከፈላት የተደረገችው ዜጋችን ሀብታሟ ይመር ስጦታው ወደ ሀገሯ እስክትሳፈር ድረስ በመንግስት መጠለያ እንዲትሆን ተደርጓል። ኤምባሲው በሂደቱ ለተባበሩ ሁሉ ምሥጋናውን ያቀርባል።

ምንጭ :- በኩዌት የኢፌዲሪ ኤምባሲ

19/12/2020

ከቤተሰቦቻቸው ሊቀላቀሉ ነው!!
ላለፉት 30 አመታት አዲስ አበባ በሚገኘው የጣሊያን ኤምባሲ ተጠልለው በቁም እስር ላይ የቆዩት ሁለቱ ከፍተኛ የደርግ ባለስልጣናት ምህረት ተደርጎላቸው ከቤተሰቦቻቸው እንዲቀላቀሉ ተወሰነ፡፡

በኤምባሲው ተጠልለው የሚገኙት የ85 አመቱ ሌተናል ኮለኔል ብርሃኑ ባየህና የ77 አመቱ ሌተናል ጄነራል አዲስ ተድላ ከቁም እስር ወጥተው ከቤተሰቦቻቸው ጋር እንዲቀላቀሉ የሚያስችላቸውን የምህረት ውሳኔ ፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ መፈረማቸው ምንጮች ለአዲስ አድማስ አስታውቀዋል፡፡

ከ4 ዓመት በፊት ሁለቱ የቀድሞ ባለስልጣናት ከእስር እንዲለቀቁ በተለያየ አካላት ጥረት ሲደረግ የቆየ ሲሆን በሀገሪቱ ብሔራዊ መግባባትና እርቅ የሚፈጠርበትን ሁኔታ እንዲያመቻች የተቋቋመው የብሔራዊ እርቀ ሠላም ኮሚሽን፣ ከመንግስት ጋር በመነጋገር መንግስት እንዲለቀቁ ውሳኔ ማሳለፉን ምንጮች ጠቁመዋል።

ባለስልጣናቱ ከተጠለሉበት የጣሊያን ኤምባሲ የሚወጡት ሙሉ ምህረት ተደርጎላቸው ሲሆን ከሰሞኑ አስፈላጊውን ሂደት አጠናቀው ከቤተሰቦቻቸው ይቀላቀላሉ ተብሏል፡፡

ሌተናል ኮለኔል ብርሃኑ ለበርካታ ዓመታት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩ ሲሆን የ77 አመቱ የእድሜ ባለፀጋው ሌተናል ጀነራል አዲስ ተድላ በበኩላቸው የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም እንደነበሩ ይታወቃል፡፡

27/11/2020

በማይካድራ ተጨማሪ የጅምላ መቃብሮች ተገኙ።

ጥቅምት 30/2013 ዓ.ም በንጹኃን የአማራ ብሔር ተወላጆች ላይ ዘርን መሠረት ያደረገ ጥቃት በማይካድራ ከተማ መፈፀሙ ይታወቃል። ይህን አስነዋሪ ተግባር የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በቦታው በመገኘት ባደረገው ጥናት እና ይፋ ባደረገው መረጃ የሟቾች ቁጥር በትንሹ 600 እንደሆነ ገልጾ ነበር።
ግድያውም ዘርን መሠረት ያደረገና በተለይም የአማራ ተወላጆች ላይ ያነጣጠረ ጅምላ ጭፍጨፋ መሆኑን ገልጿል። ይሁን እንጂ የሟቾች ቁጥር በትንሹ 600 ነው ተብሎ የተገለጸው በማይካድራ ከተማ በየቤቱ ህይወታቸው አልፎ የተገኙ እና በቤተክርስቲያን ውስጥ የተቀበሩትን ብቻ መሠረት ያደረገ ነው።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ጥናት አድርጎ ከተመለሠ በኃላ ከማይካድራ ከተማ ወጣ ባሉ የገጠር አካባቢዎች በርካታ የጅምላ መቃብሮች መገኘታቸውን የአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት ጋዜጠኞች በቦታው በመገኘት አረጋግጠዋል።
በአንድ ቦታ 18 ሰው በጉድጓድ ውስጥ በጅምላ የተጣሉ ሲሆን በሌላ የገጠር አካባቢ ደግሞ 57 ሰዎች በጎርፍ ማፋሰሻ ቦይ ውስጥ በጅምላ ተገድለው እና ተጥለው ተገኝተዋል።
በዛሬው ዕለትም በማይካድራ ሌላ የገጠር ቀበሌ ውስጥ 17 ሰዎች በጅምላ ተገድለው በጉድጓድ ውስጥ ተጥለው ተገኝተዋል። አሁንም ሴንትራል፣ ደሮ እርባታ፣ በረኸት በሚባሉ አካባቢዎች ላይ አሠሳ እየተደረገ እንደሚገኝ እና ቁጥሩ እንደሚጨምር የማይካድራ ነዋሪዎች ገልጸውልናል።
በዚህ የዘር ማጥፋት ወንጀል ተሳታፊ ናቸው የሚባሉት ተጠርጣሪዎች በብዛት ሱዳን ሐሻባ በሚባል የስደተኞች መጠለያ ውስጥ እንደሚገኙ ይነገራል።
ከዚህ በተጨማሪ በማይካድራ የዘር ማጥፋት ወንጀል ላይ ተሳታፊ ናቸው በሚል ተጠርጥረው ከተያዙት 60 ግለሠቦች ውስጥ 17ቱ በቀጥታ የወንጀሉ ተሳታፊ መሆናቸውን የማይካድራ ከተማ ጊዜያዊ አስተዳደር ገልጾልናል።
ትህነግ በወልቃይትና አካባቢው ተወላጆች ላይ በአስር ሽህ የሚቆጠሩ ዜጎችን ገድሏል፤ ከግማሽ ሚሊየን በላይ ሰዎችን ደግሞ ከአካባቢያቸው እንዲፈናቀሉ አድርጓል፡፡

Photos from TOM TOM's post 18/11/2020

ይሄ ነገር 👂

ከሰማይ

63 ሚሊዮን 569 ሺህ 112 ብር የወረደለት በአንድ ቀን ከመቃብር ሳጥን ሰሪነት ወደ ሚሊዮነር የተቀየረው ይህ ኢንዶኔዥያ የ33 ዓመቱ ጆሽዋ

ይህ የምትመልከቱት ድንጋይ meteorite የተባለ በአሜሪካ ሳይንቲስቶች የሚፈለግ ስፔስ ውስጥ የሚገኝ ድንጋይ ሲሆን

ይህ ድንጋይ ስፔስ ውስጥ የሚገኝ ነገር ግን ይህን ለማግኘት እጅግ አዳጋጅ የሆነ ነው

የድንጋዩ እድሜው ከ4.4ቢሊዮን ዓመት በላይ ያለው ሲሆን

2.1 ኪሎ ግራም የሚመዝነው ይህ ድንጋይ በዚህ በኢንዶኔዥያው ጇሸዋ በሚባል ወጣት ከቤቱ አቅራቢያ የመቃብር ሳጥን እየስራ እያለ ነበር ከሰማይ እጅግ ከባድ ድምፅ ባለው እንዲህ እንደምታዩት ቤቱን ሰርጉዶ የገባው

ጆሽዋ ምንድን ነው ብሎ መሬት ውስጥ ገብቶ የነበረውን ድንጋይ ቆፍሮ ሲያወጣው ድንጋዩ እጅግ በጣም የሚያቃጥል የነበረ ቢሆንም እስኪበርድ ጠብቆ አውጥቶታል

ይህን የሰሙት አሜሪካን ሳይንቲስቶች ለድንጋዩ 1.4 ሚሊዮር ዩሮ

ወደ ብር ሲመነዘር 63 ሚሊዮን 569 ሺህ 112 ብር

ለጆሽዋ አቅርበውላታ ጆሽዋም ይህን ድንጋይ ሽጦ በገንዘቡም ለአባቱ ና ለእናቱ ቤት ለመስራት እንዲሁም በስፍራው ለህብረተሰቡ ቤተክርስቲያን አሰራለው ብሏል::

ኢትዮጵያውያን አንድ አባባል አለን " አትሩጥ አጋንጥ " የሚባል እንግዲህ ይሄ ነው

ቸር ዋሉ 🙏❤️

ምንጭ :- Daily mail

17/11/2020

የኢትዮጵያ ወንዶች ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን የኒጀር አቻውን አሸነፈ።

ዛሬ በአዲስ አበባ ስታድየም ያለተመልካቾች ለአፍሪካ ዋንጫ ጨዋታውን ያካሄደው የኢትዮጵያ ወንዶች ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን የኒጀር አቻውን በ3 ለ 0 አሸንፏል።

ጎሎቹንም አማኑኤል ገ/ሚካኤል ፣ መስኡድ መሀመድ እና ጌታነህ ከበደ አስቆጥረዋል።

በዚህ ውጤት ምክንያትም በስድስት ነጥብ ከምድቡ ሶስተኛ ደረጃ ላይ የሚያስቀምጣቸውን ውጤት አስመዝግበዋል።

በአቤል ጀቤሳ
ሕዳር 8 ቀን 2013 ዓ.ም

17/11/2020

ክብር

15/11/2020

ሕወሓት በአስመራ ከተማ ላይ የሚሳይል ጥቃት መፈጸሙ ተገለፀ
በአስመራ ከተማ ዛሬ ሕወሓት የሚሳይል ጥቃት መፈጸሙን የኤርትራ ፕረስ ዘገበ። የአስመራ አውሮፕላን ማረፊያ እና የሀገሪቱ ማስታወቂያ ሚኒስቴር የጥቃቱ ኢላማዎች ቢሆኑም በአውሮፕላን ማረፊያው አቅራቢያ አንድ ሚሳይል ቢያርፍም በማረፊያው ላይ ጉዳት አለማድረሱ በዘገባው ተጠቁሟል።
የሕወሓት ዓላማ ኤርትራን ወደ ጦርነቱ በማስገባትና ዓለማቀፍ ትኩረት በመሳብ ዓለማቀፉ ማህበረሰብ ጣልቃ እንዲገባ ማድረግ መሆኑን የጠቀሰው ዘገባው የሀገሪቱ መንግሥት ለኢትዮጵያ ህዝብ ክብር ስንል እንታገሳለን ማለቱን ጠቅሷል።
አሶሺየትድ ፕረስ እና ዘ ቴሌግራፍም ቢያንስ ከ2 እስከ 3 ሚሳይል ወደ አስመራ እንደተተኮሰ ዘግበዋል።
በትናንትናው እለት በጎንደር እና ባህር ዳር አውሮፕላን ማረፊያዎች ላይ የሚሳይል ጥቃት መፈጸሙን ያስታወቀው ሕወሓት በኤርትራ ዋና ከተማ አስመራ እና ሌሎች ከተሞችም መሰል ጥቃቶችን እንደሚፈጽም ዛሬ ማስታወቁ ይታወቃል።

13/11/2020

የዓለም ጤና ድርጅት “በጥቂት ወራት ውስጥ” የኮቪድ ክትባት ገበያ ላይ ይውላል አለ

የዓለም ጤና ድርጅት የኮሮና ቫይረስ ክትባት በጥቂት ወራት ውስጥ ገበያ ላይ እንደሚውል ተስፋ እንደሚያደርግ ግሎባል የጤና ድርጅት አስታውቋል፡፡ ኢሚውናአይዜሽንና ክትባት ፕሮግራም ዳይሬክተር ዶክተር ሪቻርድ ሚሂጎ እንደተናገሩት አስር የሚሆኑ እጩ የክትባት መድሃኒቶች ወደ መጨረሻ የክሊኒካል ሙከራ ገብተዋል ብለዋል፡፡
ዶክተር ሚሂጎ እንደገለጹት በጣም የሚፈለገውን መድሃኒት ማግኘት አቅርቦትና ማሰራጨትን ጨምሮ በርካታ ፈተናዎች አሉ ብለዋል፡፡
የጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ ባወጣው መረጃ መሰረት በዓለም ደረጃ እስካሁን 1.2 ሚሊዮን ሰዎች የሞቱ ሲሆን 52 ሚሊዮን ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ ተጠቅተዋል፡፡

13/11/2020

በሙስና የተማረረው ግብጻዊ ራሱ ላይ እሳት ለኮሰ።

ግብፃዊው ሰው በአገሪቱ መዲና ካይሮ በሚገኘው ታህሪር አደባባይ ላይ ነው ራሱ ላይ እሳት የለኮሰው፡፡

ግብጻዊው ሰው ሙስናን በመቃወምና በማጋለጡ ከስራ መባረሩን ፤ሀገሪቱ የዘራፊዎች ምድር መሆኗ በእጅጉ እንዳማረረውም በእሳት እየተለበለበ ተናግሯል፡፡

ሚዲል ኢስት አይ እንደዘገበው ግለሰቡ የክልል ባለስልጣናት ሲሰሩት የነበረውን ሙስናን በማጋለጡ ከባንክ ስራው እንደተባረር ተናግሯል ፡፡

ግለሰቡ በፌስቡክ የቀጥታ ስርጭት ላይ ህይወቱ መበላሸቱን እና ራሱንም ቤተሰቡንም ማስተዳደር እንዳልቻለ አምርሮ ነው የተተናገረው፡፡

ሀገሪቱ በጥቂት “የሌቦች” ቡድን እየፈረሰች ነው ብሏል ፡፡

በኃላም በስፍራው የደረሱት የደህንነት ሰዎች እሳቱን በቶሎ በማጥፋት ህይወቱን ታድገውታል፡፡

በያይኔአበባ ሻምበል
ሕዳር 4 ቀን 2013 ዓ.ም

07/11/2020

ጆ ባይደን ማናቸው?

ጆ ባይደን የቀድሞ የፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ ምክትል ፕሬዝደንት ሆነው አገልግለዋል።

የባይደን ደጋፊዎቻቸው የውጪ ጉዳይ ፖሊስ አዋቂ ናቸው ይሏቸዋል።

ጆ ባይደን የፖለቲካ ሕይወታቸው የጀመረው ከ47 ዓመታት በፊት ነበር።

ባይደን የአሜሪካ ፕሬዝደንት ለመሆን ጥረት ማድረግ የጀመሩት ደግሞ ከ33 ዓመታት በፊት እ.አ.አ. 1987 ጀምሮ ነው።

በጥቁር አሜሪካውያን ዘንድ ትልቅ ተቀባይነት አላቸው።

* የጆ ባይደን ውጭ ፖሊሲ ጉዳይ ፦

ባይደን ዶናልድ ትራምፕ ያበላሹትን የውጭ ግንኙነት አስተካክላለሁ ፤ አሜሪካ ያስቀየመቻቸውን ወዳጆቿን ልብ እጠግናለሁ ብለዋል።

ከኢራን እና ከቻይና ጋር የሚከተሉት ፖሊሲም ትራምፕ ጋር የሚቃረን ነው።

ይህ መረጃ ከBBC የተወሰደ

07/11/2020

ባይደን መንበረ ስልጣናቸውን የሚቀበሉት መቼ ነው?

በአሜሪካ ሕገ-መንግሥት መሠረት አዲሱ የፈረንጅ ዓመት በገባ በ20ኛ ቀኑ አዲሱ ተመራጭ ፕሬዝነዳንት ስልጣኑን ይረከባል።
ይህም በዋሽንግተን ዲሲ በሚካሄድ ስነ-ስርዓት ይከናወናል። ፕሬዝደንቱ እና ምክትል ፕሬዝደንቷ ቃለ መሃል ይፈጽማሉ።

የምርጫ ውጤቱን ይፋ ከተደረገ በኋላ ተመራጩ ፕሬዝደንት ስልጣን እስከሚረከቡት ጊዜ ድረስ የሽግግር ቡድን ያቋቁማሉ።

ይህም ፕሬዝደንቱ ስልጣናቸውን በይፋ ከተረከቡ በኋላ ስራቸውን በፍጥነት እንዲጀምሩ ነገሮችን ቀላል ያደርጋል።



ባይደን ምርጫውን ማሸነፋቸውን ተከትሎ በመገናኛ ብዙሃን በተደጋጋሚ ከምንሰማቸው ቃላት መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል።

'ተመራጩ ፕሬዝዳት' (President-elect): ይህ ማለት እጩዉ ፕሬዝደንታዊ ምርጫውን አሸንፈዋል። ስልጣን ግን አልተረከቡም ማለት ነው። ጄነዋሪ 20 ላይ 'በዓለ ሲመት' ተብሎ በሚጠራው ስነ-ስርዓት ላይ ቃለ መሃላ ከፈጸሙ በኋላ ፕሬዝደንት ተብለው ይጠራሉ።

ካቢኔ: ባይደን በቅርቡ የካቢኔ አባላቶቻቸውን ያሳውቃሉ። ይህም ከፍተኛ የአገሪቱ ባለስልጣናት እና ኤጀንሲ መሪዎችን ያካተተ ይሆናል።

ሴልቲክ፡ ተመራጩ ፕሬዝደንት በአሜሪካው ሴክሬት ሰርቪስ (የደህንነት ጥበቃ የሚሰጠው አካል) ጥበቃ ይደረግላቸዋል። ጥበቃ ለሚያደረገው ቡድን ደግሞ ስያሜ ይሰጣል። ስያሜውን የሚሰጠው ተመራጩ ፕሬዝደንት ነው። ባይደን ለሴክሬት ሰርቪስ ቡድኑ "ሴልቲክ" የሚል ስያሜ ሰጥተዋል። ካማላ ሃሪስ በበኩኣለቸው 'ፓዮኒር' የሚል ስያሜን መርጠዋል።

07/11/2020

የአሜሪካ ምርጫ፡ ቆጠራው በቀጠለበት ምርጫ ባይደን እንደሚያሸንፉ ተንብየዋል

የማክሰኞውን የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ተከትሎ ዶናልድ ትራምን ለማሸነፍ ከጫፍ የደረሱት ጆ ባይደን እንደሚያሸንፉ በመተማመን በድጋሚ ተናግረዋል ፡፡

የዴሞክራቲክ ፓርቲው ዕጩ ኋይት ሐውስ ለመግባት ከሚያስፈልጉት 270 የኤሌክቶራል ኮሌጅ ድምፆች 253ት ያህሉ አግኝተዋል፡፡

በተጨማሪም ባይደን ወሳኝ ግዛቶች በሆኑት በጆርጂያ፣ ኔቫዳ፣ ፔንሲልቬንያ እና አሪዞና እየመሩ ነው፡፡

የባይደን ድል ፕሬዝዳንት ትራምፕ ከአራት ዓመት በኋላ በመጪው ጥር ስልጣናቸውን እንዲለቁ ያደርጋቸዋል፡፡

07/11/2020

የአሜሪካ ሪፐብሊካኖች በትራምፕን ምርጫው ተጭበርብሯል ሀሳብ ላይ ተከፋፍለዋል

ፕሬዘዳንት ትራምፕ እየተካሄደ ባለው የአሜሪካ ምርጫ ጥያቄ እያነሱ ሲሆን የራሳቸው የሪፐብሊካን ፓርቲ አባላት ፕሬዘዳንቱ ጉዳዩን ማርገብ እንዳለባቸው ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡

ምርጫው ከተካሄደ ከሶስት ቀን በኋላ በትራምፕና በተቀናቃኛቸው ጆ ባይደን መካከል በፔንሲልቫኒያ፣ በአሪዞና፣ በጆርጂያና ኖርዝ ካሮሊና በተቀራራቢ ውጤት እየተመራሩ ይገኛሉ፡፡
የትራምፕ በመረጃ ያለተደገፈ ምርጫው ተጭበርብሯል ክስ በተመለከተ የሪፐብሊካን አባል የሆኑት ሴናተር ሮይ ብለንት ለሮይተርስ እንተናገሩት ኃይት ሀውስ እንዲህ አይነቱን ክስ በመረጃ አስደግፎ ወደ ፍርድ ቤት መውሰድ አለበት ብሏል፡፡ #አሜሪካምርጫ2020

24/10/2020

የአውሮፓ ኅብረት የዉጪ ግንኙነት ኃላፊ ጆሴፕ ቦሬል በታላቁ የኅዳሴ ግድብ ሰበብ በኢትዮጵያ፣ በሱዳን እና በግብጽ መካከል ውጥረት ሊባባስ እንደማይገባ አሳሰቡ። ኃላፊው የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ከሰጡት አወዛጋቢ አስተያየት በኋላ እንዳሉት "በታላቁ የኢትዮጵያ የኅዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት ላይ ስምምነት የሚደረሰው በኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ መካከል ነው።"
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለሶስቱ አገሮች ሥምምነት አቅርበው እንደነበር በትናንትናው ዕለት ተናግረው ነበር። "ሥምምነት አቅርቤላቸው ነበር። እንዳለመታደል ሆኖ ኢትዮጵያ ሥምምነቱን ሳትቀበል ቀርታለች። እንደዚያ ማድረግ አልነበረባቸውም። ያ ትልቅ ስህተት ነው" ብለው ነበር።
"አሁን ጊዜው የተግባር እንጂ ውጥረት የሚባባስበት አይደለም" ያሉት የአውሮፓ ኅብረት የዉጪ ግንኙነት ኃላፊ ጆሴፕ ቦሬል ግን ሶስቱ አገሮች በጀመሩት ድርድር ገፍተው ከሥምምነት የመድረስ ዕድል እንዳላቸው ዛሬ ባወጡት መግለጫ አስታውቀዋል።
"የወቅቱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀ-መንበር የሆነችው ደቡብ አፍሪካ ሁሉንም ወገኖች መፍትሔ እንዲያበጁ ለማደራደር የጀመረችው ጥረት የአውሮፓ ኅብረት ሙሉ ድጋፍ አለው" ያሉት ቦሬል ድርድሩ ቀጥሎ ስኬታማ ፍጻሜ ላይ ይደርሳል የሚል ዕምነት በአውሮፓ ኅብረት ዘንድ እንዳለ ጠቁመዋል።

20/10/2020

ሹመት !

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 8ኛ ዓመት 1ኛ መደበኛ ጉባኤው ላይ በም/ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ አቅራቢነት ልዩ ልዩ ሹመቶችን አፅድቋል።

በዚህም መሠረት ፡-

1ኛ. አቶ ጥራቱ በየነ - በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማ ስራ አስኪያጅ ቢሮ ኃላፊ
2ኛ. ዶ/ር መስከረም ፈለቀ - ቤቶች ልማት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ
3ኛ. ኢ/ር አያልነሽ ሀ/ማርያም - ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ
4ኛ. ዶ/ር መስከረም ምትኩ - የፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር
5ኛ. ዶ/ር ሚልኬሳ ጃጋማ - መሬት ልማት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ
6ኛ. ዶ/ር ሙሉቀን ሀብቱ - ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ
7ኛ. አቶ ተፈራ ሞላ - ሰራተኛና ማህበራዊ ቢሮ ኃላፊ
8ኛ. አቶ ሙሉጌታ ተፈራ - ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ በመሆን ተሹመዋል፡፡

19/10/2020

ችሎት ዜና

ለፍቅር የቀረበችው በመምሰል የሰው ህይወት ያጠፋችው ግለሰብ ከነተባባሪዋ የእድሜ ልክ እስራት ተፈርዶባታል

የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው በአዳማ ከ/መስተዳድር ደምበላ ክ/ከተማ እሬቻ ቀበሌ ልዩ ቦታው ሪፍት ቫሊ ኢንተርናሽናል ወይንም ካኔት ሆቴል ነው።

ሃምሌ 12 ቀን 2012 ዓ.ም ከቀኑ 10:30 ሲሆን አንደኛ ተከሳሽ አብዱረህማን ኡስማን እና ሁለተኛ ተከሳሽ ሀናን ጌቱ የተባሉት ናቸው ድርጊቱን በጋራ የፈፀሙት።

ሟች በለው መኮንን ከተባለው ግለሰብ ያላስፈላጊ ጥቅም ለማግኘት ሲሉ ተከሳሾቹ ተመካክረው ሁለተኛ ተከሳሽ ሻሸመኔ ከተማ ላይ እንድትተዋወቀው በማድረግ ጓደኛ ይሆናሉ። ግለሰቡ ኑሮው በአዲስ አበባ ይሁን እንጂ በሻሸመኔ ከተማ የንግድ እንቅስቃሴውን ያደረገ በኑሮው ደረጃውም ሀብታም ከሚባሉት ተርታ ነው፡፡

እናም ይህንኑ ግለሰብ ለማጥመድና ለመዝረፍ በማቀድ አንደኛው ተከሳሽ አብዱረህማን የሃናን ወንድም እንደሆነ በማስመሰል ሟች በለው ወደ አዳማ ከተማ እንዲመጣ ያደርጋሉ። እርሱም በአዳማ ከተማ እንደደረሰ ሪፍት ቫሊ ወይንም ካኔት ኢንተርናሽናል ሆቴል አልጋ ቁጥር 103 ይዞ ሃናንን ይጠራታል።

ሁለቱ ተከሳሾች ቀድሞውኑ ተነጋግረው ሁኔታዎች አመቻችተው ነበርና የጠበቁት ግለሰቡ ሲደውልላት ወደተባለው ሆቴል በመጓዝ ለአንደኛ ተከሳሽ በጽሁፍ መልዕክት ሁሉንም መረጃ ታደርሰዋለች፡፡

ግለሰቡም ሁለት ጩቤ በማዘጋጀት በፖስታ ጠቅልሎ ወደ ተነገረው ስፍራ ያመራል ፡ አልጋ ክፍሉ እንደደረሰም ያንኳኳና የክፍሉን በር ከፍታ ወደ ውስጥ ታስገባዋለች፡፡

ወድያውንም አስቀድሞ ከሟች ጋር ሲጠጡበት በነበረው የወይን ጠርሙስ ጭንቅላቱን በመምታትና ጩቤውን ከአንደኛ ተከሳሽ እጅ ተቀብላ ደረቱና ብብቱ አካባቢ በመውጋት ከመሬት እንዲወድቅ ታደርገዋለች፡፡

በወደቀበትም አንደኛ ተከሳሽ ደጋግሞ አንገቱና የተለያዩ የሰውነት ክፍሉ ላይ በመውጋት ህይወቱ እንዲያልፍ ያደርጋል፡፡

ይህኔ ድምፅ የሰሙ የሆቴሉ የመስተንግዶ ባለሙያዎች ከስፍራው ሲደርሱ አንደኛ ተከሳሽ በመስኮት ወደ መሬት ይዘላል ሴቲቱም ከላይ አካላቷን በማራቆት ሊደፍራት ሲል አደጋው መድረሱን ትነግራቸውና ለማምለጥ ሙከራ ታደርጋለች፡፡

ወደ መሬት የዘለለው የድርጊቱ ዋና አቀናባሪ እግሩ ላይ የመሰበር ጉዳት ቢገጥመውም እንደምንም ታግሎ ወደ ግለሰቡ ተሸከርካሪ ኮድ 3-A 95731 አ.አ የሆነ ግምታዊ ዋጋው 1,200,000 የሚያወጣ በመግባት ፤ በውስጡ ካለው ጥሬ ገንዘብ 20,000 እና 44,000 የሚገመቱ ሁለት የእጅ ስልኮች ይዞ ለመሰወር ሲሞክር በጥበቃው ጥርጣሬ በቁጥጥር ስር ይውላል፡፡

ድርጊቱ ለፖሊስ ሪፖርት ተደርጎ የወንጀሉ ፈፃሚዎች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጓል፡፡ በተደረገው ማጣራትም የድርጊቱ ፈፃሚዎች ወንጀሉን መፈፀማቸውን ያምናሉ፡፡

ፖሊስ መዝገቡን በማደራጀት ለአዳማ ከተማ/ዞን/አ/ህግ ይልካል፡፡ አቃቤ ህግም በግድያና በዘረፋ ክስ መስርቶ ለአ/ዞ/ከ/ፍርድ ቤት ባቀረበው መሰረት ፍርድ ቤቱ በአይንና በሰነድ ማስረጃ የቀረበለትን ተመልክቶ ጥቅምት 3 ቀን 2013 ዓመት በዋለው ችሎት በሁለቱም ተከሳሾች ላይ እድሜ ልክ እስራትና እያንዳንዳቸው የ10,000 ብር ቅጣት እንደተወሰነባቸው በአዳማ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ረዳት ኢንስፔክተር ወርቅነሽ ገልሜቻ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።

12/10/2020

የኤርትራው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ወደ ኢትዮጵያ እያመሩ ነው!

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ግብዣ በኢትዮጵያ ለ3 ቀናት የሚቆይ የሚቆይ የስራ ጉብኝት ለማድረግ የኤርትራው ፕሬዝዳንት ዛሬ ጠዋት ከአስመራ አየር ማረፊያ መነሳታቸውን የሀገሪቱ የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገ/መስቀል ገልጸዋል፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳሌ እና የፕሬዝዳንቱ አማካሪ የማነ ገብረአብም የፕሬዝዳንቱ ልዑክ አባላት እንደሆኑ አቶ የማነ ገ/መስቀል በትዊተር ገጻቸው ጽፈዋል፡፡ ሁለቱ መሪዎች በሀገራቱ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች እንደሚወያዩም ነው ሚኒስትሩ የገለጹት፡፡

12/10/2020

እንግሊዛዊው አትሌት ሞ ፋራህ የጅቡቲ አምባሳደር ሆነዋል፡፡

Mo Farah, the British athlete, has become Ambassador of Djibouti's Ports and Free Zones Authority.

12/10/2020

የፌስ ቡክ ኩባንያ በፌስ ቡክ ገጹ አማካኝነት የሚሰራ ምርቶችን መሸጥ እና መግዛት የሚያስችል የፌስ ቡክ መገበያያ መተግበሪያ ለኢትዮጵያውያን ማህበረሰብ መጀመሩን አስታውቋል፡፡

የፌስ ቡክ የግብይት መድረኩ ኢትዮጵያውያን የሚፈልጓቸውን ምርቶች በቀላሉ በፌስ ቡክ ገጻቸው አማካኝነት መግዛት እና መሸጥ የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡

በኢትዮጵያም አገልግሎቱ ከዚህ ወር መጨረሻ ጀምሮ ቀስ በቀስ ተደራሽ እንደሚሆን የተገለጸ ሲሆን፤ እስከ ሕዳር ወር መጨረሻ ድረስ ሙሉ ለሙሉ እንደሚጀምር ታውቋል፡፡

የአገልግሎቱን መጀመር አስመልክቶ የፌስ ቡክ የምስራቅ አፍሪካ እና የአፍሪካ ቀንድ የሕዝብ ፖሊሲ ዋና ኃላፊ ሜርሲ ንድግዋ ‘‘በኢትዮጵያ እያደገ የመጣውን የኤሌክትሮኒክ ግብይትን የሚያግዝ የፌስ ቡክ መገበያያ መድረክ በማስጀመራችን ደስታ ይሰማናል’’ ብለዋል::

የፌስ ቡክ ገጽን በመጠቀም ኢትዮጵያውያን የተወሰነ ግብይት እያከናወኑ እንደሆነ ስለምናውቅ የፌስ ቡክ ኩባንያም ደህንነቱ እና አስተማማኝነቱ የተጠበቀ አዲስ የግብይት መተግበሪያ ለኢትዮጵያውያን ማቅረቡ ትልቅ ስኬት መሆኑንም አንስተዋል፡፡

በግብይት መተግበሪያው ላይ ያለውን የግብይት መድረክ ቁልፉን በመጫን ወይም የፌስ ቡክ ግብይት ድረ ገጽን በመጎብኘት የሚፈልጉትን የዕቃ ዓይነት ከዝርዝሮቹ መሃል በዓይነትም ሆን በቦታ መምረጥ አልያም የሚፈልጉትን የምርት ዓይነት በቀጥታ ገብተው መጻፍ ይችላሉ፡፡

የግብይት ቁልፉን ሲጫኑ ተጨማሪ ዝርዝሮችን የሚያሳይ ሲሆን በሜሴንጀር አማካኝነት መልዕክቶችን ለሻጮች መተው ያስችላል ተብሏል፡፡

በተጨማሪም የሻጩን አጭር ግለ ታሪክ በመጫን ስለ ሻጩ መረጃ ማግኘት እና የሽያጭ ደረጃ ድልድሉን ማየት የሚያስችል ሆኖ ግዢና ሻጮች ስለ ክፍያ እና ለሎች ዝርዝር ሁኔታውን መረጃ የሚለዋወጡበት መድረክ ነው፡፡

25/09/2020

ይህ የሆነው ልክ የዛሬ 20 ዓመት ነበር!
በአትሌቲክስ መድረክ ድንቅ ፉክክር፤ አስደናቂ አጨራረስ የታየበት ውድድር እየተባለ ሁሌም ይወሳል፤
አትሌት ኃይሌ ገ/ስላሴ ከኬኒያዊው ፖል ቴርጋት ጋር በሲድኒ ኦሎምፒክ ያደረጉት ትንቅንቅ።

የ10ሺህ ሜትር ወድድሩ ሊጠናቀቅ ጥቂት ሜትሮች ሲቀሩ አትሌት ኃይሌ ፍጥነቱን በመጨመር በአስደናቂ አጨራረስ የወርቅ ሜዳሊያውን ለአገሩ አስገኝቷል።
መልካም ቀን

Photos from TOM TOM's post 22/09/2020

ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ባለው ኩዋዙሉ ናታል ግዛት፣ በፖሜሮይ እና ደንዲ መሀል ባለችው ኢብሆቪኒ መንደር ዛሬ የተነሳ ፎቶን ኢትዮጵያ ውስጥ እንደተከሰተ ተደርጎ 'Ethiopian DJ የኢትዮጵያ ሙዚቃ' በተባለ ገፅ ማምሻውን ቀርቧል።

በፎቶሾፕ የሚቀናበሩ እንዲሁም ሌላ ሀገር ተከስተው ሀገር ውስጥ እንደተደረጉ የሚቀርቡ ፎቶዎችን የጉግልን ወይም TinyEye የተባለውን ድረ-ገፅ በመጠቀም ሼር ከማረግዎ በፊት ያጣሩ።

24/06/2020

ለ50 ዓመአሜሪካዊቷ የዩኒቨርስቲ ተማሪ ለ50 ዓመት የበርካቶችን አእምሮ የፈተነውንና ሳይፈታ የቆየውን የሒሳብ ቀመር በቀላሉ፣ በጥቂት ቀናት ውስጥ፣ በትርፍ ሰዓቷ ፈትታዋለች።

ሊሳ ፒኪሪሎ ሦስተኛ ዲግሪዋን በዩኒቨርስቲ ኦፍ ቴክሳስ እየሰራች ነው።

ከዩኒቨርስቲ ፕሮፌሰሯ ካሜሮን ጎርደን ጋር እያወራች በነበረበት ወቅት እግረ መንገዷን ለወሬያቸው ማጣፈጫ በሚል የሰራችውን የሒሳብ ስሌት፣ ያቃለለችውን የሒሳብ ቀመር አነሳች።

"መጮህ ጀመረ 'እንዴት በጣም ደስተኛ አልሆንሽም?'" እንዳላት ፒኪሪሎ በኳንታ ለሚታተመው የሳይንስ ዜናን የሚሰራጨው ድረገጽ ተናግራለች።

"እብድ ነውወይዘሪት ፒኪሪሎ ሦስተኛ ዲግሪዋን ሳትይዝ የረዳት ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ያሰጣት የሒሳብ ቀመር 'ኮንዌይ ኖት ፕሮብሌም' ይሰኛል።

ኮንዌይ ኖት ፕሮፕሌም (Conway knot problem) በብሪታንያዊው ሒሳብ ሊቅ ጆን ሆርቶን ኮንዌይ በ1970 የተቀመረ ነው። ፒካሪሎ ግን ስለዚህ መልመጃ የሰማችው ለመጀመሪያ ጊዜ እአአ በ2018 በአንድ ሴሚናር ላይ መሆኑን ታስታውሳለች።

ፕሮፌሰር ጎርደን "ምን ያህል እድሜ ጠገብ ዝነኛ የሒሳብ መልመጃ መሆኑን ያወቀች አይመስለኝም" ብየወይዘሪት ፒኪሪሎ ሥራ በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ የታተመ ሲሆን እርሷም ይህንን የጥያቄ ጎምቱ፣ የመልመጃዎች አውራ በመፍታቷ በማሳቹሴት ኢንስቲትዩት ኦፍ ቴክኖሎጂ የረዳት ፕሮፌሰርነት ማዕረግ አግኝታለች።

"የኮንዌይ ኖት መልመጃ ለረዥም ዓመታት በሒሳብ ሊቃውንት ሊፈታ ሳይችል ቆይቷል" ያሉት ስፔናዊው ተመራማሪ ያቬር አራማዮና ናቸው።

ይህ የሒሳብ ቀመር እንደምን ያለ ነው?

ሒሳባዊ ቋጠሮ (Mathematical knots) የአንድ የሒሳብ ዘርፍ ሲሆን የሚመደብበትም ክፍል ቶፖሎጂ ይሰኛል።

ለዋል። የሆነው" በማለትም የነበረውን ሁኔታ ያስታወሰችው።ታት በቀላል ቋንቋ፣ ቶፖሎጂ የሚያጠናው ቁሶች ቅርጻቸውን ሲቀይሩ፣ ሲጎብጡ፣ ሲጠመዘዙ እና ሲወጠሩ-ነገር ግን ሳይሰበሩ እንዴት ያለ ጠባይ እንደሚያሳዩ ነው።

ኖት ቲዎሪ (የጥልፍልልፎሽ ኀልዮት) የቶፖሎጂ አንዱ ዘርፍ ነው።

ከእውኑ ዓለም ምሳሌዎች በተጻራሪው፣ ሒሳባዊ ቋጠሮ መጨረሻዎቹ የተሳሰረ ነው። በእርግጥ ቀላሉ ቋጠሮ የቀለበት ቅርጽ አለው፤ እናም ሊዋሃድ አይችልም።

ነገር ግን የበለጠ ውስብስብ ይሆናል፤ ይህም አንዱ በአንዱ ላይ ሲጠላለፍና ሲቆላለፍ ነው።

ይህንን በቀላሉ ለማስረዳት ገመድን ማሰብ በቂ ነው የሚሉት ማሪታኒያ ሲልቬሮ ናቸው። በሴቪሊ ዩኒቨርስቲ የሒሳብ ሊቅ የሆኑት እኚህ ምሁር "የጥልፍልልፎሽ ኀልዮት በአንድ ገመድ ላይ የሚከሰትን ቅርጽ አልባነት ያጠናል" ሲሉ ያክላሉ።

"በሌላ ቋንቋ፣ ገመዱን እንዴት አድርገን እንደምንጠመዝዝ፣ እንደምናጎብጠው፣ እንደምናጥፈው፣ እንደምንጨምቀው. . .ገመዱን ለመቁረጥ የማናደርገው ነገር ማለት ነው። ያ ክልክል ነው።"ሳይፈታ የቆየውን የሒሳብ እንቆቅልሽ በቀናት ውስጥ የፈታችው ተማሪ

ቶፖሎጂ ታዲያ በተለያዩ የሳይንስ ዘርፎች ውስጥ ቁልፍ ቦታ አለው። የምጣኔ ሃብት ገበያዎችን እንዲሁም የዲኤንኤ ሞሎኪውልስን ቅርጽ ለማጥናት ይውላል።

የኮንዌይ ኖት

ከኖት ፕሮብሌም ጀርባ ያለው ሰው ጆን ሆርቶን ኮንዌይ በሚያዚያ ወር በተወለደ በ82 ዓመቱ በኮሮናበወይዘሪት ፒኪሪሎ 11 ጊዜ የተጠላለፈን የኮንዌይ ኖት ነው ተመሳሳዩን በመስራት "አቻ ጥልፍልፍ" መፍታት የቻለችው።

እርሷ በአቻነት የሰራችው ጥልፍልፎሽን የእውቁን የሒሳብ ሊቅ የ50 ዓመት ሚስጥር ለመፍታት ተጠቀመችበት።

"ቀን ቀን ለመስራት አልፈልግም ነበር፤ ያ ለሒሳብ የሚመች አይመስለኝም. . . ልክ የቤት ሥራ እንደተሰጠኝ በማሰብ ቤት ወስጄ ነው የሰራሁት" ብላለች።

ወይዘሪት ፒኪሪሎ በአሜሪካ ማይን በምትባል ገጠራማ ስፍራ ተወልዳ ያደገች ሲሆን ሒሳብን ያጠናችው በቦስተን ኮሌጅ ነው።ቫይረስ ምክንያት ሞቷል።

ሊቨርፑል የተወለደው ይህ የሒሳብ ሊቅ በዘርፉ ምሁራን ዘንድ ተወዳጅ እንደነበር ይነገርለታል።

24/06/2020

የህኢትዮጵያ የሦስትዮሽ ስምምነት ከመደረሱ በፊት የግድቡን ውሃ ሙሌት የምትጀምር ከሆነ ጉዳዩን ወደተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀጥታ ምክር ቤት እንወስደዋለን ስትል የነበረችው ግብፅ በባለፈው ሳምንት አርብ ምክር ቤቱ ጣልቃ እንዲገባ ጠይቃለች።

ግብፅ ባስገባችው የስልሳ ሦስት ገፅ ደብዳቤ ላይ ሦስቱ አገራት በድርድሩ እንዲቀጥሉና ፍትሃዊና ሚዛናዊ ስምምነት ላይ መድረሳቸውንም ምክር ቤቱ ጣልቃ በመግባት እንዲያረጋግጥ ጠይቃለች።

ምክር ቤቱ ስምምነት ከመፈረሙ በፊት ኢትዮጵያ ውሃ ከመሙላት እንድትታቀብና ጣልቃ በመግባት ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል ብላለች። በተባበሩት መንግሥታት ስብሰባ ላይም በመገኘት ጉዳዪን ማስረዳትም እንደምትፈልግ በደብዳቤው ላይ ገልፃለች።

የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በበኩላቸው ባለፈው ሳምንት አርብ ከአሶሺየትድ ፕሬስ ጋር ባደረጉት ቆይታ ግድቡን ለመሙላት የሦስትዮሽ ስምምነት አስገዳጅ እንዳልሆነና በታቀደለትም የክረምት ወቅት የመጀመሪያ ደረጃ ሙሌት ይካሄዳል በማለት አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።

ግብጽ "በወንዛችን ላይ የሚደረገውን ልማት ለመቆጣጠር እየሞከረችም ነው" በማለት ወቅሰዋል።

ስምምነት ላይ መድረስ ፈታኝ እንደሆነ የተናገሩት አቶ ገዱ " ስምምነት ላይ መድረስ ባንችልም በያዝነው ዕቅድ መሰረት የግድቡን የውሃ ሙሌት እንጀምራለን። የሌሎቹን ምርቃት የምንጠብቅ ከሆነ ግድቡ ለዓመታት ምንም ሳንሰራበት ጥቅም አልባ ነው የሚሆነው። ይህ እንዲሆን ደግሞ አንፈቅድም" ብለዋል።

አክለውም "ኢትዮጵያ በራሷ ውሃ ለማልማት ግብጽና ሱዳንን አትለምንም" ያሉት አቶ ገዱ ግድቡን በራሷ ወጪ መስራቷንም ጠቁመዋል።

የህዳሴው ግድብ ድርድር ትኩረቱን ስቶ የውሃ ድርሻ ክፍፍል ላይ ሆኗል ተባለ

በህዳሴው ግድብ ዙሪያ የሚደረገው ድርድር፡ የግብፅ ፍላጎትና የኢትዮጵያ ውሳኔ

"እየተካሄደ ያለው ድርድር የተጓተተው ግብፅ የቅኝ ግዛት ስምምነቱን ሙጥኝ በማለቷ ነው"

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ገዱ አክለውም ግድቡ የቀጠናው ትብብር ማጠናከሪያ ነው እንጂ፤ ውዝግብና ጦርነት መጎሰሚያ መሆን አይገባውም ብለዋል።

"ግብጽውያን በህዳሴ ግድብ ላይ የያዙትን ፕሮፓጋንዳ አጠናክረውታል። የፖለቲካ ቁማርም ነው እየተጫወቱ ያሉት። አንዳንዶቹም ጦርነት እንዲነሳ የሚጠብቁ ይመስላሉ" ብለዋል።

ግብጽ ኢትዮጵያ ግድቡን ውሃ የመሙላት ተግባር በቀጠናው እንዲሁም ለዓለም አቀፉ ሰላምና ደኅንነት ጠንቅ ነው ማለቷ እንዳሳዘነውም በተጨማሪ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለተባበሩት መንግሥታት የፀጥታ ምክር ቤት በላከው ደብዳቤ ገልጿል።

የሦስትዮሽ ስምምነቱ ሳይጠናቀቅ ግብጽ ምክር ቤቱን ጣልቃ እንዲገባ መጠየቋ ግራ የሚያጋባ ቢሆንም "ድርድሩ ፍሬ አልባ እንዲሆን እየሰራች ከነበረችው ግብጽ" የሚጠበቅ ነው ብሏል።

የግድቡ ድርድር ዓለም አቀፋዊ ይዘት እንዲኖረው እየጣረች እንደሆነ ያተተው መግለጫው ግብጽ ቀጠናዊ እንዲሁም አህጉራዊ መፍትሄዎችን ያልሻተችውና የዘለለችው በዚሁ ምክንያት ነው ይላል።

ግብጽ በጎርጎሳውያኑ 1959 የተፈረመውና፣ የአብዛኛውን የውሃውን ድርሻ የሚሰጣትን የቅኝ ግዛት ስምምነት ሙጥኝ ብላ ታሪካዊ ተጠቃሚነት በሚል መርህ የወንዙን ውሃ ሙሉ በሙሉ በበላይነት ለብቻዋ የመጠቀም ፍላጎት እንዳላት ደብዳቤው ጠቅሷል።

ስምምነቱ ኢትዮጵያን ያላካተተ ከመሆኑ በተጨማሪ ግብጽ 55.5 ቢሊዮን ኪዩቢክ ውሃን እንዲሁም ሱዳን 18.5 ቢሊዮን ኪዩቢክ ውሃን እንድታገኝና 86 በመቶ የናይልን ውሃ የምትገብረውን ኢትዮጵያ ያለ ውሃ የሚያስቀር አግላይና ኢፍትሃዊ ስምምነት ነው።

ኢትዮጵያ በዋሽንግተኑ የህዳሴ ግድብ ድርድር ላይ እንደማትሳተፍ አሳወቀች

የሕዳሴ ግድብ ድርድር የት ደረሰ?

ኢትዮጵያ የአረብ ሊግን የውሳኔ ሃሳብ ውድቅ አደረገችው

ግብፅጽ ድርድሩን ምክንያት በማድረግ ይህንን ስምምነት ኢትዮጵያ እንድትቀበል ኢትዮጵያ ላይ ጫና እያደረገች ሲሆን ይህ በማንኛውም ሁኔታ ተቀባይነት የለውም ብላለች ኢትዮጵያ።

ለዓመታት ሲካሄድ የነበረው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድርድር ፍሬ ሳያፈራ ባለፈው ሳምንት ተቋርጧል። ከሰኔ 2-10 ድረስ የተካሄደው የህዳሴ ግድብን የውሃ ሙሌት እና ዓመታዊ የውሃ አለቃቀቅን በተመለከተ በበይነመረብ የተካሄደው የቪዲዮ የሦስትዮሽ ድርድርም መቋጫ ሳያገኝ ቆሟል።

ከሰሞኑ በህዳሴው ግድብ ቁልፍ የሕግ ጉዳዮች ላይ ስምምነት ባለመደረሱ፣ ጉዳዩ ለአገራቱ መሪዎች እንዲተላለፍ ሱዳን ሃሳብ ማቅረቧን አልጀዚራ ዘግቧል።

የሱዳን የውሃ እና መስኖ ሚኒስትር ያሲር አባስን ዋቢ አድርጎ አልጀዚራ እንደዘገበው ሦስቱ አገራት በድርድሩ ስምምነት ላይ መድረስ አቅቷቸዋል ብሏል። የሦስትዮሽ ድርድሩ ለጊዜው የተቋረጠው ሱዳን ጉዳዩ በመሪዎች ደረጃ እንዲታይ ሃሳብ ማቅረቧን ተከትሎ እንደሆነም የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በላከው ደብዳቤ አስረድቷል።

ያሲር አባስ ለሪፖርተሮች እንደተናገሩት ከ90-95 በመቶ የሚሆኑ የቴክኒካል ጉዳዮች ላይ መስማማት እንደተቻለ፤ ነገር ግን ሕጋዊ ጉዳዮች ላይ አሁንም ቢሆን ምንም ስምምነት አለመደረሱን ተናግረዋል።

በተለይም ከውሃ ክፍፍል ጋር በተገናኘ አገራቱ መስማማት ስላቃታቸው በመሪዎች ደረጃ ሊፈታ ይገባል እንደተባለም ዘገባው ጨምሮ አስነብቧል።

የኢትዮጵያ የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴርም በበኩሉ ተመሳሳይ መግለጫ ያወጣ ሲሆን በቴክኒካል ጉዳዮች ላይ ስምምነት ቢደረስም በውሃ ሙሌት እና አለቃቅ የሕግ ጉዳዮች ላይ መሠረታዊ ልዩነቶች እንዳሉ በፌስቡክ ገጹ አስታውቋል።

በህዳሴ ግድብ ላይ የአሜሪካ እና የዓለም ባንክ ሚና እልባት ሊያገኝ እንደሚገባ መንግሥት አስታወቀ

ኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብጽ በመግለጫ ምልልስ እየተወዛገቡ ነው

በህዳሴው ግድብ ድርድር በታዛቢዎች ሚና ላይ ስምምነት አለመደረሱ ተነገረ

ሚኒስቴሩ ከሰሞኑም ድርድሩ ከህዳሴው ግድብ ውሃ አሞላልና አለቃቀቅ አልፎ በውሃ ድርሻና አጠቃቀም ላይም እንዲሆንና የኢትዮጵያን የወደፊት በአባይ ውሃ የመጠቀም መብትን የሚገድብ ዓይነት ስምምነት ላይ እንዲደረስ ፍላጎቶች ያሉ መሆናቸውንም ጠቁሟል።

ደብዳቤውም ላይ እንደተጠቀሰው ግብጽ በተደጋጋሚ የውሃ ክፍፍል ድርድር ነው በማለት በላይኛው ተፋሰስ አገራት የሚሰሩ ልማቶችን ለማገድ ብትሞክርም በአንፃራዊው ይህ ድርድር የህዳሴ ግድብ ውሃ አለቃቀቅና የግድቡ አሰራርን በተመለከተ እንደሆነ ደብዳቤው ገልጿል።

"የውሃ ክፍፍል ከሆነ ሌሎች የተፋሰሱ አገራትም ሊሳተፉ ይገባ ነበር፤ እነሱም ተጠቃሚዎች ከመሆናቸው አንፃር በውሃ ክፍፍሉ ሦስቱ አገራት ብቻ ሊወስኑላቸው አይችሉምግብጽ ኢትዮጵያ ላይ ፖለቲካዊና ዲፕሎማሲያዊ ጫና በመፍጠር ለማንበርከክና ምክር ቤቱንም በተሳሳተ መንገድ ለመውሰድ እየሞከረች ነው ያለችው ኢትዮጵያ ከሰሞኑ የደረሱባቸው ስምምነቶችም ኢትዮጵያ ምን ያህል ግድቧም ቢሆን ልዩነቶችን ለማጥበብ እየሰራች መሆኑን ማሳያ እንደሆነም ደብዳቤው ጠቅሷል።

የግብፅጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሜህ ሹክሪ በበኩላቸው ግብጽ ጉዳዩን ወደ ምክር ቤቱ የወሰደችው የዓለም አቀፉን ሰላምና ደኅንነት ለማስጠበቅ እንጂ በኢትዮጵያ ላይ ማዕቀብ ለማስጣልም ሆነ ሌላ እርምጃ እንዲወሰድባት አይደለም ማለታቸውን ኢጅፐት ኢንዲፔንደንት ዘግቧል።

የ150 ሚሊዮን ግብጻውያንና ሱዳናውያን ህይወት ላይ ተፅእኖ የሚያደርስ ከመሆኑ አንፃር የግድቡን ቀውስ በኃላፊነት የመፍታቱ ጉዳይ የምክር ቤቱ ነውም ብለዋል።

የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ኢትዮጵያ ስምምነቱ ሳይፈረም ግድቡን አልሞላም ትበል እንዲሁም ወደ ስምምነቱም ትመለስ ብሏል።

የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ አንዳርጋቸው ግብጽ ጉዳዩን ወደ ምክር ቤቱ የወሰደችው ከግድቡ ድርድር ለማምለጥ ነው ማለታቸውን እንደማይስማሙና አሁንም ቢሆን በድርድሩ እንደሚቀጥሉ ሳሜህ ምላሽ መስጠታቸውን ኢጅፕት ኢንዲፔንድንት ዘግቧል።

ዘገባው አክሎም ኢትዮጵያ ስምምነቱ ከመደረሱ በፊት የመጀመሪያ ዙር የግድቡን ውሃ ሙሌት የማትጀምር ከሆነ በድርድሩ እንደሚሳተፉ ማስታወቃቸው ተዘግቧል።

ሰኞ ዕለትም የሱዳኑ የውሃና የመስኖ ሚኒስትር ያሲር አባስ በሰጡት መግለጫ የህዳሴ ግድብ መቋጨት የሚችለው በሦስትዮሽ ድርድር መሆኑን አስታውቀው ሱዳን በድርድሩ ተስፋ እንደምታደርግ አስምረዋል።

ሁኔታው ከተባባሰ ወደ ግጭት እንደሚያመራ የጠቆሙት ሚኒስትሩ "ድርድሩ ብቻ ነው ተስፋው ብለዋል" አክለውም "የግድቡ ሙሌትን ለመጀመር ስምምነት ላይ ሊደረስ ይገባል ሱዳንም ይህንን ለመጠየቅ መብቱ አላት" ብለዋል።

በግብጽ መንግሥትን በሚደግፉ ሚዲያዎችም ላይ ኢትዮጵያ ይህንን አቋሟን እንድትለውጥ ግብፅ እርምጃ መውሰድ አለባትም ሲሉ ተሰምተዋል። የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በበኩላቸው ግብጽ ወታደራዊ እርምጃ ለመውሰድ እንደማትፈልግና ፖለቲካዊ መፍትሔን እንደምትሻ ጠቁመው ኢትዮጵያም ግድብ የመገንባት መብቱ አላት ብለዋል።

"በባለፉት ስድስት ዓመታት ግብጽ ወታደራዊ እርምጃ እንወስዳለን የሚል ፍንጭ አላሳየችም" ያሉት ሚኒስትሩ ነገር ግን ምክር ቤቱ ኢትዮጵያን ወደ ድርድሩ የማያመጣት ከሆነና የግድቡ ሙሌት ከተጀመረ ግን " ምን አይነት እርምጃ እንደምንወስድ በዚያን ጊዜ ግልፅ አድርገን እናሳውቃለን። ሁኔታውን ዝም ብለን አናይም" ብለዋል።

ግብጽ የተባበሩት መንግሥታት በህዳሴው ግድብ ጉዳይ ጣልቃ እንዲገባ ጠየቀች

የህዳሴ ግድብ ድርድሮች ላይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ውይይት ተካሄደ

በግብጽም ጥያቄ መሰረት የአረብ ሊግ አገራት ጉዳዩን በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች አማካይነት ትላንት ማክሰኞ መወያየታቸው የተሰማ ሲሆን ግብጽ ግድቡን በተመለከተ ያቀረበችው ሃሳብ በአንዳንድ አባል አገራት ተቀባይነት ሳያገኝ መቅረቱ ተሰምቷል።

በውሃ ጉዳይ ሚኒስትሮች ደረጃ የሚካሄደው ድርድር ወደ መሪዎች ይመራ የሚለው መቋጫ ያላገኘ ሲሆን ኢትዮጵያ በበኩሏ ምንም አይነት ስምምነት ላይ ይደረስም አይደረስ የመጀመሪያ ደረጃ የግድቡ ውሃ ሙሌት ሐምሌ ወር ላይ የመጀመር እቅድ አላት።

ይሄ ጉዳይ ግን በግብጽ ብቻ ሳይሆን ለግብጽ ወግናለች ተብላ ስትወቀስ በነበረችው አሜሪካም ዘንድ ተቀባይነት ያገኘ አይመስልም። ከሰሞኑም የአሜሪካ ብሔራዊ ፀጥታ ምክር ቤት ኢትዮጵያ የግድቡን ውሃ ሙሌት ከመጀመሯ በፊት የሦስትዮሽ ስምምነት ሊደረስ ይገባል የሚል የማሳሰቢያ መልዕክት በትዊተር ገፁ ላይ አስፍሯል።

"257 ሚሊዮን የሚሆን የምሥራቅ አፍሪካ ሕዝብ ኢትዮጵያ ጠንካራ አመራር እንድታሳይ ይጠብቃል። ይህ ማለት ፍትሃዊ የሆነ ስምምነት ነው ብሏል። በህዳሴ ግድብ ላይ ያሉ የቴክኒክ ጉዳዮች መፍትሔ አግኝተዋል፤ አሁን ደግሞ የህዳሴ ግድብ ውሃ ሙሌት ከመጀመሩ በፊት ስምምነት ላይ የሚደረስበት ጊዜ ሊሆን ይገባል" ብሏል በትዊተር ገፁ።

የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርም ለዚህ በሰጠው ምላሽ "ግድቡን አስመልክቶ ከመንግሥትም ሆነ ከሌሎች ተቋማት የሚሰጡ መግለጫዎች ወገንተኝነትን አለማሳየታቸውን እንዲሁም የሚደረጉ ድርድሮች ላይ እክል እንዳይፈጥሩ ጥንቃቄ ያሻቸዋል። ፍትሃዊ የሆኑ መግለጫዎች መሆን አለባቸው አለበለዚያ መግለጫ ከመስጠት መቆጠብ ያስፈልጋል" ብሏል።

የግብጽ የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ቃል አቀባይም ከሰሞኑ ድርድሩ ፍሬ አልባ ነው ሲሉ የተቹ ሲሆን ለዚህም ዋነኛ ምክንያቱ የኢትዮጵያ "ግትርነት" ነው በማለት ተችተዋል።

ቃለ አቀባዩ ኢትዮጵያ እያቀረበችው ያለው ሰነድ ቴክኒካልና ሕጋዊ መርሆችን የሚጥስ እንዲሁም የታችኛው ተፋሰስ አገራትን ፍላጎትንም ሆነ መብታቸውን የሚጋፋ ነው በማለት ወቅሰዋል።

ሰነዱንም "የሚረብሽ" ያሉት ቃል አቀባዩ ኢትዮጵያ በድርድሩ ስምምነት ላይ ለመድረስ ፍላጎት የላትም ማለታቸውን የግብጽ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

ኢትዮጵያ በበኩሏ በተደጋጋሚ ግብጽ የቅኝ ግዛት ውሎችን ሙጥኝ እንዳለችና ኢ-ፍትሃዊና አግላይ የሆነውን ስምምነት ተቀባይነት እንዲያገኝ ጫና እያደረገች ነው በማለትም ትወቀሳለች።

ባልነበረችበት የተፈረመ ስምምነት ለናይል ወንዝ 77 ቢሊየን ሜትር ኪዩብ ውሃ ለምታመነጨው ኢትዮጵያ ምንም ድርሻ የማይሰጥና ተፈጥሯዊም ሆነ ሕጋዊ መብቴን የሚነጥቅ ነው በማለትም ኢትዮጵያ ትከራከራለች።

ግብጽ ከምታነሳቸው ቅሬታዎች መካከል ኢትዮጵያ ግድቡን ሙሉ አቅም እየተጠቀመች ድርቅ ቢያጋጥም ችግሩ የሦስቱም አገራት ጉዳይ ነው የሚል አቋም ላይ መድረሷን ነው።

ረዘም ላለ ጊዜ ድርቅ የሚከሰት ከሆነ ኢትዮጵያ የታችኛው ተፋሰስ አገራት ጥቅምን ለመጠበቅ ዋስትና ልትሰጠን ይገባል በማለትም ግብጽ ትከራከራለች።

ኢትዮጵያ ያለ ታችኛው ተፋሰስ አገራት ስምምነትም ግድቡን ለመሙላት መወሰኗም ሁለቱን አገራት የማስገደድ ውሳኔ ነው ብለውታል ቃለ አቀባዩ።

የሦስትዮሽ ስምምነቱ እልባት ሳያገኝ ኢትዮጵያ የመጀመሪያ ዙር የግድቡን ውሃ ሙሌት ብትጀምርም አለመረጋጋቶችና ግጭቶች በቀጠናው እንደሚከሰትም ከሰሞኑም አስጠንቅቃለች።

ይህንንም ተከትሎ ከሰሞኑም ኢትዮጵያውያን #ግድቡ የኔ ነው በሚል በትዊተር ላይ ዘመቻም ጀምረዋል። ኢትዮጵያ ግድቡን በመሙላት እንድትቀጥልበትም ድጋፋቸውን ለግሰዋል።

የአሜሪካ፣ አውሮፓ ሕብረትና ደቡብ አፍሪካን ጨምሮ የወቅቱ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበርን አገራቱ በበይነ መረብ አማካይነት በርቀት የሚያደርጉትን ድርድር እየታዘቡት ይገኛሉ።

የሦስቱ አገራት የውጭ ጉዳይ እና የውሃ ሚኒስትሮች እንዲሁም የሕግ እና የውሃ ጉዳይ የቴክኒክ ባለሞያዎች በዋሽንግተን ዲሲ ሲደራደሩ በነበረበት ወቅት በዓመታት የተራዘመ ድርቅ እንዲሁም በተራዘመ ዓመታት አነስተኛ የውሃ ፍሰት ላይም መሰረታዊ መግባባት ተደርሷል ተብሎ የነበረ ቢሆንም ያለምንም ውጤት መቋረጡ ይታወሳል።

በወቅቱም ግብጽ የመጠጥ ውሃ አቅርቦቴን ይቀንሰዋል እንዲሁም ለእርሻ የሚያስፈልገኝ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ በየዓመቱ ይገባኛል ስትል የቆየች ሲሆን፤ ኢትዮጵያ በበኩሏ 31 ቢሊዮን ኪዩቡክ ውሃ በዓመት ለመልቀቅ ሃሳብ አቅርባ ነበር። ነገር ግን አሜሪካ በበኩሏ 37 ቢሊዮን ኪዩብክ ሜትር እንዲለቀቅ መጠየቋ ተነግሮ ነበር።

ኢትዮጵያ ወንዙ በግድቡ ስፍራ እንደሚኖረው ዓመታዊ የፍሰት መጠን ከ4 -7 ዓመታትን በሚወስድ የሙሌት ደረጃ ግድቡን የመሙላት እቅድን ብታቀርብም ግብፅጽ በበኩሏ ጥቅሜን የሚጋፋ ነው በማለት ከ12 እስከ 21 ዓመታት መውሰድ አለበት ትላለች።

ኢትዮጵያ ዋሽንግተን ሲካሄድ የነበረውንም ድርድር ያቋረጠችበት ምክንያት በግብጽ ፍላጎት ታዛቢ እንዲሆኑ የገቡት አሜሪካና የዓለም ባንክ ለግብጽ ከመወገን አልፈው የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን ላይ ጫና ለማሳደር ሞክረዋል በማለት ኢትዮጵያ መውቀሷ የሚታወስ ነው።

አሜሪካ፣ የዓለም ባንክ ከግብጽ ጎን ቆመው ነበር በተባለው በዚህ ድርድር ላይ ከመጀመሪያው ሙሌት በኋላ ኢትዮጵያ ለምትጠቀመው ውሃ ለግብጽ የተጠራቀመ የውሃ ጉድለት ማካካሻ እንድትሰጥ የሚያስገድድ እንደሆነም ተገልጾ ነበር።

ይህንንም ተከትሎ ኢትዮጵያ የግብጽ ሃሳብ በአባይ ወንዝ ላይ ተፈጥሯዊ መብት እንዳይኖራት ወይም ምንም ዓይነት የውሃ ልማት ያልተገነባበት ፍሰት እንዲኖር የሚጠብቅ ነው በማለትም ትተቻለች።

የህዳሴ ግድብ በዚህ ዓመት መጋቢት ወር ላይ 90 በመቶ የተጠጋ የሲቪል ሥራው፣ 44 በመቶ የኤሌክትሮ መካኒካል ሥራው እና 20 በመቶ የብረታ ብረት ሥራው እና አጠቃላይ የግንባታው ሂደት ወደ 75 በመቶ መድረሱም ተገልጿል።

09/06/2020

ሰኔና ሰኞ ታሪካዊ አመጣጡና ያስከተላቸው ዳፋዋች!

ዓለም ከተፈጠረበት ወይም የቀን መቁጠሪያ ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ሰኔ እና ሰኞ በአስገራሚ መንገድ በየተወሰነ ዓመት ይገጥማሉ።
የሰኔ እና ሰኞ ነገር አስገራሚነቱ በዚ’ ይጀምራል።
ሌላ አስገራሚ ነገር እናክል።
ሰኔ እና ሰኞ በ5 እና በ6 አመታት ልዩነት ይመጣና ቀጥሎ በ5እና6 በመደመር በየ11 አመት ይመጣል፤ ይህም አንድ አበቅቴ ይሆናል።
ሰኔ እና ሰኞ ሌላም አስገራሚ ባህሪ አለው። በመቶ አመት ውስጥ ሁለት ጊዜ በጎዶሎ፤ ሁለት ጊዜ በሙሉ ቁጥር እያከታተለ ይመጣል።
ከሌሎች ወራት በተለየ፤ ሰኔ እና ሰኞ በፈረንጅ ካላንደር ከገጠመ፤ በሳምንቱም በኢትዮጵያ ካላንደርም ሰኔ እና ሰኞ መልሶ ይገጥማል።

የሰኔ እና ሰኞን ግጥምጥሞሽ… እንደዋዛ ፈዛዛ በጨዋታ መልክ የሚያልፉት ሰዎች የመኖራቸውን ያህል፤ በአውደ ቀመር የተካኑ፤ ስለመጥዕቅ በምጥቅ እና በጥልቅ የሚያውቁ የጥንት አባቶች ግን፤ ነገሩን በዋዛ የሚያዩት አይመስልም። ቀን ቆጥረውና አመታት አስልተው ሰኔ እና ሰኞ የሚገጥምበትን አመት፤ በጥንቃቄ እንድናልፈው ይመክሩናል። እኛም እንደሊቃውንት አባቶቻችን፤ የባህረ ሃሳብን እውቀት እና ቀመር መሰረት አድርገን በአገራችንና በአለማችን የተከሰቱ የሰኔ እና የሰኞ ግጥምጥሞሽን፤ ትንሽ በትንሽ እንጨዋወታለን።

በኢትዮጵያ ክፉ ቀን የምንለው… ረሃብ፣ በሽታ እና ጦርነትን ነው። የሰው ብቻ ሳይሆን የከብት በሽታ ጭምር… የኑሮ ሚዛን የሚያዛባበት አጋጣሚ አለ። በ1880 ዎቹ መጀመሪያ ላይ በኢትዮጵያ አስከፊ ረሃብ ሲቀሰቀስ፤ በስተበኋላም ብዙ ቸነፈር ሲወርድ፤ ሰኔ እና ሰኞ ገጥሞ ነበር። የከዋክብት ስነ ፈለግ እውቀት የነበራቸው አባቶችም፤ የሰኔ እና ሰኞን ግጥምጥሞሽ ከከዋክብቱ ተጽዕኖ ጋር ቀምረው፤ መጪውን የረሃብ ወይም የጦርነት ዘመን በትክክል ይተነብዩ ነበር። ዛሬ የምናደርገው… የቻልነውን ያህል አውደ ታሪክ ፈትሸን፤ “በእርግጥ ሰኔ እና ሰኞ ሲገጥም ምን ተፈጠረ?” የሚለውን ይሆናል።

ከዚያ በፊት ግን አጼ ምኒልክ፣ አባታቸው ንጉሥ ኃይለ መለኮት፣ ልጃቸው ንግሥት ዘውዲቱ፣ እቴጌ ምንትዋብ፣ እቴጌ መነን… ሁሉም ከሰኔ እና ሰኞ አንድ አመት በፊት ወይም በኋላ ነው ህይወታቸው ያለፈው። ይህን ያህል ስለደጋጎቹ ካወጋን፤ ሌላውን ታሪክ በግርድፍ ፈጠን ቀልጠፍ ብለን እናወጋችኋለን።
ወደ ዝርዝር አውደ ታሪካችን ከመግባታችን በፊት፤ ጥቂት ስለሰኔ እና ሰኞ አስገራሚ ባህሪ እንግለጽላቹህ። ሰኔ እና ሰኞ በ5 እና በ6 አመት፤ ከዚያም ከ11 አመታት በኋላ ይመጣል። ከ11 አመታት በኋላ የሚመጣው ሰኔ እና ሰኞ፤ በአገሪቱ ላይ የጦርነት ወይምየበሽታ ወይም የረሃብ ደመና ሊመጣ እንደሚችል ያመላክታል። እናም ለሚቀጥሉት አመታት ዝግጅት ካልተደረገ፤ በ3ኛው አመት ላይ የከፋ ቸነፈር ይወርዳል። ለምሳሌ ከ11 አመታት በኋላ… በ1880 ሰኔና ሰኞ ገጠመ። ዝግጅት ስላልተደረገ በሚቀጥሉት ሁለት እና ሶስት አመታት ከሃምሳ ሺህ በላይ ሰዎች በረሃብ ቸነፈር አለቁ። እንዲህ እንዲህ እያልን ባለፉት 200 አመታት የሆነውን ነገር አብረን እንመልከት።

ከአንቀጹ በፊት ያስቀመጥነው አመት ሁሉም እንደፈረንጆች የቀን አቆጣጠር ሲሆን፤ ዝርዝር ታሪኩን ደግሞ ስንገልጽ በኢትዮጵያ ቀን አቆጣጠር እያልን ጽፈነዋል።
>> የሰኔ እና ሰኞ መጥፎ ግጥምጥሞሽ ተምሳሌቶች ፦
1812 በዚህ አመት ሰኔ እና ሰኞ ገጠመ። የንጉሥ ሳህለስላሴ አባት …መርድ አዝማች ወሰንሰገድ በዚህ አመት ከጦርነት በኋላ በብርቱ ቆስለው ሞቱ።
1829 በኢትዮጵያ ከፍተኛ ረሃብ ሆነ። ረሃቡን ተከትሎ የኮሌራ በሽታ በመምጣቱ በተለይ በሸዋ እጅግ ብዙ ሰው ሞተ።

1846 የዚህን አመት ሰኔ እና ሰኞን ተከትሎ፤ የሸዋ ንጉሥ የነበሩት፤ የምኒልክ አያት ንጉሥ ሳህለስላሴ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ።
1857 በ19ኛ ክፍለ ዘመን ከነበሩት የሰኔ እና ሰኞ አበቅቴዎች መካከል፤ ይሄኛው አንደኛውና ተጠቃሽ ዘመን ነው። በኢትዮጵያ አቆጠጠር 1849 ዓ.ም መሆኑ ነው። ጥንቃቄ፣ ዝግጅት፣ ጸሎት እና ግዝት ካልተደረገ በቀር፤ አበቅቴ ላይ የሚያርፈው ሰኔ እና ሰኞ በተከታታይ አመታት የሚያመጣው ቸነፈር ከበድ ያለ ይሆናል። ይህ ዘመን የአጼ ቴዎድሮስ ዘመነ መንግስት ነው። በኢትዮጵያ አቆጣጠር 1849 ሰኔ እና ሰኞ ከገጠመ በኋላ፤ አጼ ቴዎድሮስ በእጃቸው ያለውን እያጡ የነበረበት ፈታኝ ዘመን ነበር። በጎጃም ደጃች ተድላ ጓሉ፣ በሸዋ ሰይፉ መሸሻ፣ በሰቆጣ ዋግሹም ገብረ መድህን፣ በጎንደር ጋረድ ክንፉ እና ግንባሮ ካሳ፣ በትግራይ ደጃች ንጉሴ… አምጸውባቸው፤ ወሎ እና ቤጌምድርም አልገዛም ብሎ ያስቸገረበት ወቅት ነው። የጎንደር ቀሳውስት ተሰብስበው፤ ለአጼ ቴዎድሮስ አዲስ የመንግስት አሰራር እንዲከተሉ በድፍረት የተናገሩበት ሁኔታ ተከስቷል።

ከዚያ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ የሸዋ መኳንንት የሚገደሉት ተገድለው፤ የተቀሩት እጃቸውን የተቆረጡበትን አጋጣሚ እናስታውሳለን። ሌላው ቀርቶ በአመቱ የአጼ ቴዎድሮስ ሚስት፤ እቴጌ ምንትዋብ በ1851 ዓ.ም ሞቱ። ቀጥሎም የእንግሊዝ ወኪል ፕላውዴንን የአጼው ዘመድ ጋረድ ክንፉ በጦር ወግተው ገደሏቸው። ከዚያም እንግሊዛዊ አማካሪያቸው፤ ጆን ቤል ሞተ። ከዚህ በኋላ የነበረው ምስቅልቅል በቃላት ብቻ ተገልጾ የሚያልፍ አይደለም። ካልተዘጋጁበት በቀር፤ የአበቅቴው ሰኔ እና ሰኞ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ተከታታይ የችግር ቸነፈሮች አልፈዋል።

1863 በአሜሪካ ደግሞ የርስ በርስ ጦርነት የተጀመረበት፤ ሲሆን፤ በጦርነቱም ከግማሽ ሚሊዮን በላይ አሜሪካውያን ሞተዋል።
1868 አጼ ቴዎድሮስ April 17, 1868 (1860 ዓ.ም) ህይወታቸውን ያጠፉበት አመት፤ ሰኔ እና ሰኞ የገጠመበት አመት ነበር።
1891 – ከአንድ አበቅቴ ወይም ከ11 አመት በኋላ የሚመጣው የሰኔ እና ሰኞ ግጥምጥሞሽ አስፈሪ ነው። ከአበቅቴው በኋላ ጥንቃቄ እና ዝግጁነት ያስፈልጋል። ይህ ካልሆነ ግን በሁሉም የኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ እንደምናውየው አይነት የረሃብ እና የበሽታ ውሽንፍር ይከሰታል። በዚህ ዘመን በቂ ዝግጅት እና ጥንቃቄ ባለመደረጉ በአገሪቱ ታይቶ የማይታወቅ አስከፊ ነገር ሆነ። ይህ ዘመን በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ “ክፉ ዘመን” በመባል ይታወቃል። በሰሜን ከአክለ ጉዛይ ጀምሮ ቤጌምድርን ጨምሮ፤ ሸዋ እና ሃረር… እንዲሁም እስከ ደቡብ ድረስ የዘለቀ ረሃብ እና በሽታ ተስፋፋ። የአምበጣ መንጋ ሳር ቅጠሉን፣ ጥሬ እህሉን ሁሉ ጨረሰ። በዚህ እንዳይበቃ… የኮሌራ፣ የተስቦ እና የፈንጣጣ በሽታ ህዝቡን እያሰቃየ ጨረሰው። በዚህ ምክንያት የአጼ ምኒልክ የንግሥና በአል ጭምር ለሌላ ጊዜ ተዛወረ።

1896 ሰኔ እና ሰኞ የገጠመበት፤ የኢትዮጵያ እና የጣልያን ጦርነት ተቀስቅሶ፤ በአምባላጌ፣ በመቀሌ እና በአድዋ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን የሞቱበት ዘመን ነው። ምንም እንኳን ጦርነቱ በኢትዮጵያ አሸናፊነት ቢደመደምም የጦርነት መልካም ስለሌለው የሰው ልጅ ህይወት የተገበረበት፤ የሰኔ እና ሰኞ ግጥምጥም ውጤት ነው።
1914 – ሰኔ እና ሰኞ ከመግጠሙ አንድ አመት በፊት የሚሞቱ ሰዎች ከደጋጎቹ አባቶች የሚመደቡበት አጋጣሚ አለ። ለዚህም ይሆናል… አጼ ምኒልክ ህይወታቸው ያለፈው፤ አንድ አመት ቀደም ብለው ታህሳስ 3 ቀን፣ 1906 ሲሆን፤ የንጉሠ ነገሥቱ ሞት ይፋ አልተደረገም ነበር። አባታቸው ንጉሥ ኃይለመለኮት በተመሳሳይ ሁኔታ ከሰኔ እና ሰኞ ግጥምጥሞሽ አንድ አመት ቀደም ብለው እንደአውሮጳ አቆጣጠር በ1856አረፉ።
በዚህ አመት ሰኔ እና ሰኞ ሲገጥም፤ በዚያው ወር ብዙ ደስ የማይሉ የጦርነት ነገሮች በአውሮጳ ይከሰቱ ጀመር። ፈረንሳይ፣ እንግሊዝ፣ ጀርመን፣ ጃፓን እርስ በርሳቸው ተበጣብጠው፤ በመቸረሻ የአንደኛው አለም ጦርነት በዚሁ አመት ተጀመረ።

1925 ይህ የአበቅቴ ሰኔ እና ሰኞ ግጥምጥም አመት ቢሆንም፤ ህዝቡ ከህዳር በሽታ ገና ማገገሙ ነበር። የህዳር በሽታ… በንፋስ መጥቶ አርባ ሺህ ህዝብ ጨረሰ። አልጋ ወራሹና ንግሥቲቱ ጭምር ታመው አገገሙ። ህዝቡም ወደ ፈጣሪው እግዚኦታውን አበዛ። ሆኖም በዚህ አመት፤ ማለትም በኢትዮጵያ አቆጣጠር 1917 ዓ.ም ሰኔ እና ሰኞ ስለሚገጥም፤ “ምን ይሰማ ይሆን ጆሮ?” ተብሎ ሲጠበቅ፤ አስገራሚ ነገር ሆነ።
የንጉሥ ሳህለስላሴ የልጅ ልጅ… የራስ ዳርጌ ልጅ፤ ወ/ሮ ፀሃየወርቅ ዳርጌ በአልጋ ወራሽ ተፈሪ መኮንን ላይ አስገራሚና የተቀነባበረ፤ የመግደል ሙከራ አስደረጉ። አላማውም አልጋወራሹን በማስገደል፤ ልጅ እያሱን እንደገና ወደ ስልጣን ለማምጣት ሲሆን፤ ተኩሶ ለመግደል ከተመደቡት ሰዎች መካከል መሃመድ አባ ሻንቆ፤ አነጣጥሮ ሲተኩስ ጥይቱ ከሸፈበት። በሌላ አቅጣጫ አልጋወራሹን ለመግደል የተመደበው ሰው ደግሞ፤ ሊተኩስ ሲል እጁ ዝሎበት ስለተንቀጠቀጠ መተኮስ አቅቶት ተያዘ። አልጋ ወራሽ ተፈሪም ከሞት ተርፈው፤ በመግደል ሙከራ የተካፈሉት ሰዎች በሙሉ ታሰሩ። ይህም ሰኔ እና ሰኞ በገጠመበት የሰኔ ወር በመከናወኑ… ህዝቡ “ወይ ሰኔ እና ሰኞ?!” እያለ ይገረም ነበር። አልጋወራሹ ቢገደሉ ኖሮ…. ሊመጣ ከሚችለው የአበቅቴ ቁጣም ህዝቡ ዳነ።

በሌላ በኩል ግን በዚሁ አመት፤ በ1925 የጣልያን አምባገነን አመራር ተመሰረተ። የአገሪቱ ፕሬዘዳንት ቤኒቶ ሙሶሎኒ (ጃኑዋሪ 3 ቀን) የአገሪቱን ፓርላማ በትኖ፤ ብቻውን አምባገነን መሪ ሆነ። ኢትዮጵያንም ለመውረር ዝግጅት ያደርግ ጀመር። በዚህ አመት አዶልፍ ሂትለት እና ፓርቲው ብቸኛ የጀርመን መሪዎች መሆናቸውን አወጁ። በአሜሪካ የነጭ በላይነት ገነነ። በዚሁ አመት ኦገስት 28 ቀን፤ 40 ሺህ የኬኬኬ አባላት ነጭ መለዮዋቸውን ለብሰው፤ በዋሺንግተን የሰልፍ ትርኢት ሲያደርጉ የአለም መጨረሻ አስመሰሉት።
1931- ሰኔና ሰኞ በገጠመ በአመቱ ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ምኒልክ ህይወታቸው አለፈ። ይህ አመት ደግሞ በባህር ማዶ ሰዎች ዘንድ የሚታወቀው የ Great Depression መጀመሪያ በመሆኑ ነው። በአውሮጳ እና በአሜሪካ እንደመጥፎ ዘመን ይቆጠራል።
1936 - በዚህ አመት በኢትዮጵያ አስደንጋጭ ነገር ተፈጠረ። የጣሊያን ወረራ ተደረገ። ሰኔ እና ሰኞ ገጠመ። ጣልያኖች ከስሜን አልፈው፤ ማይጨውን ትሻግረው አዲስ አበባ ገቡ። ዘመኑ ለኢትዮጵያውያን የከፋ ሆነ።
1942 - የሁለተኛው አለም ጦርነት ተፋፍሞ፤ ጀርመን በመላው አውሮፓ ፍጹም የበላይነትን የተቀዳጀችበት አመት ነበር። ከዚህ አመት ጀምሮ ለቀጣይ 3 አመታት ናዚዎች - የአይሁድ ዝርያ ያላቸውን ሰዎች እያደኑ፤ በከፋ እና በሚዘገንን መንገድ ገደሏቸው፤ ዘራቸውን የማጥፋት ስራ ተሰራ በውጤቱም ከ6-11 ሚሊዮን አይሁዶች ተገደሉ።
1953 - የዚህ አመት ሰኔ እና ሰኞ በአንድ አበቅቴ (ከ11 አመት በኋላ)የሚመጣ ነው። ከአንድ አበቅቴ በኋላ… ጥንቃቄ ካልተደረገ በቀጣዩ አመታት በኋላ፤ ረብሻ እና ግርግር ይኖራል። ረሃብ እና ጦርነት ይሆናል። ጥንቃቄ መደረግ ያለበት በጾም እና በጸሎት ጭምር ነው። በዚህ የአበቅቴ ዘመን የተፈራው ረሃብ እና ቸነፈር አልመጣም። መልካም ነገር እንዲሆን ምክንያት የሆነው በቂ ዝግጅት ስለተደረገ፤ ህዝቡም በጽናት ወደ ፈጣሪው ጸሎት ስላደረሰ ሊሆን ይችላል። በ’ርግጥም በዚህ አመት ከክርስትና ቤተ-እምነቶች በተጨማሪ የቢላል መስጊድ ተመርቆ፤ እስላም እና ክርስቲያኑ ወደ አምላኩ ጸሎት ያደርስ የነበረበት መልካም ዘመን መሆኑን የታሪክ ድርሳናት ይመሰክራሉ። ለዚህም ይሆናል በአበቅቴው ሰኔና ሰኞ በአገሪቱ ላይ ክፉ ቸነፈር ሳይወርድ የቀረው።

1959 በዚህ ዘመን ሰኔ እና ሰኞ ሲገጥም… “ምን ሊመጣ ይሆን?” መባሉ አልቀረም። ሆኖም በቀጣዩ አመት በ1960ንጉሠ ነገሥቱ ለጉብኝት ወደ ብራዚል በሄዱበት ወቅት፤ የክቡር ዘበኛ ጦር አመጽ አስነስቶ፤ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ አደረገ። ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ አይታ የማታውቀውን፤ የተቀነባበረ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ አስተናገደች። በጄ/ል መንግስቱ ንዋይ እና በገርማሜ ንዋይ የተመራው መፈንቅለ መንግስት የ600 ሰዎችን ህይወት ቀጠፈ፤ ብዙዎች ታሰሩ፤ ጥቂቶች ተሰደዱ። በንጉሠ ነገሥቱ እና በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ግን ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አለፈ - የታህሳሱ ግርግር።

1964 በአባቶቻችን ዘመን አንድ የሚያስታውሱት የ”ሰኔ እና ሰኞ” ገጠመኝ ነበር። በኢትዮጵያ አቆጣጠር በ1956 ዓ.ም. ሰኔ እና ሰኞ ገጠመ። ይህንኑ ተከትሎ “ምን ይመጣ ይሆን?” ተብሎ ሲጠበቅ፤ አንድ አዲስ የመንገድ አዋጅ ወጣ። ከሰኞ ሰኔ 1 ቀን ጀምሮ፤ በግራ በኩል ይሄዱ የነበሩ ወደ ቀኝ፤ በቀኝ ይሄዱ የነበሩ መኪኖች ደግሞ በግራ በኩል እንዲያሽከረክሩ ህግ ወጣ። ከዚያ ቀን በፊት… መኪኖች በሙሉ አሁን በሚሄዱበት በተቃራኒ መንገድ ነበር የሚሄዱት። ከዚያን ወዲህ ግን… የመኪና መንገድ አካሄድ መቀየሩን በአባቴ እድሜ የነበሩ ሰዎች፤ “ወይ ሰኔ እና ሰኞ” እያሉ በመገረም ሲያወሩ እንሰማ ነበር። በዚሁ አመት 1956 ዓ.ም. አለማችንን ያስደነገጠ ትልቅ ክስተትም ተስተናግዷል። የአሜሪካው 35ኛው ፕሬዘዳንት፤ ጆን ኤፍ ኬኔዲ የተገደሉት በዚሁ ሰኔና ሰኞ በገጠመበት አመት ነበር።

1970 - በአውደ ቀመሩ ስሌት መሰረት፤ ከ6 አመታት በኋላ የሚመጣው የአበቅቴው ሰኔ እና ሰኞ፤ በመጪው አመታት በአገሪቱ ጦርነት እና ብጥብጥ ሊነሳ እንደሚችል አመላካች ነው። (በእርግጥ እንዲህ አይነቱን የዘመን ትንቢት ለመናገር የከዋክብት ስነ-ፈለግን ምጥቅዕ እውቀት መጨመር ያስፈልጋል።) የሆኖ ሆኖ በዚህም መሰረት 1962 ሰኔ እና ሰኞ ሲገጥም፤ ለኢትዮጵያ ትልቅ ማስጠንቀቂያ ነበር። በዚህ አመት በኤርትራ በርሃ የመጀመሪያዋ የመገንጠል ጥያቄ ጥይት ተተኮሰች። በውጭ አገር እና በአገር ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎች፤ በሶሻሊዝም አደረጃጀት ተመሰረቱ። እንደተፈራውም በቀጣዩ አመታት በአገሪቱ ቁጣ ወረደ። በወሎ እና አካባቢው የረሃብ ቸነፈር መጣ። የተማሪዎቹን እንቅስቃሴ ተከትሎ አመጽ ተነሳ፤ መንግስት ተገለበጠ፤ ትርፍ ቤት እና የግል መሬት ተወረሰ። ተቃዋሚዎች በዙ፤ ቀይ ሽብር ተፋፋመ። ንጉሠ ነገሥቱም ተገደሉ።
1981 - ከአንድ አበቅቴ በኋላ የሚመጣ ሰኔ እና ሰኞ ያስፈራል። ምክንያቱም የአበቅቴውን ሰኔ እና ሰኞ ተከትሎ፤ ከሶስት አመታት በኋላ የሚመጣው የረሃብ ቸነፈር ከበድ ያለ ነው። በመሆኑም በቂ ዝግጅት ካልተደረገ መጪዎቹ አመታት የከፉ እንደሚሆኑ አውደ ቀመሩ ያሳያል። ለኢትዮጵያም … መጪው ዘመን መልካም እንደማይሆን የማስጠንቀቂያ ደወል የተሰማበት ነበር። ጊዜው በኢትዮጵያ አቆጣጠር 1973 ሲሆን፤ የአበቅቴው ሰኔ እና ሰኞ ገጠመ። እንደሁልጊዜውም ከ3 አመት በኋላ፤ የረሃብ ቸነፈር በኢትዮጵያ ወረደ። ከ1976 ዓ.ም ጀምሮ የተከሰተው የረሃብ ቸነፈር፤ ከኢትዮጵያ አልፎ በመላው አለም ተሰማ። በሌላ በኩል ደግሞ ከዚህ አመት ጀምሮ፤ በሰሜን ኢትዮጵያ የሚደረገው ጸረ-ደርግ ትግል ተጠናክሮ ቀጠለ።
1987 – ይህ ዘመን ለኢትዮጵያ ክፉ የጦርነት ዘመን ሆኖ ነው ያለፈው። በሰሜን ኢትዮጵያ የሻዕቢያ፣ የወያኔ እና የኢህዴን ተዋጊዎች በጣም የተጠናከሩበት፤ የኢትዮጵያ ጦር ሰራዊት ደግሞ ተስፋ የቆረጠበት እና ብዙዎች በየቀኑ የሚሰዉበት ዘመን ነበር። በተለይም አንድ አመት ቀደም ብሎ የናደው ክፍለጦር መሪ፤ ጄነራል ታሪኩ ከተገደለ በኋላ ሁኔታዎች መልካቸውን ቀየሩ። ጦርነቱ እየተፋፋመ ሄዶ፤ ሻዕቢያ በብዙ ቦታዎች ድል አገኘ። ህወሃት እና ኢህዴን ተዋህደው፤ ኢህአዴግ የሚባል ድርጅት መሰረቱ። ጦርነቱ በጣም የከፋ ነበር። በአመቱ በጄ/ል ፋንታ በላይ የተመራ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ቢደረግም፤ ውጤቱ የብዙ ጄነራሎች ሞት ሆነ። በአጠቃላይ ይህ ዘመን እጅግ ተስፋ አስቆራጭ በመሆኑ፤ መጪው ጊዜ ጨለማ ሆኖ የታየበት ወቅት ነበር።

በዚህ አመት ሰኔ እና ሰኞ ሲገጥም… ዘመኑ ለራሺያ ጥሩ አልነበረም። የታላቋ ሶቪየት ህብረት አገራት፤ ኢስቶንያ፣ ሊቱንያ፣ ላትቭያ የነጻነት እንቅስቃሴ ጀመሩ። በዚህ አመት የተጀመረውን የነጻነት ጥያቄ ተከትሎ፤ የቀድሞዋ ሶቪየት ህብረት ቀስ በቀስ ተበታተነች። የኢራን እና ኢራቅ ጦርነት እጅግ የከፋ ደረጃ ላይ ደረሰ። የአለማችን የመጀመሪያው የባህረ ሰላጤው ጦርነት ተቀሰቀሰ። የበርሊን ግንብ ፈረሰ። መካ መዲና ለኢድ የሄዱ፤ የኢራን ሙስሊሞች ባስነሱት ረብሻ ምክንያት፤ የሳኡዲ ፖሊሶች 402 ሰዎችን ገደሉ። ይህም ከዚያ በፊትም ሆነ በኋላ ተሰምቶ የማያውቅ ግድያ ሆኖ ተመዘገበ።
1992 - ይህ ዘመን በኢትዮጵያ አቆጣጠር 1984 ነው። በዚህ ወቅት ኢህአዴግ አገሪቱን ተቆጣጥሮ የሽግግር መንግስት ያቋቋመበት፤ ብዙዎች በዘር እና በጎሳ ጸብ ምክንያት የተገደሉበት፤ ኤርትራ የተገነጠለችበት፤ በብዙ መንገድ የኢትዮጵያ ታሪክ የተቀየረበት ነው።
በሌላ በኩል… ይህ ዘመን ለአሜሪካ አስከፊ ዘመን ነበር። በዚህ አመት ሰኔ እና ስኞ ከአምስት አመታት በኋላ እንደገና የሚገጥምመበት ጊዜ ሆነ። አጋጣሚውም እስከዛሬ ድረስ የአሜሪካን ታሪክ ያጠለሸ፤ በጥቁር ቀለም የተጻፈ ቅሌት ትቶ አለፈ። ፖሊስ በጥቁር አሜሪካውያን ላይ የሚፈጽመውን በደል ተከትሎ፤ በሎስ አንጀለስ ከተማ ብቻ (ሌላውን የአሜሪካ ከተሞች ሳይጨምር) በሎስ አንጀለስ ብቻ 3 ሺህ ስድስት መቶ ቦታዎች እሳት ነደደ። አንድ ሺህ አንድ መቶ ህንጻዎች በእሳት ጋዩ። 2ሺህ ሰዎች ተጎዱ፤ ስልሳ ያህል ሰዎች ሞቱ።

1998 - በመቶ አመት አንድ ጊዜ፤ አዲስ ሚሊኒየም ከመጀመሩ በፊት የአበቅቴ ቀመር ይቀየራል። እናም በ5፣ በ6 ኣና በ11 አመት የሚመጣው ሰኔ እና ሰኞ ቀመሩ ይቀየርና ከስምንት አመታት በኋላ… ሰኔ እና ሰኞ ይገጥማል። ይህን ተከትሎ በዚህ አመት ሰኔ እና ሰኞ የሚገጥምበት ጊዜ በመሆኑ፤ በኢትዮጵያ ላይ “ምን ይመጣ ይሆን?” ተብሎ ሲጠበቅ፤ በግንቦት ወር የተሰማው ዜና መልካም ሳይሆን ቀረ። የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ጦርነት ፈነዳ። ከሰኔ ወር በኋላ ጦርነቱ ተፋፍሞ ቀጠለ። በጥቂት ወራት እና በአንድ አመት ውስጥ ከመቶ ሺህ በላይ ወታደሮች ሞቱ። ነዋሪዎች ተፈናቀሉ።
በሌላው አለም ደግሞ ጂሃድ ታወጀ። ኦሳማ ቢን ላዲን በአሜሪካውያን የሚፈለግ ሰው ቢሆንም፤ እስካሁን ጂሃድ አላወጀም ነበር። በዚህ አመት ግን በእስራኤል እና አሜሪካውያን ላይ ጅሃድ አወጀ። በዚህ ጂሃድ ምክንያት የብዙ አሜሪካውያን ህይወት ጠፋ። በዚሁ አመት በኬንያ እና በታንዛንያ በአንድ ቀን (ኦገስት 7) በአሜሪካ ኢምባሲ ቦምብ ፈንድቶ፤ 224 ሰዎች ተገደሉ፤ 4ሺህ 500 ሰዎች ላይ ጉዳት ደረሰባቸው። በተለይ ይህን የጂሃድ መልዕክት ተከትሎ፤ ከ3 አመታት በኋላ… ማለትም በ2001 ላይ፤ በኒው ዮርክ እና በሌሎች የአሜሪካ ክፍለ ግዛቶች፤ ሴፕቴምበር 11 ቀን ጥቃት ተፈጸመ።
2009 - ይህ በአንድ አበቅቴ የሚመጣ የሰኔ እና ሰኞ ግጥምጥሞሽ እንደመሆኑ መጠን፤ በሚቀጥሉት አመታት ሊያመጣ የሚችለው የሃዘን፣ የጦርነት እና የረሃብ ቸነፈር ያስፈራል። አዲሱ ሚሊኒየም ከገባ በኋላ ሰኔ እና ሰኞ የገጠመው በ2009 ዓ.ም ነበር። ከላይ እንደገለጽነው ከአንድ አበቅቴ በኋላ የሚመጣው ጊዜ፤ ለአንድ አገር የማስጠንቀቂያ ዘመን ነው። ጦርነት እና የረሃብ ቸነፈር እንዳይመጣ መጪውን ሶስት አመት በጥንቃቄ መጠበቅ ያስፈልጋል። በኢትዮጵያ አቆጣጠር 2001 ዓ.ም ነበር። በቀጣዩ 3 አመታት ውስጥ ምን ሊመጣ እንደሚችል ሲጠበቅ፤ ያልተጠበቀ ነገር ሆነ። ፓትሪያርኩ አቡነ ጳውሎስ እና ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ተከታትለው በሞት ተለዩ። በተለይ የመለስ ዜናዊን ሞት ተከትሎ፤ “መጪው ጊዜ ብጥብጥ እና ጦርነት ይዞ ሊመጣ ይችላል” ተብሎ ብዙ ስጋት ነበር። ብዙዎች እንደሚያስታውሱት፤ በዚያን ሰሞን ህዝቡ በጸሎቱ ተግቶ ወደ ፈጣሪው አለቀሰ፤ አምላክም ጸሎቱን ሰማ። የተፈራውም የርስ በርስ ጦርነት ሳይከሰት ቀረ።
በሌላ በኩል ደግሞ… ከሁለተኛው የአለም ጦርነት በኋላ አለማችን በከፍተኛ የኢኮኖሚ ድቀት ውስጥ የገባችው በ2009 ነበር። ይህ የኢኮኖሚ ድቀት የተከሰተውም በ- 2009 ነው።

2015 - ከአምስት አመታት በኋላ በ2015 ሰኔ እና ሰኞ ሲገጥም፤ አዲስ እና አስገራሚ ዜና በአሜሪካ ተሰማ። ሰኔ እና ሰኞ ተገጣጥሞ ባለፈ ማግስት ዶናልድ ትራምፕ ለአሜሪካ ፕሬዘዳንትነት እንደሚወዳደሩ በይፋ አሳወቁ። ይህም የመጥፎው ቀን ምጽአት፤ የመጀመሪያው ምልክት ሆነ።
2020 - በዚህ አመት እንደተለመደው፤ በፈረንጆቹም ሆነ በኢትዮጵያ አቆጣጠር ሰኔ እና ሰኞ ገጥመዋል። ግጥምጥሞሹ ግን… ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን፤ ለመላው አለም ኮሮና ቫይረስን ተሸክሞ፤ የበሽታ ቸነፈር ይዞ ነው የመጣው። ይህ ጥናታዊ ጽሁፍ በተጠናቀረበት ወቅት፤ በመላው አለም ሶስት መቶ ሺህ ሰዎች ህይወታቸው ሲያልፍ፤ ከመቶ ሺህ በላይ የሚሆኑት አሜሪካውያን ናቸው። በዚሁ አመት በአሜሪካ የሚደርሰውን የቀለም ልዩነት ምክንያት በማድረግ፤ ሰፊ የሆነ ሰላማዊ ሰልፍ እየተደረገ ነው። ሁኔታው ሁሉ የአለም መጨረሻ ሊመስል ይችላል። አመቱ ምን እንደሚመስል አብረን እያየነው ስለሆነ ማብራሪያ አያስፈልገውም ይሆናል። ነገር ግን ሰኔ እና ሰኞ ገጥሞ የአለማችን አውደ ህይወት ቀጥሏል።
መጪውን ዘመን መተንበይ የሚፈልጉ ሰዎች ካሉ፤ በሰኔ እና ሰኞ ግጥምጥም አመታት ላይ፤ የከዋክብትን ስነ ፈለጋዊ እውቀት ጋር ቢያቀናጁት የተሻለ ውጤት ሊያገኙ ይችላሉ። ከጊዜ በኋላ የስነ ከዋክብት እውቀት እየደበዘዘ በመምጣቱ እንጂ፤ ከባቢሎን ዘመን በፊት ጀምሮ፤ ሊቃውንት እቀት እና ጊዜያቸውን በከዋክብት ቀመር ላይ ያጠፉ ነበር። በውጤቱም በአገራቸው ላይ ሊመጣ የሚችለውን የረሃብ፣ የበሽታ፣ የድርቅ እና የጦርነት ዘመን ቀድመው መተንበይ እና መናገር ይችሉ ነበር። ጥሩ ምርት የሚገኝበትን ተድላ እና ሃሴት የሚሆንበትን፣ ታዋቂ ሰዎች እና ነገስታት የሚሞቱበትን፤ ያንን ተከትሎ የሚመጣውን ውጣ ውረድ ጭምር ይናገራሉ፤ ማስጠንቀቂያም ይሰጣሉ። እውቀቱ አሁንም አለ።

ለማንኛውም ከዚህ በታች ሰኔ እና ሰኞ የሚገጥምባቸውን አመተ ምህረቶች አስቀምጠናል (ሁሉም በፈረንጅ አቆጣጠር ነው) ትንቢት መናገር የሚፈልጉ ካሉ፤ በነዚህ አመታት የከዋክብትን ተፅእኖ (ማለትም መጪው ጊዜ፣ የጦርነት፣ የረሃብ፣ የበሽታ) መሆኑን በመተንበይ፤ ጸሎት እና ምህላ የሚያስፈልግበት ዘመን ካለም፤ ሁሉም እንደየእምነቱ ወደፈጣሪው ኤሎሄ የሚልበትን ወቅት ሊነግሩን ይችላሉ። ከዚህ በታች ያሉት አመታት ሰኔና ሰኞ የሚገጥምባቸው ናቸው።

2026፣ 2037፣ 2043፣ 2048፣ 2054፣ 2065፣ 2071፣ 2076፣ 2082፣ 2093፣ 2099 - በየ11 አመት በሚመጣው የአበቅቴ ጥሎሽ ወይም በሰኔ እና ሰኞ ግጥምጥሞሽ ማመን ወይም አለማመን የግል ምርጫ ነው። እኛ ግን እንላለን 2026 እስከሚመጣ ድረስ… መጪው ዘመን የሰላም ይሁንልን።

Want your organization to be the top-listed Government Service in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Category

Telephone

Website

su.edu.et

Address


Addis Ababa
Other Post offices in Addis Ababa (show all)
Chalachew Moges Page Chalachew Moges Page
Landing
Addis Ababa, 1089

Line to life, this is our Amendment !

Aw/Da/Sa/Bu/Gi/Ga/Da/Ku/Buxa Aw/Da/Sa/Bu/Gi/Ga/Da/Ku/Buxa
Awra
Addis Ababa

Ethiopost Ethiopost
Egypt Street
Addis Ababa

129 years of legacy and service. Many more ahead providing modern solutions to modern problems.